fa
Feedback
Deacon Biruk Bokicha

Deacon Biruk Bokicha

رفتن به کانال در Telegram

"ይህ የዲያቆን ቡሩክ ቦክቻ የቴሌ ግራም ፔጅ ነው" በዚህ ፔጅ:- ➡የቅዱሳን ጻድቃን ሰማዕታት ገድላቸውን(ታሪካቸውን)እንለቃለን። ➡የቤተክርስትያን አስተምህሮዎችን እንደ አሰፈላጊነቱ የምንለቅ ይሆናል። የYoutube ቻናላችንን Subscribe እያደረጋችሁ https://youtube.com/@dnbirukbokicha?si=vXKnXHeqUjEGmzVU

نمایش بیشتر
1 080
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
🌾‹‹በሕይወት የሚኖሩትም ስለ እነርሱ ቤዛ ሆኖ ለሞተውና ለተነሣውም እንጂ ወደ ፊት ለራሳቸው የሚኖሩ እንዳይሆኑ እርሱ ስለሁሉ ቤዛ ሆኖ ሞተ›› እንደተባለ በሕይወታችን ሁሉ ፋቃዱን በመመርመርና በመፈጸም በቅድስና ልንኖር ይገባናል፡፡2ቆሮ 5፡15 🌾ቅድስናችን በኑሮአችን ሁሉ እንዲሆን ታዘናል (1ጴጥ1፡15)፡፡ ስለዚህ በተሰማራንበት የሥራ መስክ ፣በማኅበራዊ ኑራአችን ፣በምንበላው ምግብ ፣በምንለብሰው ልብስ ፣በንግግራችንና በመሳሰለው ሁሉ ለእግዚአብሔር ደስ የሚያሰኘውን በማድረግ እግዚአብሔርን በሚሞት ሥጋችን እናክብረው፡፡ ‹‹እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ የኃጢአትንም ጭንቀት ከእኛ አስወግደን በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግስት እንሩጥ፡፡ ➡የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን እንከተለው፤ እርሱ ነውርን ንቆ ፣ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጧል ›› ተብሎ እንደተጻፈ ደምን እስከ ማፍሰስ ድረስ ተጋድሎ አድርገን ከኃጢአት ርቀት በቅድስና እንድንኖር ይገባናል(ዕብ 12፡1)። ሥጋዊ ምኞታችንንና መሻታችንን ሰቅለን አሮጌው ሰዋችንን አስወግደን ንስሐ ገብተን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ተቀብለን በቅድስና እንድናኖር ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን፡፡ 🌾ወስብሐት ለእግዚአብሔር🙏

🌾ቅድስት🌾 (የዐቢይ ጾም ሁለተኛ ሳምንት) 🌾«ቅድስት» ማለት የዘይቤ ፍችው « የተቀደሰች የተለየች » ማለት ነው፡፡ ምስጢራዊ መልእክቱ ግን የምስጢረ አድኅኖት ታላላቅ ሥራውን ለመጀመር መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶሰ በገዳመ ቆሮንቶስ ገብቶ ከቆመ ሳያርፍ፣ ከዘረጋ ሳያጥፍ የጾማት የአርብዓው ቀንና ሌሊት ልዩ የሆነችና ክብርት ጾም የምትጀመርበትን ሁለተኛ ሳምንት ከልብ ያሳስበናል፡፡ ማቴ. 4-2 🌾ቅድሰት የዐቢይ ጾም ሁለተኛ ሰንበት ስያሜ ነው፡፡ ስያሜውም ከኢትዮያዊው የዜማ ሊቅ ከቅዱስ ያሬድ የተገኘ ነው፡፡ ከዚህ ሰንበት ዋዜማ ጀምሮ ስለ ዕለተ ሰንበት ቅድስና ይዘመራል፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም ሰንበቱን ስለ ቅድስና ልጆቿን ታስተምርበታለች ፡፡ በቅዳሴ ጊዜ የሚሰበከው ምስባክ ፤ የሚነበቡ መልዕክታት ፤የሐዋርያት ሥራ ና ወንጌል ስለ ቅድስት የሚያስተምሩ ናቸው፡፡ 🌾‹‹ቅዱስ›› ማለት ልዩ፤ክቡር ማለት ነው፡፡ እግዚአብሔር አምላካችን በባሕርዩ ቅዱስ ነው፡፡ ይህም ቅድስና ከማንም ያላገኘው የባሕርይ ገንዘቡ ነው፡፡ መጻሕፍትም የባሕርይ ቅድስናውን ተባብረው መስክረዋል፡፡ ባባሕርዩ ቅዱስ ስለሆነ ‹‹ቅዱስ፡ቅዱስ፡ቅዱስ›› እየተባለ ይመሰገናል፡፡( ኢሳ 6፡1-3፤40፡25 ራዕ 15፡4 ፤ 1ሳሙ2፡2-3፡፡) ➡እኛም ቅዱስ ልጁ በሥጋ ተገልጦ እንዳስተማረን በየዕለት ጸሎታችን ‹‹ስምህ ይቀደስ›› እንለዋለን፡፡ የቅድስና ምንጭ ፡ ቅድስናን የሚሰጥ እርሱ ብቻ ነው፡፡ ‹‹ ቅዱስ›› የሚለው ቃል ለሰዎች ፡ለመላእክት ፡ ለቦታ ፡ለዕቃ፡ ለዕለታት … ቢቀጸልም ቅድስናቸው በባሕርይው ቅዱስ ከሆነው ከእግዚአብሔር የተገኘ ነው፡፡ይህም የጸጋ ቅድስና ይባላል፡፡ 🌾እግዚአብሔር ቅዱስ ስለሆነ በመልኩና በምሳሌው አክብሮ የፈጠረንን እኛም ቅዱሳን እንድንሆን ይፈለጋል፡፡ቅዱስ ጴጥሮስ ‹‹ዳሩ ግን እኔ ቅዱስ ነኝና ቅዱሳን ሁን›› ተብሎ ስለተጻፈ የጠራቸው ቅዱስ እንደሆነ እናንተ ደግሞ በኑሮአችሁ ሁሉ ቅዱሳን ሁኑ ›› ያለንም ይህንን ሲያስተምረን ነው፡፡ ከመፈጠራችን አስቀድሞ መጠን በሌለው ፍቅር የወደደን እግዚአብሔር ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣን ፤ለውርደት ሳይሆን ለክብር፤ለርኩሰት ሳይሆን ለቅድስና፤ለሞት ሳይሆን ለሕይወት ነው፡፡ ➡የመፈጠራችንም ዓላማ በፊቱ በፍጹም ምግባርና ሃማኖት በመመላለስ ከእርሱ ጋር እንድንኖር ነው፡፡ ብርሃን ከጨለማ፡ ጽድቅ ከኃጢአት፡ጋር ኅብረት የለውምና ከእርሱ ጋር ለዘላለም ነግሰን ለመኖር በቅድስና መኖር ይጠበቅብናል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም ‹‹ እግዚአብሔር ለቅድስና እንጂ ለርኩሰት አልጠራንምና ›› ያለንም ለዚህ ነው፡፡/1ተሰ 4*7/ 🌾እግዚአብሔር እኛን የፈጠረበትን አላማ ለኤፌሶን ክርስቲያኖች እንዲህ ገልጾላቸዋል ‹‹ በክርስቶስ ኢየሱስ ሰማያዊ ሥፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አባት እግዚአብሔር ይመስገን፡፡ ብሎ ካመሰገነ በኋላ ‹‹ ዓለም ሳይፈጠር በፊቱ ቅዱሳን ፡ንጹሐንና ያለነውር በፍቅር ያደርገን ዘንድ ለእርሱ መረጠን›› ኤፌ 1፡3-4 አስቀድሞ ስለወደደንና ስላከበረንም ከሌሎች ፍጥረታት በተለየ መልኩ የሚያስፈልገንን ሁሉ አዘጋጅቶ በእጆቹ ካበጀን በኋላ የሥነ ፍጥረት ዘውድ አድርጎ በገነት አኖረን ፡፡(ዘፍ 1፡26 ፤መዝ 8፡1) ➡የቀደመው አዳም አታድርግ የተባለውን በማድረጉ በንዝህላልነትና በስንፍና በከይሲ ዲያብሎስም ምክር ተዋረደ፡፡ በሞተ ሥጋ ላይም ሞተ ነፍስ ፤በርዕደተ መቃብር ላይ ርዕደተ ሲኦል ተፈረደበት፡ በባሕርዩ ሞት ገባበት፡ተዳደፈ፡፡ ክፉ ፍትወታት የሚያጠቁትና የሚያሸንፉት የዲያብሎስና የኃጢአት ባርያ ሆነ፡፡ በማይለወጥ ፍቅር የወደደን እግዚአብሔር ግን ጠፍተን እንድንቀር አልተወንም፡፡ በሰጠን ተስፋ፡በተቆጠረው ሱባኤና በተነገረው ትንቢት መሰረት ዘመኑ ሲደርስ በተዋህዶ ሰው ሆነ፤ የተዋረደ ሥጋችንን አከበረ፡፡ 🌾በከበረ ደሙ ዋጀን፤ከኃጢአታችን አጠበን፡፡ በእርሱ ምክንያት የእግዚአብሔር ልጆች ተባልን ፡፡ጌታችንና መድኃኒታችን ሰው የሆነውና ለመዳናችን የሆነውን ዋጋ ሁሉ የከፈለው ለእኛ ያለውን ፍቅርና ለኃጢአት ያለውን ጥላቻ ለእኛ ለማሳየት ነው፡፡ ‹‹ ነገር ግን የኃጢአትን ሥራ ይሽር ዘንድ ከእርሱ ጋር የተሰቀለውን አሮጌውን ሰውነታችን እንደሆነ ይህን እናውቃለን ›› የተባለውም ለዚህ ነው፡፡ (ሮሜ 6፡6) ➡እኛን ወደ ቀደመ ክብራችን ለመመለስ የተከፈለውም ዋጋ ታላቅ ከሆነው የጋብቻ ምስጢር ጋር በማያያዝ እንዲህ ገልፆታል ‹‹ ክርስቶስ አካሉ ለሆነችው ቤተ ክርሰቲያን ራስዋ አዳኝዋም እንደሆነ ወንድ ለሴት ራስዋ ነውና … ወንዶችም ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያንን እንደወደዳት ራሱንም ስለእርስዋ ቤዛ አድርጎ እንደሰጠላት ሚስቶቻቸውን ይውደዱ፡፡ በውኃ ጥምቀትና በቃሉ ይቀድሳትና ያነጻት ዘንድ የነጻችና የተቀደሰች ትሆን ዘንድ እንጂ በላይዋ እድፈት ወይም ርኩሰት እንዳይገኝባት ቤተ ክስቲያኑን ለእርሱ የከበረች ያደርጋት ዘንድ…›› ኤፌ 5፡23-28 ➡ስለዚህ ጌታችን በደሙ ኃጢአታችንን እንደ ቸርነቱ ይቅር ብሎናል፡፡ኤፌ 1፡7 ከእንግዲህ የራሳችን አይደለንም ፡፡ በሰውነታችንም ኃጢአትና ዐመፃን ልናደርግበት አይገባም ፡፡‹‹በዚህ በሚሞት ሥጋችሁ ኃጢአት አታንግሷት፤ለምኞቱ እሺ አትበሉት፡፡ ከሙታን ተለይቶ እንደተነሳ ራሳችሁን ለእግዚአብሔር መሥዋዕት አድርጉ እንጂ ሰውነታችሁን ለኃጢአት የዐመፅ የጦር መሣሪያ አታድርጉት፤ ሰውነታችሁንም ለእግዚአብሔር የጽድቅ የጦር መሣሪያ አድርጉ››ተብለናል፡፡ (ሮሜ6፡12-13) 🌾የተወደዳችሁ ምዕመናን እግዚአብሔር ደስ ብሎት የሚቀበለውን ህይወት ለመኖር አንፈልጋለን ፡፡ ለመሆኑ ይህ ሊሆን የሚችለው እንዴት ብንመላለስ ነው? መልሱን ሐዋርያው ቅዱስ ያዕቆብ ‹‹አንደበቱን ሳይገታ ልቡን እያሳተ እግዚአብሔርን የሚያመልክ የሚመስለው ማንም ቢኖር የእርሱ አምልኮቱ ከንቱ ነው፡፡ ንጹሕ የሆነ ነውርም የሌለበት አምልኮ በእግዚአብሔር አብ ዘንድ ይህ ነው፤ወላጆች የሌሉአቸውን ልጆች ባልቴቶችንም በችግራቸው መጠየቅ በዓለምም ከሚገኝ ርኩሰት ሰውነትን መጠበቅ ነው፡፡››በማለት ይመልስልናል( ያዕ 1፡26-27)፡፡ 🌾በክርስቶስ ደም የተቀደሰና የእግዚአብሔር ማደሪያ የሆነውን ሰውነታችንን በዓለም ከሚገኝ ርኩሰት መጠበቅ የሰማያዊ ርስት ወራሾች ያደርገናል፡፡ በዓለም የሚገኘውን ርኩሰትም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹የሥጋ ሥራ ›› በማለት ገልጾታል፡፡‹‹እርሱም ዝሙት ፣ርኩሰት፣መዳራት፣ጣዖት ማምለክ፣ሥራይ ማድረግ፣መጣላት፣ ኩራት፣የምንዝር ጌጥ ፣ቅናት፣ቁጣ ፣ጥርጥር፣ፉክክር፣ ምቀኝነት፣ መጋደል፣ ስካር ፣ይህንም የመሰለ ሁሉ ነው፡፡››እነዚህን የሚያደርጉ ሰዎችም ከመንግስተ እግዚአብሔር በአፍአ ወይም በውጭ እንደሚቀሩ ሲያስረዳ‹‹አስቀድሜ እንደነገርኋችሁ ይህን የሚያደርግ የእግዚአብሔርን መንግስት አያይም›› ብሏል ( ገላ5፡19)። ➡በሕይወታችን ሁሉ የምግባርና የሃይማኖት ፍሬ አፍርተን መገኘት ለቅድስና የጠራንን እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት ነው፡፡እነዚህንም ነገሮች ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹የመንፈስ ፍሬዎች ›› ብሏቸዋል፡፡ እነርሱም ‹‹ፍቅር፣ደስታ ፣ሰላም፣ትዕግስት፣ምጽዋት፣ቸርነት ፣እምነት ፣ገርነት ንጽሕና ››ናቸው፡፡ገላ 5፡22 እግዚአብሔር ማደርያው ይሆን ዘንድ የመረጠውን ሰውነታችንን እርሱ የሚከብርበትን ሥራ ልናደርግበት ያስፈልጋል፡፡

photo content

🌾ያን ጊዜ አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስ በመብረቅ ላይ ተጭኖ በረረ እነዚያ አጋንንት ወደአሉበትም ወረደ። ደመናትም ከበቡአቸው መላእክትም በእሳት ሰይፍ መተሩአቸው በመብረቅም አጨዱ አቸው አመድም ሆነው በነፋስ በተኑአቸው። የእነዚያም አጋንንት ቁጥራቸው ሰባት መቶ ሺህ እልፍ ከአንዱ ሺህ ነበር። ከዚህም በኃላ ጌታ ክርስቶስን የካዱ ወዳሉበት ወደ ምእራብ ሀገር ወሰደው። ➡ነገስታቱና መሳፍንቱ መኳንንቱም በሚወጡበትና በሚገቡበት ጉዳና ላይ አቆመው ጌታችንም በዚች ጉዳና ብዙ መከራ ያገኝሀል ግን በርታ ታገስ ብሎት በዚያ ተወው። በዚያን ጊዜም የአርብ ንጉስ ጣዖታቱን አስይዞ መኳንንቱን ሰራዊቱን አስከትሎ በዚያች ጎዳና መጣ አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስን በጎዳና ውስጥ በተገናኙት ጊዜ ጣኦታቱ ወድቀው ተሰባበሩ። 🌾ንጉሱም አባታችንን በአየው ጊዜ አንተ ጠጉር ለባሽ ምንድነህ ሰው ነህን አለው።አባታችንም አዎን ክብር ያለው የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያው የሆንኩ ሰው ነኝ ብሎ ለከሀዲው ንጉስ መለሰለት። ንጉሱም ዳግመኛ አባታችንን በዚያ አይሁድ በሰቀሉት ታምናለህን አለው አባታችንም በሰው ፊት አምንበታለሁ።ስለ እኔ በተሰቀለው አላፍርበትም ስለ እኔ ብቻ የተሰቀለ አይደለም ስለ አንተና ከአንተ ጋራ ስለ አሉትም ነው እንጂ ንጉስ ሆይ የዘላለም ህይወትን ታገኛላችሁ እመኑበት አለው። 🌾ንጉሱም ይህን ነገር በሰማ ጊዜ ተቆጣ ሰራዊቱንም ጠርቶ በፍጥረት እሳትን አንድዱ ለተሰቀለው ለናዝሬቱ ሰው ባሪያው ነኝ የሚለውን ጠጉር ለባሽ ወስዳችሁ ጨምሩት አላቸው።የእሳቱም ነበልባል በረጅም ዛፍ መጠን ከፍ ከፍ እስከሚል አነደዱ። አባታችን ግን ንጉሱና ሰራዊቱ ሁሉ እያዩት አልፎ በፈቃዱ ወደ እሳቱ ገባ። ➡እሳቱም እንደወንዝ ውኃ ሆነ ሰረዊቱም እጅግ አደነቁ እኩሌቶቹም የክብር ባለቤት በሆነ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ። ንጉሱም ሲያደንቁ በአየ ጊዜ ፈፅሞ ተቆጣ ከሰባ ሰባት አርበኞቹ ጋራ በቁጣ ተነስቶ ያደነቁትንና ያመኑትን አንገታቸውን ቆረጠ ። 🌾በዚያችም ቀን የተቆረጡ አርባ መቶ ሺህ ሆነው ተቆጠሩ።ንጉሱም የአባታችንን አንገት ሊቆርጥ ሰይፉን መዞ ተወርውሮ ሄደ። ያን ጊዜም ከመብረቅና ከነጎድጓድ ጋራ ታላቅ ንውፅውፅታ ሆነ ንጉሱንም ከሰራዊቱ ጋራ አጠፋው ከከሀዲው ንጉስ ጋራ የሞቱት ቁጥራቸው አራት ሺህ እልፍ ሆነ። 🌾ጌታችንም አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስን ጠላቶችህንና የኔንም ጠላቶች አጠፋሁልህ አለው።አባተችን ግን በመብረቅ የሞቱትን ሬሳቸውን ነፍሳቸውንም መላእክተ ፅልመት ወደ ስቃይ ሲወስዱአቸው በአየ ጊዜ መድኃኒታችንን እሊህን ስሁታን ማርልኝ ሰው ስሁትና ከዳተኛ ነውና አቤቱ አንተ ግን መሀሪ ይቅር ባይ ታጋሽም ነህ አለው።አባታችንም ይህን ሲናገር ጌታችን ተሰወረ። 🌾አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስም ከዚያ ሄደ ታላቅ ገደልም አገኘ እግሮቹንም በገመድ አስሮ በገደሉ ውስጥ ተዘቅዝቆ ተሰቀለ።ሰይጣንም መጥቶ ያቺን ገመድ ቆረጣት ወደ ታችም ተወርውሮ ወረደ።ቅዱስ ሚካኤልም ቀድሞ አባታችንን ያዘው በእግርህ ላቁምህ ወይም በራስህ አለው በራሴ እቆም ዘንድ ተወኝ አለው ትቶት ሄደ። 🌾በዚያም በራሱ ቁሞ በጥርሶቹም ደንጊያ ነክሶ እስከ ሰላሳ አመት ኖረ አንጀቱና ናላው ሁሉ እየፈሰሰ አልቆ መላ አካሉ እንደእንጨት ቅርፊት ሆነ። ከሰላሳ አመትም በኃላ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አባታችንን ገብረ መንፈስ ቅዱስ እያለ ሶስት ጊዜ ጠራው። እርሱም እነሆኝ ጌታዬ አለ ጌታችንም እነዚያን ከሀዱዎች ምሬልሀለሁ ከዚህ ተነሳ አለው።ያን ጊዜ የነከሰውን ደንጊያ ትቶ ተነሳ።ጥርሱም ተነቅሎ በድንጊያ ተተክሎ ቀረ። 🌾ክንፎችም ተሰጥተውት እየበረረ ከእግዚአብሔር ፊት ደረሰ ጌታውንም ከማርክልኝ ከስጋቸው ጋራ ተነስተው በመጠመቅ ክርስቲያኖች ይሁኑ ብሎ ለመነው። መድኃኒታችንም በሽተኞችን ልትፈውስ ሙታንን ልታስነሳ ስልጣን ሰጥቼሀለሁ አሁንም ወደተገደሉት ሄደህ በመስቀል ምልክት በላያቸው አማትብ ህይወት መድኃኒት በሆነ ስሜም አስነሳቸው አለው።ያን ጊዜም በድኖቻቸው ወዳሉበት ሂዶ አስነሳቸው አጥምቆም ክርስቲያኖች አደረጋቸው ከእርሳቸውም ሄደ። 🌾ከዚህ ዓለም የሚለይበት በቀረበ ጊዜ እነሆ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እነሆ ተገለጠለት። ስሙን ለሚጠራና መታሰቢያውን ለሚያደርግ እስከ አስራ አምስት ትውልድ የምህረት ቃል ኪዳን ሰጠው።የእድሜውም ዘመናት አምስት መቶ ስልሳ ሁለት ሲሆን በሰላም በፍቅር አረፈ። ጌታችንም ነፍሱን ተቀበለ አቅፎም ሳማት በመላእክትና በቅዱሳን ሁሉ ምስጋና አሳረጋት። 🌾ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን አሜን፡፡ (ስንክሳር_ዘወርኀ_መጋቢት_አምስት) Deacon Biruk Bokicha

🌾መጋቢት_5🌾 🌾አቡነ_ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ🌾 🌾መጋቢት አምስት በዚችም ቀን ተአምራቱና ትሩፋቱ እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ የእግዚአብሔር ማደሪያ የሆነ ቅዱስ አባት ተጋዳይ አባ ገብረ መንፈስ ቅዱስ የእረፍቱ ቀን መታሰቢያ ሆነ፡፡ ➡ይህም ቅዱስ አባት በተወለደባት ቀን ድንቅ የሆነ ስራን ሰራ ተነስቶ ከእናቱ እቅፍ ወርዶ ከጨለማ ወደ ብርሀን ላወጣኸኝ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይሁን እያለ ለስላሴ ሰግዷልና ምስጋናም አቅርቧልና። 🌾ህፃኑም ሶስት አመት በሆነው ጊዜ የእግዚአብሔር መልክተኛ ቅዱስ ገብርኤል ወርዶ ህፃኑን ከእናቱ እቅፍ አንስቶ ብዙ ባህታውያን ወዳሉበት ገዳም ወስዶ በደጅ አኖረው ወደ አበምኔቱ ወደ አባ ዘመደ ብርሀንም ገብቶ ስለ ህፃኑ እግዚአብሔር ያዘዘውን ሁሉ ነገረው። ➡በዚያን ጊዜም ነገሩ እውነት እንደሆነ ይረዳ ዘንድ አባ ዘመደ ብርሀን ተነስቶ ወደ ደጅ ወጣ። መልአኩም እንደ ነገረው ህፃኑ ከበር ተቀምጦ ፈገግታን ተሞልቶ አገኘው። እጅግም ደስ ብሎት ለእግዚአብሄር ሰገደ ህፃኑንም አንስቶ ሳመው ታቅፎም ወደ በአቱ አስገባው። 🌾በፍቅር በስነስርአት አሳደገው። የዳዊትን መዝሙርና ቤተ ክርስቲያን የምትቀበላቸውን መፃህፍት ሁሉ ብሉይንና ሀዲስን አስተማረው። ከዚያም በኃላም ክህነት ይሰጠው ዘንድ ስሙ አብርሀም ወደሚባል ጳጳስ ወሰደው ጳጳሱም በአየው ጊዜ ደስ አለው።የዲቁና ማእረግንም ሾመው እንደ ቀዳሜ ሰማእት እስጢፋኖስም ፀጋንና ሞገስን የተመላ ሆነ። 🌾ከጥቂት ቀኖች በኃላም በጌታችን ትእዛዝ ቅስና ተቀበለ። በፆም በፀሎት በስግደት በብዙ ትጋትም እየተጋደለ በበረሀ ውስጥ ብቻውን ኖረ። በበረሀም ብዙ ዘመናትን ሲኖር ነፍሱን "ነፍሴ ሆይ እወቂ በእግዚአብሔር ፊት ራቁትሽን ትቆሚ ዘንድ እንዳለሽ እንግዲህስ ፅኚ በርቺ ታገሺ!" ይለት ነበር። ቆዳው ከዐጥንቱ እስቲጣበቅ ያለ መብልና ያለ መጠጥ በእንዲህ ያለ ግብር በገድል ተጠምዶ ኖረ።ከእፅዋት ፍሬዎች ወይም ከእንጨት ስሮች አልተመገበምና ለስጋውም የሚጠቅም ምንም ምን ምክንያት አልፈለገም። 🌾ለገብረ መንፈስ ቅዱስ እግዚአብሔር እንዲህ አለው ከእንግዲህ በአለም ካሉ ሰዎች ከካህናት ከመነኮሳት ወይም ከምእመናን ህዝባውያን እንዳያውቁህ አደርግልሀለሁ።እንዳንተ ካሉ በቀር አንተ ራስህ ብትፈቅድ እንጂ መላእክትም ይጎበኙሀል። 🌾የብርሀን ሰረገላም ይሁንልህ መድረስ ወደምትሻበት ሁሉ ብረር እኔንም ማየትና በፈለግህ ጊዜ ከአባቴና ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ በሶስትነቴ ታየኛለህ።አሁንም ወደ ኢትዮጵያ ምድር ሂድ በዚያም ከደይን የምታወጥቸው ነፍሳት አሉህ አለው። 🌾ከዚህም በኃላ ስልሳ አንበሶች ስልሳ ነብሮች በፊት በኃላ አጅበውት ወደ ኢትዮጵያ ምድር ተጓዙ። የእግዚአብሔር መልእክተኛ ቅዱስ ገብርኤልም ከአንበሶችና ከነብሮች ጋር በነፋስ ሰረገላ አሳፍሮ ይመራው ነበር። ወደ ምደረ ከብድም አደረሰው ከዚያም ወደ ልዩ ተራራ ወደ ደብረ ዝቋላ ወሰደው። 🌾አባታችንም በባህሩ ቁሞ ምስራቁን ምዕራቡን ሰሜኑን ደቡቡን አራቱን ማእዘን ተመለከተ።የኢትዮጵያ ሰዎች የሚሰሩትን ኃጢአታቸውን በአይኖቹ ፊት የተገለጠ ሆኖ አየ። በራሱም ተዘቅዝቆ ተወርውሮ ወደ ባህሩ ውስጥ ገባ እሊህን የእጅህ ፍጥረቶች የሆኑትን ካልማርካቸው ከእዚህ ባህር እንዳልወጣ በእግሮቼም እንዳልቆም በህያው ስምህ እምላለሁ እያለ ማለ እንዲሁም ሆኖ አርባ ቀን አርባ ሌሊት ኖረ። 🌾ስምህን የጠራውን መታሰቢያህን ያደረገውን እምርልሀለሁ የሚል ቃል በመልአክ አማካይነት ወደ አባታችን መጣ። አባታችንም መልአኩን መላውን የኢትዮጵያን ሰው ካልማረልኝ ከዚህ ባህር አልወጣም አለው መልአኩም ከአጠገቡ ሄደ። 🌾አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስም በዚያ ባህር ውስጥ መቶ ዓመት ኖረ ስጋው ሁሉ አለቀ ደሙም በባህሩ ውስጥ ፈሰሰ አጥንቶቹም እንደበረዶ ነጭ ሆነው ታዩ። አጋንንትም ከአራቱ ማእዘን በየቀኑ ሰባት መቶ ሽህ ሶስት መቶ ሽህ እየሆኑ በመምጣት በቀስታቸው ይነድፉታል እስከ መቶ አመትም አጥንቶቹን በሻፎ ድንጋይ ይፍቁታል ይህን ሁሉ መከራ በትእግስት ሲቀበል ኖረ። 🌾ከዚህም በኃላ ጌታችን ወደርሱ መጥቶ ከባህሩ ዳር ቆመ። አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስንም መላውን የኢትዮጵያ ሰው ምሬልሀለሁና ተነስተህ ውጣ አለው ያንጊዜም ወጣ አጥንቶቹም እንደ ወንፊት ቀዳደሰ የተበሳሱ ሆነው ተገኙ ጌታም ዳሰሰውና ጤነኛ አደረገው ወደ ምድር ከብድም ሰደደው። 🌾ከዚያም ወደ ላይ ወጥቶ ከፀሀ ከሰማይ በታች እስከ ሰባት አመት ኖረ። ዳግመኛም ወደ ምድረ ከብድ ተልኮ እንደ አምድም የተተከለ ሆኖ ሰባተረ አመት ቆሞ ኖረ። ወደ ሰማይም ሲመለከት ቅንድቦቹን አልከደነም ራሱንም ወደ መሬት ዝቅ አላደረገም ነበር እጆቹም ወደ ሰማይ ተዘርግተዋል። እነሆ ሰይጣንም በቁራ ተመስሎ መጣ አይኖቹንም ወደ ሰማይ ያንጋጠጡ ሁለቱን አይኖቹን አንቁሮ አሳወረው። እርሱ ግን ምንም ሳያጓድል እስከ ሁለት ሳምንት ድረስ እንደ ቀድሞው በመትጋት ሲፀልይ ኖረ። 🌾ከዚህም በኃላ ሚካኤልና ገብርኤል መጥተው በፊቱ ቆሙ በሁለቱ አይኖቹ ላይም እፍ አሉበት ብርሀንም ተሰጥቷቸው እንደ ቀድሞው አዩ። ከሰማይ ታላቅ ኃይል ተሰጥቶሀልና ጠላቶችህን ትበቀላቸው ዘንድ ወደ ዝቋላ ሂድ አሉት ከዚያም መላእክት ከአጠገቡ ሄዱ። እርሱም ተነስቶ ወደ ዝቋላ ተጓዘ በጎዳናም ሲጓዝ ሶስት ሽማግሌዎች ከእንጨት ጥላ በታች ተቀምጠው አየ አባታችንም በአያቸው ጊዜ ልሰውራቸው ብሎ በልቡ አሰበ። ➡እንርሱም ፈጥነው በእግዚአብሔር ዙፋን ተማጥነናልና ሶስታችንንም በጀርባህ እያዘልክ አንዳንድ ምእራፍ ሸኘን እንጂ አትተውን ብለው ተጣሩ። በመጣም ጊዜ ሁለመናቸውን ሽበት የከበባቸው የደከሙ ሽማግሎች ሁነው አገኛቸው አንደኛውንም አንስቶ በጀርባው አዘለው ወደ አንድ ምእራፍም አደረሰው ሽማግሌውም ከዚህ አሳርፈኝ አንተ ደክመሀል የማትበላ የማትጠጣ ስለሆንክ አለው አባታችንም ሽማግሌ ሆይ በምን አወቅከኝ አለ። 🌾ሽማግሌውም ሂደህ ባልንጀሮቼን አምጣልኝ አለው ተመልሶ ሁለቱ ወደአሉበትም ደርሶ ሁለተኛውን ሽማግሌ በጀርባው አዝሎ ወደ ቀደመው ሽማግሌ አድርሶ አብሮ አስቀመጠው ሶስተኛም ተመልሶ ሶስተኛውን ሽማግሌ አዝሎ ሁለቱ ወዳሉበት አድርሶ በአንድነት አኖረው፡፡ 🌾አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስም እነዚያን አረጋውያን እናነተ ከወዴትናችሁ መአዛችሁ ልብ ይመስጣል እጅግም ደስ ያሰኛል አላቸው።እነርሱ ግን ተነስተው ቆሙ አንድ ሲሆኑ ሶስት ሶስት ሲሆኑ አንድ መሆናቸውን ገለጡለት የአባቶች አለቃ አብርሀም እንደ አየ። 🌾ያንጊዜም የእግዚአብሔርን የጌትነቱን ክብር አየ የእሊያ አረጋውያንም ፊታቸው ተንቦገቦገ ከፀሀይና ከመብረቅ ብልጭታም ሰባት እጅ በራ አባታችንም በምስጢራት ጎርፍ የተዋጠ ሆኖ ፈራ ተንቀጠቀጠ በምድር ላይም ወደቀ። ህልምን የሚአልምም መሰለው ከዚያም ጌታችን አባታችንን አነቃውና መቶ አመት ያህል ስጋህን ሲነዱፉህ አጥንቶችህን ሲፍቁህ የኖሩ አጋንንትን ታጠፋቸው ዘንድ ወደ ዝቋላ ተራራ ውጣ አለው። 🌾እኔ እንደ ወሰድኩህ ባለማወቃቸው በባህር ውስጥ አለ በማለት በትእቢት ላይ ናቸው ሰባቱ ሊቃነ መላእክትም ይረዱሀል መባርቅትም በፊት በኃላ ሆነው ይከተሉሀል አለው።

photo content

➡ጌታችን ዲያብሎስን በተዋሐደው ሥጋ ሳይሆን በመለኮቱ ኃይል ብቻ ድል እንዳደረገው አስመስለው የሚናገሩ ጌታችን በተዋሐደው ሥጋ ዲያብሎስን ድል ማድረጉን የሚክዱትን መናፍቃን በገሰጸበት ትምህርቱ ቅዱስ ሳዊሮስም የደገኛውን የጎርጎርዮስን ትምህርት ጠቅሶ እንዲህ አለ፡ “ሰይጣን በገዳመ ቆሮንቶስ በተፈታተነው ጊዜ ታገሠ፤ ግን ፈተናውን ሽቶ አይደለም፤ የሚፈታተን የዲያብሎስን ጦሩን ያጠፋ ዘንድ ነው እንጂ፡፡ ➡ዳግመኛ በመለኮቱ ኃይል ዲያብሎስን አልተዋጋውም፤ በሚታመም በሚሞት ሥጋ ድል አደረገው እንጂ፤ ዳግመኛም በዚህ ሥጋ ኃጢአት ወደዚህ ዓለም እንዳይመጣ በኃጢአት ምክንያት በሁሉ ላይ ሞት ተፈርዶአልና፤ በዚህ ሥጋም የኃጢአት ፍዳ ጠፋ፣ ይህ ሥጋም ኃጢአትን ያለማ ዲያብሎስን ድል ነሳው አለ፡፡” (ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ሳዊሮስ ምዕራፍ 85፡16-17) 🌾የመጀመሪያው ፈተና በዚያው በገዳመ ቆሮንቶስ ሲሆን ፈተናውም ስስት ነበር፡፡ ዲያብሎስ ሥጋን የተዋሐደውን አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስን ተርቦ ቢያየው ‹‹የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንክ እነዚህ ድንጋዮች ዳቦ እንዲሆኑ እዘዝ›› በማለት ፈትኖታል፡፡ ሁለተኛው ፈተና ደግሞ በቤተመቅደስ ሲሆን ፈተናውም ትዕቢት ነበር፡፡ ‹‹መላእክት ያነሱኃል ተብሎ ተጽፏልና ራስህን ከመቅደስ ጫፍ ወርውር›› (መዝ 90፡11) ይህ ፈተና ከመጻሕፍት ጥቅስ ጠቅሶ የፈተነበት ነው፡፡ ➡ሦስተኛው ፈተና ደግሞ በተራራ ጫፍ (በሰገነት) ሲሆን ፈተናውም የፍቅረ ንዋይ ነበር፡፡ ‹‹ወድቀህ ብትሰግድልኝ የዓለምን መንግስታት ከብራቸውንም ሁሉ እሰጥሀለሁ›› በማለት ፈትኖታል፡፡ እነዚህ ፈተናዎች ዛሬም በክርስትና ያሉ ዐበይት ፈተናዎች ናቸው፡፡ እኛም ጌታችንን አብነት አድርገን ሰይጣን በትዕቢት ቢፈትነን በትህትና፣ በስስት ቢፈትነን በትዕግስት፣ በፍቅረ ንዋይ (ገንዘብን በመውደድ) ቢፈትነን በጸሊአ ንዋይ (ገንዘብን ባለመውደድ) ልናሸንፈው ይገባል፡፡ 🌾የተፈተኑት እሴቶች ምንድን ናቸው?🌾 🌾ለገዳማውያን አብነት ለመሆን የተፈተነው ፈተና የጽናት ፈተና ነው፡፡ የገዳማውያን ጾራቸው ስስት (መሳሳት) ነውና በመጽናት ላይ ለሚመጣባቸው ፈተና አብነት ሊሆን ተፈተነ፡፡ ገዳማውያን እምነትን፣ እውቀትን፣ ጽናትን እንዲያሟሉ ይጠበቅባቸዋልና፡፡ በቤተመቅደስ ለሚኖሩ ካህናት/በምዕመናን አገልጋዮች በብዛት የሚፈተኑ በትጋታቸው/እውቀታቸው ነው፡፡ እውቀት ያስታብያል ፍቅር ግን ያንጻል እንደተባለ ክርስትናን ተምረናል አውቀናል በማለት መታበይ ስላለ የካህናት ጾራቸው ትዕቢት ነው፡፡ ➡ከዚህም የተነሳ መጽሐፍ ተጠቅሶ ፈተናው ይመጣልና ዲያብሎስም ከመጽሐፍ ጠቅሶ ፈተነው፡፡ በባለስልጣናት ዘንድ የሚፈተነው ደግሞ እምነት ነው፡፡ ጾራቸውም ፍቅረ ንዋይ ነውና፡፡ ወድቃችሁ ብታመልኩኝ በሀብት ላይ ሀብት፣ በስልጣን ላይ ስልጣን እጨምርላችኋላሁ ብሎ ይፈትናል፡፡ የሀሰት አባት ነውና የሌለውን የራሱ አድርጎ ይፈትንበታል፡፡ ስለዚህም ጌታችን ለሦስቱም አብነት ለመሆን ተፈተነ፡፡ 🌾የፈተናዎቹ መፍትሔስ ምን ነበር?🌾 🌾ሁሉን የሚያውቅ ሁሉን የሚችል አምላክ በተለያየ መንገድ የመጡትን ሦስቱን ፈተናዎች እንደየአመጣጣቸው መለሳቸው፡፡ በስስት የመጣውን በትዕግስት ድል ነሳው፡፡ ‹‹ይህንን ድንጋይ ዳቦ አድርግ›› በማለት የመጣውን ፈተና ‹‹ሰው በእንጀራ ብቻ አይኖርም፣ በእግዚአብሔር ቃል እንጂ›› ብሎ መለሰለት (ዘዳ 8፡3)፡፡ ይህም ሰው ለሥጋ በሚመገበው እንጀራ ብቻ ሳይሆን ለነፍስ ምግብ በሚሆነው ቃለ እግዚአብሔርን በመስማትም ጭምር ነው የሚኖረው ማለቱ ነው፡፡ በትዕቢት የመጣውን ፈተና ደግሞ በትህትና ድል ነሳው፡፡ ‹‹መላእክቱ በእጃቸው ያነሱሃል›› ተብሎ ተጽፏልና ራስህን ወርውር ቢለው ‹‹ጌታ አምላክህን አትፈታተነው ተብሎ ተጽፏልና›› (ዘዳ 6፡16) በማለት አሳፈረው፡፡ በዚህም አእምሮአችን ረቂቅ፣ ማዕረጋችን ምጡቅ እያሉ በስጦታ በተሰጣቸው ስልጣን ለሚታበዩ የቤተመቅደስ ሰዎች ትህትናን አስተማረ፡፡ ➡በፍቅረ ንዋይ የመጣውን በጸሊዐ ንዋይ ድል ነሳው፡፡ ‹‹ሂድ አንተ ሰይጣን ለጌታ ለአምላክህ ስገድ እርሱንም ብቻ አምልክ ተብሎ ተጽፏልና›› (ዘዳ 6፡13) በማለት መልሶታል፡፡ ነገስታት/ባለስልጣናት ቤታቸውን በከፍታ/በሰገነት ሠርተው ለሀብትና ለሥልጣን ሲሮጡ በባዕድ አምልኮ ይፈተናሉና ይህንን ድል መንሻ ሠራላቸው፡፡ 🌾ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገዳመ ቆሮንቶስ ከተፈተነባቸው ሦስት ፈተናዎች የምንገነዘበው ፈታኝ የሚፈትነው በደካማ ጎን በመግባት መሆኑን ነው፡፡ የተራበውን በምግብ፣ ያወቀ የሚመስለውን በእውቀቱ፣ ሀብት/ስልጣን የሚወደውን ደግሞ በሀብት/በስልጣን ገብቶ ይፈትነዋል፡፡ በደካማ ጎን ለሚመጡት ፈተናዎች ድል መንሻ የእግዚአብሔር ቃል መሆኑን ጌታችን ዲያብሎስን ካሳፈረባቸው ሦስት መንገዶች እናስተውላለን፡፡ ሦስቱንም ፈተናዎች በመጻሕፍት ያለውን እውነት በመግለጥ ዲያብሎስን አሳፍሮታልና፡፡ ➡ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዲያብሎስን ድል ከነሳው በኋላ ፈታኙ እንደራቀው መላእክቱም መጥተው እንዳገለገሉት ሲናገር ‹‹ያን ጊዜ ዲያብሎስ ተወው፡፡ እነሆ መላእክት ቀርበው ያገለግሉት ነበር›› (ማቴ 4፡11) ብሏል፡፡ እኛም ፈተናን ድል ስንነሳ ዲያብሎስ (ፈታኝ) ይርቃል፤ መላእክት (ተራዳኢዎች) ይቀርቡናል፡፡ ➡በመጨረሻም ጌታችን በዲያብሎስ ከተፈተነበት ፈተና የምንማረው ፈተናን ድል ለመንሳት ጾምና ጸሎት መቅደም እንዳለበት ነው፡፡ የእምነት ጥሩር የእግዚአብሔር ዕቃ ጦር ይህ ነውና፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹የመዳን ራስ ቁር፣ እምነት ጋሻ፣ የመንፈስም ሰይፍ የእግዚአብሔር ቃል ነው›› (ኤፌ 6፡10-18) እንዳለው ከዲያብሎስ የሚመጣውን ፈተና ድል ለመንሳት ጽኑ እምነት፣ ጾም፣ ጸሎት፣ ስግደትና ምጽዋት ያስፈልጋል፡፡ ➡ፈታኝ ዲያብሎስን በገዳመ ቆሮንቶስ ድል ያደረገ፣ ለቅዱሳን ሁሉ ዲያብሎስን የሚያሸንፉበት ኀይል የሰጠ አምላካችን እግዚአብሔር ለእኛም በጾማችን ወራት ከክፋት ሁሉ መራቅን እንዲያስችለን፣ የዲያብሎስንም ፈተና ድል የምናደርግበትን ጥበብ መንፈሳዊ፣ ኀይል መንፈሳዊ ያድለን ዘንድ ቅዱስ ፈቃዱ ይሁንልን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን። (ምንጭ- አስተምሕሮ.com)

🌾ፆመ ኢየሱስ/ዐቢይ ጾም🌾 🌾ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በ30 ዓመቱ በማየ ዮርዳኖስ በዕደ ዮሐንስ ከተጠመቀ በኋላ ሳይውል ሳያድር ወደ ገዳመ ቆሮንቶስ ሄደ፡፡ በዚያም አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾመ፡፡ ይህም ጌታችን የጾመው ጾም ልዩ ልዩ መጠሪያዎች አሉት። እንደ ነቢያት ስርዓት አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ስለጾመ ጾመ አርብዓ (አርባ ጾም) ይባላል። ስሙ መድኀኒት የሆነ ጌታ የነፍስ ቁስል የሆኑ ሦስቱን ዐበይት ኃጢአቶች (ስስት፣ ትዕቢትና ፍቅረ ንዋይ) ድል ያደረገበት በመሆኑ የድል ጾም፣ ጾመ ኢየሱስ በመባል ይታወቃል። ➡የፍጥረት ሁሉ ጌታ፣ ልዑለ ባሕርይ፣ ሰው የሆነ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ የጾመው በመሆኑ ከሌሎች አጽዋማት ተለይቶ ዐቢይ (ታላቅ፣ ዋና) ጾም ይባላል። ለረዥም ጊዜ የሚጾም፣ ብዙ መንፈሳዊ በረከት የሚገኝበት ጾም በመሆኑ ብዙ ምርት ከሚያስገኝ ሰፊ እርሻ ጋር በማመሳሰል ጾመ ሁዳዴ ይባላል። 🌾ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ ስለዚህ የጌታ ጾም ሲጽፍ ‹‹ከዚያ ወዲያ ኢየሱስ ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ወደ ምድረ በዳ ወሰደው፥ አርባ ቀንና አርባ ሌሊትም ከጦመ በኋላ ተራበ›› በማለት ገልጾታል፡፡ ከዚህ በኋላ ነው ፈታኝ ወደ እርሱ የቀረበው፡፡ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያናችን ይህንን የጌታችንን በዲያብሎስ መፈተንን ሊቃውንት አባቶች ያመሰጠሩትን በመተንተን ታስተምራለች፡፡ እኛም በዚህች የአስተምህሮ ጦማር ይህንን የሊቃውንትን ትምህርት መሠረት በማድረግ የጌታችን በዲያብሎስ መፈተንና ድል ማድረጉ ለእኛ ያለውን መንፈሳዊ ትርጉም እንዳስሳለን፡፡ ይህንንም በሰባት ጥያቄዎች ሥር አቅርበነዋል፡፡ 🌾ፈታኙ ማነው?🌾 🌾ጌታችንን ለመፈተን ፈታኝ ሆኖ የቀረበው ጥንተ ጠላት ዲያብሎስ ነው፡፡ ይህ ፈታኝ በመጀመሪያ ራሱ ተፈትኖ የወደቀ ስለሆነ የሰውን ልጅ መፈተን የባሕርዩ ነው፡፡ አዳምን ፈትኖ ያሳተው፣ ኢዮብንና ሌሎችን አባቶች የፈተነው፣ በበርካታ ቅዱሳን ዜና ሕይወት በፈታኝነቱ የተገለጠው፣ ዛሬም መልካም የሚሠሩትን የሚፈትነው፣ ቅድስት ቤተክርስቲያንንም በየዘመናቱ የሚፈታተናት ይህ ፈታኝ ነው፡፡ ➡በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ አገላለፅ በቤተክርስቲያን ላይ ዝናሩን የጨረሰው ነገር ግን ያላጠፋት ዲያብሎስ ነው ክርስቶስን የፈተነው፡፡ ዛሬም በክርስቶስ የምናምን ክርስቲያኖችን በልዩ ልዩ መንገድ ይፈትነናል፡፡ ጌታችን በጾሙ ወራት ዲያብሎስን ድል ማድረጉን ያሳየን እኛም ኃይለ አጋንንትን የምናሸንፍበት ኃይል ጾም፣ ጸሎት እና ስግደት መሆናቸውን ሲያስተምረን ነው፡፡ ፈታኙን ድል ነሥቶ ድል የማድረጊያ ኀይል የሚሆኑንን ጾምን፣ ጸሎትንና ስግደትን ባርኮልናል። 🌾ጌታችን ለምን ተፈተነ?🌾 🌾በገዳመ ቆሮንቶስ የተፈተነው የሰውን ልጅ ለማዳን ሰው ሆኖ የመጣው ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ “አቤቱ ወደ ፈተና አታግባን” ብለን እንድንጸልይ ያስተማረን፣ ወደ ፈተና በገባን ጊዜም በቅዱስ ስሙ፣ በህያው ቃልኪዳኑ ተማምነን “አባታችን ሆይ በሰማያት የምትኖር” ብለን ስንጠራው የሚመልስልን ሰው የሆነ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ለምን ተፈተነ? የጌታችን መፈተን እንደሌሎች ቅዱሳን በፈተና በመጽናት ጸጋን ገንዘብ ለማድረግ አይደለም፤ እርሱ የጸጋ ሁሉ ምንጭ (አስገኝ፣ ሰጭ) ነውና፡፡ ይልቁንስ የሰው ልጅ በዚህ ምድር ላይ በሥጋ ሲኖር ፈተና እንዳለበት ሊያስተምር እርሱ ተፈተነ፡፡ በባሕርዩ መፈተን የሌለበት አምላክ የሰውን ልጅ ፈተና ሰው ሆኖ ተፈተነ፡፡ ➡በዚህም በሕይወታችን መፈተን እንዳለብን አስተማረን፡፡ እርሱ በፈጠረው ፍጡር (በዲያብሎስ) የፈጠረውን ፍጡር (አዳምን) ለማዳን ተፈተነ፡፡ ጌታችን የተፈተነበት ዓላማ የሰው ልጅ የዲያብሎስን ፈተና እንዴት ድል እንደሚያደርግ አብነት፣ አርአያ ሊሆን ነው፡፡ ፈጣሪ በፍጡር ለፍጡራኑ አብነት ሊሆነን በፈቃዱ ተፈተነ፡፡ እርሱ እጸድቅ አይል ጻድቅ፣ እቀደስ አይል ቅዱስ፣ እከብር አይል ክቡር ሲሆን ለሰው ልጅ አርአያ ሊሆን በተለየ አካሉ ባሕርያችንን ባሕርይው አድርጎ በማስመሰል ሳይሆን በእውነት በዲያብሎስ ተፈተነ፡፡ 🌾ጌታችን መቼ ተፈተነ?🌾 🌾በዮርዳኖስ ወንዝ በዮሐንስ እጅ ተጠምቆ፣ በገዳመ ቆሮንቶስ 40 ቀንና 40 ሌሊት ከጾመ በኋላ በተራበበት ወቅት ተፈተነ፡፡ እንዲሁ በሰው ልጅ ላይም ፈተና የሚመጣው አምኖ ተጠምቆ በጎ ምግባራትን መሥራት ሲጀምር ነውና ይህንን ለማጠየቅ በዚህ ወቅት ተፈተነ፡፡ ክርስትና ከፈተና የምናመልጥበት (ሳንፈተን የምናሸንፍበት) መንገድ ሳይሆን በፈተና ውስጥ አልፈን፣ ድል በማድረግ ከሥጋ ሞት በኋላ የዘለዓለም ሕይወትና ክብር የምናገኝበት ፍኖተ ጽድቅ (የእውነት መንገድ) ነው። ክርስቲያኖች ምግባር ትሩፋትን (ጾም፣ ጸሎት፣ ምጽዋት፣ ስግደት) መስራት ሲጀምሩ ነው ፈተና የሚበዛባቸው፡፡ ➡ከቅዱሳን አባቶቻችንና እናቶቻችን ዜና ሕይወት (ገድል) እንደምንማረው ብዙዎቹ ቅዱሳን በገድል በትሩፋት እያደጉ በሄዱ ጊዜ የዲያብሎስ ፈተና ዓይነትና ብዛት ይጨምርባቸዋል። ምንም ዲያብሎስ ፈተናውን ቢያበዛ በገድል በትሩፋት የጸኑት በመስቀሉ ኀይል፣ በእግዚአብሔር ቸርነት ፈታኛቸውን ድል ይነሱታል። መፈተን የማደግ እንጂ የመውደቅ ምልክት አይደለምና። በዚህ ወቅት የሥጋንና የዲያብሎስን ፈተና ለማለፍ ተግተው ልንጸልይ ይገባል፡፡ ወደ ፈተና እንዳትገቡ ተግታችሁ ጸልዩ ተብሎ ተጽፏልና፡፡ 🌾ጌታችን በየት ተፈተነ?🌾 🌾ሦስቱን ፈተናዎች በሦስት ቦታዎች ተፈተነ፡፡ አንዱን በገዳም፣ ሁለተኛውን በቤተመቅደስ፣ ሦስተኛውን ደግሞ በተራራ (በቤተመንግስት) ተፈተነ፡፡ በገዳም ለሚኖሩ ባሕታውያን (መነኮሳት) አብነት ሊሆናቸው በገዳም ተፈተነ፡፡ በቤተመቅደስ ለሚያገለግሉና ለሚገለገሉ ካህናትና ምዕመናን አብነት ሊሆናቸው በቤተመቅደስ ተፈተነ፡፡ በተራራ (በዓለም) ለሚኖሩ አብነት ሊሆናቸው በተራራ ተፈተነ፡፡ ➡በገዳም ሆነው በጾም በጸሎት የጸኑ ባሕታውያን ለመብቃት (ወደ ፍጹም መንፈሳዊነት ለማደግ) ሲተጉ ይፈተናሉና ለእነርሱ አብነት ሊሆን በገዳም ተፈተነ፡፡ በቤተመቅደስ በእምነት ጸንተው የሚኖሩ ካህናትና ምዕመናን ትሩፋትን ለመሥራት ሲተጉ ይፈተናሉና በቤተመቅደስም ተፈተነ፡፡ በቤተመንግስት (በከፍታ) የሚኖሩ ባለስልጣናትና ዓለማውያን ለማመን፣ በጎ ምግባራትን ለመሥራት ሲተጉ በዲያብሎስ ይፈተናሉና በዚያም ተፈተነ፡፡ 🌾ፈተናዎቹስ ምን ነበሩ?🌾 🌾ጌታችን ሦስት ታላላቅ ፈተናዎችን ተፈተነ፡፡ ሦስቱንም እንደየአመጣጣቸው በትዕግስት ድል አደረጋቸው፡፡ የእስክንድሪያው ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ አባታችን ቴዎዶስዮስ ለአንጾኪያው ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ሳዊሮስ በጻፈው ጦማር እንደተናገረው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተዋሐደው ሥጋ ዲያብሎስን ድል ስለነሳው የእኛ ባሕርይም ከእርሱ የተነሳ በዲያብሎስ ላይ መሰልጠን የሚችል ሆነ፡፡ “ጌታ ሰይጣንን ድል ቢነሣው የሚደነቅ ሥራ አይደለም፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቀድሞ ድል ተነሥቶ የነበረ ሥጋን የተዋሐደ ባይሆን በባሕርይ ከእኛ ጋር አንድ በሚሆን ሥጋ እዳ በደል ያልተገኘበት እርሱ በሥጋ መከራን የተቀበለ ባይሆን ኖሮስ መከራ መቀበሉ ባልተደነቀም ነበር፤ ሞትንም በሥጋው ያጠፋው ባይሆን ኖሮ ሞትን የሚያሰለጥን ኃጢአት ባልጠፋም ነበር፤ የሞት ሥልጣንም ባልተሻረም ነበር፡፡” እንዲል (ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ቴዎዶስዮስ 82፡7)

photo content

🍂ጾመ ሰብአ ነነዌ🍂 🍂‹‹ጾመ ሰብአ ነነዌ፤ የነነዌ ሰዎች ጾም›› የሦስት ቀን ጾም የጾሙት በነነዌ ይኖሩ የነበሩ ሰዎች ናቸው፡፡ ከተማዋም (ነነዌ) በጤግሮስ ወንዝ ዳርቻ የምትገኝ ስትኾን መሥራቿም ናምሩድ ነው (ዘፍ.፲፥፲፩-፲፪)፡፡ ጥንታዊቷ የነነዌ ከተማ ለአሦር መነሻ የሆነች፤ እጅግ ሰፊና ያማረች፤ የቅጥሯ ርዝመትም ፲፪ ኪሎ ሜትር የሚሸፈን ነበር፡፡ በከተማዋ ንጉሡ ሰናክሬም ብዙ ሕንጻዎችን ገንብቶ ነበር (ዮናስ ፬፥፲፩)፡፡ ➡በዚያ ዘመን የነበሩ የነነዌ ሰዎች ኃጢአታቸው በዝቶ እግዚአብሔር ሊያጠፋቸው ሲል ዮናስ የስሙ ትርጓሜ ‹ርግብ› የሆነ በዳግማዊ ኢዮርብዓም ዘመነ መንግሥት የነበረ ነቢይን ቸርነትና ምሕረቱ የማያልቅበት እግዚአብሔር መክሮ፣ ዘክሮ እንዲመልሳቸውና ንስሐ እንዲገቡ ነቢዩ ዮናስን ወደ ነነዌ ሕዝብ ላከው (ሉቃ.፲፩፥፴)፡፡ ይህ ነቢይ መኖሪያው በገሊላ በጋትሔፌር ድንበር ከተማ ነበረ፤ አባቱም አማቴ ይባላል፡፡ ➡በዚያን ጊዜ ኢዮርብዓም ሶርያውያንን አባሮ የእስራኤልን ድንበር እንዲመልስ ነቢዩ ዮናስ ትንቢትን ተናገረ (፪ኛነገ.፲፬፥፳፭፤ ዮናስ ፩፥፩)፡፡ ነቢዩ ኤልያስ ያስነሣው የሰራጵታዋ መበለት ሕፃን ነቢዩ ዮናስ እንደ ሆነ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ያስረዳል (፩ኛነገ.፲፯፥፲፱)፡፡ መድኃኒታችን ክርስቶስም የዮናስን ከዓሣ ሆድ መውጣት የራሱ ትንሣኤ ምሳሌ አድርጎ ነግሮናል (ማቴ.፲፪፥፲፱-፵፪፤ ሉቃ.፲፩፥፴-፴፪)፡፡ 🍂እግዚአብሔር አምላክም ‹‹ሔደህ በነነዌ ላይ ስበክ›› ባለው ጊዜ ነቢዩ ዮናስ ‹‹አንተ መሐሪ ነህ፤ ልትጠፉ ነው ብዬ ተናግሬ ብትምራቸው ሐሰተኛ ነቢይ እባላለሁ›› ብሎ ላለመታዘዝ እስራኤልን ለቆ በመርከብ ወደ ተርሴስ ሸሸ፡፡ እግዚአብሔርም ታላቅ ነፋስን አስነሥቶ መርከቧ በማዕበል እንድትመታ አደረገ፡፡ ከዮናስ ጋር በመርከቧ ተሳፍረው የነበሩ ነጋድያንም ያላቸውን ሀብት ወደ ባሕሩ መጣል ሲጀምሩ ነቢዩ ዮናስ ጥፋቱን ተገንዝቦ ‹‹ማዕበሉ በእኔ ምክንያት የመጣ ስለሆነ ንብረታችሁን ሳይሆን እኔን ወደ ባሕር ጣሉኝ›› ብሎ ተማጸናቸው፡፡ ➡እነርሱም ‹‹ስለዚህ ሰው ነፍስ እንዳንጠፋ፣ ንጹሕም ደም በእኛ ላይ እንዳይደረግብን አይሆንም›› አሉ፡፡ ወደ ባሕሩ ለመጣል ዕጣ በተጣጣሉ ጊዜም ዕጣው በዮናስ ላይ ስለ ወጣ ነጋድያኑ ዮናስን ወደ ባሕሩ ጣሉት፡፡ ወዲያውኑ ከእግዚአብሔር ዘንድ የታዘዘ ታላቅ ዓሣ አንበሪ ዮናስን በአፉ ተቀብሎ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት አሳድሮ ወደ ነነዌ አደረሰው፡፡ እግዚአብሔር የቅል ተክልን ምሳሌ በማድረግ ቅጠሉ በመድረቁ ዮናስ ባዘነ ጊዜ ‹‹አንተ ላልደከምክበት እና በአንድ ቀን በቅሎ ላደገ ቅል ስታዝን እነሆ በታላቂቱ ነነዌ ከተማ ያሉ ከአንድ መቶ ሃያ ሺሕ በላይ ሕዝብና እንስሳቱ የእጄ ፍጥረቶች ስለ ሆኑ ያሳዝኑኛል›› በማለት ነቢዩ ዮናስም ውሸታም ላለመባል መኮብለሉ ስሕተት መሆኑን አስረድቶታል፡፡ ➡ዮናስም ነነዌ መሬት ላይ መድረሱን ባወቀ ጊዜ ከእግዚአብሔር መሸሽ አለመቻሉን ተረዳ፤ የነነዌ ሰዎችንም ‹‹ንስሐ ግቡ›› እያለ መስበክ ጀመረ፡፡ የነነዌ ሰዎችም ንስሐ በገቡ ጊዜ እግዚአብሔር ይቅር ብሎ ከጥፋት አድኗቸዋል፡፡ ሐሰት እንዳይባልም እሳቱ እንደ ደመና ሆኖ ከላይ ታይቶአል፡፡ የታላላቁ ዛፍ ቅጠል እስኪጠወልግ ድረስ አድርቆ ለሕዝቡ አሳይቷቸዋል፡፡ ንስሐቸው በከንቱ እንዳልቀረ አስረድቷቸዋል (ትንቢተ ዮናስ)፡፡ ታኅሣሥ ፭ ቀን የሚነበበው የመጽሐፈ ስንክሳር ክፍል ‹‹ወበልዐ አሐደ ኀምለ›› በማለት ንስሐ ያልገቡ አንድ አገር ያህል ሰዎች በእሳቱ እንደ ጠፉ ይነግረናል፡፡ ➡ጾመ ነነዌ የሦስት ቀን ሱባኤ ነው፤ በሦስት ቀናት ጾምና ጸሎት ንስሐ የገቡ የነነዌ ሰዎች ከጥፋት እንደ ዳኑ ሁሉ፣ በብሉይ ኪዳን አስቴር ሦስት ቀን ጾማ፣ ጸልያ በእስራኤል ላይ የመጣውን መቅሠፍት እንዲመለስ አድርጋለች (አስ.፬፥፲፭-፲፮)፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ከበዓል ስትመለስ ሕፃኑ ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ መንገድ ላይ ጠፍቶአት ከሦስት ቀን ፍለጋ በኋላ በቤተ መቅደስ አግኝታዋለች (ሉቃ.፪፥፵፮)፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ለሄሮድስ በሰጠው ምላሽ መልስ ሦስት ቀን የሱባኤ ፍጻሜ መሆኑን ገልጿል (ሉቃ.፲፫፥፴፪)፡፡ ➡ጾመ ነነዌ የእግዚአብሔርን ቸርነትና መሐሪነት የምናስታውስበት ጾም ነው፡፡ ይኸውም እኛ ፍጡራኑ በበደልን ጊዜ ፈጽሞ ከማጥፋት ይልቅ ምክንያት ፈልጎ እንድንድን ያደርገናል፡፡ ዮናስ ለስብከት ፈቃደኛ ባይሆን እንኳን እግዚአብሔር በተለየ ጥበቡ እንዲሔድ አድርጎታል፡፡ በእርግጥ እግዚአብሔር ሌላ የሚልከው ነቢይ አጥቶም አይደለም፤ እርሱንም ጭምር ሊያስተምረው ስለ ፈለገ እንጂ፡፡ የነነዌ ሰዎች የተነሳሕያን ምሳሌ ናቸው፡፡ ይህም ማለት ሰው ጥፋቱን አምኖ ንስሐ ከገባ እግዚአብሔር ይቅር ማለቱን አይተውም፡፡ ለዚህም ነው ዮናስን ‹‹አንተ ላልደከምክበት እና በአንድ ቀን በቅሎ ላደገ ቅል ስታዝን እነሆ በታላቂቱ ነነዌ ከተማ ያሉ ከአንድ መቶ ሃያ ሺሕ በላይ ሕዝብና እንስሳቱ የእጄ ፍጥረቶች ስለ ሆኑ ያሳዝኑኛል›› ያለው፡፡ ➡ቀደምት የቤተ ክርስቲያን አባቶቻችን ይህን እና ሌሎች አጽዋማትን እንድንጾም የወሰኑልን ያለ ምክንያት አይደለም፡፡ ሕጉ የተዘጋጀልን እንደ ነነዌ ሰዎች እኛም ጾመን፣ ጸልየን ከኃጢአታችን እንነጻ ዘንድ ነው፡፡ ዛሬ ዓለማችን በኃጢአት ማዕበል እየተናወጠች ባለችበት ወቅት እኛም እንደ ነነዌ ሰዎች ከበደላችን ብንመለስ እና ንስሐ ብንገባ ቸሩ ፈጣሪያችን እግዚአብሔር ይቅርታና ምሕረት የባሕርይ ገንዘቡ ስለ ሆነ ‹‹ወደ እኔ ተመለሱ፤ እኔም ይቅር እላችኋለሁ፤›› ይለናል፡፡ ➡ስለሆነም በነቢዩ ዮናስ ላይ የተደረጉ ተአምራትንና ካለመታዘዝ የሚመጣ ቅጣት ቀላል አለመሆኑን በማስተዋል፣ ለነነዌ ሰዎች የወረደውን ምሕረት በመገንዘብ ለእግዚአብሔርም ሆነ ለሃይማኖት አባቶች እና ለወላጆቻችን መታዘዝ ይገባናል፡፡ ስንጾምም እግዚአብሔር አምላካችን መዓቱን በምሕረት፣ ቍጣውን በትዕግሥት መልሶ በኃጢአት ለጠፋው ዓለም ይቅርታውን ይልካል፡፡ በመጾማችን ራሳችን ከመዓትና ከመቅሠፍት ከመዳናችን ባሻገር በእኛ በደል ምክንያት አገራችን፣ ዕፀዋቱና እንስሳቱም ሳይቀር ከድርቅና ከቸነፈር ይተርፋሉና፡፡ 🍂ወስብሐት ለእግዚአብሔር

photo content

🌾ኪዳነ ምህረት🌾 🍂ኪዳነምህረት ስንል የምህረት ቃልኪዳን ማለት ነው፡፡በዚህ ውስጥም ምህረት አድራጊው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን ምህረት ተቀባይም መላው የአዳም ዘር ነው፡፡ 🍂እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በምድራዊ ቆይታዋ ዘውትር ወደ ክርስቶስ መካነ መቃብር ጎለጎታ እየወረደች ትፀልይ ነበር፡፡ ልጇ እና ወዳጇ ጌታችን መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያደረገችው ልመናና ፀሎት ተመልክቶና ሰምቶ የምህረት ቃል ኪዳን ገባለት ፡፡ 🍂እንኳን የእናቱን ፀሎት እና ልመና ቀርቶ ዘውትር በሀጥያት የምንዘፈቀውን እኛን ክፉዎቹን የሚሰማ አምላክ ስለ አንቺ ፣ ስለ እናቴ ክብርና ፀጋ ስል ይኸው ቃሌ ብሎ ቃልኪዳን አደረገ፡፡ « ከመረጥሁት ጋር ቃል ኪዳኔን አደረግሁ። … » መዝ, 89 : 3 እንዲል መፅሐፉ፡፡ 🍂ስሟን ለሚጠሩ፣ በእርሷ አማላጅነት ለሚታመኑ በምድር በረከትን በሰማይ የዘለዓለም መንግስትን እንደሚወርሱ የምህረት እና የቸርነት ቃልኪዳን ሰጥቷታል ፡፡ ➡ታላቁ መፅሐፍ እንዲህ ይላል፦ 🍂ቀስቲቱም በደመና ትሆናለች፤ በእኔና በምድር ላይ በሚኖር ሥጋ ባለው በሕያው ነፍስ ሁሉ መካከል ያለውን የዘላለም ቃል ኪዳን ለማሰብ አያታለሁ። " ኦሪት ዘፍ. 9 : 16 🍂በዚህም መሠረት ቃልኪዳኗን ምክንያት በማድረግ ኪዳነ-ምህረት እያልን እንጠራታለን! 🌾እንኳን ለ«ኪዳነምህረት» አደረሳችሁ። የእመቤታችን ምህረት እና ረድዔት፤በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን!🙏 ሼር Share

"በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን 🙏 "የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የአስራት ልጆች በወደደንና በአፈቀረን ፍቅሩን እስከ መስቀል ድረስ በገለጠልን በጌታችን በመዳኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ፍፁም ሰላም እንደምን ቆያችሁ። "ዛሬ የYoutube ቻናል ላስተዋውቃችሁ በዚህም ቻናል መንፈሳዊ መዝሙሮች/ዝማሬዎች/ስብከቶች የሚለቀቁበት የYoutube ቻናል ነው። "ይህም ቻናል ስሙ #DeaconBirukBokicha ተብሎ ተሰይሙዋል Subscribe በማድረግ እንድታበረታቱ በአክብሮት እንጠይቃለን። "ሰላመ እግዚአብሔር አይለየን🙏 https://youtube.com/@dnbirukbokicha?si=vXKnXHeqUjEGmzVU

photo content

🍂ስለ #ኢትዮጵያ ትንሣኤ ስለ ሚመጣው ንጉሥ የተናገረው ሰማዕት ተወለደ 🍂 🌾በዚችም ዕለት የኀርምኖስ ልጅ የሰማዕት ፊቅጦር የልደቱ መታሰቢያ ነው። 🌾በረከቱም ከኛ ጋር ትኑር ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን አሜን። "ሼር በማድረግ ያጋሩ ፔጃችንም ይሰፋ ዘንድ እርዱን።

photo content

🌾አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የካቲት ዐሥር በዚች ቀን ከዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ የዕልፍዮስ ልጅ የከበረ ሐዋርያ ያዕቆብ በሰማዕትነት ሞተ። 🍂ይህም ሐዋርያ በብዙ ሀገሮች ውስጥ ከሰበከ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ ወደ ምኩራብ ገብቶ የክብር ባለቤት የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሃይማኖትን በግልጥ አስተማረ። 🍂አይሁድም ደሙ በእኛ ላይ ይሁን ብለው ከሕዝብ መካከል ነጥቀው ወሰዱት ለሮም ንጉሥ እንደራሴ ለንጉሥ ቀላውዴዎስም አቀረቡትና ይህ ሰው ስለ ቄሣር ሳይሆን ስለ ሌላ ንጉሥ ይሰብካል ብለው ወነጀሉት። 🍂ንጉሡም በሰማ ጊዜ በደንጊያ እንዲወግሩት አዘዘ አይሁድም ፈጥነው ወገሩት ንፍሱንም በጌታችን እጅ ሰጠ ምእመናንም ሥጋውን ገንዘው በክብር ቀበሩት። 🌾ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በሐዋርያ ያዕቆብ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። (Deacon Biruk Bokicha)

"ሆዳችሁ ጠግቦ ከምታቀርቡት አንድ መቶ ጸሎትና ተራራ ከሚያርድ ድምጻችሁ ይልቅ... "በጾም ውስጥ ሆናችሁ የምታቀርቡት አንድ ጸሎት ተሰሚነት አለው። (አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ)