fa
Feedback
የካ ክ/ከተማ ወረዳ 4 ት/ጽ/ቤት ቻናል Yeka sub city wereda 4 Education office channel

የካ ክ/ከተማ ወረዳ 4 ት/ጽ/ቤት ቻናል Yeka sub city wereda 4 Education office channel

رفتن به کانال در Telegram

Government Educational organization

نمایش بیشتر
360
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
#እንኳን አደረሳቹህ #ኢሬቻ #2016 👉በኦሮሞ ሕዝብ ዘንድ  ከጨለማው የክረምት ወራት ብሩህ ወደ ሆነው የመጪው ጊዜ ላሸጋገረ ፈጣሪ ምስጋና የሚቀርብበት የምስጋና በዓል ለሆነው  የኢሬቻ  በዓል  እንኳን በሰላም አደረሳቹህ:: 👉በአሉ የሰላም ፣የደስታ ፣የፍቅር እና የጤና እንዲሆንላቹህ ልባዊ ምኞታችን ነው :፡ የየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04 ት/ጽ/ቤት Baga nagaan Geessan#Irreecha Bara #2016 👉 Ayyaana Irreecha, kan Uummata Oromoo ji'oota qorraa dukkanaa'aa irraa gara waqtii birraa ifa ta'etti jijjiirameef ayyaana galateeffannaa ta'e, nagaa fi baga gammaddan isiniif hawwa. 👉 Nagaa, gammachuu, jaalalaa fi fayyaa akka argattan hawwii keenya guddaadhaa. ✅Wajjiira Barnoota kuta Bulchiinsa magaala Eekkaa Aana 04

እዳ አለብሽ ካልከኝ እከፍልሃለሁ “ወሳኙና ትኩረታችንን ልንጥልበት የሚገባው ነገር እኛ ለሰዎች አደረግን ብለን የምናስበው ውለታ ላይ ብቻ ሳይሆን ሌሎች ለእኛ ያደረጉልንንና አሁን የደረስንበት ደረጃ ለመድረስ ወሳኝ በሆኑት ነገሮችም ጭምር ላይ ሊሆን ይገባዋል” ለሰዎች “ይህንና ያንን ውለታ ሰርቻለሁ” በማለት ከመዘገባቸው ነጥቦች አጠገብ ሌሎች ሰዎች ለእርሱ ያደረጉለትም ጭምር በመመዝገብ ሁኔታውን አመዛዝኖ የሚመለከት ሰው እጅግ ውብ የሆነ አእምሮ ያለው ሰው ነው፡፡ እንዲህ አይነቱ ሰው ከራሱ ይልቅ ሌሎችን ያስቀደመ ሰው ከመሆኑ ባሻገር የትኩረትን ምስጢር በሚገባ የተረዳ ሰው ነው፡፡ የአስራ ሶስት አመት ልጅ ነው፡፡ በእናቱ ላይ ፊቱን ካኮማተረና ካኮረፈ ሰንበት ብሏል፡፡ ለምን ጸባዩ እንደተቀያየረ ለማወቅ ብዙ ብትጠይቀውም መልስ አልሰጥ ስላላት፣ “ጉርምስና” ጀምሮታል” ብላ ተወት አድርጋዋለች፡፡ አንድ ቀን ወደ እናቱ መጣና አንድን ደብዳቤ ሰጣት፡፡ በእንደዚህ መልኩ ደብዳቤን ከልጇ ተቀብላ ስለማታውቅ ለማንበብ ቸኩላ ስትመለከተው እንዲህ የሚል ጸሑፍ አገኘች፡፡ ይህንን ደብዳቤ ለመጻፍ የፈለኩት ያለብሽን እዳ ላስታውስሽና እንድትከፍለኝ ለመጠየቅ ነው፡፡ • ግቢ ውስጥ ያደገውን ሳር የቆረጥኩበት = 5 ብር • ክፍሌን ያጸዳሁበት = 2 ብር • ወደ ሱቅ የተላላኩበት = 3 ብር • ሱቅ ስትሄጂ ወንድምህን ጠብቅ ብልሽኝ የጠበቅኩበት = 4 ብር • ቆሻሻ የደፋሁበት = 5 ብር • ትምህርት ቤት ጥሩ ውጤት ያመጣሁበት = 5 ብር ያለብሽ እዳ ጠቅላላ ድምር = 24 ብር ብዙ ውለታ ያደረገችለትና በጣም የምትወደው ልጇ ሁኔታውን በዚህ መልኩ ማየቱና ያደረገውን ሁሉ እንደ እዳ መቁጠሩ በጣም አስገረማት፡፡ ሁኔታውን በምን መልክ እንደምትይዘው ካሰበች በኋላ ወረቀቱን ገለበጠችና እንዲህ የሚል የምላሽ ደብዳቤ ጻፈችለት፡- እዳዬን ስላስታወስከኝ አመሰግናለሁ፡፡ በመጀመሪያ አንተ ያለብህን እዳ ላስታውስህና አሁንም እዳ አለብሽ ካልከኝ እከፍልሃለሁ፡፡ • ዘጠኝ ወር ሙሉ ማህጸኔ ውስጥ የተሸከምኩበት = ከክፍያ ነጻ • በታመምክ ጊዜ ሁሉ ወደ ሃኪም ቤት ያመላለስኩበትና ገንዘብ ከፍዬ ያሳከምኩበት = ከክፍያ ነጻ • ሌሊት ስታለቅስ ቁጭ ብዬ በመንከባከብ ያደርኩበት = ከክፍያ ነጻ • ከልጅነትህ ጀምሮ ጡት ያጠባሁበትና በየቀኑ ምግብ ሰርቼ ያበላሁበት = ከክፍያ ነጻ • መጫወቻ፣ ልብስና ጫማ የገዛሁበት = ከክፍያ ነጻ • አንድ ነገር እንዳይደርስብህ ወደ ፈጣሪ ጸሎት በማድረግ ያሳለፍኳቸው ቀናትና ሰዓታት = ከክፍያ ነጻ ያለብህ እዳ ጠቅላላ ድምር = 0 ይህንን የእናቱን ደብዳቤ ያነበበው ይህ የአስራ ሶስት አመት ልጅ ሳያስበው አይኖቹ በእንባ ተሞሉ፡፡ እስከዛሬ የታየው እሱ አደረኩኝ የሚለው እንጂ የተደረገለት ነገር አልነበረም፡፡ የእናቱ ምላሽ እድሜ ልኩን የማይረሳ ትዝታን ተወለት፡፡ አንዳንድ ሰዎች እነሱ የከፈሉትን መስዋእትነት ብቻ የመቁጠር ዝንባሌ አላቸው፡፡ ካለፈው ሁኔታቸው አልፈው እዚህ ለመድረሳቸው ምክንያት የሆናቸው ሰውና ሁኔታ እንዳለ ለማሰብ ጊዜም የላቸው፡፡ የታሪኩን ተግባራዊነት ለእናንተው ትቼዋለሁ፡፡ (“ትኩረት” ከተሰነው የዶ/ር ኢዮብ መጽሐፍ የተቀነጨበ)

እንኳን ለደመራ እና የመስቀል በአል አደረሳችሁ። መልካም በአል እንመኛለን🙏 የካ ክ/ከተማ ወረዳ 4 ት/ጽ/ቤት
እንኳን ለደመራ እና የመስቀል በአል አደረሳችሁ። መልካም በአል እንመኛለን🙏 የካ ክ/ከተማ ወረዳ 4 ት/ጽ/ቤት

መልካም በአል እንመኛለን👏 የካ ክ/ከተማ ወረዳ 4 ትምህርት ጽ/ቤት
መልካም በአል እንመኛለን👏 የካ ክ/ከተማ ወረዳ 4 ትምህርት ጽ/ቤት

የአዲስ ብርሃን ቅ.አ/አንደኛ እና መለስተኛ ደረጃ ት/ቤት በቀን 7/1/16 የትምህርት አጀማመር

👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆 ከላይ የምትመለከቱትን ልጅ በማፋለግ አባቱን መምህር ለማ ኦሊን እንተባበራቸው።

አፋልጉኝ ልጀ ማለትም ዮሀንስ ለማ ከትላንት ጀምሮ ስለጠፋብኝ አፋልጉኝ።
አፋልጉኝ ልጀ ማለትም ዮሀንስ ለማ ከትላንት ጀምሮ ስለጠፋብኝ አፋልጉኝ።

አስቸኳይ!! ✅ሀሙስ ጠዋት  2:00 ቅዱስ ዮሴፍ ትምህርት ቤት የሚፈተኑ ተማሪዎች ፈተና መዘጋጀት ያለባቸው ✅የ8ኛ ክፍል ብቻ ሆኖ 👉ሒሳብ 👉እንግሊዘኛ እና 👉አጠቃላይ ሳይንስ ብቻ መሆኑን እናሳውቃቸው!!!

ማስታወቂያ በወረዳችን ለሚገኙ ት/ቤቶች ቅዱስ ዮሴፍ/st.Joseph/ ስኮላርሺፕ የተመዘገቡ ተማሪዎች ሀሙስ 18/12/2015ዓ.ም ጠዋት በት/ቤቱ ተገኝተው ፈተና እንዲፈተኑ አሳውቋቸው።

Yeka Education channel, [04/08/2023, 20:18] [ Forwarded from Yeka Education channel ] [Photo] የትምህርት እድል!! 👉በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርስቲ ቀ/ሚንሊክ ሳይንስ ሸርድ ካንፓሶ Habtamu, [04/08/2023, 20:21] 👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆 ከላይ በተገለጹት አዳሪ ት/ቤቶች 8ኛ ክፍል ያጠናቀቃችሁና ተወዳድራችሁ መግባት የምትፈልጉ ተማሪዎች በማስታወቂያው መሰረት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።

Repost from Yeka Education
የትምህርት እድል!! 👉በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርስቲ ቀ/ሚንሊክ ሳይንስ ሸርድ ካንፓሶ
የትምህርት እድል!! 👉በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርስቲ ቀ/ሚንሊክ ሳይንስ ሸርድ ካንፓሶ

Repost from Yeka Education
👉የትምህርት እድል!! 👉ገላን የወንዶች አዳሪ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት መማር ለምትፈልጉ ወንድ ተማሪዎች የወጣ የትምህርት እድል!!
+2
👉የትምህርት እድል!! 👉ገላን የወንዶች አዳሪ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት መማር ለምትፈልጉ ወንድ ተማሪዎች የወጣ የትምህርት እድል!!

Repost from Yeka Education
👉የትምህርት እድል!! 👉እቴጌ መነን የልጅ አገረዶች አዳሪ 2ኛ ደ/ ት/ቤት የወጣ የት/ት እድል!!
+4
👉የትምህርት እድል!! 👉እቴጌ መነን የልጅ አገረዶች አዳሪ 2ኛ ደ/ ት/ቤት የወጣ የት/ት እድል!!

ማስታወቂያ! 👉በ2015 የትምህርት ዘመን 6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ እና ሀገራቀፍ ፈተና ተፈታኝ ለሆናችሁ ተማሪዎች በሙሉ 👉ቀደም ሲል በቀጥታ / ኦላይን መመዝገባችሁ ይታወቃል፡፡ ከዚህ ጋርም በተያያዘ የተመዘገባችሁበትን መረጃ ትክክለኛነት ለማረጋገጥ እንዲቻል 👉ለ6ኛ ክፍል https://aa6.ministry.et እና 👉ለ8ኛ ክፍል https://aa.ministry.et ሊንኮችን በመጫን 👉View Result የሚለውን በመጫን የመለያ ቁጥራችሁን  እና ስም  / Registration Number and First Name  በማስገባት ማየት የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ስህተት ካለበት ለትምህርት ቤታችሁ በስቸኳይ እንድታሳውቁ እናሳስባለን፡፡ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ለ8ኛ ክፍል የሚለውን ሊንክ ተጭናችሁ ቴሌግራም vpn off አድርጋችሁ ስምና registration ቁጥራችሁን በማስገባት ውጤታችሁን መመልከት ትችላላችሁ።ለበለጠ መረጃ የእኛን ቴሌግራም channel እና group ተከታተሉ።ለሌሎችም አጋሩ።

Repost from Yeka Education
አስቸኳይ በየካ ክ/ከተማ 12ኛ ክፍል ተፈታኝ ለሆናቹህ ሁሉም ተማሪዎች(አስፈታኝ ት/ቤቶች) ☑️ሁሉም የሶሻል ተማሪዎች ወደ መፈተኛ ዩንቨስቲ መግቢያ እሁድ ጠዋት 1:00 በ16/11/2015 ዓ.ም በተ
አስቸኳይ በየካ ክ/ከተማ 12ኛ ክፍል ተፈታኝ ለሆናቹህ ሁሉም ተማሪዎች(አስፈታኝ ት/ቤቶች) ☑️ሁሉም የሶሻል ተማሪዎች ወደ መፈተኛ ዩንቨስቲ መግቢያ እሁድ ጠዋት 1:00 በ16/11/2015 ዓ.ም በተመደቡበት የፈተና ማእከል ት/ቤት ነው:: ☑️ ሁሉም የናቹራል ተማሪዎች መግቢያ ሳምንት እሁድ(በ23/11/2015)ሲሆን 1:00 ላይ በፈተና ማእከል በሆኑ ከ7ቱ በአንዱ በተመደቡበት ት/ቤት መገኘት አለባቸው !! ☑️ ከፈተና ጣቢያ ማእከል ውጭ ሳይቆጠሩ በግል ትራስፖርት መሄድ በፍጹም የተከለከለ እና ወደ መፈተኛ ዩንቨርስቲ መግባት የማይቻል መሆኑን እናሳስባለን:: ☑️የግል ት/ቤቶች በተመደባቹህበት ከ7ቱ በአንዱ የፈተና ማእከል በተባለው ቀንና ሰአት ተማሪዎቻቹህን ይዛቹህ እንድትገኙ በጥብቅ እናሳስባለን:: ➩ሸርርርርር የየካ ክ/ከተማ ት/ጽ/ቤት

ከቀን26/10/2015ዓ.ም እስከ 29/10/2015ዓ.ም ድረስ የ2015ዓ.ም የ8ኛ ክፍልና የ6ኛ ክፍል ሀገር አቀፍና ክልላዊ ፈተና በአዲስ አበባ ከተማ ደረጃ የሚሰጥ ሲሆን ለተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ መልካም እድል እንመኛለን።የወረዳችን ትምህርት ቤቶች በቀበና ት/ቤት የሚፈተኑ ሲሆን እንደ የካ ክ/ከተማ ፈተናው በ15 መፈተኛ ጣቢያዎች ፈተናው ይሰጣል።