ትምህርት ክፍል Official channel
رفتن به کانال در Telegram
ይህ በቦሌ ሰ/ም/ፀ/ቅ/ጊዮርጊስ እና ቅ/አርሴማ ቤተ ክርስቲያን አንቀፀ ምስራቅ ሰ/ት/ቤት መንፈሳዊ ጽሑፎችን እንዲሁም ወቅታዊ የቤተ-ክርስቲያን መረጃዎችን የምንለቅበት የቴሌግራም ገፃችን ነው።
نمایش بیشتر730
مشترکین
+124 ساعت
+47 روز
+930 روز
در حال بارگیری داده...
کانالهای مشابه
ابر برچسبها
هیچ دادهای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
ژوئیه '26
ژوئیه '260
در 0 کانالها
ژوئن '26
+39
در 0 کانالها
Get PRO
مه '26
+30
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '26
+17
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '26
+14
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '26
+15
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '26
+33
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '25
+28
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '25
+28
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '25
+24
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '25
+22
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '25
+23
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '25
+28
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '25
+18
در 0 کانالها
Get PRO
مه '25
+11
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '25
+22
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '25
+11
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '25
+5
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '25
+23
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '24
+16
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '24
+45
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '24
+19
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '24
+50
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '24
+64
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '24
+44
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '24
+33
در 0 کانالها
Get PRO
مه '24
+17
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '24
+26
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '24
+22
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '24
+81
در 1 کانالها
Get PRO
ژانویه '24
+176
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '23
+286
در 0 کانالها
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 01 ژوئیه | 0 |
پستهای کانال
🌿🍁🌿
ቅዱስ ሙሴ ጸሊም የሐሳብ ኃጢአቶች ያጠቁት ነበር፡፡ ሁልጊዜም ስለ እነዚህ ሐሳቦች ሊያማክረው ወደ ንስሐ አባቱ ወደ ቅዱስ ኤስድሮስ ይሔድ ነበር፡፡ ለአሥራ አራት ጊዜያት ከተመላለሰ በኋላ ቅዱስ ኤስድሮስ ከበአቱ በላይ ይዞት ወጣና ‹‹ወደ ምእራብ ተመልከትና ያየኸውን ንገረኝ›› አለው፡፡ ‹‹አጋንንት ወደ መነኮሳት የእሳት ጦሮችን ሲወረውሩ አየሁ›› አለው፡፡ ቀጥሎም ‹‹ወደ ምሥራቅ ተመልከት ፤ ምን ይታይሃል?›› አለው፡፡ ሙሴ ጸሊምም ‹‹መላእክት ጦሮቹን እየመከቱ ለመነኮሳቱ ሲከላከሉ አየሁ›› አለ፡፡ ‹‹እንግዲያውስ ማናቸው ይበልጣሉ ፤ የሚያጠቁን ወይስ የሚጠብቁን?›› ቅዱስ ሙሴ መለሰ ‹‹የሚጠብቁን!›› ወዲያውኑ ይኽን ሲናገር ክፉ ሃሳቦች እርሱን መዋጋት አቆሙ፡፡
1ኛ ጴጥ.5÷8 "በመጠን ኑሩ ንቁም፥ ባላጋራችሁ ዲያብሎስ የሚውጠውን ፈልጎ እንደሚያገሣ አንበሳ ይዞራልና፤"
ዕብ.12÷1-2 "እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፥ እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ"
ዜና መዋ. 3÷7 "ጽኑ፥ አይዞአችሁ ከእኛም ጋር ያለው ከእርሱ ጋር ካለው ይበልጣልና"
(ሰኔ 24 የቅዱስ ሙሴ ጸሊም ኢትዮጵያዊው የእረፍቱ መታሰቢያ ነው ➛ የቅዱስ ምልጃ አይለየን)
✨✨✨✨🍁🍁🍁✨✨✨✨✨✨
| 2 | بدون متن... | 119 |
| 3 | https://www.youtube.com/live/5btRxk3qKWE?si=KECZGJxWucU1u1d3 | 60 |
| 4 | #ሰኔ_21
#እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም (ህንጸተ ቤተክርስቲያን)
ሰኔ ሃያ አንድ በዚች ዕለት የአዳምና የዘሩ ድኅነት የተደረገባት አምላክን የወለደች የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የታላቁ በዓል መታሰቢያና በዓለም ሁሉ የቤተ ክርስቲያን መታነፅ መታሰቢያ ነው።
ከሁሉ አስቀድሞ ያቺ ቤተ ክርስቲያን በሐዋርያት ዘመን ብቻዋን ታነፀች።
ይኸውም ጳውሎስና በርናባስ በአሕዛብ ውስጥ በሰበኩ ጊዜ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ ከሰዎች ቤቶች በቀር ቅዱስ ቊርባንን የሚቀበሉበት ቤተ ክርስቲያንም አልነበራቸውም ነበር። ስለዚህም ወደ ጴጥሮስና ወደ ሐዋርያት ሁሉ ስለ ቤተ ክርስቲያን መታነፅ ጉዳይ እየለመኑ መልእክትን ላኩ።
ሐዋርያትም እንዲህ ብለው መለሱላቸው ክብር ይግባውና ያለ ጌታችን ፈቃድ እኛ ምንም ምን አንሠራም። ነገር ግን የምንሠራውን እስኪያስረዳን ድረስ ወደ እግዚአብሔር እየጸለዩና እየማለዱ አንድ ሱባኤ ይጾሙ ዘንድ ወደ ሃይማኖት የተመለሱ አሕዛብን እዘዙአቸው እንዲህም አዘዙአቸው።
በሱባዔውም ፍጻሜ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገለጸላቸው ሐዋርያትንም ሁሉ ከየአገሮች ሁሉ እስከ ፊልጵስዮስ በደመና ሰበሰባቸው ከእርሳቸውም ጋር ጳውሎስና በርናባስ ነበሩ ጌታችንም ባረካቸው እንዲህም ብሎ ነገራቸው "ይቺ ዕለት በእናቴ በማርያም ስም በአራቱ ማእዘነ ዓለም አብያተ ክርስቲያናት እንድታንፁ የፈቀድኩባት ናት።"
ይህንንም ብሎ ከከተማዋ በስተ ምሥራቅ በኲል አወጣቸው የቤተ ክርስቲያኒቱንም ቦታና መሠረቷን ወሰነላቸው ከእርሳቸውም ጋራ የእግዚአብሔር ኃይል ነበረ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሕንፃዋ እስከ ተፈፀመ ድረስ ደንጊያዎች በሐዋርያት እጆች ውስጥ ይለመልሙ ነበረ ጌታችንም ነዋየ ቅድሳቷን አልባሳትዋንና መሠዊያዋን አዘጋጀ።
ከዚህ በኋላ ጌታችን እጁን በጴጥሮስ ራስ ላይ ጭኖ በአራቱ ማእዘነ ዓለም ውስጥ "አርሳይሮስ" ብሎ ሾመው ይህም "ሊቀ ጳጳሳት" ማለት ነው። ለሐዋርያት አለቃ ጴጥሮስ ከጽንፍ እስከ ጽንፍ የጳጳሳት አለቃ ይሆን ዘንድ ይገባዋል ይገባዋል ይገባዋል እያሉ ሰማያውያን መላእክትና ምድራውያን ሰዎች ሦስት ጊዜ አሰምተው ተናገሩ።
ከዚህም በኋላ ጌታችን ሐዋርያትን የቊርባኑን ቅዳሴ ሥርዓት ያከናውኑ ዘንድ ለሕዝቡም ሥጋውን ደሙን ያቀብሏቸው ዘንድ አዘዛቸው እንዲህም የሚል አለ ራሱ መድኃኒታችን ቀድሶ ሥጋውንና ደሙን ለሐዋርያት አቀበላቸው። እንዲህም አላቸው በዚች ቀን የእጃቸውን ሥራ እንዳይሠሩ ሕዝቡን ሁሉ እዘዙአቸው ይኸውም በሰኔ ወር ሃያ አንድ ቀን ነው።
ከዚህም በኋላ መድኃኒታችን ከእርሳቸው ዘንድ በታላቅ ክብር ወደ ሰማያት ዐረገ። ከዚያችም ቀን ጀመሮ አባቶቻችን ሐዋርያት በዓለሙ ሁሉ ውስጥ አምላክን በወለደች በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስም ቤተ ክርስቲያን የሚያሳንፁ ሆኑ።
በቂሣርያው ሊቀ ጳጳሳት በባስልዮስ ዘመን እንዲህ ሆነ በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስም ቤተ ክርስቲያን በሠራ ጊዜ በውስጡ የእመቤታችን የማርያምን ሥዕል ይሥልበት ዘንድ ሠሌዳ ፈለገ ሰዎችም በአንድ ባለጸጋ ዘንድ ስለ አለ አንድ መልካም ሠሌዳ ነገሩት።
ቅዱስ ባስልዮስም ሠሌዳውን እንዲሰጠው ወደ ባለጸጋው ላከ ባለጸጋውም ይህ ሠሌዳ ለልጆቼ ነው አለ እንጂ ፈቃደኛ አልሆነም። ከዚያም አልፎ በመድፈር በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ላይ የስድብ ቃል ተናገረ ወዲያውኑም በድንገት ወድቆ ሞተ ልጆቹም ፈሩ ያንንም ሠሌዳ ከብዙ ወርቅና እንቊ ጋራ ወደ ቅዱስ ባስልዮስ አምጥተው የአባታቸውን በደል ያቃልልለት ዘንድ ለመኑት።
ቅዱስ ባስልዮስም ያንን ሠሌዳ ወስዶ የእመቤታችንን ሥዕል ይሥልበት ዘንድ ለሠዓሊ ሰጠው። እመቤታችንም ቅድስት ድንግል ማርያም በሌሊት ራእይ ለቅዱስ ባስልዮስ ተገለጸችለት ሥዕሏንም በዚያ ሠሌዳ ላይ እንዳይሥል ከለከለችው። ከዐመፀኛ ሰው እጅ ወስዶታልና። እጅግም ያማረ የእመቤታችን ሥዕሏ የተሣለበት የሁለት ደናግልም ሥዕል ያንዲቱ በቀኝ ያንዲቱ በግራ ሆኖ የተሣለበት ቀይ ሠሌዳ ያለበትን ቦታ ነገረችው።
ቅዱስ ባስልዮስም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ አመለከተችው ወደዚያ ቦታ ሔደ ያንንም ሠሌዳ አገኘው ወደዚያች ቤተ ክርስቲያንም በታላቅ ደስታ አመጣው።
ከዚህም በኋላ ዳግመኛ በአንድ ጣዖት ቤት ሁለት ምሰሶዎች እንዳሉ አስረዳቸው እነርሱንም አምጥቶ በመቅደሱ ፊት ለፊት እንዲአቆማቸው በላያቸውም ሥዕሏን እንዲያኖር አዘዘችው።
ቅዱስ ባስልዮስም እነዚያን ምሰሶዎች ያመጣቸው ዘንድ ሔደ መሠርያኑም ሊከለክሉት ፈለጉ ጌታችንም ኃይላቸውን ደመሰሰ እነዚያንም ምሰሶዎች አምጥቶ በቤተ መቅደሱ ፊት ለፊት አቆማቸው በላያቸውም የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሥዕሏን አስቀመጠ እግዚአብሔርም ከእነዚያ ምሰሶዎች በታች የውኃ ምንጭ አፈለቀ በውስጥዋም የሚታጠብ ሁሉ ከአለበት ደዌ ሁሉ የሚድን ሆነ።
እንዲሁም ከእመቤታችን ማርያም ሥዕል በሽተኞችን ሁሉ የሚፈውስ የዘይት ቅባት ፈሰሰ ይህ ሁሉ የሆነ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን በከበረችበት በሰኔ ወር በሃያ አንድ ቀን ነው።
በዚያችም ቀን እንዲህ ሆነ አንዲት ሴት መጥታ ታጠበች ወዲያውኑም ሁለመናዋ በለምጽ ተሸፈነ ቅዱስ ባስልዮስም ወደርሱ አስቀርቦ በእርሷ ላይ የሆነውን ጠየቃት እርሷም የእኅቷን ባል እንደወደደችና እኅቷን በመርዝ ገድላ እንዳገባችው ነገረችው። ቅዱስ ባስልዮስም ታላላቅ ሦስት ኃጢአቶችን ሠራሽ ግን ወደ እግዚአብሔር ንስሐ ግቢ ምንአልባት በደልሽን ይቅር ይልሽ እንደ ሆነ አላት በዚያን ጊዜም ምድር ተሠንጥቃ እንደ ዳታን ዋጠቻት እርሷ የረከሰች ስትሆን ወደ ቤተ ክርስቲያን መግባትን ደፍራለችና።
እኛ ሁላችን የክርስቲያን ወገኖች አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ለከበረች ድንግል ማርያም ለመታሰቢያዋ መንፈሳዊ በዓልን ልናደርግ ይገባናል ሰለ እርሷ ለአዳምና ለሁላችን ለልጆቹ ድኅነት ሆኖአልና ይህንንም በዓል ለማድረግ የሚተጋ የተመሰገነ ነው።
እርሷን ለመረጣትና ለወደዳት በሥጋም እንድትወልደው ላደረግ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በእርሷ በእመቤታችን ድንግል ማርያም አማላጅነት ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን ።
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ሰኔ ) | 160 |
| 5 | بدون متن... | 184 |
| 6 | የ2018 ዓ.ም የምዘና መርሐ ግብር ማስተካከያ
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ውስጥ ለምትገኙ ሰንሰበት ት/ቤቶች በሙሉ እንደሚታወቀው በ2018 ዓ.ም የትምህርት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት የ4ኛ ፣8ኛ እና 10ኛ ክፍል የማጠቃለያ ሀምሌ 12 መሆኑ ይታወቃል ይሁን እንጂ መንግስት አዲስ ባስተካከለው የዚህ አመት የ12ኛ ክፍል የአስኳላው ትምህርት ፈተና የሚሰጠው ከሰኔ 24 እስከ ሀምሌ 17 በመሆኑ እና መርሀ ግብሩ በመጋጨቱ በአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የሚሰጠው የ4ኛ፣8ኛ እና 10ኛ ክፍል ምዘና ወደ ሀምሌ 26/2018 ዓ.ም የተቀየረ መሆኑን እናሳውቃለን ።
በዚህም መሰረት ሰንበት ት/ቤቶች በእለቱ ተማሪዎቻችሁን እንድታዘጋጁ እና ለአንድነቱ ያላሟላችሁት እና ያላካችሁት መረጃ ካለ በ1 ሳምንት ውስጥ እንድታጠናቅቁ እናሳስባለን።
በዚህ አመት ምዘናውን የሚወስዱ ተማሪዎች ቁጥር ከ20000 በላይ በመሆኑና ቁጥሩ በጣም ስለጨመረ ምዘናው የሚሰጠው በፈተና ማእከል ስለሆነ ሂደቱን በተመለከተ ከክፍለ ከተማችሁ ትምህርት ክፍሎች ጋር በመነጋገር አስፈላጊውን ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን።
የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ትምህርት ክፍል | 201 |
| 7 | እንኳን ለቅዱስ ገብርኤል ወረሃዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
"ወደ እግዚአብሔርም በብርቱ ይጩሁ ሰዎችም ሁሉ ከክፉ መንገዳቸውና በእጃቸው ካለው ግፍ ይመለሱ።" ትን.ዮና. 3÷8
🕯ሳምንታዊው የአርብ ጸሎት🕯
👉 ውዳሴ ማርያም
👉 መሐረነ አብ
👉 መዝሙረ ዳዊት
👉ስንክሳር
🗓 ሰኔ 19ቀን 2018 ዓ.ም
⏰ ከቀኑ 12:00ሰዓት ጀምሮ
💒 በሰንበት ት/ቤቱ አዳራሽ
ኑ በህብረት ስለ ሀገራችንና ስለ ቤተክርስቲያናችን ሰላም እና አንድነት ወደ ፈጣሪያችን በጋራ እንጸልይ‼ | 167 |
| 8 | የ2018 ዓ.ም የምዘና መርሐ ግብር ማስተካከያ
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ውስጥ ለምትገኙ ሰንሰበት ት/ቤቶች በሙሉ እንደሚታወቀው በ2018 ዓ.ም የትምህርት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት የ4ኛ ፣8ኛ እና 10ኛ ክፍል የማጠቃለያ ሀምሌ 12 መሆኑ ይታወቃል ይሁን እንጂ መንግስት አዲስ ባስተካከለው የዚህ አመት የ12ኛ ክፍል የአስኳላው ትምህርት ፈተና የሚሰጠው ከሰኔ 24 እስከ ሀምሌ 17 በመሆኑ እና መርሀ ግብሩ በመጋጨቱ በአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የሚሰጠው የ4ኛ፣8ኛ እና 10ኛ ክፍል ምዘና ወደ ሀምሌ 26/2018 ዓ.ም የተቀየረ መሆኑን እናሳውቃለን ።
በዚህም መሰረት ሰንበት ት/ቤቶች በእለቱ ተማሪዎቻችሁን እንድታዘጋጁ እና ለአንድነቱ ያላሟላችሁት እና ያላካችሁት መረጃ ካለ በ1 ሳምንት ውስጥ እንድታጠናቅቁ እናሳስባለን።
በዚህ አመት ምዘናውን የሚወስዱ ተማሪዎች ቁጥር ከ20000 በላይ በመሆኑና ቁጥሩ በጣም ስለጨመረ ምዘናው የሚሰጠው በፈተና ማእከል ስለሆነ ሂደቱን በተመለከተ ከክፍለ ከተማችሁ ትምህርት ክፍሎች ጋር በመነጋገር አስፈላጊውን ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን።
የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ትምህርት ክፍል | 170 |
| 9 | በቤተ ክርስቲያናችን ሥር የሚገኘው ምግባረ ሰናይ ሆስፒታል ከህንድ ማላንካራ ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ጋር በመተባበር ከህንድ ሀኪሞችን በማምጣት የዐይን ሞራ ግርዶሽ ህክምና በነፃ ለመስጠት አቅዷል። በመሆኑም ይሄንኑ ህክምና የሚፈልጉትን በመመዝገብ ላይ ስለሆኑ በተቻላችሁ አቅም በየአጥቢያዎቻችን ያሉ አባቶች የህክምናው ተጠቃሚ እንዲሆኑ መልዕክት አስተላልፉ። | 171 |
| 10 | በቤተ ክርስቲያናችን ሥር የሚገኘው ምግባረ ሰናይ ሆስፒታል ከህንድ ማላንካራ ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ጋር በመተባበር ከህንድ ሀኪሞችን በማምጣት የዐይን ሞራ ግርዶሽ ህክምና በነፃ ለመስጠት አቅዷል። በመሆኑም ይሄንኑ ህክምና የሚፈልጉትን በመመዝገብ ላይ ስለሆኑ በተቻላችሁ አቅም በየአጥቢያዎቻችን ያሉ አባቶች የህክምናው ተጠቃሚ እንዲሆኑ መልዕክት አስተላልፉ። | 316 |
| 11 | بدون متن... | 376 |
| 12 | #ቅዱስ_ሚናስ (#ማር_ሚና)
ቅዱስ ሚናስ (ማር ሚና) በምድረ ግብጽ ተወዳጅ ከሆኑ ሰማዕታት ዋነኛው ነው። በግብጻውያን ልዩ ቦታ አለው ማር ሚናስን ጠርተው አይጠግቡትም። ምክንያቱም ከታላላቅ ሰማዕታት አንዱ በመሆኑና ዛሬም ድረስ ለጆሮና ለዐይን ድንቅ የሆኑ ተአምራትን ስለሚሠራ ነው። በተለይ ለታመመ ለደከመና ለተጨነቀ ፈጥኖ ደራሽ ባለ በጎ መድኃኒት ፈዋሽና አማላጅ ነው።
ቅዱስ ሚናስ ትርጉሙ ታማኝና ቡሩክ ማለት ነው። በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን የነበረ የደጋግ ክርስቲያኖች ልጅ፣ በልጅነቱ የቅድስና ሕይወትን ያጣጣመ፣ በዘመኑ ሰው እጅግ ተወዳጅ የነበረ፣ ሃብትን ክብርን ሥልጣንን ንቆ በጾምና በጸሎት የተወሰነ፣ በመጨረሻም በክርስቶስ ስላመነ በአላውያን ከብዙ መከራና ስቃይ በኋላ ህዳር 15 በሰማዕትነት ያረፈበት ሲሆን ሰኔ 15 ደግሞ ቤተ ክርስቲያኑ መርዩጥ በተባለ አገር የከበረችበት ነው።
#በአንድ_ወቅት፦
ዐሥራ ስምንት ቀሳውስት በሥራ ጉዳይ አቡነ ቄርሎስ ፮ኛን ለማነጋገር መርዩጥ ወደ ሚገኘው የቅዱስ ሚናስ ገዳም ጉዞ ጀመሩ። ቀሳውስቱ በጉዞአቸው መንገድ ስተው ሲባዝኑ ከአንድ የበረሓ ሰው ጋር ተገናኙ።
የበረሓው ሰው መርዩጥ የሚገኘው የቅዱስ ሚናስ ገዳም ለመሄድ መንገድ እንደሳቱ ቀድሞ ተረድቶ ነበርና "የማር ሚናስን ገዳም ነው የምትፈልጉት? በማለት ይጠይቃቸዋል። እነርሱም ችግራቸውን እንዴት እንዳወቀ በልባቸው እያደነቁ "አዎን" አሉት። የበረሓው ሰውም እየመራ ከገዳሙ አደረሳቸው አቡነ ቄርሎስ ፮ኛም ወደ በር ወጥተው ተቀበሏቸው።
ከዚያም "ምነው ዘገያችሁ? መንገድ ሳታችሁ እንዴ?" ብለው እንደ ቀልድ ጠየቋቸው። እነርሱም "አዎን! በጣም ተቸግረን ሳለን ይህ የበረሓ ሰው ደርሶልን መንገዱን አሳየን" ብለው ወደ ሰውየው ለማመልከት ዘወር ሲሉ እርሱ በአካባቢው የለም። አቡነ ቄርሎስም "መንገድ እንደጠፋችሁ ስለተረዳሁ ሚናስን ልኬላችሁ ይዟችሁ የመጣው እርሱ ነው" አሏቸው።
አምላካችን ከቅዱሱ ሰማዕት በረከትን ይክፈለን!! | 344 |
| 13 | እንዴት አደራችሁ የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት በሙሉ
እንደሚታወቀው ወር በገባ በ14 የፃድቁ አባታችንን ወርሃዊ መታሰቢያ በዓልን እናከብራለን በዛሬው እለትም ሰኔ 14/10/2018 ዓ.ም በደብራችን አውደምህረት እናከብራለን ሁሉም የሰንበት ትምህርት ቤቱ አባል ከ11:30 ሰዓት ጀምሮ እንድትገኙ እናሳስባለን።
ጸሎት በአንድ ላይ እንድናደርስ በጊዜ እንገኝ።
ሰዓት ይከበር | 212 |
| 14 | እንኳን ለቅዱስ ሚካኤል አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
"ወደ እግዚአብሔርም በብርቱ ይጩሁ ሰዎችም ሁሉ ከክፉ መንገዳቸውና በእጃቸው ካለው ግፍ ይመለሱ።" ትን.ዮና. 3÷8
🕯ሳምንታዊው የአርብ ጸሎት🕯
👉 ውዳሴ ማርያም
👉 መሐረነ አብ
👉ስንክሳር
🗓 ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም
⏰ ከቀኑ 12:00ሰዓት ጀምሮ
💒 በሰንበት ት/ቤቱ አዳራሽ
ኑ በህብረት ስለ ሀገራችንና ስለ ቤተክርስቲያናችን ሰላም እና አንድነት ወደ ፈጣሪያችን በጋራ እንጸልይ‼ | 268 |
| 15 | ከዚህ በኋላ ባለ ጠጋው ከሄደበት በተመለሰ ጊዜ በደስታ የሆነውን የመሰንቆና የእንዚራ ድምፅ ሰምቶ ‹‹ይህ የምሰማው ምንድነው›› ብሎ ጠየቀ፡፡ እነርሱም ‹‹ስሙ ባሕራን ለተባለ የአንተን ደብዳቤ ላመጣ ጐልማሳ ሰው ልጅህ ዕገሊትን አጋቡት፡፡ እነሆ ዓርባ ቀናት በሰርግ ላይ ነው፡፡ ገንዘብህንና ጥሪትህን ሁሉ ወንዶችና ሴቶች ባሮችህን አንተ እንዳዘዝህ ሰጥተውታል›› አሉት፡፡ ይህንም በሰማ ጊዜ ደንግጦ ከፈረሱ ላይ ወደቀ በድንገትም ሞተ፡፡
ባሕራንም ከዚህ በኋላ የቅዱስ ሚካኤልን ዝክር በሚገባ እየዘከረና ለቤተ ክርስቲያኑም እየታዘዘ የሚያገለግል ሆነ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዓሉን በሚገባ አክብረን በረከት እንድንቀበል ይርዳን፤ የቅዱስ ሚካኤል የረድኤቱ ኀይል በሀገራችን በሃይማኖታቸው ምክንያት ከተሠውት የክርስቲያን ወገኖች ጋር ይሁን፤ለዘለዓለሙ አሜን፡፡
ምንጭ፡– ድርሳነ ቅዱስ ሚካኤል፣ ስንክሳር ዘወርኃ ሰኔ | 259 |
| 16 | ሚካኤል ማለት በዕብራይስጥ ቋንቋ ሚ-መኑ፣ካ-ከመ፣ኤል-አምላክ መኑ ከማከ አምላክ? እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው? ማለት ነው።(ኪ.ወ.ክ)።
ቅዱስ ሚካኤል ዲያብሎስ በትዕቢቱ ፈጣሪነትን ሽቶ በዓለመ መላእክት ሁከት ባስነሣ ጊዜ የቅዱሳን መላእክት ፊታውራሪ ሆኖ ዲያብሎስን የተዋጋ ጽኑዕ መልአክ ነው።
"በሰማይም ሰልፍ ሆነ ሚካኤልና መላእክቱ ዘንዶውን ተዋጉት፣ዘንዶውም ከመላእክቱ ጋር ተዋጋ አልቻላቸውም። ከዚያም ወዲያ በሰማይ ሥፍራ አልተገኘላቸውም።"(ራእይ ፳፪:፯)
ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት ነው። ይሁዳ በመልእክቱ "የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በማለት ሊቀ መላእክትነቱን ገልጾአል። (ይሁዳ ፱)
ይህችውም ቅሩበ መንበር ተደርጎ የተፈጠረው ዲያብሎስ የተዋት ክብሩ ናት።
ቅዱስ ሚካኤል ይቅር የሚል ከመዓት የራቀ ነው።(ሄኖ፥፲፥፩፪)
ለሰው ባደረገው በጎነት ለሕዝቡ ሁሉ ታዛዥ ነው። የቅዱስ ሚካኤል ሹመት በነገደ መላእክት ላይ ብቻ አይደለም፤ ነገር ግን የእግዚአብሔር ሕዝብ በሆኑት ላይ ጭምር ነው፡፡ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል፣ ለእኛ ለሰዎች አማላጅ ሲሆን ለቅዱሳ ጻድቃንና ሰማዕታት ደግሞ አጋዣቸው ነው፤ በሕይወታቸውና በተጋድሏቸውም እስከ መጨረሻው ይረዳቸዋል፡፡
ይህንንም በቤተ ክርስቲያናችን በመጽሐፈ ስንክሳር እና በድርሳነ ሚካኤል ሰኔ ፲፪ ቀን ተጽፎ እናገኘዋለን። ይህም ቀን መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ተከብሮ የሚውልበት ታላቅ ዕለት ነው፡፡ በእስክንድርያ ከተማ ክላወባጥራ የተባለች ንግሥት የበጥሊሙስ ልጅ ዙሐል በሚባል ኮከብ ስም ያሠራችው ታላቅ ምኲራብ ነበር፤ ሕዝቡም ሰኔ በገባ በዐሥራ ሁለት የዚህን ጣዖት በዓል ያከብሩ ነበር። ይህንንም ግብራቸውን እንዲተው አባታችን እለ እስክንድሮስ ቢነግራቸው አይሆንም አሉት።
በኋላም ጻድቅ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ሲነግሥ አብያተ ክርስቲያናት ይትረኃዋ ወአብያተ ጣዖታት ይትአጸዋ የሚል አዋጅ ስለወጣ በዚህ ምቹ ጊዜም የጣዖት አምልኮ እንደምን ያለ ክፉ ግብር እንደሆነና በጎ ዋጋም እንደሌለው ነግሮ እንዲተዉ ቢጠይቃቸው እኛስ ይህን አንተውም አሉት። እርሱም በጥበብ እንዲህ አላቸው፤ ‹‹ይህን ግብር ብትተው በዚህች ቦታ የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤልን ቤተ ክርስቲያን እንሠራለን። መሥዋዕታችሁንም በዚያ ለቅዱስ እግዚአብሔር ታቀርባላችሁ አላቸው።›› በዚህ ተደስተው ተመለሱና ያንን የጣዖት ቤት አፍርሰው እጅግ ያማረች ቤተ ክርስቲያንን በመልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ስም ሠሩ። የመልአኩንም በዓለ ንግሥ በዚህች ዕለት አከበሯት። ከዚያን ጊዜም ጀምሮ የከበረ የመላእክት አለቃ የመልአኩ የሚካኤል የመታሰቢያውን በዓል በሰኔ ዐሥራ ሁለት ቀን በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ይከበራል፡፡ዳግመኛም ንዑድ ክቡር የሚሆን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ባሕራንን በሰኔ ዐሥራ ሁለት ቀን ያዳነበት ድንቅ ተአምርም ይህ ነው። አንድ ደግ ሰው በዚያች ሀገር ይኖር ነበር። ክፉ ጎረቤትም ነበረው። ይህም ደግ ሰው ነዳያንን እጅግ የሚወድ የቅዱስ ሚካኤልንም ዝክር ሳያስታጉል የሚዘክር ሰው ነው። በዚህ ሥራው ግን ይህ ክፉ ጎረቤቱ ይዘብትበት ነበር። በኋላም ያ ደግ ሰው የሚሞትበት ቀን ሲደርስ ሚስቱን ዝክረ ሚካኤልን እንዳታቋርጥና ነዳያንን እንዳትዘነጋ ነግሯት ያርፋል። እርሷም ፀንሳ ነበርና እርሱ ከሞተ በኋላ የመውለጃዋ ጊዜ ደረሰ። ምጥም ቢጠናባት ወደ መልአኩ ጮኸች፤ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤልም ተራዳትና መልከ መልካም የሆነ ወንድ ልጅ ወለደች። መልአኩም እንዲህ አላት። ‹‹ልጅሽ የዚህ የጎረቤትሽን ሀብት ይወርሳል።›› መልአኩም ለጎረቤታቸው ጆሮውም ከፍቶለት ነበርና ይህን ነገር ሰማ። በዚህም ‹‹በምን ምክንያት ወስጄ ላጥፋው›› ብሎ ሲያስብ ሴቲቱ ልጅዋን ብቻዋን ለማሳደግ ተቸገረች፤ ‹‹ላሳድግልሽ፤ ለአንቺም ይኸው ገንዘብ እሰጥሻለሁ›› ብሎ ብዙ ወርቅ ሰጣት። እርሱም ‹‹ከእንግዲህ አርፋለሁ›› ብሎ ልጁን መጣያ ሳጥን ያዘጋጅና ወደ ባሕር ቢጥለው ባሕሩም ሩቅ ሀገር ወስዶት ከዳር ይጥለዋል።
ከዚህም በኋላ አንድ በጎቹን ያሠማራ ሰው ያገኘዋል። ያንንም ሳጥን ወስዶ ከቤት ያኖረዋል፤ በምን መክፈት እንደሚችል ሲያስብ ዳግመኛ ወደ ባሕሩ እንዲሄድ እግዚአብሔር ሐሳብ ያሳድርበትና ተነሥቶ ይሄዳል። ሲሄድም ዓሣ አጥማጅ ያገኝና ዓሣ ለእርሱና ለቤተሰቡ እንዲያጠምድለት ይነግረዋል። ያም ዓሣ አጥማጅ ሲያጠምድ ታላቅ ዓሣ አገኘና ሰጠው። ዋጋውን ሰጥቶም ወደ ቤት ተመለሰና ሆዱን ቢሰነጥቀው ቁልፉን በዚያ አገኘው። በዚያም ሳጥኑን ቢከፍት መልከ መልካም ልጅ አገኘ። ልጅም ስላልነበረው እጅጉን ተደሰተ። ባሕራን ብሎም ሰየመው።
ከብዙ ጊዜያት በኋላ ያ ክፉ ሰው ከንግድ ተመልሶ በዚያ መንገድ ሲያልፍ መሸበትና ከዚህ ሰው ቤት አደረ። ባሕራንንም ተመለከተውና ሰውየውን ልጁ እንደሆነ ለማወቅ ታሪኩን ጠየቀው፤ ሰውየውም የሆነውን ሁሉ ነገረው። ክፉ ሰውየውም ልጁ እንዳልሞተ ባወቀ ጊዜ ደነገጠና መልእክት ሊልከው ስለሚፈልግ የባሕራንን አባት ልጁን እንዲሰጠው ጠየቀው። እርሱም ተስማምቶ ሰጠው። በክፋትም ተነሣሥቶ ባሕራንን እንዳገኘው እንዲገድለው ለአገልጋዩ ደብዳቤ ጽፎ አገልጋዩና እርሱ ብቻ የሚያውቁትን ማኅተም አድርጎ ሰጠው። ‹‹ይቺን ደብዳቤ በምታነባት ጊዜ ደብዳቤዋን ይዞ የመጣውን ገድለህ በጉድጓድ ውስጥ ጣለው፡፡ ማንም እንዳያውቅ›› ለባሕራንም ለመንገዱ የሚሆነውን ስንቅ ሰጠው፡፡
የራሱን የሞት ደብዳቤ እንደያዘ ሳያውቅ ባሕራን ወደ ታዘዘበት ሥፍራ ተጓዘ፤ ከዚያ ሰው ቤት ለመድረስ ሲቀርብ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል በንጉሥ ጭፍራ አምሳል በነጭ ፈረስ ላይ ተቀምጦ ‹‹አንተ ጐልማሳ የያዝኸው ምንድነው›› አለው፡፡ ‹‹ወደ ዕገሌ ሀገር ወደ ቤቱ ለማድረስ ከአንድ ባለ ጠጋ የተጻፈች መልእክት ናት›› አለው፡፡ ‹‹ያቺን ደብዳቤ አሳየኝ›› አለው፤ እርሱም ስለ ፈራ ሰጠው፡፡ የሞቱን ደብዳቤ ያቺን የሞት መልእክት ደምስሶ በሕይወት ቀየረለት። በእርሱም ፈንታ በንፍሐት ለውጦ እንዲህ ብሎ ጻፈ፤ ‹‹ይቺን ደብዳቤ ይዞ ለመጣ ባሕራን ለሚባል ሰው ይቺ ደብዳቤ ደርሳ በምትነበብበት ጊዜ ልጄ ዕገሊትን አጋቡት፡፡ በውስጥና በውጭ ያለ ንብረቴንና ጥሪቴን፣ ወንዶችና ሴቶች ባሮቼን፣ ጠቅላላ ንብረቴንም አውርሼዋለሁና የፈለገውንም ሊያደርግ ሥልጣን ሰጥቼዋለሁና እኔን አትጠብቁኝ፡፡ እኔ ብዙ እዘገያለሁ የኔ ሹም እገሌ ሆይ! በእኔና በአንተ መካከል ይቺ ምልክት እነኋት፡፡››
አሽጐ ለባሕራን ሰጠውና ‹‹ወደ ባለ ጠጋው ቤት ሂደህ ይቺን ደብዳቤ ለሹሙ ስጠው፡፡ በጎዳናም እኔ እንደ ተገናኘሁህ አትንገረው፡፡ እንዳይገድልህም ይህን የሞት ደብዳቤ ለውጬልሃለሁ›› አለው፡፡ ባሕራንም ‹‹እሺ ጌታዬ ያዘዝኸኝን ሁሉ አደርጋለሁ›› አለ፡፡
ባሕራንም ወደ ባለ ጠጋው ቤት በደረሰ ጊዜ ያቺን ደብዳቤ ለሹሙ ሰጠው፡፡ ካነበባት በኋላም በመካከላቸው ያለውን ምልክት አገኘ፡፡ አስተውሎም እርግጠኛ እንደ ሆነ ዐወቀ፡፡ ለባሕራን ሰርግ አዘጋጅቶ እንደሚገባ በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት በተክሊል የባለ ጠጋውን ልጅ አጋቡት፡፡ ዓርባ ቀን ያህልም ደስታና ሐሴት እያደረጉ ኖሩ፡፡ ሀብቱንም ሁሉ አወረሱት። | 286 |
| 17 | بدون متن... | 247 |
| 18 | ብሒለ አበው
"ቅዱሳን ሐዋርያት ዓለምን ድል የነሱትና የወንጌልን ዘር የዘሩት በቅምጥልነትና በምቾት ሕይወት ውስጥ ሆነው አይደለም፤ ይልቁንም በጾም፣ በጸሎትና በትጋት ራሳቸውን ለእግዚአብሔር አስገዝተው ነው እንጂ። ጾም መሣሪያችን ነው፤ ነገር ግን ስጋህን ከምግብ ስትከለክለው ነፍስህ የሐዋርያትን የፍቅርና የትሕትና ፈለግ እንድትከተል አድርጋት። በሐዋርያት ጾም ወቅት ልባችንን ለአገልግሎት፣ አንደበታችንን ለእውነትና እጃችንን ለምጽዋት ልናዘጋጅ ይገባል። ወንድሙን እየጠላና በልቡ ቂም ይዞ የሚጾም ሰው፣ የሐዋርያትን ፍቅር አልተረዳም፤ ጾሙም ፍሬ የለውም። ስለዚህ ጾማችን ከቅዱሳኑ ጋር የሚያስተሳስረን የእውነተኛ ንስሐ መጀመሪያ ይሁንልን።"
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ያለ ጽናት የምትለማመደው ሥራ ፍሬ አይኖረውም፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ንቅሐ ልቡና ራስን ማወቅና ራስን መግዛት የነፍስ መሪዎቿ ናቸው።
አባ ጴሜን
"ጠላት በበዛበት ቦታ የምኖር ከሆነ ብርቱ ወታደር እሆናለሁ።"
አባ ጴሜን
ትግል፡ ፈተናና መከራ ከሌሉ የድል አክሊል፤ ጠላት ከሌለ ድልማድረግ አይኖርም።"
ባስልዮስ ዘቂሳርያ | 446 |
| 19 | https://youtu.be/7CDS7xp6kgo | 356 |
| 20 | "ወደ እግዚአብሔርም በብርቱ ይጩሁ ሰዎችም ሁሉ ከክፉ መንገዳቸውና በእጃቸው ካለው ግፍ ይመለሱ።" ትን.ዮና. 3÷8
🕯ሳምንታዊው የአርብ ጸሎት🕯
👉 ውዳሴ ማርያም
👉 መሐረነ አብ
👉ስንክሳር
🗓 ሰኔ 05 ቀን 2018 ዓ.ም
⏰ ከቀኑ 12:00ሰዓት ጀምሮ
💒 በሰንበት ት/ቤቱ አዳራሽ
ኑ በህብረት ስለ ሀገራችንና ስለ ቤተክርስቲያናችን ሰላም እና አንድነት ወደ ፈጣሪያችን በጋራ እንጸልይ‼ | 363 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
