fa
Feedback
በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

رفتن به کانال در Telegram

አዝናኝና አስተማሪ ጽሁፎች ለማገኘት join አደርጉን 🙏እባካችሁ ለሌሎችም አጋሩልን🙏 @matter_of_facts

نمایش بیشتر
2 949
مشترکین
-224 ساعت
-37 روز
+4730 روز

در حال بارگیری داده...

ابر برچسب‌ها
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
ژوئیه '26
ژوئیه '26
+79
در 1 کانال‌ها
ژوئن '26
+78
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '26
+100
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '26
+69
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '26
+63
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '26
+59
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '26
+77
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '25
+76
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '25
+62
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '25
+54
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '25
+53
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '25
+88
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '25
+63
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '25
+87
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '25
+89
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '25
+91
در 1 کانال‌ها
Get PRO
مارس '25
+74
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '25
+67
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '25
+102
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '24
+146
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '24
+100
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '24
+107
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '24
+116
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '24
+145
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '24
+82
در 1 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '24
+100
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '24
+95
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '24
+107
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '24
+94
در 1 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '24
+87
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '24
+102
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '23
+107
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '23
+77
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '23
+61
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '23
+60
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '23
+79
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '23
+73
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '23
+85
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '23
+78
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '23
+62
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '23
+61
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '23
+84
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '23
+92
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '22
+142
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '22
+109
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '22
+125
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '22
+125
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '22
+60
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '22
+41
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '22
+53
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '22
+45
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '22
+32
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '22
+45
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '22
+25
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '22
+42
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '21
+27
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '21
+41
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '21
+63
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '21
+56
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '21
+31
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '21
+44
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '21
+71
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '21
+40
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '21
+52
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '21
+47
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '21
+38
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '21
+48
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '20
+597
در 0 کانال‌ها
تاریخ
رشد مشترکین
اشارات
کانال‌ها
26 ژوئیه+2
25 ژوئیه+2
24 ژوئیه+2
23 ژوئیه+1
22 ژوئیه+4
21 ژوئیه+2
20 ژوئیه+1
19 ژوئیه+3
18 ژوئیه+7
17 ژوئیه+3
16 ژوئیه+1
15 ژوئیه+6
14 ژوئیه+1
13 ژوئیه+6
12 ژوئیه+1
11 ژوئیه+6
10 ژوئیه+4
09 ژوئیه+1
08 ژوئیه+2
07 ژوئیه+5
06 ژوئیه+1
05 ژوئیه+5
04 ژوئیه+3
03 ژوئیه+2
02 ژوئیه+4
01 ژوئیه+4
پست‌های کانال
ምክሩ (በእውቀቱ ስዪም) የሆነ ጊዜ ላይ ምኡዝ ሰፈሩ በሚገኘው ካፌ በረንዳ ላይ ቁጭ ብሎ በማኪያቶ ነፍሱን በማስደሰት ላይ ነበር፤ ካጠገቡ ሶስት ወጠምሻዎች አንዱን ጠረጴዛ ከበው ሻይ ቡና ይባባላሉ ፤ አንደኛው ሰውየ የባጥ የፎቁን ያወራል፤ አፉን በከፈተ ቁጥር ከውስጡ ከፍተኛ ጠረን እየተመዘዘ ይወጣና የእናት አገራችንን ንጹህ አየር ይበክለዋል፤ ምኡዝ የሰውየው ጉዋደኞቹ በጠረኑ ተመርዘው አለመሞታቸው አስደነቀው፤ ማሽተት የተሳናቸው ሰዎች መኖራቸውን አወቀ ፤ የኒህ ሰዎች አፍንጫ ዋና ጥቅም ፊታቸውን ለሁለት መግመስ እንደሆነ ገባው፤ ከራሱ ጋራ ትንሽ ሲሙዋገት ከቆየ በሁዋላ “ወንድሜ አንዴ ብቻህን ላናግርህ “አለውና ወደ ጉዋሮ ወሰደው፤ - “ይህንን ጉዳይ በጉዋደኞችህ ፊት ልመክርህ አልፈለግሁም፤ አፍህ መልካም ቃል እንጂ መልካም መአዛ ስለማያመነጭ መፍትሄ ፈልግለት ፤” አለው “ ምን ማለት ነው ? “ አለ ሰውየው በንዴት፤ “ያፍህ ሽታ ልክ አይደለም፤ ከላይ ከላይ ከሆነ ቦርሸው፣ ከውስጥ ከሆነ ታከመው” “ሰውየ ታውቀኛለህ? ምናባህ ነው የምትቀባጥረው?” አለ ሰውየው መዳፉ ላይ ሀይል እያሰባሰበ፤ ምኡዝ በለዘበ ቃል ለማስረዳት ያደረገው ሙከራ ከንቱ አንደሆነ ሲሰማው ይለይለት ብሎ አንዲህ አለ፤ “ ያፍህ ጠረን በድንበር አካባቢ ቢነሰነሰ የውጭ ወራሪ አይደፍረንም ነበር” ሰውየው እጁን ሰነዘረና ቢልቦርድ የሚያህል አይበሉባውን ምኡዝ ፊት ላይ አሳረፈው፤ ከምኡዝ አፍንጫ ደም ቡልቅ አለ ፤ “የሚገርመው መመታቴን ብዙ አልጠላሁትም፤ ሲነስረኝ አፍንጫየ ለጊዜው ማሽተት አቆመ” ብሎ ትረካውን ደመደመ፤ ይህንን ሲነግረኝ ሆዴን እስኪያመኝ ሳቅሁና፤ ” እዛው በጉዋደኖቹ ፊት ብትነግረው ይሻል ነበር፤ ቢያንስ ገላጋይ አታጣም ነበር “ አልሁት፤ “ዝም በል ባክህ ! “ አለ ምኡዝ “ ሁሉም ቡጢና አርግጫ ሊያዋጡ ምን ይውጠኝ ነበር! እንኩዋን በዚህ አለፈልኝ ! https://t.me/matter_of_facts

2
ወጣቶች ነበርን በእውቀቱ ስዩም ጊዜ ሲራመድ ኮቴው ድምጥ አልባ ከየት ተነስቶ ወደ የት ገባ ከየት ተነስቶ ወዴት ደረሰ ጠጉር መንጥሮ፣ ፊት እያረሰ፤ ወጣቶች ነበርን ቅጽር የሰራን ፤ አምባ የሰበርን ኮካ ኮላውን ባሲድ በርዘን ብንጎነጨው፤ የማይመርዘን፤ በራዱን ያጋልን፣ ሙት ልብ ያስነሳን ግራዋ በልተን ፤ ሎሚ ያገሳን፤ ተስፋችን ብዙ፤ እድሚያችን ለጋ ስንሰማራ፣ ትርጉም ፍለጋ ገላችን አይፈዝ፣ ጭቃ ቢለሰን የማናስቀይም፤ ቡትቶ ለብሰን ገጻችን ብሩህ፤ ልባችን ሽፍታ ስንመነጠቅ፤ ወደ ከፍታ የስኬት ገነት፣ ደጃፏን ከፍታ ምትቀበለን ፣ እየመሰለን ከቁመታችን፤ በላይ የዘለልን፤ ወጣቶች ነበርን ዛሬ እንደዋዛ ዘንድሮን ምሰን፤ ታችአምናን ቀበርን፤ https://t.me/matter_of_facts
342
3
የጋራ ድል (በእውቀቱ ስዩም) የስፔን ደጋፊ ብሆን ምን ያስገርማል? ስፔን በስነፅሁፍ አክብራ የጋበዘችኝ አገር ናት፤ ስፔን ሁለተኛ አገሬ ናት ብል ኩሸት አይሆንም፤ ስፔን እንድታሸንፍ ፈልጊያለሁ፤ ያም ሆኖ፣ ከጉዋደኛየ ከካሳ ጋራ አር-ጄንቲና ታሸንፋለች ብየ በአራት ሺ ብር ተወዳደርሁ፤ ስፔን ካሸነፈች እፈነጥዛለሁ፤ አርጄንቲና ካሸነፈች ደግሞ ላብ ያልገነፈለበት ፣ እንቅልፍ ያልተሰዋበት አራት ሺ ብር አካውንቴን ያጠበድላል ብየ አሰብኩ፤ በሁለቱም በኩል አሸናፊው ነኝ የሚል መላ መጣልኝ፤ በመጨረሻ እንዳያችሁት ስፔን፣ በረኛ ሳይሆን በር የሆነውን የአርጀንቲናን ግብጠባቂ ጣጥሳ አገባች፤ ዋንጫውን ጨበጠችው፤ደስ አለኝ፤ግን ደስታየ ወደ ፈንጠዝያ አልተሸጋገረም፤ ለካ ደስታ ስነልቦናዊ ነገር ሲሆን ፈንጠዝያ ግን የዳበረ ኢኮኖሚ የሚጠይቅ ነገር ኑሩዋል! እያደር የአለም የእግር ኩዋስ የእግር እሳት ሆነብኝ☹ የአራት ሺ ብሬ መሄድ ፣አካውንቴ ላይ ያለው ቁጥር መመናመን ዋንጫውን መራራ ጥዋ አደረገብኝ፤ -“ ካሸነፍኩህ አራት ሺ ብሩን ፣ ስፔን ኢምባሲ ፊትለፊት ለሚቀመጡ ነዳያን እመጠውተዋለሁ- “ሲለኝ የነበረው ካሳ ዛሬ በማለዳው ወደ ፍቅሬ ኩንስፓኛ ሲገባ አየሁት፤ ቅን ስለማስብ፣ ለናዳያኑ ዱለት ሊያስቁዋጥርላቸው እንደሆነ ገመትኩ፤ ካሳ ወደ ምግብ ቤቱ ሲገባ ጀርባውን እያየሁ የቆየ ወግ ትዝ አለኝ፤ አንድ ባለሀገር ተጎጃም መጥተው ጎጃም በረንዳ አካባቢ ሲማስኑ ቆይተው ሱርያቸውን ቢዳብሱ በምስጢር ኪሳቸው የቁዋጥሩዋት ሶስት መቶ ብር የለችም ፤ መገን ያራዳ ልጅ መንትፎዋቸዋል፤ ከዚያ ፣አንድ የተሳቢ መኪና ሹፌርን እርዳታ ለምነው ከማዳበርያ ጋር ተደርበው ተጭነው ወደ አገራቸው መመለስ ጀመሩ፤ ግን እንጦጦ አፋፍ ላይ ሲደርሱ ፊታቸውን ወደ ሸገር በር መለስ አድርገው ቁጭት ባጠላበት ድምጥ አንዲህ አሉ፤ “ ሸዋ! እንግዲህ ተኝተህ ብላ” https://t.me/matter_of_facts
714
4
ኦሮማን (በእውቀቱ ስዩም) ሰሞኑን እንደ አዲስ አስቴር አወቀን ሳደምጥ፣ በአሉ ግርማ ትዝ አለኝ፤ የበአሉን ኦሮማይ ታስታውሱታላችሁ ? ፀጋየ ሀይለማርያም ጋዜጠኛ ነው፤ ሮማን የተባለች ውብ ኩሩ እጮኛ አለችው፤ ሊጋቡ ጥቂት ወራት ሲቀራቸው በቀይ ኮከብ ጥሪ አስመራ ለግዳጅ ተላከ፤ በዚያም በዘመቻው መሀል ፊያሜታ የተባለች ያስመራ ሴት ተዋወቀ፤ ከባድ ፎንቃ ገባለት፤ ባስመራይቱና በሸገሪቱ ሴቶች ፍቅር መሀል ተወጥሮ በታሪካዊው ዘመቻ ላይ ተሳተፈ ፤ በመጨረሻ ሮማን አስመራ መጥታ ከሌላ ሴት ጋር ፍቅር አንደያዘው ተረዳች፤ ፊያሜታ ለሱ ብላ ህይወትዋን ትሰጣለች፤ በመጨረሻም ፊያሜታን በሞት ሮማንን በቅያሜ አጥቶ አጥቶ ብቻውን ሲቀር ልቦለዱ ይጠናቀቃል፤ ሮማን አዲስአበባ ሆና የአስቴር አወቀን ክር ካሴት ልካለት ነበር፤፤ ፊያሜታ ሮማን የላከችውን ካሴት ሰባብራ ክሩን ጎልጉላ ፊቱ ላይ የምትነበትንበት ትእይንት አይረሳኝም፤ አሁን ድንገት ጉደኛ ሀሳብ ብልጭ አለልኝ ፤ ኦሮማይን የደረሰው ስብሀት ቢሆን ኖሮ ብየ አሰብሁ፤ አንዲህ ነበር የሚሆነው፤ ሮማን እና ፊያሜታ አስመራ ተገናኝተው እየተጨዋወቱ ነው፤ -ስትገናኙ እጮኛው መሆኔን ነግሮሽ ነበር ? “አለች ሮማን ፊያሜታ ራስዋን በአዎንታ ነቀነቀች፤ “እና እጮኛ አንዳለው እያወቅሽ አፈቀርሽው?” ፊያሜታ ጸጉሯን ነስንሳ “አዝናለሁ፤ ነገሩ እዚህ ይደርሳል ብየ አላሰብኩም ነበር፤ ሕይወት አንደ ደራሽ ውሀ ገፍቶ የት አንደሚያደርሰን አናውቅም’ አለችና በስፕራይት ጠርሙስ የተቀዳ ቢራዋን ተጎነጨች፤ የቢራ ጠርሙሶች ተለቅመው ለምሽግ መስርያ ወደ ናቅፋ ስለተወሰዱ አስመራ ውስጥ የቢራ ጠርሙስ እጥረት ሰፍኑዋል፤ ለጥቂት ሰከንዶች በዝምታ ተዋጡ፤ “ ጸግሽ ነገ ወደ ግንባር ይሄዳል” አለች ሮማን፤ “ አውቃለሁ “ መለሰች ፊያሜታ፤ “ በወጣበት ይቀራል የሚል ስጋት አለኝ ‘ አለች ሮማን እንባ ባቀረረ አይን የናቅፋ ተራራ ወዳለበት አቅጣጫ እየተመለከተች” “ አትስጊ፣ ሻእቢያ ጋዜጠኛ አይገድልም” አለች ፊያሜታ በውስጥ አዋቂ ስሜት ; “አይምሰልሽ፤ ሻቢያ ከመድፍ በላይ ብእር፣ ወረቀትና ካሜራ ያሰጋዋል፤ ጠመንጃቸውን የሚያሙዋሹት ፀግሽን በመግደል ይሆናል” ፊያሜታ ዝም አለች፤ ሮማንም በጸጥታ ስታስብ ከቆየች በሁዋላ፤ “የምታግዥኝ ከሆነ ለጸግሽ አንድ የመጨረሻ ስጦታ ልሰጠው አስቢያለሁ” “ምን ?” አለች ፊያሜታ፤ ‘ ጸግሽ አንችንም እኔንም እኩል አንደሚያፈቅር አውቃለሁ፤ ለሚያፈቅራቸው ሴቶች አንደ ሞት ማበላለጥ አያውቅም፤ስለዚህ በህይወቱ የመጨረሻዋን ሌሊት አብረነው አንድናሳልፍ እፈልጋለሁ፤ “የምርሽን ነው?” ፊያሜታ በግርምት ጠየቀች፤ “አንድ ጀግና ለብዙሀን ህይወቱን መስጠቱ አግባብ ከሆነ ፣ ብዙሀን ላንድ ጀግና እቅፋቸውን መስጠታቸው ተገቢ ነው” አለች ሮማን ፍርጥም ብላ፤ ያን እለት ማታ፣ ፀጋየ በሮማንና በፊያሜታ መሀል ፣ባራት ጡቶች መሀል፣ አንደተንጋለለ በልቡ አንዲህ አለ፤ “ ይገርማል ! ሻእቢያና ደርግ ስልጣንን እንዲህ መጋራት ቢያውቁ ኖሮ ባፍሪቃ ቀንድ ለዘላለም ሰላም ይነግስ ነበር” https://t.me/matter_of_facts
1 154
5
በረንዳ (በእውቀቱ ስዩም) ባለፈው ከያሬድ ሹመቴ እና ከምኡዝ ጋራ የሆነ ምግብ ቤት በረንዳ ላይ ቁጭ ብለን ምሳ ስንበላ አንድ ጎስቆል ያሉ አዛውንት መጡና “ልጆቸ ርቦኛል “አሉን ምኡዝ ፣ “ካለ ይስጥዎት” አላቸውና መብላቱን ቀጠለ፤ ያሬድ ምኡዝን ክፉኛ ገላመጠውና’ ‘ አባቴ ቁጭ በሉና ከኛ ጋር ይብሉ” ብሎ ጋበዛቸው፤ እኔ አዛውንቱ እንዲበሉ ፈልጊያለሁ፤ ግን አብሮ መብላቱን ልቀበለው አልቻልኩም፤ ስለዚህ “በልተን ሲበቃን የተረፈውን እንሰጣቸዋለን” የሚል ለጽድቅ የማያበቃ ለኩነኔም የማይዳርግ ሀሳብ አቀረብኩ፤ ያሬድ ግን አመረረ “ሂዱና ታጥበዎ ይምጡ አባቴ” አላቸው፤ ምኡዝ በንዴት ጨሰ፤ “ለምን ሜቄዶኒያ ቁጥር 2 ብለህ አትከፍትም?” ብሎ አንባረቀበት፤ “ምንድነው ችግርህ ? “ አለው ያሬድ; ምኡዝ ለወሬ የማይመች ሰፊ ሀተታ አቀረበ፤ ሲጨመቅ ይህን ይመስላል፤ (አንድ ሰው ራሱን መመገብ የማይችል ከሆነ፤ ሰነፍ ነው፤ አለያም ደደብ ነው፤ አለያም አቅመቢሰ ነው፤ ወይም አመለ ቢስ ነው፤ ከሰዎች ጋር ተስማምቶ መስራት አይችልም፤ ታድያ አንዲህ ያለው ሰው ለመኖር አይመጥንም፤ ብትረዳው አታሻሽለውም፤ ስታበላው በምድሪቱ ላይ ሸክም የሚሆንበትን ጊዜ ታራዝምበታለህ እንጂ አትጠቅመውም ) ሰውየው ታጥበው መጥተው ከኛ ጋራ መብላት ጀመሩ፤ ሰማንያ ያህል የቴኒስ ኩዋስ የሚያካክሉ ጉራሾችን ወዳፋቸው ከወረወሩ በሁዋላ በረጅሙ ተንፍሰው “ ሆሆ ለዚህ ሆዴ ይጠላኛል ዘመዴ አለች እርያ” ብለው ተረቱ፤ ከዚያ ወደኔ ዞር ብለው - “ አጅሬው ለካ ይቺን እየዋጥህ ነው የጉሬዛ ሙሽራ የመሰልከው” አሉና ብቻቸውን ሳቁ፤ ከዚያ ወደ አስተናጋጁዋ ዞረው “አንቺ ቂንጥራም እስቲ አንድ ሲንግል ድራፍት ወዲህ በይ “ ብለው ጮሁ፤ ‘አባቴ ስሚናገሩት ነገር ጥንቃቄ ያድርጉ፤ ደሞ እዚህ ድራፍት አይሸጥም” አለ ያሬድ፤ አዛውንቱ የያሬድን ግሳፄ ከመ ገብስ አልቆጠሩትም፤ በር ላይ ቆሞ ለውዝ ወደ ሚሸጠው ልጅ ልጅ እየጠቆሙ” ያን ጥንዚዛ ባርያ ብንለከው ከጎረቤት አያመጣልንም ?” አሉ፤ በመጨረሻ ያሬድ “ሚስት አለዎት ? ` በማለት ጠየቃቸው፤ “እሱማ አለችኝ” አሉ በታከተ ድምጥ፤ “የተረፈውን ይውሰዱላት” አዛውንቱ ፈገግ ብለው የመለሱትን ባልፅፈው ደስ ይለኝ ነበር; “ምሽቴማ ይሄን ተቀመሰች ጥጋብዋን አልችለውም፤ ባይሆን ለውሽማየ እቁዋጥርላታለሁ’ https://t.me/matter_of_facts
1 091
6
(ተስፋዬ ሀይለማርያም) ባሻዬ! ምክር ቤታችን የሥራ ዘመኑን ጨረሰ አሉ? ምክር ቤቱ በ5 ዓመቱ ውስጥ የዶክተር ደሳለኝ ጫኔን የፀጉር ዕድገት ያህል እንኳን ሳያድግ ተሰናበተ። በአንድ አገር ውስጥ የሚገኙ የምክር ቤት አባላት ስብሰባ ላይ አንዱ የምክር ቤት አባል እጁን አውጥቶ እንዲህ አለ፣ " የተከበሩ አፈ ጉባዔ፣ ከዚህ ምክር ቤት አባላት ውስጥ ግማሾቹ ደደቦች ናቸው" "የተከበሩ የምክር ቤት አባል፣ ንግግሮ ትክክል አይደለም። ከአንድ የምክር ቤት አባል አይጠበቅም። እባክዎን ንግግሮን አስተካክለው ይናገሩ!" "እሺ የተከበሩ አፈ ጉባዔ ይቅርታ እጠይቃለሁ። ንግግሬንም አስተካክዬ እናገራለሁ። ከዚህ ምክር ቤት አባላት ውሰጥ ግማሾቹ ደደቦች አይደሉም " "የተከበሩ የምክር ቤት አባል ማስተካከያውን ተቀብለናል። ወደሚቀጥለው አጀንዳችን እንገባለን" ህዝቡም ከመቀመጫው ተነስቶ አጨበጨበ። ባሻዬ! ምክር ቤታችን በጭብጨባ ተወልዶ በጭብጨባ ተሰናበተ። https://t.me/matter_of_facts
865
7
አልፎሂያጅ ትዝታ (በእውቀቱ ስዩም) ሰሞኑ የምርቃት ሰሞን ስለሆነ ነው መሰል የግቢ ትዝታ ተቀሰቀሰብኝ፤ ከማይረሱኝ የዶርማችን ተማሪዎች አንዱ ሚኪያስ ነበር፤ ረጅምና ጎበጥ ያለ ነው፤ ለምንም ነገር ትግስት አልነበረውም፤ ለምሳሌ ካፌ ወረፋ መጠበቅ አይሆንለትም ፤ በጊዜው አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ምግባቸውን በወረፋ አንዲያነሱ አይገደዱም ነበር፤ ሚኪ በጥቁር ገበያ የገዛውን ጥቁር መነጥር ገድግዶ ፣ በበትር ወለሉን እየዳበሰ ሰልፉን ጥሶ ይገባና ምሳውን ይረከባል ፤ መጀመርያ አጭበርባሪነቱን እያየሁ፣ ምን አይነት ይሉኝታ ቢስ ሰው ነው እያልሁ አስበሳጭበት ነበር፤ እየቆየሁ ግን እኔም የወረፋ ሰልፍ እየሰለቸኝ መጣ፤ ከጥቂት ቆይታ በሁዋላ፣ ሚኪያስን እየመራሁ በመግባት የካፌው ልዩ ጥቅም ተካፋይ መሆን ጀመርሁ፤ ሚኪያስ ማጥናት አይወድም፤ ጊዜውን የሚያሳልፈው ከተማውን በመዞር በማውደልደልና የመነን ተማሪዎችን በመላከፍ ነው፤ እንዲያም ሆኖ ፈተናው ጥቂት ቀናተ ሲቀሩት ለክፉ ቀን ያስቀመጣቸውን አጤርራዎችን አጥንቶ ያልፋል፤ የሆነ ቀን ነው፤ ፈተና ሁለት ቀናት ብቻ ቀርተውታል፤ሚኪያስ ዶርማችንን ከፍቶ ገባ፤ ዙርያ ገባውን ቃኘ፤ ሁለቱ ደባሎቻችን ኬኔዲ ማደር መርጠው ሄደዋል፤ የቀረነው እኔና ዛዛ ጨቡ ብቻ ነን ፤ ዛዛ ጨቡ በደቡብ ክልል የዱራሜ ተወላጅ ነው፤ የሰባተኛው ቀን የአድቬንቲስት የሚባል እምነት ተከታይ እንደነበር ትዝ ይለኛል ፤ የወጣለት ቸካይ ነበር ፤ ማጥናት ከመውደዱ የተነሳ አንዳንድዜ የሚጠና ነገር ሲያልቅበት ያስረኛ ክፍል የጆግራፊ ደብተሩን ሳይቀር ይገርባል ፤ ‘ምን ያረግልሀል?’ ስለው “ ጥሩ ትዝታ ስለሚቀሰቅስብኝ ነው” ይላል፤ ከሳምንቱ ስድስቱን ቀን ከወረቀት ጋር ተቆራኝቶ ያሳልፋል፤ ቅዳሜ ላይ ግን የፈሰሰ ውሀ አያቃናም፤ እግሩን ተጣጥቦ ቆጥ አልጋው ላይ ቁጭ ብሎ እንደ እግዜር ለማረፍ ይሞክራል፤ ግን መቦዘንም ለካ የተለየ ስጦታ ይጠይቃል፤ ብዙ ሳይቆይ ግዙፍ መጣፍ ቅዱስ ገልጦ መቸከል ይጀምራል፤ ሚያኪያስ ገንቦ እሚያህል ቀይ ፌርሙስ አለው፤ የፌርሙሱ ማሞቂያ ስለረገፈ በፌርሙስ ስም የሚንቀሳቀስ ማንቆርያ ነው ብንለው ይሻላል፤ የዶርሙ ጀማ ፌርሙሱን ሳይቤርያ የሚል ስም አውጥቶለታል፤ አንዳንዴ እንዲያውም በሶ ይበጠብጥበታል እያሉ ያሙታል፤ ከከሸፈው ፌርሙስ “ ቡና እንደ ወረደ” ማለቴ” ቡና እንበረደ “ቀድቶ ባንድ ትንፋሽ ጨለጠ፤ ከዚያ ቁራጭ ሻማ ከኪሱ አውጥቶ በላይተር ለኮሰ፤ -ማብራት ኢያለ ሻማ ማለኮስ ለሚን አስፋለገ ?” አለው ዛዛ -በኩራዝ እያጠናሁ ስላደግሁ ሙዱን ለማምጣት ፈልጌ ነው’ በማለት መለሰ ሚኪያስ፤ ከዚያ ደብተሮቹን ደርድሮ ዘረጋጋና እንደ ጦርሜዳ ካርታ ለሁለት ደቂቃ ያክል ተመሰጠባቸው፤ ብዙም አልቆየ፤ አፉን በየማእዘኑ ከፋፍቶ ካዛጋ በሁዋላ ፣ “አራት ሰአት ተኩል ላይ ቀስቅሱኝ አደራ “አለና ያልጋውን መሰላል በኩራት መውጣት ጀመረ፤ ወደ ጨረቃ የሚሄድ መንኮራኩር መሰላል ላይ የሚወጣ እንጂ የቆጥ አልጋ የሚሳፈር አይመስልም፤ አራት ሰአት ተኩል ሲሆን ዛዛ ጨቡ ወደ ኤርምያስ ቆጥ ወጥቶ ኮሌታውን ጨምድዶ ይወዘውዘው ጀመር፤ የሚቀስሰው ሳይሆን የሚበቀለው ነው ሚመስለው፤ እኛ መከራችንን እያየን እያጠናን አንተ ያለ ሀሳብ እንቅልፍህን ትለጥጣለህ የሚል ነው የሚመስለው፤ -ምንድነው? ‘ “አለ ሚኪያስ ከንቅልፉ ብንን ብሎ እየተካሄደ ያለውን ነገር ለመረዳት እየሞከረ፤ -አራት ሰአት ታኩል ላይ ቃስቅሱኝ ቢለህ ናበር ‘’ አለ ዛዛ፤ ሚኪያስ ፣ ከምሽቱ አራት ሰአት የሚባለው ነገር የተፈጠረበትን ቀን ሳይረግም የቀረ አይመስለኝም፤ -በቃ ስድስት ሰአት ላይ ቀስቅ- አለና ቀስቅሱኝ ከሚለው ቃል ውስጥ” ሱኝ” የምትለዋን ለኛ ጥሎልኝ እንቅልፍ ጣለው፤ ስድስት ሰአት ላይ እኔ በተራየ ቆጡ ላይ ወጥቸ ‘ ሚኪ ሚኪ አትነሳም ወይ?’ በማለት ጮህሁ፤ በጊዜው ፣እነ ዋለልኝ መኮንን ያሳትሙት የነበረውን ታገል መጽሄት ማንበብ አዘወትር ስለነበር፣’ አትነሳም ወይ?’ የሚለው ቃል ካፌ ሲወጣ የሆነ አብዮታዊ ቃና ነበረው፤ ሚኪያስ ብድግ አለና ከንፈሩ ላይ የቀረውን ጣፋጭ ህልም አጣጣመ፤ ከዚያ ደግሞ ለመተኛት ሲያሙዋሙቅ፣ -ተነስኮ ነው የምልህ ‘ አልሁት በታላቅ ቁጣ፤ ሚኪ በተቀራራቢ ቁጣ እንዲህ አለኝ ፤ -ጀ-ህ ለዘላለም አይነሳልህና ብነሳ ባልነሳ ምን አባህ አገባህ?’ ከአመታት በሁዋላ ቤተሰብ ልጠይቅ ስሄድ እግረመንገዴን ለአለቃ ክንፌ ተናግሬ ርግማኑ እንዲያከሽፉልኝ አድርጊያለሁ፤ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ግለሰብንም ሆነ ህብረተሰብን ከማንቃት ተቆጥቤ ኖርሁ፤ https://t.me/matter_of_facts
1 315
8
ቅንጦትን ስሻ (በእውቀቱ ስዩም) ለነገ አይልም ፣ ከላይ ሲያዳላ ላንደኛው ቴስታ፣ ለሌላው ቴስላ፤ እኔም በፈቃድ፣ ዝተት ለብሼ በፎቆች መሀል፤ ድንኩዋን ቀልሼ ቃርሚያ ፈጭቸ፤ ኩርማን ጋግሬ ጎመን አስግሬ እንጀራ አጥምጄ በቃኝ ማለትን ፣ተለማምጄ ስኖር፣ ከሌላው፣ አያዳላልኝ ቅንጦትን ስሻ፣ አንቺን ላከልኝ:: https://t.me/matter_of_facts
1 332
9
ሁኔታው (በእውቀቱ ስዩም) ድሮ ልጅ እያለን ‘ንግድ የጀመርኩት አንቁላል በመሸጥ ነው’ የሚሉ ባለሀብቶች በጎረቤት ቲቪ ይታዩ ነበር፤ አሁን ጎልምሸ ሳስበው ‘ እኮ አንዴት?’ እያልሁ ራሴን እጠይቃለሁ፤ ይሸጡት የነበረው እንቁላል ምናልባት የድራጎን እንቁላል ይሆን ? የዘንድሮ ኑሮ ሰውን ሁሉ ባለ አምስት ኮከብ ስስታም አድርጎታል፤ ባለፈው ስድስት ኪሎ ካምፓስ ግቢ ውስጥ ጥገኝነት አግኝተው ከሚኖሩ ከሲታ ውሾች አንዱ የህግ ዲፓርትመንት አካባቢ የበቀለውን ሳር ሲቀማምስ አየሁት፤ የምሬን ነው፤ ከጥቂት አመታት በሁዋላ ያዲስአበባ ውሾች ባጠቃላይ ከበጎች ጋር ሳር መሻማት ይጀምራሉ፤ የዝግመተ-ለውጥ አሰራር አንዲህ ነው፤ መዲናይቱ ውስጥ ያሉ ምግብ ቤቶች ደንበኞች የጋጡትን አጥንት መጣል ትተዋል፤ አብዛኛው ተመጋቢ አጥንት አንደ ሽንብራ ካልቆረጠመ የበላ አይመስለውም፤ ቅቅል ለመብላት አቅዶ የሚወጣ ሰው ዘነዘና አንደ አጭር ምኒሽር ታጥቆ ነው የሚወጣው ፤ ባለፈው አንዱ የሆነ የፍየል ቅልጥም እንደ ሺሻ ሲስብ ከቆየ በሁዋላ ተቆርጦ የቀረ መቅኒ መኖር አለመኖሩን ለማረጋገጥ አንደ ቴሌኮፕ አይኑ ላይ ደገነው፤ እኔ አምልህ፤ ዠለሳዊ! ከኦጋዴን አስከ አድዋ ድልድይ ድረስ በእግሩ ከመጣ ፍየል መቅኒ መጠበቅህ እምገርም እምደንቅ ነው፤ አንዳንድ ቅቅል ቤቶች ደግሞ፣ ለመቆርጠም የሚያዳግቱ አጥንቶችን ለቻይኖች ይሸጡላቸዋል ሲባል ሰምቻለሁ፤ ቻኖች ባገለገለ አጥንት የተቀቀለ ጎመን ቾፕስቲክ ያስቆረጥማል ብለው ያምናሉ፤ ባለፈው አንዱ ባለንጀራችን ፣ ላንዱ ነዳይ አስር ብር ዘረጋለትና ዘጠኝ ብር ካልመለስክልኝ እያለ ሲጨቃጨቅ አይቸው አፍሬ ልሞት! እሱ ግን የኔን ሩቡን ያህል አላፈረም፤ ደሞ መልሱን ከተቀበለ በሁዋላ ከለማኙ ፊትለፊት ተገትሮ ቀረ፤ ‘መንግስተ ሰማያትን ያዋርስልኝ ‘ የሚል ምርቃት እየጠበቀ አንደሆነ ጠርጥርያለሁ፤ በቀደም ደግሞ አንድ ወዳጃችን እንዲህ እያለ ሲያማርር ሰማሁት፤ ‘ድሮ ሲደብረኝ ጫት በመቃም ድብርቴን ረሳ ነበር፤ አሁን የጫት ዋጋ ሰማይ ነካ፤ ምን ልልህ ነው፤ ድሮ በሱስ እደበቅ ነበር ፤ አሁን ሱስ ራሱ እኔን ሲያየኝ መደበቅ ጀምሩዋል’ https://t.me/matter_of_facts
1 548
10
እንዴት እየኖርን ነው? (በእውቀቱ ስዩም) ጥሩወርቅ ገና ለጋ እያለች፣ አጤ ቴዎድሮስ በጦርሜዳ ላይ ማርከው በግድ አግብተዋት እየከፋት ትኖር ነበር ፤ ከዚያ አንግሊዝ መጣና የባልዮውን መንግስት አፍርሶ ከደባሪ ትዳር ገላገላት ፤ ግን በነጻነት ከወገኗ ጋር አልቀላቀላትም፤ በምርኮኝነት ወደ አንግሊዝ ሊወስዳት ወሰነ፤ መንገድ ላይ ትታመም ጀመር ፤ በቃሬዛ ስትጉዋጉዋዝ የተመለከታት አንድ ከማራኪው ወገን የሆነ ሰው “ እቴጌ በርታ በሉ ይድናሉ “ ብሎ ሊያጥናናት ሞከረ፤ እስዋ ግን ይህን መለሰች፤ “ባክህ ለመሞት ጊዜየ ተወስኑዋል፤ ደሞ ብሞትም አላዝንም ፤ጥንቱን ስፈጠርም ለመከራ የተመደብሁ ነኝ፤ አሁን መድሀኒያለም ቃል ወደ ገባው ህይወት ለመድረስ ብቻ ነው ምኞቴ” ብርያን ማጌ ዘመናዊ የእንግሊዝ ፈላስፋ ነበር፤ የሆነ ጊዜ ላይ ህይወቱን ዞር ብሎ አይቶ የተናገረውን በራሴ አባባል ሳቀርበው እንዲህ ይነበባል፤ “ህይወት ትርጉም እልባ መሆኑ ተረጋገጠ አንበል ፤ ከሞት በሁዋላም ያለው እጣየ ለዘላለም ተረስቶ መቅረት መሆኑን በማያሻማ መንገድ አውቂያለሁ እንበል ፤ ከዚህ ሁሉ እውቀት በሁዋላ ፣ ድጋሜ መወለድን ትመርጥ ነበር ተብየ ብጠየቅ፣ ‘ አዎ ‘ብየ ጮክ ብየ እመልሳለሁ ፤ መኖሬን ወድጀዋለሁ፤ በህይወቴ ላይ ብዙ ችግር ቢያጋጥመኝም ፣ በኔ ባህርይ ላይም ችግር ቢኖርም ፣ በዚህ ምድር ላይ በመኖሬ በቃል ልገልጠው የማልችል የአመስጋኝነት ስሜት ይሰማኛል፤ መሞትን ሳስብ ፍርሀት ይሰማኛል ፤ ግን መጭው ዘላለማዊ ውድመት ፣ በዚህ ምድር በህይወት ለቆየንበት ፣ልንከፍለው የሚገባ ዋጋ እንደሆነ ይሰማኛል’ ሁላችንም እንሞታለን፤ እንደ አስደሳቹ ድምኣዊ ሰማኸኝ በለው በህመም፤ ወይም ከወሎ ወደ አዲሳባ ሲመጡ መሬት አንደከዳቸው መንገደኞች በአደጋ ሊሆን ይችላል፤ እየተዋለድን ወይ እየተጋደልን የምንሞትም አንኖራለን፤ ዋናው ጥያቄ እንዴት ኖሩ? የሚለው ነው፤ ይቹን ልጥፍ የሚያነቡት ርስዎ እስካሁን የኖሩትን ህይወት አንዴት ነው የሚገመግሙት ?ኑሮዎ አንደ እቴጌ ሞትን የሚያስናፍቅ ነው ፤ ወይስ አንደ ፈላስፋው ደጋግሞ መወለድን የሚያስመኝ ነው ? ወይስ አንዳንድ ቀን ‘በሞትኩኝ’ ፤ በሌላ ቀን ‘እንኳን ኖርኩኝ ‘ እያሉ ያዘግማሉ? https://t.me/matter_of_facts
1 249
11
አምባሩን ያጌጠበት ሌላ... (አሌክስ አብርሃም) አንድ ቀን ከመዝሙርና ከግዜር ቃል ውጭ ምንም የማያውቅ ጴንጤ ጓደኛየ ፊቱ ቅጭም ብሎ መጣና እቤቴ አደረ። ሌሊት ድንገት ተነሳና ተንበርክኮ እያለቀሰ መፀለይ ጀመረ። ለምን ጌታ ሆይ ለምን? እያለ! እና በመሃል በቀስታ ሲዘምር ተመሰጨ ሳዳምጠው መዝሙሩ ለየት አለብኝ።ገርሞኝ በደንብ አዳመጥኩት። አሃ ይሄ ነገር .... ጧት ቁርስ ስንበላ ጠየኩት "ይሄ ዘፈን ጌታን ተቀበለ እንዴ?" "የቱ ዘፈን?" የፀጋየ እሸቱ ... ፀጋ እሸቱ ማነው? ፀጋ አላልኩም ፀጋየ ነው...ሌሊት እየፀለይክ "አምባሩን ያጌጠበት ሌላ ተከሳሽ አምሮት ያጣ ገላ" ስትል ነውኮ ያደርከው። "ጌታ ይገስፅህ" አለና ሳቁ አመለጠው። ለካስ ሚስኪን ወዳጀ አንዲት የቸርች እህት "አባለክ" ተብሎ ከቸርች ታግዶ አንጀቱ እርር ብሎ ነው። ብዙ ጴንጤወች እንደሚሉት "ታክሲ ውስጥ የሰማው ዘፈን" አእምሮውን ተቆጣጥሮት ይሆናል። አሳዛኙ ነገር ትክክለኛው አባላጊና ይሄ ሚስኪን ስማቸው ከነአያት ከመገጣጠሙ ውጭ ምንም ግንኙነት አልነበራቸውም። የልጅቱ የተከበሩ ቤተሰቦች ማርገዟን ሲያውቁ አበዱ። ወደክፍለ ሐገር ላኳትና በስልክ ሲያናዝዟት ስሙን ተናገረች። ሽማግሌወች ደውለው ሲጠይቋትም ደገመችው። ሽማግሌወች "አገኘነው" አሉና ሚስኪን ወዳጀ ሻላላላባ እያለ ሲሄድ የምን ሻላላላባ ነው! ባልተገባ.. ባልተቀደሰ... ባልተፈቀደ...ባልተወደደ.. መንገድ ጌታን በድልሃል... የምዕመኑንም አሳዝነሀል፣ ቤተክርስቲያኗ በመተዳደሪያ ደንቧ አንቀፅ ቀ፣ ንኡስ አንቀፅ ጰ መሠረት ለአንድ ዓመት ከማንኛውም አገልግሎት ታግደህ እየፆምክ እየፀለይክ በንስሃ እንድትቆይ ወስናለች።" ነገሩ ተጣርቶ ወዳጀ ላልሰራው ሀጢያት በፆም ከስቶ ሲመለስ፣ ጉባኤው ፊት በስህተት መታገዱ ተገለፀ። ፓስተሩ የተናገረው ነገር ግን ብስጭት አደረገው ። "ሰይጣን የቅዱሳንን ልብ ለማውረድ በሐሰት ይወነጅላል ነፃ የሚያወጣ አምላክ ግን ስራ ላይ ነው ወገኖቸ.....እና ወንድማችን እህታችንን አላባለገም፤ ጌታ ይረዳዋል ወደፊትም አያባልግም"😁 https://t.me/matter_of_facts
1 218
12
አከራይ ተከራይ ሲባል ምንጊዜም ትዝ የሚለኝ አስቂኝ ነገር... (አሌክስ አብርሃም) አንድ ሰፊ የግለሰብ ግቢ ውስጥ ተከራይቸ እኖር ነበር። ብዙ ነበርን ተከራዮቹ ፤ ከእኔ ቤት ቀጥሎ የሚኖረው ተከራይ አንድ አስተማሪ ሲሆን ቅዳሜ ቅዳሜ ብቻ ጢንቢራው እስኪዞር ከመስከርና "ገንዘብ አለያየን ደሃ በመሆኔ" እያለ ከመዝፈን ውጭ ሽቁጥቁጥ፣ የግቢውን በር እንኳን ሲያልፍ ጫማውን ሊያወልቅ የሚዳዳው ትሁት ሰው ነበረ። አንድ ቅዳሜ ግን ምናባቱ...ማለቴ ምን ጠጥቶ እንደመጣ እንጃ ግቢውን በአንድ እግሩ አቆመው። የሆነ ለማሽቃበጥ የሚረዳ መጠጥ ይመስለኛል የጠጣው። ገና ከመግባቱ "ሁላችንም ኪራይ መጨመር አለብን " ብሎ ጮኸ። "አከራዮቻችን ዝም ስላሉ ብቻ ዝም ማለት ልክ ነው? አይደለም! ቤት መስራት ብዙ ዋጋ ያስከፍላል ካርታ አለ...ፕላን አለ...ለመሃንዲስና ምናምን ጉቦ አለ...ብሎኬት አለ...ሲሚንቶ አለ...ለአከራይ ማን ያስብለት?... መሯቸው ሸጠውት ቢሄዱስ? እኔ ከነገ ጀምሮ ሃምሳ ብር ጨምሪያለሁ...ሁልሽም ኪራይ ጨምሪ...እንትና መቶ ብር...እንትና ስልሳ ብር ... አንተ አብርሃም ሰባ ብር ፣ የውሃም እኛ መክፈል አለብን.....(በቃ ይሄ ሰው ራሱን ሊያጠፋ ወስኗል ማለት ነው ብየ አሰብኩ) አከራያችን ጋቢያቸውን ለብሰው ብቅ አሉና እንደወትሮው "እንዲህ ከረበሽክ ከነገ ጀምሮ ቤት ፈልግ" ይሉታል ብለን ስንጠብቅ ፍቅር በሆነ ድምፅ "መምህር ና እራት ብላ እስቲ... " ወሬ ልመለከት ስንወጣ አከራየ ጋር እንደመጋኛ ተገጣጠምን። ወደእኔ እያዮ "የሚጠጣ ሰውኮ በሆዱ ክፋት የለም..." 🤔 እና ልጠጣልወት? https://t.me/matter_of_facts
1 078
13
የሰሞኑ የታርጋ ዋጋ ጋር በተያያዘ ከሚሰጡ ኮሜንቶች የተመቸኝ መንግስት ህዝቡን በደንብ ሲያውቀው በደንብ አድርጎ ናቀው
የሰሞኑ የታርጋ ዋጋ ጋር በተያያዘ ከሚሰጡ ኮሜንቶች የተመቸኝ መንግስት ህዝቡን በደንብ ሲያውቀው በደንብ አድርጎ ናቀው
1 134
14
ዛሬም እዚያው (በእውቀቱ ስዩም) ከጥቂት ቀናት በፊት የድሮ ጋዜጣ (1963) እያነበብሁ ለመሳቅም ለማዘንም ቸግሮኝ ነበር ፤ ጋዜጣው በፊትለፊት ገጹ ሰውነታቸውን ስለሚያዳብሩ ስፖርተኞች ዘገባ አቅርቡዋል፤ ከሰውነት አዳባሪዎች መካከል ስጦታው ቀበቶ የተባለ ወጣት አነጋግሩዋል፤ ከዘገባው የሚከተለውን ልቀንጭብላችሁ፤- -“ከዝቅተኛ ቤተሰብ የሚወጡ ወጣቶች ሰውነታቸወን በሚያዳብሩበት ጊዜ የቤተሰባቸውን በጀት ያፋልሳሉ፤ ቤተሰቡ ቢበላ ባይበላ የነሱ ጉዳይ ባለመሆኑ የተገኘውን በውድም በግድም እየቀረቡ ጥማታቸውን እና ረሃባቸውን ለመወጣት ይመርጣሉ እየተባለ ይነገራል፤ ስጦታው ቀበቶ የሃያ ሁለት አመት ወጣት ነው፤ ቁርስ እንቁላል ጥብስ ወተት ያስፈልጋል፤ ምሳ የአንድ ሰው ድርሻ እንደ ጉዝጉዋዝ ትቆጠራለች፤ ራትም የተገኘውን እመገባለሁ፤ስጦታው የከረሜላ ፋብሪካ ሰራተኛ በመሆኑ የወር ገቢው ለምግቡ አታደርሰውም፤ ለሆዳም በሬ ጭድ ያዝለታል አንደሚባለው አቶ ዘለቀ ዋከኔን የመሰለ ርህሩህ ሰው ጥሎለታል፤ አቶ ዘለቀ ለስጦታ በቀን እስከ አራት ብር ባጀት መድበውለታል ፤ ከዚህ በተረፈ የተገኘውን ጥሬም ቢሆን ተመግቤ መዋል ስለምችል እንደሌሎች የምግብ እጥረት በሚየጋጥመበት ጊዜ የት ልድረስ ብየ አልጨነቅም በማለት ይናገራል” አንብቤ ስጨርስ ክፉኛ ተከዝኩ፤ አካል አዳባሪውን ወጣት ከ “ሆዳም በሬ” ስፖንሰሩን ከ “ጭድ አቅራቢ” ጋራ አነጻጽሮ ማቅረብ በጋዜጠኝነት ታሪካችን ውስጥ አቻ የሌለው አሰቃቂው ዘገባ ይመስለኛል፤ የጋዜጣው ዘገባ ብዙ ነገር ያሳስበናል ፤ አንድም፣ ምግብ በየዘመኑ እንዴት ብርቅ ሆኖብን አንደኖረ ያሳያል ፤ ስፖርተኛው ጎረምሳ ከሌላው ሰው፣- ለምሳሌ ከቢሮ ሰራተኛው የሚበልጥ የምግብ አቅርቦት እንደሚያስፈልገው ጋዜጠኛው የተረዳ አይመስልም፤ ይልቅስ ፣ ስፖንሰሩ በጋዜጠኛው አገላለፅ -ርህሩሁ ሰውየ አቶ ዘለቀ -የተሻለ ግንዛቤ አላቸው፤ ግን ዋናው ምክንያት ይሄ አይመስለኝም፤ ውስጥ ውስጡን ጋዜጠኛው በጎረምሳው ስፖርተኛ እድል የቀና ይመስላል፤ እሱንም በቀን አራት ብር እየቆረጠ የሚደጉመው ባለሀብት ሳያምረው አልቀረም፤ እንዲህ ያለ ዘገባ ሊመነጭ የሚችለው ምግብ ብርቅ ከሆነበት አገር ውስጥ ብቻ ነው ይሄ ዘገባ በወጣበት ሰሞን ቻይና ጠኒያም አገር ነበረች፤ ዛሬ ግን አብዛኛው ቻይና ብስና እስኪይዘው መብላት ይችላል፤ መካከለኛ ህይወት ያለው ፈረንጅ ምሳ ሲበላ የማየት እድል ገጥሞሀል ? ምሳ ላይ ሳይሆን ማሳ ላይ ያለ ነው የሚመስልህ፤ ይህንን ስታይ አንድን ኢትዮጵያዊ ሆዳም ብሎ መጥራት ትልቅ ግፍ አንደሆነ ትረዳለህ፤ ምግብ ላይ Appetizer , Starter, Dessert የተሰኙ ቃላት ራሱ በመዘገበ ቃላታችን ላይ የሉም፤ ከላይ የጠቀስሁት ዘገባ ከወጣ በሁዋላ ስንት የባህል አብዮት ተካሄደ? ስንት የርሻ የቴክኖሎጂ ፍሬ ተፈለፈለ ? ግን ዛሬም ወተት እና አንቁላል ብርቅ እንደሆነብን አለን፤ https://t.me/matter_of_facts
1 162
15
ምንገድ ላይ (በእውቀቱ ስዩም) በቀደም ከሆነ ቦታ ተነስቼ ወደ አልሆነ ቦታ ስራመድ ኡራኤል ፊትለፊት ካለው አስፋልት ላይ ስደርስ የሚገርም ነገር ተከሰተ፤ አንድ የጎዳና ተዳዳሪ ቡሌ በፌስታል, ሸክፎ አስፋልት እያቁዋረጠ ሳለ አንድ ሞተረኛ ከላይ ሲንደርደር መጥቶ ደንብቆ ጣለው ፤ የሸገር ሞተረኞች ለምን እንደሚካልቡ አይገባኝም፤ አለምን ከጥፋት የሚታደግ መልክት ለማድረስ የሚነዱ እንጂ የጠወለገ በለጨ የጫኑ አይመስሉም፤ ሞተረኛው ከሞተሩ ተስፈንጥሮ አስፋልቱ ዳር ተዘረረ ፤ ሞተሩ ግን በራሱ ፈቃድ እየበረረ ሂዶ ባቅራቢያው ከሚገኝ ጋራጅ ውስጥ ገብቶ ተሰወረ፤ የጎዳናው ሰውየ ተሽቀንጥሮ መንገዱ ጠርዝ ላይ ተገኘ፤ ወድያው ባካባቢው የነበረው ህዝብ ሞተረኛውን እና የጎዳናውን ሰውየ ተካፍለው ከበብ ከበብ አድርገው ቆሙ፤ ብብዙዎች ፊት ላይ ሀዘን በግልፅ ይነበባል ፤ ቢያንስ ከሁለት አንዱ አለመሞታቸው ብዙዎችን ያስደበረ ይመስለኛል ፤ እኔ ሁሌም ከተጎጂው ጎን መሰለፍ ስለሚያስደስተኝ ፣ ከጎዳና ተዳዳሪው አጠገብ ቆምኩ፤ ተጎጂው ቀና ብሎ አየኝ፤ መላከ ሞትን ያባረረ ኡራኤል መስየ ታይቸው ይሆንን ብየ ራሴን ሸነገልሁ፤ የጎዳናው ሰውየ የፈራሁትን ያህል አልተጎዳም፤ ደጋግሞ የመገጨት ልምድ ያካበተ ይመስላል፤ የቀኝ እግሩ መሀል አገዳ ላይ ብቻ የመድማትና የመጫጫር ምልክት አየሁ፤ -አይዞህ ወንድም ጥላ! በዚች እግርህን ታይበት ‘ አልሁና ከቦርሳየ ውስጥ ሁለት መቶ ብር በማውጣት ዘረጋሁለት፤ በልግስናየ ልቡ ተነክቶ ተጠምጥሞብኝ ያለቅሳል የሚል ግምት ነበረኝ፤ ‘እናትህ ትጎዳ ! (በትክክል ያለኝ እንኩዋ ከ-ትጎዳ-ይከፋል )፤ በሁለት መቶ ብር ምንላቀቅ መስሎሀል?’ አለና እጅጌየን ጥቅጥቅ አርጎ ያዘኝ; ክፉኛ አንደዞረበት ተገለጠልኝ፤ ‘አይዞህ ዠለሳዊ ! በዚህ ደግሞ ጭንቅላትህን ታይበት’ አልሁና ቸክ ፈርሜለት ጉዞየን ቀጠልሁ፤ https://t.me/matter_of_facts
1 110
16
ወይራው (በእውቀቱ ስዩም) ስለባርሴሎና ቆይታየ በቁምነገርና በጨዋታ የመዘገብኩት አለ፤ ቁምነገሩን ላዘቦት ቀን ላዘግየውና ጨዋታውን ላቃምሳችሁ፤ ባርሴሎና ወደ ሜዲትራንያን ውቅያኖስ የቀረበች ከተማ ናት፤ ባርሳዎች ወደ ሰሜን አፍሪካ ዘንበል ይላሉ ፤ ከሞሮኮዎች ጋራ ሲገናኙ አኛ የወንዜ ልጅ እንደምንባባል እነሱም የውቅያኖሴ ልጅ ይባባላሉ፤ ከተማ ውስጥ የሚርመሰመሰው የደላው፣ ያማረ የተዋበ ህዝብ ነው፤ የሴቶች ቁንጅና ከመብዛቱ የሆነ ጊዜ ላይ የተነሳ እጅ እጅ ይልሀል፤ አራት ቀናት ያክል ሆቴል ተቀምጫለሁ፤ አዘጋጆች፣ ከቁርስ በቀር ምሳና ራት የምበላበት ስምንት ያህል ካርድ ሰጥተውኛል፤ እኔ ግን የሰጡኝን ካርዱን ሁሉ አሙዋጥጨ አልተጠቀምኩበትም፤ በቀን አንድ ጊዜ ብቻ እየበላሁ ፤ ኣራት ካርድ ብቻ ተጠቅሜ ሌላውን መለስኩላቸው፤ ኤርምያስ አመልጋ በቀን አንዴ ቢበላ ለጤናው ሄኖክ ወንድም ደግሞ ለኪናዊ ተልእኮው ነው፤ አንተስ ለምን ብትሉኝ መልሴ ግልጥ ነው፤ በምግብ ከተጎዳ አገር መጥቶ ፣ አገኘሁ ብሎ ሲወጥቀው ሰነበተ አንዲሉኝ አልፈለኩም፤ ( ላንቺ ነው ኢትዮጵያ፤ ያንን የመሰለ ሳልመን ጥብስ እያማረኝ የማርኩት አንቺን ላለማስፎገር ነው🙂 ) የአውሮፓ ምግብ ብዙ አይመቸኝም፤ ያማረና የጣፈጠ ነገር በመስራት ጥልያን ፈረንሳይ ይሻላሉ መሰል፤ ግም መብል ያለው እንግሊዝና ጀርመን ነው፤ ጀርመን በድንች የቆረበ ህዝብ ነው ማለት ይቻላል፤ ግብዳ የተቀቀለ ድንች ይሰነጥቁና በውስጡ ሌላ ሚጢጢ ድንች ይቀረቅሩበታል፤ ከዚያ እንደደና ነገር አንስተው በጥርሳቸው ይመግዙታል፤ ዶነር የተባለ ምግብ መሰል መኖም አላቸው፤ ያንን ከበላህ ጤፍ የለመደ ሆድህ በጀርባህ ይዞራል፤ ለመፍሳትም ራሱ የሀኪም እገዛ ያስፈልግሀል፤ ባርሳዎች ምግባቸው የጨዋ ፣ መጠጣቸው የአማልክት ነው ፤ በየመብሉ ውስጥ ወይራ በተለያየ መንገድ ይገባል)፤ሰላጣው አሳው በወይራ ዘይት ነው ሚሰራው ፤ ዳቦው ሳይቀር ወይራ ገብቶበታል፤ እኛ ለመቆዘምያ ቆሉ አንደምንቆረጥም እነሱ ደግሞ የወይራ ፍሬ እየቀማመሱ ይደብራሉ፤ ካንዱ ጋራ ስናወራ “እናንት አገር ምን አይነት ዘይት ነው የምትጠቀሙት?” ሲል ጠየቀኝ፤ “ ልጅ ሳለሁ ከአባ ታምሩ ወፍጮ ቤት የተጨመቀ የኑግ ዘይት ነበር የምንጠቀመው፤ አሁን ዘይት ብለው የሚሸጡልንን ፈሳሽ ግን የሱፍ ይሁን ያደይ አበባ ማወቅ አልቻልኩም “ በማለት መለስኩለት፤ “ወይራ የላችሁም?” ‘ትቀልዳለህ እንዴ? አስቴር አወቀ “ክትክታና ወይራ ‘ብላ ስትዘፍን አልሰማህም ?ወይስ ጭራሽ አስቱነትን ታውቃትም? እኛኮ የናንትን አገር ኩዋስ ተጫዋቾት የጫማ ቁጥር ሳይቀር እናውቃለን ፤ እስከመቸ አናንተን ብቻ እያወቅን እንኖራለን ? በፈረቃ አንተዋወቅ እንጂ! ለማንኛውም ወደ ጥያቄህ ስመለስ ወይራ አለን፤ ግን ወይራውን የምንጠቀመው ለዘይት አይደለም፤ እናቴ ጠላ ከመጥመቁዋ በፊት ጋኑን በወይራ ታጥነው እንደነበር አልረሳም፤ በወይራ የታጠነ ጋን ጠላ ያጣፍጣል ሲባል ሰምቻለሁ፤ ከዚያ በተረፈ ደግሞ አባቴ የወይራ ሽመል ነበረው” “ጣሙ አንዴት ነው ታድያ ?” “የጠላውን የመቅመስ እድል አልነበረኝም፤ የሽመሉን ግን ካንድም ሁለቴ አጣጥሜዋለሁ፤ አና ይሄውልህ፤ በልጅነቴ ያስመረረኝን ወይራ እናንተ አገር መጥቸ ተበቀልሁት “ https://t.me/matter_of_facts
1 502
17
ሰው የፈለገ ቢሳሳት የመቃብር ሐውልት ላይ ፊደል ይሳሳታል? (አሌክስ አብርሃም) አሜሪካ ውስጥ በአገሩ ዘግናኝ ወንጀል የፈፀመ፣ ወይም ቢሊየን ብሮች የዘረፈ ወንጀለኛ ተሰዶ ይኖራል። አሁን እንደምነግራችሁ አይነት ሚስኪን ሰው ደግሞ አለ፣ በአንዲት ፊደል ምክንያት ለስደት የተዳረገ። በአንዲት ፊደል ብቻ! ባለፈው ወደሆነ ቦታ በኡበር ታክሲ እየሄድኩ ነበር። ሹፌሩ ከማሌዢያ የመጣ ትልቅ ሰው ነው። እያወራኝ "ሀገሬ ላይ በጣም አሪፍ ቢዝነስ ነበረኝ። የመቃብር ላይ ጽሑፍ እጽፍ ነበር፤ ተንደላቅቄ ነበር የምኖረው" አለኝ። ባዘነ ድምፅ። "እና ታዲያ ለምን ወደዚህ መጣህ?" "የተሰደድኩት የአንድ የተረገመ ባለስልጣን ሚስት የመቃብር እምነበረድ ላይ አንዲት ፊደል ተሳስቼ በመጻፌ፣ ሊገድለኝ ስለፈለገ ነበር" አለኝ። "እውነትህን ነው? ለአንዲት ፊደል?!" "አዎ ጌታዬ! አየህ፣ የምንጠቀመው ማላይኛ (ባሃሳ ማሌዢያ ይሉታል) በላቲን ፊደላት ነው የሚጻፈው። አንዲት ፊደል የምትፈጥረው ስህተት ቀላል እንዳይመስልህ። በእኛ ቋንቋ 'Kota' ማለት 'ከተማ' ማለት ነው። እኔም ሐውልቱ ላይ (('ባልሽ ብቻ ሳይሆን ቸርነትሽን የቀመሰው ሙሉ ከተማው አንቺን ይናፍቃል)) ብዬ አሳምሬ ጻፍኩ። ነገር ግን የሐውልቱ ምርቃት ቀን፣ ድፍን የከተማው ባለስልጣናትና ሀብታሞች በተሰበሰቡበት የተሸፈነበት ጨርቅ ሲነሳ... 'Kota' የሚለው ቃል ላይ ተሳስቼ 'a'ን በ 'e' ተክቻት ነበር። የተረገመች 'e'!" አለና መሪውን በቡጢ ነረተው። "እና 'e' ስትጨምርበት ምን ሆነ?" አልኩት። "Kote ሆነ!" "እኮ 'Kote' ምንድን ነው?" "የወንድ ብልት!" https://t.me/matter_of_facts
1 433
18
እንኳን ስደት ቻይና ያልወሰደኝ! (አሌክስ አብርሃም) በአሜሪካ እና በቻይና መካከል ያለው የእንግዳ አቀባበል ወይም የዲፕሎማሲያዊ ፕሮቶኮል ልዩነት ታዝባችኋል? አሜሪካ እንደቻይና ሰልፍ ትርኢት ብሎ ነገር የለም። ዋይት ሀውስ ትሄዳለህ የምትለውን ብለህ ፣ ምሳህን በልተህና ፎቶ ተነስተህ በአዳሪው አውሮፕላን ወደአገርህ። ቻይና እንግዶችን በደመቀ ሁኔታ፣ በብዙ ሺህ በሚቆጠሩ ሰዎች ሰልፍ እና በታላቅ ትርኢት ትቀበላለች። ያ ሁሉ ሕዝብ እንደአንድ ሰው አንድ አይነት ስቴፕ ሲከተል ይደንቀኛል። ያው የቻይና የመንግስት መዋቅር ማዕከላዊ በመሆኑ፣ መንግስት ብዙ ሰዎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ አስተባብሮ ለትልቅ ትርኢት የማሰለፍ አቅሙ ከፍተኛ ነው። ማንኛውም ሰው ና ከተባለ ሂዶ ይሰለፋል። እንዲህ ያሉ ሰልፎች የሀገሪቱን አንድነት፣ ስርዓት እና ለታላቅ እንግዳ የሚሰጠውን ክብር ለመግለጽ እንደ መሣሪያ ያገለግላሉ። ወዳጀ... ወደአሜሪካ ተሻገር... በአሜሪካ ሰዎችን የግድ በሰልፍ እንዲወጡ ማድረግ ወይም ተማሪዎችን ከትምህርት ቤት አውጥቶ እንግዳ እንዲቀበሉ ማድረግ እንደ ግለሰብ ነፃነት ጥሰት ሊታይ ይችላል። አይታሰብም። ኢንዲቪጅዋሊዝም መጅኑን ነው። ና ተሰለፍ ብትለው ፒዛውን እየገመጠና በደምበጃን ኮካውን እየከካ መሃል ጣቱን ሊያሳይህ ይችላል። እንግዳ አቀባበሉ ብዙውን ጊዜ በዲፕሎማሲያዊ ክበቦች እና በታወቁ የክብር ቦታዎች (ለምሳሌ በዋይት ሀውስ ግቢ) ብቻ የተገደበ ነው። ዋናው የመጣህበት ነዳጅ (ማነው ጉዳይ) ነው። ማንኛውም ለመንግስት እንግዳ የሚወጣ ወጪ በግብር ከፋዩ ገንዘብ የሚሸፈን በመሆኑ፣ በጣም የተጋነኑ እና እጅግ ብዙ ሰው የሚሳተፍባቸው ትርኢቶች "የሕዝብን ገንዘብ ማባከን" ተብለው በፖለቲከኞች እና በሕዝብ ዘንድ ትችት ሊያስከትሉ ይችላሉ። ቻይና እንዲህ ያለ መዘባነን የለም። ባከነ ብትል "በኡንቱዙ ካንቱዙ" ካራቴ ያባክንሃል። ሕዝብ ነህ እንጅ ምንድነህ! የሆነ ሆኖ ሶስተኛ ክፍል ተማሪ እያለሁ ስፖርት አስተማሪያችን ግንቦት 20ን ማስስፖርት? በሚባል ነገር ለማክበር ወደመቶ ሃምሳ ተማሪ መረጠ። እኔ አልፈልግም ብልም አስገድዶ ነው ያስገባኝ። ሁለት ወር አሰለጠነን (ግነት አይደለም... ከዚያ ሁሉ ተማሪ ፈፅሞ የማይሆንልኝ ወንጋራ እኔ ብቻ ነበርኩ። የግሩፕ ስራ አይሆንልኝም) የመጀመሪያው ፊሽካ ወደቀኝ፣ ሁለተኛው አምስት እርምጃ ወደኋላ፣ ሶስተኛው አስር እርምጃ በሩጫ ወደቀኝ ነጭ ጨርቅ እያውለበለቡ ሄዶ ... በጀርባ መተኛት.... ወዘተ በመጨረሻ እንግዶቹ መጥተው ትርኢቱ ቀረበ። ገና የመጀመሪያ ፊሽካ ሲጮህ ይዟዟርብኝ ጀመረ። የመጨረሻው ፊሽካ ሲነፋ ሁሉም የሮጠውን ሩጦ በጀርባው ሲለሸለሽ እኔ የእርምጃው ቁጥርና አቅጣጫ ተወጫበረብኝ። (ደሴ ሆጤ ሜዳን ካወቃችሁት) እጅ ሊሰጥ ወደጠላት ምሽግ እንደሚሮጥ ወታደር ነጭ ጨርቅ እያውለበለብኩ ሜዳውን አልፌ በካታንጋ በኩል መብራት ሃይል ግቢ ልገባ ስል ተመልካቹ ነው እጅና እግሬን ይዞ ወደሰልፉ የመለሰኝ😁 (እንኳን ቲክቶክ የሌለበት ጊዜ ሆነ ) ቲቸር ተናዶ "ገና ቦርከና ትገባለህ" አለኝ።(ቦርከናን ለማታውቁ ለእኛ ለደሴ ልጆች ከአለም አንደኛ ወንዝ ነው) ነፍሱን ይማር በወሩ ነው መሰል አረፈ። (በአንተ ብስጭት ነው ቲቸር ያረፈው የሚለኝ ልጅ አለ እስከአሁን) ኧረ በመኪና አደጋ ነው ብል፣ እኮ ብቻውን በብስጭት እያወራ መንገድ ሲሻገር...! https://t.me/matter_of_facts
1 197
19
የኛ ሴቶች የደፈሯችሁ በከንፈራቸው ነው... (አሌክስ አብርሃም) በጣሊያን ሰሜናዊ ክፍል የሚገነባ የከፍተኛ ፍጥነት ባቡር ሀዲድ አለ። የጣሊያኑን ቱሪን ከፈረንሳዩ ሊዮን ከተሞች የሚያገናኝ። ሕዝቡ ግንባታውን ተቃወመ። ምክንያቱ ደግሞ የባቡር ሀዲዱ እንዲያልፍባቸው የታቀዱት የአልፕስ ተራራዎች ሲቆፈሩ እንደ አስቤስቶስ እና ዩራኒየም ያሉ አደገኛ ንጥረ ነገሮች ሊወጡና የአካባቢውን ውሃና አየር ሊበክሉ ይችላሉ ፣ በግንባታው ምክንያት የሚፈናቀሉ ሰወችም አልተስማሙም፣ ለግንባታው የሚፈሰው በቢሊየን የሚቆጠር ዮሮ ለትምህርት፣ ለጤናና ለአገር ውስጥ መሠረተ ልማት ማሻሻያ ይዋል የሚል ነው። ይሄው መንግስትና ሕዝብ እንደተነታረከ 35 ዓመት አለፈው። No TAV (No Treno Alta Velocità) የሚባል የተቃውሞ መሀበር ሁሉ አላቸው። ታዲያ የሆነ ጊዜ ለተቃውሞ ሕዝቡ ወጣ፣ ለመከላከልም ፖሊስ ቆመጡን ይዞ ተሰለፈ። ኒና ዴ ቺፍሬ የተባለች ወጣት ድንገት ያደረገችው ነገር ዓለምን ያጥለቀለቀ ዜና ሆነ። አንዱን ፖሊስ በሄልሜቱ ላይ አማላይ በሆነ ሁኔታ ስትስመው ካሜራ ያዛት። ዓለም 35 ዓመት ከተጮኸለት ተቃውሞ ይልቅ ይች መሳሳም መሰጠችው። (ሴሰኛ ዓለም) የጣሊያን ፖሊስ ግን ጉዳዩን በቀላሉ አልተመለከተውም ። ይች ዱርየ ፖሊሴን ስማብኛለች አማላብኛለች ብሎ ፍርድ ቤት ገተራት! የጣሊያን የፖሊስ ማህበር (COISP) ሁለት ዋና ዋና ክሶችን ነበር ያቀረበው። 1. ፖሊሱ ሳይፈልግና ሳይፈቅድ በግዳጅ ስመዋለች የፆታ ትንኮሳ ነው ትቀፍደድልኝ አለ። 2. የመንግስት ባለስልጣንን መስደብ ወይም ማዋረድ ወይም ማቂያቃል ነው፤ ድርጊቱ ፖሊሱን ለማዋረድና ትንኮሳ ለማድረግ የታለመ ነው በሚል። (ልማቱን ለማሰናከል የሚል ክሰሰ ጣሊያን የለም?) ምንም እንኳን በወቅቱ አቃቤ ህግ ምርመራ ቢጀምርም ድርጊቱ ከፖለቲካዊ ተቃውሞ እና ከወቅቱ ግልፍተኝነት የመነጨ እንጂ "ወሲባዊ ጥቃት" የመፈጸም ፍላጎት የለውም በሚል ውሳኔ ተቋጭቷል። የፖሊስ መሃበሩ መሪ "እስካሁን አንድ ፖሊስ አንዲትን ሴት ቢስም ዓለም ይገለባበጥ ነበር" ሲሉ አማረሩ። እዚህ ላይ "ልጅቱ የሳመቻችሁ በከንፈሯ ነው፤ የእናንተ ፖሊሶች ሴቶቻችንን በቆመጥ ሲስሟቸው ነው የኖሩት" የሚል ሀሳብ ፀሀፊው ውልብ አለበት። (አንባቢ ሆይ በባቡር ሀዲዱ ግንባታ ከተፈናቀሉትና መርዛማ ኬሚካል መንደራቸውን ከበከለባቸው ሰወች ይልቅ ምናለ ፖሊሱ ሄልሜት ባይለብስ ኑሮ እያልክ እንደምታስብ ገብቶኛል። ምን ያለኸው ነህ?😁) https://t.me/matter_of_facts
998
20
መታያ (በእውቀቱ ስዩም) በማህበራዊ ሚድያ የሚታወቅ ጉልቤ ልጅ አለ፤ ስፖርትን አጥብቆ ይሰራል፤ መብል ላይም አይሰንፍም ፤ ደግነቱ በልቶ አስመሰጋኝ ነው፤ የተትረፈረፈ ጉልበት እንዳለው ያስታውቃል፤ የመኪና ጎማ በርግጫ መትቶ ወደ በረባሶ መቀየር የሚችል ፍጡር ነው፤ ችሎታውንና ጉልበቱን ለማሳየት ከሚጠቀምባቸው ነገሮች አንዱ ያስገርመኛል፤ ችግር ከክፍለሀገር አባርሮ ያመጣቸው ሊስትሮዎችን በርጥብ አፋቸውን እንዲሽሩ ካደረገ በሁዋላ የራስቅላቸውን በኩርኩም እየደፈጠጠ ይቦድድባቸዋል ፤ የሆነ ጊዜ ላይ አንዱን ምስኪን “ አንገቴ አንቀህ ያዘኝ “ብሎ አዘዘው ፤ እነቀኝ ባዩ ሲጀመር አንገት የለውም፤ የጎማ ክምር በቴስታ አብዝቶ ከመምታቱ የተነሳ አንገቱ ወደ ደረቱ ሰጥሞ ከሳንባው አጠገብ ጥገኝነት ጠይቁዋል፤ ምስኪኑ አንገቱን ከደረቱ ለመለየት ሲዳብስ ጉልቤው ዠለስ ከታች በጠረባ አንሳፈፈው፤ ጠረባው የተለመደው ያደግንበት ጠረባ እንዳይመስላችሁ፤ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት በፈንጅነት መመዝግብ ያለበት ነው፤ ይህ በእንዲህ እያለ የኪክ ቦክሰር ግጥሚያ አዘጋጆች የበቀደሙን አሸናፊ አንዲገጥም ጥሪ አቀረቡለት ፤ አጅሬ በክፍያ ማነስ እያሳበበ ማፈግፈግ ጀመረ፤ የቲኬቱን ሙሉ ክፍያ ቢሰጡት ራሱ የሚወዳደር አይመስለኝም፤ ይሄ ሰውየ የብዙዎቻችን ምሳሌ ነው፤ በዚህ አለም ጀግና ተብለው የሚጠሩ ሰዎች የሆነ መስዋእትነት የከፈሉ ናቸው ፤ አካልህን ሰላምህን ፣ምቾትህን ይባስ ብሎም ሕይወትህን ሳትገብር የጀግንነት አክሊል የድል ብስራት የለም፤ “ትግሉን ስትጀምር በነበረው ቁመናህ ትግሉን ከጨረስህ አልታገልህም ማለት ነው” ይላል ምኡዝ ፤ ብላቴና እያለሁ፤ በከተማችን እንዲህ ሆነ፤ ደረቱ ላይ ድንጋይ ያስፈልጣል የሚባል ሰውየ ወደ ከተማችን ብቅ አለ፤ ህዝቡ ያንድ ብር ትኬት ገዝቶ በመግባት ትርኢቱ የሚታይበትን የቀበሌ አዳራሽ አጨናነቀው፤ አስፈላጩ በጀርባው ተኛ ፤ ረዳቱ ለአቅመ ወፍጮ የደረሰ ድንጋይ ደረቱ ላይ አስቀመጠለት፤ አስፈላጩ በረጅሙ ተነፈሰና” አንት የድንባዣም ልይ! እምብርቴ ላይኮ ነው የጎለትከው፤ ምነ ትንሽ ወደ ላይ ፈቀቅ ብታረገው “ብሎ አዘዘው፤ ረዳቱ እንደታዘዘው አደረገ፤ ከዚያ ረዳቱ የበርሊን ግንብን ለማፍረስ ያገለገለ ግብዳ መዶሻ አንስቶ ድንጋዩ ላይ ማነጣጠር ጀመረ፤ አስፈላጩ ሰውየ “ ቆይ ለማሙዋሻ ያህል በመርቴሎ ሞክረው” ሲል ለመነው ፤(መርቴሎ ሚስማር ማስገቢያና መንቀያ ቲንሽ መዶሻ ናት ) ከብዙ ደቂቃዎች በሁዋላ ህዝቡ ማጉረምረም ጀመረ፤ “የምታረጉትን አድርጉና አሰናብቱን እንጂ፤ ስራ አለብንኮ ‘ አለ ህዝቡ፤ ይህን ጊዜ አስፈላጩ በጀርባው አንደተንጋለለ አንዲህ አለ፤ “ተቸኮላችሁ ህዱ ! ውጤቱ በማታው የስፖርት ዘገባ መቅረቡ አይቀርም፤ በዚያ ታልቀረበ በፖሊስና ህብረተሰብ ፕሮግራም ላይ ጠብቁት”🙂 https://t.me/matter_of_facts
995