fa
Feedback
የግጥም ምሽት በቴሌግራም

የግጥም ምሽት በቴሌግራም

رفتن به کانال در Telegram

ይህ ቻናል ከተለያዩ መጽሐፍት የተቀነጨቡ ግጥሞች የሚቀርቡበት እንዲሁም ወርሃዊ የግጥም ውድድሮች የሚካሄዱበት ነው ግጥም ለምትወዱ ሁሉ...የራሳችሁን ሙከራም የምታቀርቡበት ነው ለማንኛውም አስታየት @Nirvana134 እንዲሁም @simba23 ላይ አለን ፧ @yegetem32

نمایش بیشتر
5 931
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-87 روز
-4030 روز
آرشیو پست ها
ወስፌን ከስንደዶ ነበረ ሳዋጀው፣ ክፉ ቀን መጣና ተሰድጄ አረፍኩ በበአት ላለ ሰው፣ ዛሬ ነገ እያልኩ ሰፌዴን ሳልጨርስ በሰበዙ ቀረው፣😂 ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ✍ሳሙኤል አለሙ @Samu
ወስፌን ከስንደዶ ነበረ ሳዋጀው፣ ክፉ ቀን መጣና ተሰድጄ አረፍኩ በበአት ላለ ሰው፣ ዛሬ ነገ እያልኩ ሰፌዴን ሳልጨርስ በሰበዙ ቀረው፣😂 ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ✍ሳሙኤል አለሙ @Samuelalemu5 @yegetem32 @yegetem32

መጠጥ ኮርኒስ ሳይነካ በፊት የተፃፈ ሲሆን የአርቲስት ራሄል ጌቱ ((አልጓጓም))ን ወደ ((አላቆምም)) ቀየርኩት..... ፈታ በሉበት🤣🤣 . . . አላቆምም ........., ይሁን እንጂ መጠጥ ቢንርም ካልመሰለኝ እኔ አላቆምም😂 ባያድለኝ ብርን ለኔ እኖራለው ከዚም ከዛም ብድር ብዬ ========== ኪሴ ኩሩ ኪሴ ቀና ቆርኪ ልጬ ባላገኝ መኪና😂 ልደር እንጂ ከ"ባሩ" ላይ ቆሜ በእውኔ ባጣ አያለው በህልሜ ======== አላቆም...እኔ ...አላቆም ቀን ቢሄድ ቀን ቢመጣ ውዬ አላድርም መጠጥ ሳልጠጣ =========== መልከ መልካም ሰካራም ነኝ አልሰማም ስጠራ ሂሳብ እስኪከፈል ምንም አላወራ ራሴን ሆኜ እንደ አመሌ እጠብቃለው ከፋዩን እከሌ😂 =========== አላቆም....እኔ....አላቆም ቀን ቢሄድ ቀን ቢመጣ ውዬ አላድርም መጠጥ ሳልጠጣ ========== . . . ✍ሳሙኤል አለሙ Join us👇👇 @yegetem32 @yegetem32

በር ና ብሄር (ሳሙኤል አለሙ) ...... ...... ሳንኳኳ ነበረ ከደጃፍ ላይ ቆሜ እንደ ትላንትና በሩን ደጋግሜ ደግሜ ደግሜ እጄ ክንደ ብርቱ የተዘጋውን በር ማንኳኳቱን ያዘ በማንኳኳት ሳቢያ ሰው ይመጣል ብሎ እጄ ደነዘዘ ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። "አቤት" የሚል ጠፋ ደርሶ በር ከፋች ቀረው ዘለግ ላለ ጊዜ ደረት እንደ ደቃች "አንኳኩ ይከፈታል" ነበር ቅዱስ ቃሉ ሲገባኝ ጊዜ ቅሉ በር በብሄር ሆኖ መግባት አይቻልም ካልተመሳሰሉ ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። #samuel_alemu @samuelalemuu @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32

ፀሎት (ፅድቅና ኩነኔ) """""""""""""""""" ግደል ብዬ አለምን ንግዴ ቢቀዘቅዝ፥ ስፀልይ አዝኜ፤ ለሟች መቀበሪያ ነግዶ አትራፊ ፥ሳጥኑን ሻጭ ሆኜ..! ይውደቅልኝ አልል ሰው ይቀጭ ይሰበር፥ መፀለይን ስሻ፤ ሆዴን ማጥገቢያዬ መተዳደሪያዬ፥ ቢሆንም ወጌሻ! ሰው ይታመም ብዬ ከተማፅኖ መሀል ፥አልከት እንደነገር፤ የእለት ጉርሴን ማግኛ ሙያና ተግባሬ ፥ምን ቢሆንም ዶክተር! ሰው ይሰረቅ ብዬ ፀሎት ልመናዬ ፥ከፈጣሪም አይደርስ፤ ቀዬና መንደሩ ፥ሰላሙ ይደፍርስ፤ ወንጀል ተከላካይ ሌባውን አሳዳጅ ፥ምንም ብሆን ፖሊስ! ይህም ሁሉ ሲሆን ክፉ ነገር ባይኖር ከገንዘብ ጎድዬ፥ ከእንጀራዬ ባጣ፤ አልማፀን ነገር በሰው ችግር የኖርኩ ፥ፀሎቴ ቅጥ ያጣ። በዱአና ፀሎት በንዋይ ብዳብር ፥ከገንዘብ ህመሜ፤ ከሰማየ ሰማይ ከፈጣሪ ዘንዳ ፥ቢሰምርልኝ እኔ፤ በሰማይ ጩኸቴ የማላተርፍ ነገር በአንድ ጎን ፀድቄ ፥በአንድ ጎን ኩነኔ! አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32

____ የምዕዳን ጀምበር ____ .......©ሲራክ አንቺ ሁኚ ÷ ደማም ፣ እኔ ልሁን÷ አመዳም ፣ በፍቅርሽ ነው እንጂ ÷ በቃልሽ አልደማም ። ............... @yegetem32 @yegetem32

°°°°° ፊርማ °°°°°° ©ሲራክ ያልፈካው አበባ ሲቀጠፍ ለዝና፣ ለለማኝ ይሰጣል ያልታደለው መና። .... @yegetem32 @yegetem32

ሳቅሽ """""""" ሳቅሽ ላይ ከትሞ የልቤ ቁም ነገር የህይወቴ ልቦና፤ ጥርሶችሽ ላይ ሊፈስ ጓዝ ጨርቁን ሸክፎ ወደአንቺው ሲያቀና! ገስግሶ ገስግሶ ከከንፈርሽ ቀዬ ከጥርስሽ ሲታደም፤ ይጠፋል ጭንቀቱ ብን ብሎ ይሄዳል ይድናል ከህመም! ከአንደበትሽ ግርማ ቅጭል ቅጭል ብሎ ሲሰማ ሳቅሽ፤ ከተቀመጠበት እሮጦ ይወድቃል ሰይጣኑ ሲሸሽ! ሰው ከድብርት ወጥቶ በፍልቅልቅ ሳቅሽ ከደስታ ሲቃመስ፤ ተባብሎ ተባብሎ ከሀሴት ይገባል ጎትቶት ያንቺ ጥርስ! ስለጥርስሽ ውበት ለፍልቅልቅ ሳቅሽ አይ ስንቱ ተብሎ ሲነገር ሲወሳ፤ ብዙ ተሞግሶም እንደዋዛ ሆኖ ስንቱ እየተረሳ፤ ይሄ ከንቱ ፍጥረት ህይወት ስትዘሪበት በፈገግታሽ ወድቆ በሳቅሽ ተነሳ! አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32

የሰሜኑ አህያ ከደቡቡ በቅሎ ከሜዳ አሰማርቶ ከየት ነህ? ሳይለው ይግጣል ተስማምቶ ሰው ነኝ ያለ ፍጡር የባልንጀራውን ስጋ ጠርጎ በልቶ ቅርጫ ይቀራጫል ሆዱ ተቀብትቶ ✍ሳሙኤል አለሙ @samuelalemuu @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32

እንቆቅልሽ በ እንቆቅልሽ (ሳሙኤል አለሙ) . . እንዴት ነሽ ሀገሬ እንደምንድነሽ ምድሬ በስራ ስንዳክር ነግቶ የመሸ ለአይነ-ስጋ ሳኖን ጊዜ ጥሎን ሸሸ እናም አሁን ካገኘሁሽ ዘንዳ አንዳንድ እንቆቅልሽ ከርመው ያልተፈቱ ቅር አለኝ አንቺን ዋስ አድርጌ አንቺን ማስፈታቱ ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። በአንዱ ጋር ስቀደድ በአንዱ ጋር ስሰፋ ህመሜን የሚያውቅ አዋቂ ሲጠፋ እኔው የታመምኩ እኔኑ ያስታመምኩ....ነበረ የከረምኩ ብቻ ግን ለክፉ አልሰጥም ልጆች ያላት እናት አመመኝ እያለች ከአልጋ አሰነብትም ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። እንቆቅልሽ ምን አውቅልህ እንቆቅልሽ ምን አውቅልህ በጠቢባን ዘመን ፈርኦኖች ሞተው ከጎን ሎሌ ይኖራል ድንገት ነፍሱ ነፍስን ብትዘራ ከምግብ መጠጡ ሎሌው ያቀርበዋል ከሞላው ጎተራ ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። አያድርገውና በድንገት ቢባንን ባለራዕይው ከመቃብር መለስ ቀለስ ይላል መለዮ ለባሹ ከመቃብር ስርስር ምግብ አልሰነቀ ውሃ አላስቀመጠ ጠብ"መቅጃ" ብቻ ነው ከጎን የሸጎጠ ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። አውጥተሽ አውርደሽ ካልመጣልሽ መልሱ ከአንድ አንቺ ውጪ ሀገር ስጪኝ እና ልገላግልሽ በሱ ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። መቐሌ ሄጄ ሁሉ መስሎኝ ደጄ ፈልጌ የማገኝ ጌጥአቸውን በጄ (ለአንባቢያን ደህንነት ሲባል "ጥ" በ "ታ" ተተክቶል😂) ግና ምን ያደርጋል እንቆቅልሹን ተረስቶ ስኳትን ከርሜ "ሳላየው አልመጣም" ከሚል ሀሳብ ጋራ ግብግብ ገጥሜ እዚያው ነኝ እዚያው ነኝ ቆዝሜ ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። #samuel_alemu @samuelalemuu @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32

#የመዳፍ_ላይ_እድፍ ~~~~ ©#ሲራክ ~~~~~ . በሀሰት ድባብ ፀዳል ከአይናችን አንደበት የእምባ ፀበል ደርቋል ደግሞም ወዲህ ማዶ.... የግንባር ስር ደዌ ኮርቶ ተንፀባርቋል በውብ መቃ ብዕር በህብረ ቀለም ወዙ አሉን የሀቅ አለም ከማጣት ልቦና ከመገኘት ጓዙ በመሸከፍ ወኔ በጮራነት ልሳን ሰፍረው ያልፈዘዙ ከእጓላዊት ሸራፋ እቅፍ ከአባትነት የሰማይ ግፍ ከማስመሰል ተውኔት ጥንስስ ከልማዳት ድግግም ዳስ እነሆ ክቡድ ቃል በራስህ መካከል ላይነሳ ወድቋል በስንፍና መርፌ ለተጣፈው ሱሪህ ሳትሰጠው መባ እዮሃ አበባ እዮሃ እዮሃ እዮሃ አበባ ዘመንህ ተወልዷል አሜኑን ተውና ወየው ብለህ ግባ እዮሃ ለአንተ ነው.... እነሆ ይሰበር የቀን ሰባራ ጣት እነሆ ተስፋችን በቀኙ ይንጋላት ምድር ገጿ ነትቦ በደም ስትጣጠብ ከሰማይ አክናፋት ስርየት ሲታቀብ አሜን ይሁን ላንተ ለእኔ ግን ወየው ነው ፈጣሪ ሚበዛው ምልኪ ሲረክስ ነው እምነት ሲጎል ነው... ለአንተ ነኝ ባዩ ሰው አልጋህ ላይ ተጋድሞ ከመሬት ምትተኛው ወየው ልበል እንጂ እኔማ ምን ቀረኝ እኛማ ምን ቀረን ካለ መድረስ ቀረን የትም ወድቀን ወድቀን የሸከፍነው ሀሳብ እያወላገደን /°°°°°°° #ሲራክ @siraaq °°°°\ /______~~~~~~________\ @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32

የቡሄ ፀሃይ """""""""""""" አንቺ የሳሎን ጌጥ ቢቆጡሽ አባትሽ ከቤት የማትወጪ እኔ በአመት አንዴ ሆያ ሆዬ እያልኩኝ ከቤታችሁ መጪ በነሀሴ ዝናብ ብቅ የምትይ ፀሀይ ብርሃን አመንጪ ከእናትሽ ጀርባ ሙልሙል ዳቦ ይዘሽ ነይ ውጪ ነይ ውጪ!! አይንሽን እያየሁ "ቡሄ በሉ" እያልኩኝ ስትይ አ.ፈ.ር ቀና ምቱ ተዛባብኝ አፌ ተሳሰረ ግጥሙም ጠፋና። እናትሽ ታዘቡ አባትሽ ተቆጡ ወንድምሽ ደነፋ እኔን ውሀበላኝ የማረገው አጣሁ መላ ቅጤ ጠፋ። ብቻ እዘማምራለሁ "ቡሄ በሉ.....ቡሄ በሉ ይቺን ቆንጆ ለእኔ በሉ እኔም ላቁም መስለምለሙ እሷም ትተው መሽኮርመሙ እዛ ማዶ ጭስ ይጨሳል እዚ ማዶ ልቤ ጨሷል የሷን ፍቅር ይፈልጋል አል'ያ ግን ጨሶ ያልቃል ድምፅዋን ብሰማ ብሩህ ነው ቀኔማ" ብዬ እንኳን ሳልጨርስ መዘማመሬን፤ አባቷ ደቆሱኝ በዱላ ጎኔን። ከቀልብያ ሆኜ ሳልጀምር እሩጫ፤ ዋልጌ ነህ እያለ ይነግረኝ ነበረ የእናቷ ግልምጫ። አቤት የወንድሟ በእኔ ግጥም ስንኝ በብስጭት ናውዞ፤ ካልገደልኩት ይላል በአገላጋዮች ተከቦ ተይዞ። ምን አለ ፈጣሪ ከቤቷ በረንዳ እሷን እያየሁኝ ከሙልሙሉም ዳቦ እየገማመጥኩኝ እሷ ፈገግ ብላ እኔ እየጨፈርኩኝ አመቱን በሙሉ ሆ እያልኩኝ በኖርኩኝ!!! አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) @Run_Viva_Run @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32

በራሴ """"""" ልነሳ ከድክ ድክ ልፍጠን በራሴ እርምጃ ልስበር ቀፎዬን ልውጣ ዕድሜዬን ከምጃጃ! ልጥገብ በራሴ ፍቃድ ያላንቺ አጎራረስ ቀሚስሽን ይዤ አልኑር ልፍጠን በራሴ ዝግመት ጥገኝነት እንዳይሆን የፍቅራችን መሰረት! አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) @Run_Viva_Run @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32

ስትናፍቂኝ ጊዜ ከኔ ዘንድ የቀረ ፎቶሽን ታቅፌ፣ ምላሽ ጠብቃለው "ይናገራል ፎቶ" የሚል ግጥም ፅፌ፣ #samuel_alemu @Samuelalemu5 @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32

የሰው ቅኔ """""""""""" ቅኔ የሰው ተግባር ቅኔ የሰው ነገር ለህይወቱ ማስያዣ ከልቡ ሲጣጣር አላላሁኝ ብሎ አጠባብቆ ሲያስር ቅኔ የሰው ተግባር ቅኔ የሰው ነገር! እፀድቅ አገኝ ብሎ በፀበሉ ፃዲቅ አንድ ስንዝር ሄዶ በእምነቱ ሲፀድቅ ሁለት ስንዝር ኃላ ከመፅደቁ ሲርቅ ከሞላበት ሲጎል ለመቆም ሲወድቅ እንደ ተልባ ቁልል ሄዶ ሲንሸራተት የእንቧይ ካብ ሲሆን ቁልቁሉን ሲንኳተት ቅኔ የሰው ነገር ዘላለም ሲዋትት! አወይ ይሄ ፍጡር በስጋዊ ተድላ በአስተሳሰብ ጠኔ ከትዝብት ሲያውለው የሰም የወርቅ ቅኔ ሊፀድቅ በደገሰው ሲጋብዝ ይውላል ላለው ሰው ፊሊተር ላጣ ሰው ቅራሬ ቅኔ ተግባር የሰው የሰው ተግባር ቅኔ! አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) @Run_Viva_Run @yegetem32 @yegetem32

==> ወንጌላዊ ፍቅር ____ °°°°//©ሲራክ--\\ ፍቅርሽ ጠሊቅ ባህር በልቤ ምህዳር ሰፍቶ ሚዘረጋ ናፍቆትሽ ወጀብ ነው ጀልባ ላልኳት ህይወት ለአንዲት ጀምበር እንኳን ረግቶ ማያረጋ እናም አሁን ደግሞ.... ትዝታሽ ነፋስ ነው ዋሽንቷ ነፍሴ ላይ ትንፋሽ የሚዘራ ሹም ነው በኔ ጀልባ ባህሩን ቀስቅሶ ወጀብ የሚጠራ እናም ደግሞ አንቺ ጠበል ነሽ ለአካሌ መልህቅ ነሽ ለነፍሴ ጀልባይቱን መግቻ የኑረቴ ገዳም ደብሬን አሳማሪ የፍትረትን ትብታብ ስውር ቅኔ መፍቻ -----------//////--------- ==> ወንጌላዊ ፍቅር ____ °°°°//©ሲራክ--\\ ፍቅርሽ ጠሊቅ ባህር በልቤ ምህዳር ሰፍቶ ሚዘረጋ ናፍቆትሽ ወጀብ ነው ጀልባ ላልኳት ህይወት ለአንዲት ጀምበር እንኳን ረግቶ ማያረጋ እናም አሁን ደግሞ.... ትዝታሽ ነፋስ ነው ዋሽንቷ ነፍሴ ላይ ትንፋሽ የሚዘራ ሹም ነው በኔ ጀልባ ባህሩን ቀስቅሶ ወጀብ የሚጠራ እናም ደግሞ አንቺ ጠበል ነሽ ለአካሌ መልህቅ ነሽ ለነፍሴ ጀልባይቱን መግቻ የኑረቴ ገዳም ደብሬን አሳማሪ የፍትረትን ትብታብ ስውር ቅኔ መፍቻ -----------//////--------- @yegetem32 @yegetem32

​​ግለ ወሲብ / ሴጋ /ማስተርቤሽን/ የፈጸመ ሰው ተክሊል ይገባዋል? እነዚህ የእግዚአብሔር ልጆች ከተቃራኒ ጾታ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት ሳያደርጉ ለእንደዚህ አይነት የዝሙት ተግባር በመጋለጣቸው ከሚያነሷቸው ጥያቄዎች መካከል አንዱ ከወንድ ጋር በምንጣፍ አንድ አልሆንኩም ነገር ግን ማስተርቤሽን ፈጽሚያለሁ ድንግል ልባል እችላለሁ ለደናግላን የሚፈጸመው ሥርዓተ ተክሊልስ ለእኔ ልፈጸምልኝ ይችላል? የሚለው ዋነኛ ነው። በዚህ ዙርያ ሙሉ ትምህርቱን ለማግኘት https://t.me/joinchat/AAAAAEqIr4y5A-KFH2Iexw

: እንደ ሙሴ በትር .. (የ'ዋርካ ስር ቃል .. ) : አንድ .. ሁለት .. እያለ ቀን በ'ቀን ድል ሆኖ ሳምንት እያከለ ወራትን ተሻግሮ ዓመታት ሸኝቶ ዘመን የታደለ ህልም አለሽ አውቃለሁ እንደ ፀደይ ሰማይ የተደላደለ .. አንድ .. ያኔ በልጅነት ከየኔታ ደጃፍ መደብ ላይ ተቀምጠሽ ሀ ሲሉ ሀ ብለሽ ፊደልን ስትቆጥሪ ይነግሩሽን ደግመሽ አንቺ ግን በሀሳብ እሩ .. ቅ ሄደሽ ነበር በ"ተስፋ ተስበሽ .. አየሽ .. የልጅነትን ዳር ፥ ድንበሩን አልፈሽው በምናብ ጎዳና ተጉዘሽ ነበረ ተስፋ ይሉትን ህልም ሀ ብለሽ ያኖርሽው። ሁለት .. በ "ሀ" የቋጠርሽው የተስፋሽ መቀነት ከሰማይ ቢርቅም አንቺ ግን ታውቂያለሽ በይሆናል መንገድ ወደ ህልምሽ መትመም (ተጓዥም አይድለሽ .. ) ሀ ብለሽ በተስፋ የጀመርሽው ጉዞ ግቡን እንዲመታ እምነት አከልሽበት .. መቀበልን አውቀሽ .. ከታላቁ የኔታ .. አየሽ .. መጠየቅ ባልበዛው የልጅነት ዓለም መቀበል እምነት ነው ወደ ተስፋ መንገድ ሁ እያሉ ማዝገም። ሦስት .. በሚያምረው ተራራ የዘራሽው ተስፋ እየለመለመ እምነትሽ ያፈካው የህይወትሽ አፀድ ሰው እያስገረመ አንድ .. ሁለት .. እያለ ከ ሀ የጀመርሽው እምነት'ና ተስፋሽ ፍቅር(ሂ) አበቀለ። አየሽ .. በ ሀ የጀመሩ ወደ ሁ ሲዘልቁ የህይወት ውብ ቅኔ ሂ ላይ የሚፈታ .. ፍቅር አይድል ወርቁ!? ሀ ተስፋ ፣ ሁ እምነት ፣ ሂ ፍቅር ይኸው ነበር ህልምሽ እንደ ሙሴ በትር .. የኑረትን ባህር ከፍሎ የሚያሻግር!! 👉@Tedder12 @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32

: እንደ ሙሴ በትር .. (የ'ዋርካ ስር ቃል .. ) : አንድ .. ሁለት .. እያለ ቀን በ'ቀን ድል ሆኖ ሳምንት እያከለ ወራትን ተሻግሮ ዓመታት ሸኝቶ ዘመን የታደለ ህልም አለሽ አውቃለሁ እንደ ፀደይ ሰማይ የተደላደለ .. አንድ .. ያኔ በልጅነት ከየኔታ ደጃፍ መደብ ላይ ተቀምጠሽ ሀ ሲሉ ሀ ብለሽ ፊደልን ስትቆጥሪ ይነግሩሽን ደግመሽ አንቺ ግን በሀሳብ እሩ .. ቅ ሄደሽ ነበር በ"ተስፋ ተስበሽ .. አየሽ .. የልጅነትን ዳር ፥ ድንበሩን አልፈሽው በምናብ ጎዳና ተጉዘሽ ነበረ ተስፋ ይሉትን ህልም ሀ ብለሽ ያኖርሽው። ሁለት .. በ "ሀ" የቋጠርሽው የተስፋሽ መቀነት ከሰማይ ቢርቅም አንቺ ግን ታውቂያለሽ በይሆናል መንገድ ወደ ህልምሽ መትመም (ተጓዥም አይድለሽ .. ) ሀ ብለሽ በተስፋ የጀመርሽው ጉዞ ግቡን እንዲመታ እምነት አከልሽበት .. መቀበልን አውቀሽ .. ከታላቁ የኔታ .. አየሽ .. መጠየቅ ባልበዛው የልጅነት ዓለም መቀበል እምነት ነው ወደ ተስፋ መንገድ ሁ እያሉ ማዝገም። ሦስት .. በሚያምረው ተራራ የዘራሽው ተስፋ እየለመለመ እምነትሽ ያፈካው የህይወትሽ አፀድ ሰው እያስገረመ አንድ .. ሁለት .. እያለ ከ ሀ የጀመርሽው እምነት'ና ተስፋሽ ፍቅር(ሂ) አበቀለ። አየሽ .. በ ሀ የጀመሩ ወደ ሁ ሲዘልቁ የህይወት ውብ ቅኔ ሂ ላይ የሚፈታ .. ፍቅር አይድል ወርቁ!? ሀ ተስፋ ፣ ሁ እምነት ፣ ሂ ፍቅር ይኸው ነበር ህልምሽ እንደ ሙሴ በትር .. የኑረትን ባህር ከፍሎ የሚያሻግር!! 👉@Tedder12 @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32

እምነት """""""" አቤት ለበይክ ብሎ እምነት አንጠልጥሎ ትርፍ ሀሳቡን ጥሎ ለአላህ ይታዘዛል፤ የእግዜር ቃል ነውና ያለ አንዳች ድርድር ልጁን ለመሰዋት ሰይፉን ይመዛል፥ ለፈጣሪ ይገዛል! የእምነት ጥግ የእውነት ምርግ ጠንካራ ምሰሶ መቼም የማይላላ፤ ሰውኛ ባህሪን አሽቀንጥሮ ጥሎ ልጅን ለመሰዋት ያሲዛል ሻሞላ፤ የፈጣሪ ስራ! ምን ሊረባው እሱ የኢስማኢል ህይወት በከንቱ ቢቀጠፍ፤ ምን ሊረባው እሱ ከሳር ክዳን ጎጆ አንድ ሳር ቢመዘዝ! ምን ሊረባው እሱ ፍጥረት ለዱንያ በከንቱ ቢማልል፤ ምን ሊረባው እሱ ከጥቅጥቅ ጎፈሬ አንድ ፀጉር ቢጎድል! ምን ሊረባው እሱ ከእህል ጎተራ አንድ ዘር ቢጠረግ፤ ይለውጥ የለም ወይ ነፍስን በነፍስ ሽሮ መስዋቱን በበግ! አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) @Run_Viva_Run @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32

♦️ለመላው የእስልምና እምነት ተከታይ ለሆናችሁ በሙሉ እንኳ #ለ1441ኛው የኢድ አል አደሀ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን ♦️ይህን በዓል ስናከብር እራሳችንን ከኮሮና ቫይረስ እየጠበቅን የተቸገሩ ወገኖቻችንን በመርዳት በመተሳሰብ እንዲሁም በኮሮና ቫይረስ ተይዘው ሆስፒታል ያሉትን ወገኖቻችን እያሰብን ለሀገራችን ሰላም እና ጤናን እንመኛለን "መልካም በዓል ይሁንላችሁ ከ የግጥም ምሽት በቴሌግራም ቻናል @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32