አ/ም ሰንበት ት/ቤት ትምህርት ክፍል official channel
رفتن به کانال در Telegram
ይህ በቦሌ ሰ/ም/ፀ/ቅ/ጊዮርጊስ እና ቅ/አርሴማ ቤተ ክርስቲያን አንቀፀ ምስራቅ ሰ/ት/ቤት መንፈሳዊ ጽሑፎችን እንዲሁም ወቅታዊ የቤተ-ክርስቲያን መረጃዎችን የምንለቅበት የቴሌግራም ገፃችን ነው።
نمایش بیشتر721
مشترکین
-224 ساعت
-27 روز
-630 روز
در حال بارگیری داده...
کانالهای مشابه
ابر برچسبها
هیچ دادهای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
ژوئیه '26
ژوئیه '26
+10
در 0 کانالها
ژوئن '26
+39
در 0 کانالها
Get PRO
مه '26
+30
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '26
+17
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '26
+14
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '26
+15
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '26
+33
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '25
+28
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '25
+28
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '25
+24
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '25
+22
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '25
+23
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '25
+28
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '25
+18
در 0 کانالها
Get PRO
مه '25
+11
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '25
+22
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '25
+11
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '25
+5
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '25
+23
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '24
+16
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '24
+45
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '24
+19
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '24
+50
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '24
+64
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '24
+44
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '24
+33
در 0 کانالها
Get PRO
مه '24
+17
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '24
+26
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '24
+22
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '24
+81
در 1 کانالها
Get PRO
ژانویه '24
+176
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '23
+286
در 0 کانالها
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 21 ژوئیه | +1 | |||
| 20 ژوئیه | 0 | |||
| 19 ژوئیه | +1 | |||
| 18 ژوئیه | 0 | |||
| 17 ژوئیه | +2 | |||
| 16 ژوئیه | +1 | |||
| 15 ژوئیه | 0 | |||
| 14 ژوئیه | 0 | |||
| 13 ژوئیه | 0 | |||
| 12 ژوئیه | +1 | |||
| 11 ژوئیه | +2 | |||
| 10 ژوئیه | 0 | |||
| 09 ژوئیه | 0 | |||
| 08 ژوئیه | 0 | |||
| 07 ژوئیه | 0 | |||
| 06 ژوئیه | 0 | |||
| 05 ژوئیه | 0 | |||
| 04 ژوئیه | 0 | |||
| 03 ژوئیه | +1 | |||
| 02 ژوئیه | +1 | |||
| 01 ژوئیه | 0 |
پستهای کانال
ሥጋ ሁሉ እንደ ሣር ክብሩም ሁሉ እንደ ሣር አበባ ነውና ። ሣሩ ይጠወልጋል አበባውም ይረግፋል ። 1ጴጥ 1:24
ለምንኩስና ለተጠሩት ቡሩካን ይህ እኛ ሥጋውያን የምንጓጓለት ሠርግ፣ ትዳር፣ ወግማዕረጉ ክብሩ እነሱ የሚሸሹት ነገር ነው ። እነዚህ ነገሮች በራሳቸው ሐጢአት ስለሆኑ ሳይሆን ምድራዊው ነገር ለአንድ ደቂቃ እንኳን ልባቸውን እንዲሰርቅባቸው ስለማይፈልጉ ነው ። ቀንም ማታም ማሰብ የሚፈልጉት ክርስቶስንና መንግስቱን ነው ። መድኃኔዓለምን የሚወዱበት ፍቅር እንዲህ ሊባል የማይቻልና በቅናት የተመላ ነው። ሽርፍራፊ ሰከንድ ልባቸው ያለክርስቶስ እንዲያስብ አይፈቅዱም ። እንደኛ ቅዳሴ ላይ ሆነው ልባቸውን አስር ቦታ የበተኑ አይደሉም ። እንደ ቅዱስ ገብረክርስቶስ እጣቢና ቆሻሻ እየተደፋባቸው ምህረት እየለመኑ የማያልፈውን መዓዛ ኢየሱስ ክርስቶስን የገለጡ ናቸው እንጂ ። 💛
የሙሽራው ገብረክርስቶስና የቅዱሳን መነኮሳት ሁሉ በረከታቸው ይደርብን ።
| 2 | 📢 በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ስር ለምትገኙ 61ዱም ሰንበት ትምህርት ቤቶች
ጥበብ አካዳሚ ከለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጋር በደረሰው የጋራ መግባባት መሠረት፣ በአንድነቱ ስር በሚገኙ 61ዱም ሰንበት ትምህርት ቤቶች ውስጥ ለሚገኙ መስፈርቱን ለሚያሟሉ አባላት የሥራ እድል አመቻችቷል።
💼 የክፍት ሥራ መደቦች እና መስፈርቶች
1. መምህር
የትምህርት ደረጃ: ዲግሪ ወይም ዲፕሎማ
የሥራ ልምድ: 0 ዓመት
2. ረዳት መምህር
የትምህርት ደረጃ: ዲግሪ ወይም ዲፕሎማ
የሥራ ልምድ: 0 ዓመት
3. ጥበቃ
የትምህርት ደረጃ: 8ኛ ክፍል እና ከዚያ በላይ
የሥራ ልምድ: 0 ዓመት
4. ጽዳት
የትምህርት ደረጃ: 6ኛ ክፍል እና ከዚያ በላይ
የሥራ ልምድ: 0 ዓመት
ደሞዝ በአካዳሚው እስኬል መሠረት 📌 ተጨማሪ መስፈርት
የሰንበት ትምህርት ቤት አባል የሆነ/ች እና ከሰንበት ትምህርት ቤቱ በሰብሳቢ የተፈረመ የድጋፍ ደብዳቤ ማቅረብ የሚችል/ምትችል።
📝 አመዘጋገብ
መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች ዛሬ 14/11/2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ከታች ባለው ሊንክ አማካኝነት መረጃችሁን እና የሕይወት ታሪካችሁን (CV) በመላክ መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፦
🔗 የመመዝገቢያ ሊንክ: @Davoethio2016
💡 መረጃው ለሌሎች የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት እንዲደርስ መረጃውን ያጋሩ! | 58 |
| 3 | بدون متن... | 105 |
| 4 | እንዴት አደራችሁ የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት በሙሉ
እንደሚታወቀው ወር በገባ በ14 የፃድቁ አባታችንን ወርሃዊ መታሰቢያ በዓልን እናከብራለን በነገው እለትም ሀምሌ 14/11/2018 ዓ.ም በደብራችን አውደምህረት እናከብራለን ሁሉም የሰንበት ትምህርት ቤቱ አባል ከ11:30 ሰዓት ጀምሮ እንድትገኙ እናሳስባለን።
ጸሎት በአንድ ላይ እንድናደርስ በጊዜ እንገኝ።
ሰዓት ይከበር | 140 |
| 5 | ክፍት የሥራ ማስታወቂያ ለ0 ዓመት/ 2018 ዓ.ም ተመራቂዎች
በ accounting (ብዛት 2 ፣ ፃታ ሴት)
በ management (ብዛት 1 ፣ ፃታ ሴት)
በ software engineering (ብዛት 4)
👉 የተሟላ cv በtelegram account @bettybee12 ይላኩ | 172 |
| 6 | ፈተና ላለፋችሁ ሁሉም አባላት በሙሉ
ፈተና የመጨረሻ ግዜ የሚሰጠው ዛሬ ስለሆነ አሳማኝ ምክንያት አምጥታችሁ እንድትፈተኑ እናሳስባለን። | 185 |
| 7 | #ኮከበ_ገዳም_አባ_ብሾይ
ኮከበ ገዳም የተባለው ቅዱስ አባ ብሶይ (ብሾይ) በጽኑ ተጋድሎ፣ በትሕትና እና በፍቅር የኖረ ታላቅ አባት ሲኾን፣ በሰፊው ተጋድሎት ካለፈ በኋላ ሐምሌ 8 ቀን በ417 ዓ.ም ዐርፏል።
በሕፃንነቱ የተመረጠው ለጌታ አገልግሎት የተለየው ይኽ ቅዱስ፣ በገዳመ ሲሐት በጾምና በጸሎት በመጽናት እጅግ ከፍ ያለ የቅድስና ማዕረግ ላይ ደርሷል፤ ጌታችንን በነዳይ አምሳል እግሩን በማጠብ፣ በአረጋዊ አምሳልም በጀርባው አዝሎ በመውጣት ባሳየው ትሕትና ምክንያት ቅዱስ ሥጋው ሳይበሰብስና ሳይፈርስ እስከ ዛሬ ድረስ በገዳሙ ተአምራትን እያደረገ ይገኛል።
በመንፈስ ቅዱስ ህልውና ላይ ክህደት የነበረበትን ሰው በመጽሐፍ ቅዱስ ምሳሌዎች አስተምሮ የመለሰው አባ ብሶይ፣ በቅድስና ሕይወቱ ለብዙዎች አባትና መሪ ሆኖ አልፏል። | 323 |
| 8 | + +
አባ ብሶይ ዘገዳመ መቃርስ፡- የዓለም ሁሉ ኮከብ የተባሉት የአባ መቃርስ ገዳሙ አባ ብሶይ በግብፅ ተወለዱ፡፡ ሰባት ወንድሞችም ስለነበሯቸው እናታቸው በሌሊት ራእይ አየች፡፡ መልአኩ ተገልጦላት ‹‹እግዚአብሔር ያገለግለኝ ዘንድ ከልጆችሽ አንዱን ስጪኝ›› ብሎሻል አላት፡፡ ‹‹ሁሉም የእርሱ ገንዘቦቹ ናቸውና የወደድከውን ውሰድ›› አለችው፡፡ መልአኩ የብሶይን ራስ ይዞ የተመረጠው እርሱ መሆኑን ነገራት፡፡ የብሶይም ሥጋው የከሳ ነበርና እናቱ መልአኩን ‹‹ከጠንካራዎቹ ውስጥ አንዱን ውሰድ›› አለችው፡፡ መልአኩም እግዚአብሔር የመረጠው ብሶይን መሆኑን ነግሯት ተሰወረ፡፡
አቡነ ብሶይ ባደጉ ጊዜ ወደ አስቄጥስ ገዳም ገብተው በአባ ባይሞይ እጅ መነኮሱ፡፡ እርሳቸውም ዮሐንስ ሐፂርን ያመነኮሱት ናቸው፡፡ ብሶይም ከበፊቱ አብዝተው በጽኑ ተጋድሎ መኖር ጀመሩ፡፡ ምንም ሳይቀምሱ 40 ቀንና 40 ሌሊት ይጾሙ ይጸልዩ ነበር፡፡ ጌታችንም ብዙ ጊዜ እየተገለጠላቸው ያነጋግራቸው ነበር፡፡ የጌታችንን እግሩን እያጠቡት እጣቢውን ይጠጡ ነበር፡፡ አንድ ቀንም እንዲሁ ጌታችንን ያጠበበትን ውኃ ግማሹን ብቻ ጠጥተው ግመሹን ለደቀ መዝሙራቸው ተውለት፡፡ ደቀ መዝሙራቸውም በመጣ ጊዜ ከእግር ማጠቢያው
ውስጥ ያለውን ውኃ እንዲጠጣ ቢነግሩት በልቡ ‹‹ለምን በመቅጃው ውስጥ ካለው ከጥሩው ውኃ አይሰጡኝም›› ብሎ አሰበና ሳይጠጣው ቀረ፡፡ ለሁለተኛም ጊዜ ጠጣው ብለው ታዛዥነቱንም እንዲያሳያቸው ቢለምኑት እምቢ አላቸው፡፡ ለ3ኛ ጊዜ ግድ ጠጣ ብለውት ደቀ መዝሙራቸው ውኃ ወዳለበት ኩስኩስት ቢሄድ ውኃው ዐይኑ እያየው ከኩስኩስቱ ላይ ደረቀና ጠፋበት፡፡ የጌታችን እግር እጣቢ መሆኑንም በነገሩት ጊዜ በድንጋጤ እንደበድን ሆነ፡፡ እንዲያረጋጋው በማሰብ ራሱን እብድ በማስመሰል ይኖር ወደነበረ አንድ ትልቅ ጻድቅ ጋር ልከውት አበረታው፡፡ ድንጋጤውም ባልተሸለው ጊዜ አባ ብሶይ ድጋሚ ወደዚያ አባት ላኩትና ሲሄድ ያንን ዕብድ መሳይ ቅዱስ አባት ዐርፈው አገኛቸው፡፡ አባ ብሶይም በትራቸውን ሰጥተው በአስክሬናቸው ላይ እንዲያኖረው ለረድኡ ሰጡትና ሄዶ በትራቸውን በአስክሬኑ ላይ አኑሮት ‹‹ተነሥተህ እንድታነጋግረኝ አባቴ አዞሃል›› ቢላቸው ከሞት አፈፍ ብለው ተነሥተው ‹‹አንተም ለአባትህ ታዛዥ ብትሆን ኖሮ የጌታችንን በረከት አጥተህ እንደዚህ ዓይነቱ ድንጋጤ ላይ ባልወደክ ነበር›› ብለውት ተመልሰው ዐረፉ፡፡
ጻድቁ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስም ለአባ ብሶይ በአካለ ነፍስ ተገልጦላቸው በሰማያት የመነኮሳትን ክብር አይቶ ቀድሞ የምንኩስናን ክብር እንዲህ መሆኑን ቢያውቅ ኖሮ ይመነኩስ እንደነበር ሲነግራቸው እሳቸውም ‹‹አንተስ ምን ጎደለህ የጣዖት አምልኮን አጥፍተህ የቀናች ሃይማኖትን አጽንተሃል›› አሉት፡፡ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስም ‹‹ክብርንስ እግዚአብሔር አብዝቶ ሰጥቶኛል ነገር ግን የመነኮሳትን ክብር ያህል አይሆንም፣ እነርሱ በእሳት ክንፎች እየበረሩ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ሲገቡ አይቻቸዋለሁ›› ብሏቸዋል፡፡
ክብርና ምስጋና ይግባውና ‹‹መንፈስ ቅዱስ የለም›› እያለ የሚያስተምር አንድ የካደ መነኩሴ በእንዴና አገር መኖሩን በመንፈስ አውቀው አባ ብሶይ እጅግ አዘኑ›፡ መስሚያ ጆሮዎቻቸውንም ሦስት አድርገው ሄደው ከሚያስተምርበት ደርሰው ተገናኙት፡፡ ሕዝቡም አባታችንን ሰላምታ ሰጥተው ከእሳቸው ከተባረኩ በኋላ ስለ ሦስቱ ጆሮዎቻቸው ቢጠይቋቸው ‹‹እኔ ልዩ ሦስት አካላት አሉኝ፣ ሥራዬ ሁሉ በእነርሱ አምሳል ነው›› በማለት ሰለ ሥሉስ ቅዱስ አንድነትና ሦስትነት ቅዱሳት መጻሕፍትን እየጠቀሱ ሕዝቡን አስተምረው ከስሕተት ትምህርት ታድገዋቸዋል፡፡ ሕዝቡም ንስሓ ገብተው ወደ ቀናች ሃይማኖት ተመለሱ፡፡ አባ ብሶይን ደቀመዛሙርቶቻቸው ‹‹ጌታችን ለእኛም እንዲገለጥልን ጸልይልን›› አሏቸው፡፡ አባም በጸሎታቸው ጌታችንን ሲጠይቁት ‹‹ነገ በጠዋት ወደ ተራራው ይውጡ በዚያ እገለጥላቸዋለሁ›› አላቸውና ለመነኮሳቱ ሁሉ ይህንን ተናገሩ፡፡ በጠዋትም ተነሥተው ሁሉም ጌታን ለማየት እየተቻኮሉ ወጡ፡፡ በተራራው ግርጌም አንድ የደከሙ ሽማግሌ መነኮሳቱን ‹‹ወዴት ትሄዳላችሁ?›› እያሉ ሲጠይቋቸው ‹‹ጌታችን በተራራው ላይ ሊገለጥልን ነውና እርሱን ለማየት እንሄዳለን›› እያሉ እየተቻሉ ሲሄዱ ሽማግሌው ‹‹እኔንም ይዛችሁኝ ሂዱና ጌታችንን ልየው›› አሏቸው፡፡ ነገር ግን ሁሉም መነኮሳት ትተዋቸው ሄዱ፡፡ አባ ቢሶይ ከሁሉም መጨረሻ ሆነው ወደ ተራራው ሲወጡ ሽማግሌውን አይተው ‹‹አባቴ ወዴት መሄድ ፈልገው ነው?›› ሲሏቸው ሽማግሌውም ‹‹ወደ ተራራው መውጣት ፈልጌ ነበር›› አሏቸው፡፡ አባ ቢሶይ ሽማግሌውን ተሸክመዋቸው ተራራውን መውጣት ጀመሩ፡፡ በመጀመሪያ በጣም ቀለዋቸው ነበር ነገር ግን ተራራውን እየወጡ በመጡ ቁጥር እጅግ እየከበዷቸው መጡ፡፡ የተሸከሟቸውንም ሽማግሌ ሁለቱንም እግራቸውን ሲመለከቷቸው በችንካር ተቸንክረዋል፡፡ መልካቸውም እየተለወጠ መጣ፡፡ ያ ሽማግሌ ግን ራሱ ጌታችን ነበር፡፡
ወደ ተራራውም ወጥተው ጌታችንን ለማየት ሲጠባበቁ የነበሩት መነኮሳት ‹‹ጌታችን የታለ? መች ተገለጠልን?›› ብለው ጠየቋቸው፡፡ አባ ብሶይ ‹‹ጌታችንም ከተራራው ግርጌ ተገልጦላችሁ ነበር ነገር ግን እናንተ ትታችሁት መጥታችኋል›› በማለት የሆነውን ሁሉ ነገሯቸው፡፡ አባ ብሶይ እጅግ ብዙ ተአምራት በማድረግ በታላቅ ተጋድሎ ኖረው ሐምሌ 8 ቀን በታላቅ ክብር ዐርፈዋል፡፡ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን! | 1 |
| 9 | بدون متن... | 391 |
| 10 | 🌟 የክረምት አገልግሎት ጥሪ 🌟
ለሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት ለማገልገል ፈቃደኛ የሆናችሁ አባላት በሙሉ፤ ክረምቱን በጋራ በበረከትና በበጎ ፈቃድ አገልግሎት የምናሳልፍበት ጥሪ ቀርቦላችኋል።
📅 የአገልግሎት ዝርዝር
ቀናት፦ ከሰኞ እስከ አርብ (የሚመችዎትን ቀን መምረጥ ይቻላል)
ሰዓት፦ ከጠዋቱ 2:30 - 6:00 ሰዓት
📩 እንዴት ማሳወቅ ይቻላል?
ማገልገል የምትፈልጉ አባላት ከታች በተቀመጡት አድራሻዎች "ማገልገል እችላለሁ" የሚል መልዕክት በመላክ እንድታሳውቁን በልዑል እግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን።
📞 ስልክ ቁጥር፦ 0989300473/0973010522
✈️ ቴሌግራም፦ 09 89 30 04 73 Dagmawit
✨ "ክረምቱን በበረከት እንሞላ!!" ✨ | 299 |
| 11 | #ቅድስት_ሥላሴ (#ሐምሌ_7)
ሐምሌ ሰባት በዚች ቀን ሥሉስ ቅዱስ በአብርሃም ቤት የተገለጡበት ነው፡፡ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በስም በአካል በግብር ሦስትነት በባሕርይ በሕልውናና በፈቃድ አንድነት የጸኑ ናቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ተገኙ፣ በዚህ ጊዜ ያልፋሉ አይባሉም መጀመሪያም መጨረሻም እነርሱ ናቸውና፡፡ ርሕሩሐን ናቸውና በእናት ሥርዓት ‹‹ቅድስት ሥላሴ›› እንላቸዋለን፡፡ የሚጠላቸው (የማያምንባቸውን) አይጠሉም፡፡ የሚወዳቸውን ግን እጽፍ ድርብ ይወዱታል፣ በቤቱም መጥተው ያድራሉ፡፡ ከፍጥረታት ወገን ከእመቤታችን ቀጥሎ የአብርሃምን ያህል በሥላሴ ዘንድ የተወደደ ፍጡር የለም፡፡ አባታችን ቅዱስ አብርሃም የደግነት ሁሉ አባት ነውና በኬብሮን በመምሬ ዛፍ ሥር ሥላሴን ተቀብሎ አስተናግዷል፡፡
አባታችን አብርሃም በ99 ዓመቱ እናታችን ሣራ በ89 ዓመቷ ሥላሴን በድንኳናቸው አስተናገዱ፡፡ አብርሃም እግራቸውን አጠበ፡፡ በጀርባውም አዘላቸው፡፡ ምሳቸውንም አቀረበላቸው፡፡ እነርሱም እንደሚበሉ ሆኑለት፡፡ በዚያው ዕለትም የይስሃቅን መወለድ አበሠሩት፡፡ አብርሃም ከደግነቱና እንግዳ ከመውደዱ የተነሣ በተመሳቀለ ጎዳና ላይ ድንኳን ሠርቶ የወጣ የመረደውን፣ የመጣ የሄደውን ሁሉ እየተቀበለ እግዚአብሔርን እያገለገለ የሚኖር ጻድቅ ነበር፡፡ ለዚህም ነው አብርሃም በወይራ ግራር (በመምሬ) ዛፍ ሥር ተቀምጦ ሳለ እግዚአብሔር አንድነቱን ሦስትነቱን የገለጠለት፡፡ ዘፍ 18፡1-25፣ ሮሜ 4፡-3፡፡ ቀትር ሰዓት ላይ በድንኳኑ ደጅ ተቀምጦ እንግዳ ሲጠብቅ እግዚአብሔር ታየው ተነጋገረው፡፡ አንገቱን ቀና አድርጎ ዐይኑን አራምዶ በተመለከተ ጊዜ እነሆ ሦስት ሰዎች ከበላዩ ባለ ተራራ ላይ ቆመው አያቸው፣ ወደ እርሱም ሲወርዱ አይቶ ፈጥኖ ሄዶ ከሰግደላቸው በኋላ ‹‹አቤቱ በፊትህስ ሞገስ አግኝቼ እንደሆነ ባሪያህን አትለፈኝ ብዬ እለምናለሁ፤ ጥቂት ውኃ ይምጣላችሁ እግራችሁን ታጠቡ…›› እያለ በትሕትና በመጋበዝ ወደ ድንኳኑ አስገብቶ በሚገባ ጋበዛቸው፡፡ ‹‹በፊትህስ ሞገስ አግኝቼ›› ብሎ አንድነታቸውን፣ ‹‹ጥቂት ውኃ ይምጣላችሁ እግራችሁን ታጠቡ›› ብሎ የሦስትነታቸውን ምስጢር ገልጾአል፡፡
ያች ሥላሴ የገቡባት የአብርሃም ድንኳን የእመቤታችን ምሳሌ ናት፡፡ ሥላሴ ወደ አብርሃም ድንኳን እንደገቡ ሁሉ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያምም አብ ለአጽንዖ፣ መንፈስ ቅዱስ ለአንጽሖ፣ ወልድ በተለየ አካሉ ሥጋዋን ለመዋሐድ የማደራቸው ምሳሌ በመሆኑ አማናዊቷ የሥላሴ ማደሪያ የአብርሃም ድንኳን እመቤታችን ናት፡፡ ሉቃ 1፡35፡፡
እግዚአብሔርም አብርሃምን የዛሬ ዓመት ልጅ እንደሚወልድ ነግሮት በዓመቱ ይስሐቅን ወልዷል፡፡ ሁለቱ ሰዎች ከአብርሃም ድንኳን ወጥተው ወደ ሰዶም ወደ ገሞራ ሄዱ፣ አብርሃምም ይሸኛቸው ዘንድ አብሯቸው ሄደ፡፡ የሄዱትም ሁለቱ ሰዎች አብና መንፈስ ቅዱስ ናቸው፡፡ ነገር ግን አንዱ ወልድ በአብርሃም ቤት ቀርቷል ይኸውም ከቤተ አብርሃም ሰው እንደሚሆን ለማጠየቅ ነው፡፡ አብርሃምም ተመልሶ በእግዚአብሔር ፊት ቆመ፡፡ እግዚአብሔርም የሚሠራውን ሁሉ ከአብርሃም አይሠውርም ነበርና የሰዶምን የገሞራን ጥፋት ነገረው፡፡ አብርሃምም ይቅር እንዲላቸው አብዝቶ ለመነላቸው፡፡
ሥሉስ ቅዱስን የአብርሃሙ ሥላሴን በምግባር በሃይማኖት ሆነን እናገለግል ዘንድ የቅዱሳኑ ጸሎት ይርዳን!
( ስንክሳር ዘተዋሕዶ ፌስቡክ ፔጅ) | 259 |
| 12 | ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ የመጀመሪያውን ጉዞ ያደረገው ከኢየሩሳሌም ወደ አንጾኪያ ከተመለሰ በኋላ በልዑል እግዚአብሔር ጥሪ በአሕዛብ ሀገር ወንጌልን ለመስበክ ከበርናባስ ነው።
በዚህ ጉዞአቸው በጠቅላላ ወደ ፪፼ (ሁለት ሺህ) ኪሎ ሜትር የሚደርስ መንገድ በእግር ተጉዟል። ይህም ጉዞ የተከናወነው በ፵፮ ዓ.ም. አካባቢ ነው።
ሁለተኛው ጉዞ የተከናወነው በ፶ ዓ.ም. ገደማ ነው። በመጀመሪያው ጉዞ ማርቆስ አብሮ ተጉዞ ነበር። ነገር ግን ጵንፍልያ ከተማ ሲደርስ እናቱ ስለናፈቀችው መመለስ በመፈለጉ በርናባስ ወደ ኢየሩሳሌም ይዞት መጣ።
ስለዚህም በሁለተኛው ጉዞ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ሲላስን ይዞ ወደ ኪልቂያ ሶርያ ሲጓዝ በርናባስ ደግሞ ማርቆስን አስከትሎ ወደ ቆጵሮስ ሄደ።
በዚህ ጉዞው ቅዱስ ጳውሎስ እስከ ግሪክ ደርሶአል።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ የመንፈስ ልጁ ጢሞቴዎስን ያገኘው በዚሁ ጉዞው በልስጥራ ከተማ ነው።
ሦስተኛው ጉዞ የተከናወነው በ፶፬ ዓ.ም. ነው።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ከልዩ ልዩ ሀገሮች ክርስቲያኖች የሰበሰበውን ዕርዳታ ለኢየሩሳሌም ቤተ ክርስቲያን በመያዝ ሦስተኛውን ጉዞ አጠናቅቆ ኢየሩሳሌም ገባ።
ነገር ግን ኢየሩሳሌም የገባበት ጊዜ የፋሲካ በዓል ስለነበር ከልዩ ልዩ ሀገሮች የተሰበሰቡ አይሁድ በከተማዋ ነበሩ።
እነዚህ በዝርወት የሚኖሩ አይሁድ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስን በየሀገራቸው በትምህርቱ የተነሣ ሲቃወሙት የነበሩ ናቸው።
እኒህ አይሁድ ቅዱስ ጳውሎስን በኢየሩሳሌም ሲያዩት ታላቅ ተቃውሞ አነሡበት።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ተቃውሞ አነሡበት። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ተቃውሞአቸውን ለመግታት እንደ አይሁድ ሕግ በቤተ መቅደስ የመንጻት ሥርዓት መፈጸም ጀመረ።
ነገር ግን ከኤፌሶን የተከተለውን ጥሮፊሞስን ወደ መቅደስ ያስገባው ስለመሰላቸው ተቃውሞአቸው በረታ።
ከተማውንም አወኩት፤ ይህ ቅዱስ ጳውሎስን በ፶፰ ዓ.ም. ለሮም እሥር ዳረገው። ከብዙ መከራና ስቃይ በኋላ ታስሮ ሮም ገባ።
በዚያም በቁም እሥር ለሁለት ዓመታት ያህል ወንጌልን ሰበከ። የሁለቱን ዓመት የቁም እሥር እንደጨረሰ ወደ ኔሮን ፍርድ ቤት ቀረበ።
ይህም በ፷ዎቹ ዓ.ም ነው። በፍርድ ቤቱ በተደረገው ምርመራ የሮሜን ሕግ የሚቃወም ምንም ወንጀል ስላልተገኘበት በነፃ ተለቀቀ፤
ከዚህ በኋላ ነው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ አራተኛውንና የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ያልመዘገበውን ጉዞውን ያደረገው።
ይህ ጉዞው በመታሠሩ አዝነው ተክዘው የነበሩ ክርስቲያኖችን ለማጽናናት የጀመራቸውን ሥራዎች ፍጻሜ ለማየት የተደረገ ጉዞ ነው።
በመጨረሻ በ፷፬ ዓ.ም. ኔሮን በጥጋቡ የሮማ ከተማ ስትቃጠል ምን እንደምትመስል ማየት እፈልጋለሁ ብሎ አቃጠላት።
የሮም ሕዝብ በከተማው መቃጠል በማዘኑና በማመፁ ነገሩን ሁሉ በክርስቲያኖች ላይ አሳበበ።
በዚህም የተነሣ ክርስቲያን የተባለ ሁሉ መሰደድ፣ መሠየፍ፣ መታረድ እጣ ፈንታው ሆነ።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም በኒቆጵልዮን ከተማ ሲያስተምር በ፷፭ ዓ.ም. ተይዞ ወደ ወኅኒ ገባ።
ለሁለት ዓመት ከስድስት ወር በጨለማ ቤት ታሥሮ ከቆየ በኋላ በ፸፬ ዓመት ዕድሜው በሮም ከተማ በኦስትያ መንገድ አንገቱን ተሰይፎ በ፷፯ ዓ.ም. ሐምሌ ፭ ቀን በሰማዕትነት ዐረፈ።
ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ሁለት፤ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ደግሞ ዐስራ አራት መልእክታትን ጽፈዋል።
የቅዱሳኑ ሐዋርያት ረድኤትና በረከታቸው ከሁላችን ጋር ይሁን፤ አሜን።
ምንጭ፦
✔መጽሐፈ ስንክሳር ዘወርኃ ሐምሌ ፭፤
✔መጽሐፍ ቅዱስ-ሐዲስ ኪዳን፣
✔ቤተ ክርስቲያንህን ዕወቅ ቁጥር ፩፤ በማኅበረ ቅዱሳን | 359 |
| 13 | የሮም ሕዝብ በደረሰው አደጋ እጅጉን ተቆጣ። ኔሮንም በክርስቲያኖች አመካኘ። በዚህም የተነሣ በሮማ ከተማ ሁለት ዓይነት ወሬ መናፈስ ጀመረ።
የሮማ አማልክት በክርስቲያኖች ሃይማኖት ስለተቆጡ በከተማዋ እሳት አዘነቡባት የሚለው የመጀመሪያው ሲሆን ክርስቲያኖች ሆን ብለው ከተማዋን አቃጥለዋታል የሚለው ደግሞ ሁለተኛው ወሬ ነበር።
የከተማው መጋየት ያበሳጨው የሮማ ሕዝብ፣ ክርስቲያን የሆነውን ሁሉ እያወጣ መግደሉን ተያያዘው።
ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ ሰዓት በእሥር ነበርና ተሠይፎ ዐረፈ። ይህን የሰሙት የአግቢኖስና የአግሪጳ ሚስቶች (የሮም ባለሟሎች ነበሩ) «ባይሆን አንተ ትረፍልን» ብለው በከተማዋ ግንብ በገመድ አሥረው በቅርጫት በማውረድ ቅፅረ ሮማን ለቅቆ እንዲወጣ አደረጉት።
ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በኦፒየም ጎዳና ጉዞውን ቀጠለ። ሮማን ለቀቀ። እያዘገመ በሸመገለ ጉልበቱ ሲጓዝ አንድ ቀይ ጐልማሳ ወደ እርሱ ሲመጣ አየ።
እየቀረበ ሲመጣ ጌታችን መሆኑን ተረዳ። ወዲያው በፊቱ ተደፋና «ጌታዬ ወዴት እየተጓዝክ ነው?» አለና ጠየቀው። «ዳግም በሮም ልሰቀል» አለው።
በዚህ ሰዓት ቅዱስ ጴጥሮስ አዘነና እንደገና ወደ ሮማ ተመለሰ። የኔሮን ወታደሮች እየፈለጉት ነበር። «እነሆኝ ስቀሉኝ» አለ ቅዱስ ጴጥሮስ።
ያን ጊዜ ቅዱስ ጴጥሮስን ይዘው አሠሩት። ከጥቂት ቀናት በኋላም ሮማውያን የመስቀያውን እንጨት አቀረቡለት።
ያን ጊዜ «እኔ እንደ ጌታዬ ልሰቀል አይገባኝም» በማለት ቁልቁል እንዲሰቅሉት ለመነ። ያለውንም አደረጉለት። ሐምሌ ፭ ቀን ፷፯ ዓ.ም. በሰማዕትነት ዐረፈ።
ብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወ ቅዱስ ጳውሎስ
፪. ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ዘሩ ከዕብራዊያን፣ ከብንያም ነገድ ሲሆን የተወለደውም በጠርሴስ ከተማ ነው።
ጠርሴስ በንግድዋ የታወቀች የኪልቂያ ዋና ከተማ ናት። በከተማዋ እስከ አምስት መቶ ሺህ የሚገመቱ ከየሀገሩ የተሰባሰቡ ሕዝቦች ነበሩባት።
ሮማውያን በሥራቸው ለሚተዳደሩት ሕዝቦች ሮማዊ ዜግነትን ይሰጡ ስለነበር፥ የቅዱስ ጳውሎስ አባት በዜግነት ሮማዊ ነበር። ይህም ለቅዱስ ጳውሎስ ተላልፎለታል።
ቅዱስ ጳውሎስ በ፲፭ ዓመት ዕድሜው ወደ ትውልድ ሀገሩ በመመለስ በኢየሩሳሌም ከነበረው የታወቀው የገማልያል ትምህርት ቤት ገባ።
በዚያም የአይሁድን ሕግና ሥርዓት እየተማረ እስከ ፴ ዓመቱ ቆየ። ገማልያል ፈሪሳዊ ስለነበር ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ይህን ተቀብሎታል። በ፴ ዓመቱ የአይሁድ ሸንጎ አካል ሆኖ ተቆጠረ።
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚያስተምርበት ዘመን ቅዱስ ጳውሎስ በኢየሩሳሌም ስለነበረ ሁኔታዎቹን ሁሉ ያውቃል።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በአይሁድ ሸንጎ አባልነት ለሁለት ዓመታት በሠራበት ወቅት ለኦሪታዊ እምነቱ ቀናተኛ ፈሪሳዊ በመሆኑ ክርስቲያኖችን በማናቸውም አጋጣሚ ይቃወም ነበር።
እንዲያውም ሊቀዲያቆናት እስጢፋኖስን በማስተማሩ ምክንያት ተከሶ ለአይሁድ ሸንጎ በቀረበ ጊዜ የተከራከረው እርሱ ነበር።
በድንጋይ ተወግሮ በሰማዕትነት ሲያርፍም የወጋሪዎችን ልብስ ይጠብቅ የነበረው እርሱ ነው።
በ፴፪ ዓመት እድሜው ከኢየሩሳሌም ፪፻፳፫ (ሁለት መቶ ሃያ ሦስት) ኪ.ሜ. ርቀት በስተሰሜን በኩል በምትገኘው የደማስቆ ከተማ ብዙ ክርስቲያኖች መኖራቸውን ሲሰማ ወደ ሊቀ ካህናቱ ቀርቦ ክርስቲያኖችን ለማጥፋት የሚያስችለውን የፈቃድ ደብዳቤ አገኘ።
ከዚህም በኋላ ጭፍሮችን አስከትሎ ወደ ደማስቆ አመራ።
ሐዋርያው ጳውሎስ ወደ ከተማዋ ለመድረስ ጥቂት ሲቀረው ነበር ከሰማይ የወረደው ብርሃን አካባቢውን ያለበሰውና «ሳውል ሳውል ለምን ታሳድደኛለህ?» የሚለውን ድምፅ የሰማው።
ሐዋርያው ጳውሎስም «ጌታ ሆይ ማን ነህ?» ብሎ ጠየቀ። «አንተ የምታሳድደኝ እኔ የናዝሬቱ ኢየሱስ ነኝ። የመውጊያውን ብረት ብትቃወም ለአንተ ይብስብሃል» ሲል መድኃኒታችን ተናገረው።
ያን ጊዜም በወደቀበት ሆኖ እየተንቀጠቀጠ «ጌታ ሆይ ምን አደርግ ዘንድ ትወዳለህ?» ሲል ጠየቀ።
ከዚህ በኋላ ተነሥቶ ወደ ደማስቆ እንዲገባ ተነገረው። (የሐዋ. ፱፥፩)
የሐዋርያው ዓይኖች ለማየት አልቻሉም። እየተመራ ወደ ደማስቆ ገባ።
ለሦስት ቀናት ያህልም እህል ሳይቀምስ ቆየ።
በዚያች ዕለት እግዚአብሔር አምላክ በደማስቆ ለሚገኘው እና ሐናንያ ለተባለው አባት በራእይ ተገለጠለት።
ቅዱስ ጳውሎስም ያለበትን አድራሻ ነገረውና ሄዶ እንዲያጠምቀው አዘዘው። ሐናንያ አስቀድሞ የቅዱስ ጳውሎስን ማንነት ያውቃል።
አብዛኞቹ በደማስቆ የሚገኙት የቅዱስ ጳውሎስን ማንነት ያውቃል።
አብዛኞቹ በደማስቆ የሚገኙት ክርስቲያኖች ከኢየሩሳሌም በስደት የመጡ ናቸው።
ያን ስደት ያስነሣው ደግሞ በቅዱስ እስጢፋኖስ ላይ የደረሰው መከራ ነው።
በዚህ የቅዱስ እስጢፋኖስ ሰማዕትነት ደግሞ ዋናው ተዋናይ ሐዋርያው ጳውሎስ ነበር።
ይህን የሚያውቀው ሐናንያ በቅድሚያ ከእግዚአብሔር ጋር መከራከር ጀምሮ ነበር። እግዚአብሔር አያውቀው ይመስል ስለ ቅዱስ ጳውሎስ ማስረዳት ጀመረ።
በመጨረሻ ግን «ይህ በአሕዛብም በነገሥታትም በእሥራኤልም ልጆች ፊት ስሜን ይሸከም ዘንድ ለእኔ የተመረጠ ዕቃ ነውና ሂድ፤ ስለ ስሜ ስንት መከራ ሊቀበል እንዲያስፈልገው እኔ አመለክተዋለሁና» በማለት እግዚአብሔር ሐናንያን ላከው።
ሐናንያ ቅዱስ ጳውሎስን ካጠመቀውና ካስተማረው በኋላ ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ዓረብ ሀገር መሄዱን ራሱ ተናግሮአል። (ገላ ፩፥፲፯)
ለ፫ ዓመታት በዓረቢያ በረሃ ከቆየ በኋላ ወደ ደማስቆ ከተማ ተመለሰ።
በዚያም በነበሩ አይሁድ መካከል በፊት ያሳድደው የነበረውን ኢየሱስ ክርስቶስን መስበክ ጀመረ።
ከዚያ በፊት በፈሪሳዊነቱና ለአይሁድ ሕግ በነበረው ቅንዓት የሚታወቀው ጳውሎስ ዛሬ ወንጌል ሲሰበክ በማየታቸው አይሁድ ተነሡበት።
በዚህም የተነሣ የደማስቆ ክርስቲያኖች በቅርጫት አውርደው ወደ ኢየሩሳሌም ላኩት።
ቅዱስ ጳውሎስ ኢየሩሳሌም ሲደርስ የገጠመው ሁለት ችግር ነበር። በቅድሚያ አይሁድ ጳውሎስን እንደሚያውቁት እና እንደለመዱት ሆኖ ስላላገኙት ሊገድሉት ተነሡ።
በሌላ በኲል ደግሞ ክርስቲያኖች የቅዱስ ጳውሎስን መመለስ ሊያምኑ አልቻሉም።
በመጨረሻ ግን በርናባስ ወደ ሐዋርያት ዘንድ ወስዶ የጳውሎስን መመለስ በመተረክ እንዲያምኑት አደረጋቸው።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በኢየሩሳሌም በድፍረት በማስተማሩ አይሁድ ስለተቃወሙት ከተማዋን ትቶ በቂሳርያ በኲል ወደ ትውልድ ሀገሩ ጠርሴስ ተመለሰ።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በጠርሴስ ከተማ ለዘጠኝ ዓመታት ቆይቷል።
ከኢየሩሳሌም ውጭ የአሕዛብ ከተማ በነበረችው በአንጾኪያ የክርስትና ሃይማኖት ተስፋፋ።
ከኢየሩሳሌም የተሰደዱት ክርስቲያኖች የአንጾኪያን ሕዝብ ተግተው በማስተማራቸው ዝናው እስከ ኢየሩሳሌም ደረሰ።
በዚህም ምክንያት በኢየሩሳሌም የነበሩት አበው በርናባስን ወደ አንጾኪያ ላኩት።
በርናባስ የግሪክ ቋንቋ ችሎታ ያለውን፣ ከማንኛውም ሰው ጋር መግባብ የሚችለውን፣ ደግሞም እግዚአብሔር ለአሕዛብ ሐዋርያ እንዲሆን የመረጠውን ቅዱስ ጳውሎስን ከጠርሴስ በማምጣት በአንጾኪያ ሥራቸውን ጀመሩ።
በገላትያ መልእክቱ ምዕራፍ ፪ ላይ ራሱ እንደገለጠው ከአሥራ አራት ዓመት በኋላ ወደ ኢየሩሳሌም ከአንጾኪያ ክርስቲያኖች የሰበሰበውን ርዳታ ይዞ ወጣ።
በዚህም በአይሁድና በአሕዛብ መካከል የነበረውን መለያየት ክርስትና አንድ እንዳደረገው አስመሰክሯል። | 254 |
| 14 | ፩. ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ
ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ የተወለደው በገሊላ ባሕር ዳር በምትገኘው በቤተሳይዳ ነው።
የአባቱ ስም ዮና ይባላል። ከአምስት ዓመቱ ጀምሮ ያደገው በቅፍርናሆም ከተማ ሲሆን በጐልማሳነቱ ከወንድሙ ከእንድርያስ ጋር በገሊላ ባሕር ዓሳ ማሥገር ጀመረ።
ለደቀመዛሙርነት ሲመረጥ ዕድሜው ፶፭ ዓመት እንደነበረ ይነገራ፤ ወደ ጌታችን ያመጣውም ወንድሙ እንድርያስ ነው።
ቅዱስ ጴጥሮስ በርናባስና ወንጌላዊው ማርቆስ ቤተ ዘመድ ናቸው። የማርቆስ አባት አርስጦቡሎስና በርናባስ በእናት የሚገናኙ ወንድማማች ናቸው።
ቅዱስ ጴጥሮስ ያገባው የበርናባስና የአርስጦቡሎስን እኅት ስለነበር በጋብቻ ይዛመዳሉ።
ቅዱስ ጴጥሮስ ለሐዋርያነት ሲጠራ መተዳደሪያው የነበረውን መረቡንና ታንኳውን እንዲሁም አባቱን እርግፍ አድርጐ ትቶ ጌታውን የተከተለ ሐዋርያ ነው።
የቅዱስ ጴጥሮስ በመጀመሪያ ስሙን ስምዖን ብላ እናቱ የጠራችው በነገዷ ስም እንደሆነ ይነገራል።
በቂሳርያ ከተማ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ «ማን ትሉኛላችሁ?» ብሎ በጠየቀ ጊዜ «አንተ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ» ብሎ ለአይሁድ ሊቃውንት የተሰወረውን ምሥጢረ ተዋሕዶ ገልጦ በመመስከሩ ጌታችን «አንተ ጴጥሮስ ነህ» ብሎታል ይህም በላቲን ቋንቋ ዐለት ማለት ነው፤ በአርማይክ ደግሞ ኬፋ ይባላል።
ቅዱስ ጴጥሮስ ከአዕማድ ወይንም የምሥጢር ሐዋርያት ከእነ ዮሐንስ እና ያዕቆብ ጋር የሚቆጠር ነው።
ከሐዋርያት ሁሉ ቀደም ቀደም የማለት ባሕርይ ነበረው። ጌታ በጥብርያዶስ ባሕር ላይ ሌሊት በእግሩ ሲመጣ ቢመለከት ወደ አንተ እመጣ ዘንድ እዘዘኝ በማለት ካስፈቀደ በኋላ ወደ ጌታ ለመምጣት መንገድ ጀምሮ በመሐል ቤት ጥርጣሬ ገባውና መስጠም ስለጀመረ ጌታችን «ያመንክ እንጂ ያላመንክ አትሁን» ብሎ ገስፆ ከመስጠም አድኖታል። (ማቴ ፲፬፥፳፪-፴፫)
በቅፍርናሆም ጉባኤ ጌታን ምሥጢረ ቁርባንን ሲያስተምር፣ አይሁድ ስላልገባቸው ወደ ኋላ አፈገፈጉ። ከደቀ መዛሙርቱም «ብዙዎቹ ወደ ኋላ ተመለሱ» በዚህን ጊዜ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ «እናንተ ደግሞ ልትሄዱ ትወዳላችሁ?» ብሎ ሐዋርያትን ጠየቃቸው።
በዚህ ሰዓት «ጌታ ሆይ ወደ ማን እንሄዳለን? አንተ የዘላለም የሕይወት ቃል አለህ። እኛስ አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ እንደሆንክ እናምናለን» በማለት ሐዋርያትን ወክሎ የመለሰ እርሱ ነው። (ዮሐ ፮፥፷፮-፷፰)
ቅዱስ ጴጥሮስ ጌታን ይወድ ነበር። ፍቅሩ ግን ቅንዓት የተቀላቀለበት በመሆኑ ጌታችን ለደቀ መዛሙርቱ የሞቱን ነገር ቀድሞ ሲነግራቸው አይሁንብህ በማለት ተከራክሯል። (ማቴ ፲፮፥፳፫)
በኋላም «ሁሉም በአንተ ቢሰናከሉ እኔ ከቶ አልሰናከልም» ብሎ በራሱ ቅንዓት ተማምኖ ተናግሮ ነበር። ጌታችን «ዶሮ ሳይጮህ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ» እያለው እንኳን «ከአንተ ጋር መሞት እንኳን የሚያስፈልገኝ ቢሆን ከቶ አልክድህም» በማለት የተናገረ ሰው ነው። (ማቴ ፳፮፥፴፬)
ቅዱስ ጴጥሮስ አስቀድሞ የተናገረውን ቃል ለመጠበቅ ሞክሮ ነበር። ጌታ ዛሬ «የሰው ልጅ አሳልፎ ይሰጣል» ብሎ አስተምሮአቸው ነበርና መከላከያ ይሆነኛል ብሎ ሠይፍ ደብቆ ይዞ ነበር።
የሮም ጭፎሮችም ጌታን ለመያዝ ሲጠጉ የሊቀ ካህናቱን ባርያ (ማልኰስን) በሠይፍ ጆሮውን ቆረጠው። ጌታችን ግን ሞቱ በፍቃዱ ለድኅነተ ዓለም ነውና «ሠይፍህን ወደ ሰገባው» መልስ ሲል ገሠፀው።
ቅዱስ ጴጥሮስ የሚታወቅበት ሌላው ትልቁ ነገር ንስሐው ነው። ጌታው የነገረው መድረሱን፣ ቃል የገባለትን አምላኩን መበደሉን እንዳወቀ ከግቢው ወጥቶ አለቀሰ።
ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በዕድሜው ታላቅነት በሐዋርያት ዘንድ እንደ አባት ይታይ ስለነበር ጌታ በተለያቸው ጊዜ ሐዋርያቱን ሊመግብ ወደሚያውቀው ሙያ ዓሳ ወደ ማሥገሩ ተሠማራ።
ጌታም አስቀድሞ የመረጠው እርሱ ነውና ቢክደው እንኳን በንስሐ በመመለሱ ንስሐውን መቀበሉን፤ ዛሬም እንደሚወደው ይገልጽለትም ዘንድ በጥብርያዶስ ባሕር ተገለጠለት። (ዮሐ ፲፰፥፲)
ሦስት ጊዜ ክዶት ነበርና ቀኖና ሰጠው። አሁን ቅዱስ ጴጥሮስ በራስ መተማመኑ እንዳላዋጣው ዐውቆአልና «ትወደኛለህን?» ተብሎ ሲጠየቅ «አንተ ታውቃለህ» ነበረ መልሱ።
የራሱ ዕውቀት የት እንዳደረሰው ያውቃልና ጌታችንም ኅዳጌ በቀል (በቀልን የሚተው) ነውና ዛሬም እንደሚወደው፣ በንስሐ ተመልሶአልና ዛሬም ለእርሱ የሰጠውን ክብር እንደማያጐድልበት ሲነግረው ግልገሎቼን አሠማራ፣ ጠቦቶቼን ጠብቅ፣ በጐቼን አሠማራ» በማለት አደራውን አስረከበው። ከዚያም በሞቱ እንደምን አድርጐ እግዚአብሔርን አንደሚያከብረው ነግሮት ወደ ሰማያት ዐረገ። (ዮሐ ፳፩፥፲፭-፲፯)
ቅዱስ ጴጥሮስ በአራቱም የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ላይ በተቀመጡት የሐዋርያት ዝርዝር ቀዳሚውን ሥፍራ ይዞ ይገኛል።
ይህም፦
፩. በሽምግልና አባትነቱ፣
፪. ጌታ በቂሳርያ በሰጠው ቃል ኪዳን፣
፫. የሐዋርያት አፈ ጉባዔ ሆኖ ይናገር ስለነበር፣
፬. በጥብርያዶስ ባሕር በተሰጠው ቃል መሠረት ነው።
በዚህም የተነሣ በይሁዳ ምትክ ሌላ ሐዋርያ እንዲመረጥ ሐሳብ ያቀረበ እርሱ ነበር።
በበዓለ ሃምሳም ለደቀመዛሙርቱ መንፈስ ቅዱስ በወረደላቸው ጊዜ ለተሰበሰቡት አይሁድ አፈ ጉባዔ ሆኖ ወንጌልን የሰበከ ፫፼ (ሦስት ሺህ) ምእመናንንም አሳምኖ የመጀመሪያዋን አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን በኢየሩሳሌም የመሠረተ እርሱ ነው። (የሐዋ. ፩፥፲፮-፳፫፣ ፪፥፲፬-፴)
አስቀድሞ ፈሪ የነበረውና በሊቀ ካህናት ቀያፋ ግቢ ጌታውን የካደው ቅዱስ ጴጥሮስ፣ የመንፈስ ቅዱስን ኃይል ካገኘ በኋላ ግን በአይሁድ ሸንጐ ድውይ ፈወስክ ተብሎ በተከሰሰ ጊዜ በድፍረት ስለ መድኃኔዓለም ክርስቶስ መሰከረ።
ቆርነሌዎስን በማጥመቅ ወንጌልን ለአሕዛብ አስቀድሞ የሰበከው ሐዋርያ ነው። ይህ ሐዋርያ ልዑል እግዚአብሔር ባደለው ጸጋ ጥላው እንኳን ድውያንን ይፈውስ ነበር። የሐዋ ፭፥፲፭።
በሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ ፲፭ ላይ በ፶ ዓ.ም. አካባቢ በኢየሩሳሌም በተደረገው የሐዋርያት ሲኖዶስ ከአንጾኪያ ክርስቲያኖች ለቀረበው ጥያቄ የመጀመሪያውን መልስ የሰጠው እርሱ ነበር።
ስለ ቅዱስ ጴጥሮስ መልክና ቁመና ጥንታዊያን መዛግብት እንደሚከተለው ያቀርቡታል። «ፊቱ ሰፋ ያለ ሲሆን ሪዛምና መካከለኛ ቁመት የነበረው ራሰ በራ ሰው ነው። በማናቸውም ነገር ፈጣንና ቀልጣፋ ነበር።»
በቤተ ክርስቲያን ታሪክ መሠረት ቅዱስ ጴጥሮስ በፍልስጥኤም፣ በሶርያ፣ በጳንጦን፣ በገላትያ፣ በቀጰዶቅያ፣ በቢታንያ እና በሮሜ ሰብኳል።
ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በሮሜ አንድ ዓመት ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር ካስተማረ በኋላ የሮሜ ክርስቲያኖች እየበዙ ከመምጣታቸውም በላይ የክርስትናው ጉዞ እስከ ሮማ ባለሥልጣናት ደረሰ።
የኔሮን የቅርብ ባለሥልጣናት የሆኑት የአልቢኖስና የአግሪጳ ሚስቶች ወደ ክርስትናው ገቡ። በዚህን ጊዜ ኔሮን ንጉሠ ሮማ በቅንዓት ተነሣባቸው።
ኔሮን በሮም የነገሠው በ፶፬ ዓ.ም. ነው። በመንግሥቱ መጀመሪያ ደግ ሰው ነበረ። ነገር ግን በነገሠ በዓመቱ የጨካኝነት ዐመሉ ብቅ ማለት ጀመረ እና የአባቱን ልጅ አስገደለ።
በ፶፱ ዓ.ም. ደግሞ እናቱን በመርዝ ገደለ። በ፷፫ ዓ.ም. እያስተማረ ያሰደገውን መምህሩን ፣ በ፷፪ ዓ.ም. የልጅነት ሚስቱን አግታሺያን አስገደለ።
ከእርስዋ በኋላ ያገባትን ሚስቱንም ፓፒያን በርግጫ ብሎ ገደላት።
ኔሮን በ፷፬ ዓ.ም. እርሱ ከከተማው ወጣ ብሎ በሚገኘው ቤተ መንግሥቱ ተቀምጦ የሮማን ከተማ እሳት ለቀቀባት። | 208 |
| 15 | ብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወቅዱስ ጳውሎስ
የቅዱሳን ሐዋርያት ታሪክ ገድልና ሥራ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ በሙሉ አልሰፈረም።
አርባዕቱ ወንጌላት ሐዋርያት እንዴት እንደተጠሩና እስከ ዕርገት ድረስ የነበራቸውን ሁኔታ ሲጽፉ፤ ወንጌላዊው ሉቃስ ደግሞ የሐዋርያትን ታሪክ እስከ ፷ዎቹ መጀመሪያ ያለውን ጽፏል።
ከዚህ በመለስ ያለውን የሐዋርያት ታሪክ ለማወቅ ግን ዋናው ምንጩ የቤተ ክርስቲያን የታሪክ መጻሕፍት ናቸው።
የሐዋርያት ደቀመዛሙርት እነ ፓፒያስ፣ ፖሊካርፐስ፣ አግናጥዮስ፣ ቀሌምንጦስ ዘሮም ወዘተ. የአባቶቻቸውን ታሪክ ጽፈው አቆይተውልናል።
ከዚህ በኋላ ጊዜም በ፪ኛውና በ፫ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተነሱት የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ጸሐፍት እነ አውሳብዮስ፣ ሩፊኖስ፣ ጄሮም፣ ወዘተ. በትውፊት የተቀበሉትን መዝግበው አልፈዋል።
ቅዱሳን ሐዋርያት ገድላቸው የተጻፈላቸው፣ በዓላቸው የተከበረላቸው የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች ናቸው።
በቤተ ክርስቲያናችን በሐምሌ ፭ ቀን በታላቅ ድምቀት በዓላቸው ከሚከበረው ሐዋርያት መካከል የሐዋርያው የቅዱስ ጴጥሮስና የሐዋርያው የቅዱስ ጳውሎስ ታሪክ እንደሚከተለው ነው። | 241 |
| 16 | بدون متن... | 284 |
| 17 | ፈተና 11:00 ስለሆነ ሁሉም አባል በሰዓት እንዲገኝ። | 261 |
| 18 | ለወላጅ እና ለአባላት
ሁሉም አባል የቀረበትን ወርሃዊ መዋጮ የመክፈል ግዴታ አለበት። የአመቱን ያልከፈላችሁ አባላት በሙሉ ቅዳሜ እና እሁድ እንድትከፍሉ ከወዲሁ እናሳዉቃለን። ማለት አብዛኛዉ አባላት የስድስት ወር ስለሆነ የከፈለው የቀረዉን ክፍያ በ04 እና 05 /11/2018 ዓ.ም እንድትከፍሉ እናሳስባለን። ለህጻናት ከአንደኛ ክፍል እስከ ስድስተኛ ክፍል በየወር 40*6= 240 ብር ሲሆን ለወጣቶች ማለት ከሰባተኛ ክፍል እስከ 12 ክፍል ድረስ ያላችሁ ደግሞ 6*50=300 ብር መሆኑን እናሳዉቃለን። የዓመቱን የከፈላችሁትን አይመለከትም። | 356 |
| 19 | 1 | 322 |
| 20 | አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሰኔ ሠላሳ በዚች ዕለት ነቢይ ሰማዕትና ሐዋርያ የሆነ መጥምቁ ዮሐንስ ተወለደ ።
ይህም በእናቱ ማኅፀን ውስጥ ሳለ ለእግዚአብሔር ልጅ የሰገደው ነው ። ይህም በመድጎን ክርስቶስ ራስ ላይ እጁን ጭኖ በውኃ ያጠምቀው ዘንድ የተገባው ነው ። በቅዱስ ወንጌል እንደ ተነገረ ወንድ ልጅን ትወልድ ዘንድ የኤልሳቤጥ የፅንሷ ወራት በተፈጸመ ጊዜ ወንድ ልጅን ወለደች ። ዘመዶቿና ጐረቤቶቿ እግዚአብሔር ቸርነቱን እንዳበዛላት በሰሙ ጊዜ ስለርስዋ ደስ አላቸው ።
በስምንተኛውም ቀን ሊገዝሩት መጡ በአባቱ ስም ዘካርያስ ብለው ጠሩት ። እናቱ ግን አይሆንም ዮሐንስ ይባል አለች ። ከዘመዶችሽ ስሙ እንዲህ የሚባል የለም አሏት ። አባቱንም ጠቅሰው ማን ሊባል ትወዳለህ አሉት ። እርሱም ብራና ለምኖ ስሙ ዮሐንስ ይባል ብሎ ጻፈ ። ሁሉም አደነቁ ። ያን ጊዜም አንደበቱ ከድዳነት ተፈትቶለት ተናገረ እግዚአብሔርንም ፈጽሞ አመሰገነው ። ስለ ልጁና ስለ መድኃኒታችን መምጣት ልጁ ዮሐንስም የልዑል ነቢይ እንደሚባልና በእግዚአብሔርም ፊት እንደሚሔድ ትንቢት ተናገረ ።
ሰብአ ሰገልም መጥተው ከሔዱ በኋላ ሄሮድስ ሕፃናትን በገደላቸው ጊዜ ስለ ሕፃኑ ዮሐንስ ለሄሮድስ ነገሩት እንዲገድሉትም ጭፍሮችን ላከ ጭፍሮችም ወደ አባቱ ዘካርያስ መጡ ሕፃኑንም ከእርሱ ፈለጉት አባቱም አንሥቶ በትከሻዎቹ ተሸክሞ ወደ ቤተ መቅደስ ከእርሱ ጋራ እንዲሔዱና ሕፃኑን ከዚያ እንዲወስዱት ወታደሮችን ለመናቸው ።
ከዚህም በኋላ ሕፃኑን በመሠዊያው ጠርዝ ላይ አኖረውና ከዚህ ራሳችሁ ተቀብላችሁ ውሰዱት አላቸው ወዲያውኑ የእግዚአብሔር መልአክ ነጥቆ ወደ በረሀ ወሰደው ። ጭፍሮችም ባላገኙት ጊዜ አባቱ ዘካርያስን ገደሉት ። ሕፃኑ ግን አድጎ ለእስራኤል እስከተገለጠበት ጊዜ ድረስ በበረሀ ውስጥ ኖረ ።
የእግዚአብሔርን መንገድ ጥረጉ ጥርጊያውንም አስተካክሉ እያለ በምድረ በዳ የሚጮህ የዐዋጅ ነጋሪ ድምፅ እነሆ ብሎ ኢሳይያስ የተናገረለት ይህ ነው ። ሚልክያስም ስለሱ እንዲህ አለ ። በፊትህ ጐዳናዬን አስተካክሎ የሚጠርግ መልእክተኛዬን
እኔ እሰዳለሁ ራሱ መድኃኒታችንም ስለርሱ ሲናገር ሴቶች ከወለዱአቸው መጥምቁ ዮሐንስን የሚበልጠው የለም ብሏል ።
ይህ የእግዚአብሔርን ልጅ በአጠመቀውና የማትዳሠሥ ራሱን በዳሠሠው ጊዜ የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት የሚል የአብን ቃል ሰምቷልና ።
ዳግመኛም ክብር ይግባውና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ራስ ላይ መንፈስ ቅዱስ ወርዶ ሲቀመጥ አየ ። እኛም መድኃኒታችን እንዲምረንና ይቅር እንዲለን በአማላጅነቱ እያመን መታሰቢያውን እናድርግ በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን ። | 346 |
