Deacon Biruk Bokicha
رفتن به کانال در Telegram
"ይህ የዲያቆን ቡሩክ ቦክቻ የቴሌ ግራም ፔጅ ነው" በዚህ ፔጅ:- ➡የቅዱሳን ጻድቃን ሰማዕታት ገድላቸውን(ታሪካቸውን)እንለቃለን። ➡የቤተክርስትያን አስተምህሮዎችን እንደ አሰፈላጊነቱ የምንለቅ ይሆናል። የYoutube ቻናላችንን Subscribe እያደረጋችሁ https://youtube.com/@dnbirukbokicha?si=vXKnXHeqUjEGmzVU
نمایش بیشتر1 080
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
در حال بارگیری داده...
کانالهای مشابه
ابر برچسبها
هیچ دادهای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
مه '24
مه '240
در 13 کانالها
آوریل '24
+8
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '24
+11
در 14 کانالها
Get PRO
فوریه '24
+24
در 1 کانالها
Get PRO
ژانویه '24
+49
در 16 کانالها
Get PRO
دسامبر '23
+81
در 18 کانالها
Get PRO
نوامبر '23
+123
در 19 کانالها
Get PRO
اکتبر '23
+30
در 20 کانالها
Get PRO
سپتامبر '23
+70
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '23
+94
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '23
+69
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '23
+25
در 0 کانالها
Get PRO
مه '23
+9
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '23
+7
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '23
+7
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '23
+13
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '23
+6
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '22
+9
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '22
+7
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '22
+5
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '22
+18
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '22
+44
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '22
+111
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '22
+55
در 0 کانالها
Get PRO
مه '22
+96
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '22
+148
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '22
+183
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '22
+160
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '22
+142
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '21
+109
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '21
+149
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '21
+59
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '21
+186
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '21
+84
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '21
+128
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '21
+290
در 0 کانالها
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 01 مه | 0 |
پستهای کانال
| 2 | بدون متن... | 85 |
| 3 | 🌿ሆሳዕና🌿
(ስምንተኛው የዐቢይ ጾም ሳምንት)
🌿ሆሳዕና የሚለው ቃል በዕብራይስጥ ሆሼዕናህÂ የሚል ሲሆን ትርጉሙም እባክህ አሁን አድንÂ ማለት ነው፡፡ ይህ ቃል በዘመነ ብሉይ በቀደምት ነቢያት ዘንድ የተለመደ ቃል ነው፡፡ አቤቱ እባክህ አሁን አድን፣ አቤቱ እባክህ አሁን አቅና፣ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ቡሩከ ነው፡፡Â መዝ.117፡25-26
🌿የሆሳዕና በዓል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ጀርባ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ የሚቀድሙትና የሚከተሉት ሕዝብ በተለይም አእሩግና ሕፃናት ሆሳዕና ለዳዊት ልጅ፣ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፣ ሆሳዕና በአርያምÂ በማለት ጌታችንን በክብር መቀበላቸው የሚታወስበት በዓል ነው፡፡ በዓሉም ሆሳዕና የሚለውን ስያሜ ያገኘው በዕለቱ ከተዘመረው መዝሙር ነው፡፡
➡በሌላ አነጋገር ይህ ዕለት የጸበርት እሑድÂ /Palm Sunday/ ይባላል፡፡ ታሪካዊ አመጣጡ የመልካም ምኞትና የድል አድራጊነት መገለጫ ሆኖ ከደገኛው አባታችን ይስሐቅ ልደት ጋር ተያይዞ የመጣ ነው፡፡ ይኸውም ሣራ የወላድነት ዕድሜዋን ጨርሳ ልማደ እንስት ከተቋረጠባት በኋላ ሁሉን ቻይ የሆነ አምላክ ይስሐቅን በሰጣት ጊዜ ዘመዶችዋ የተሰማቸውን ደስታ ለመግለጽ የዘንባባ ዝንጣፊ በመያዝ የጎበኟትን አምላክ አመስግነዋል፡፡
🌿እስራኤል ከአስከፊው የግብፃውያን አገዛዝ ተላቀው ባሕረ ኤርትራን በደረቅ ሲሻገሩ የተሰማቸውን እጥፍ ድርብ ደስታ በገለጡ ጊዜ፣ እንዲሁም ዮዲት የተባለች ንግሥተ እስራኤል ሆሎፎርኒስ የተባለ አላዊ ንጉሥን ድል ባደረገች ጊዜ ቤተ እስራኤል እንደ ሰንደቅ ዓለማ የዘንባባ ዝንጣፊ በመያዝ አደባባይ ወጥተው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል፡፡
🌿በዘመነ ሐዲስም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰውን ዘር ከዲያብሎስ ቁራኝነት ከሲኦል ባርነት ነጻ ለማውጣት ወደ ዙፋን መስቀሉ /ሉቃ.22፤18/ በተጓዘ ጊዜ ሕፃናት እና አእሩግ ነጻ የሚወጡበት ቀን መድረሱን እነርሱ ሳያውቁ እግዚአብሔር ባወቀ ዘንባባ በመያዝ ዘምረዋል፡፡
🌿እስራኤል ዘንባባ በመያዝ እንዳመሰገኑት እኛም አስራኤል ዘነፍስ ዕለቱን ዘንባባ /ጸበርት/ በግንባራችን በማሰር በዓሉን በየዓመቱ እያስታወስን እናከብራለን፡፡ በዚህ ዕለት ዘንባባ እየተባረከ ለሕዝቡ ይታደላል፡፡
🌿ሕፃናትና አእሩግ ለዳዊት ልጅ መድኃኒት መባል ይገባዋል፡፡Â እያሉ ዘምረዋል፡፡ ይህ ሁሉ በአንድ ወገን የነበረው የአቀባበል ሥነ ሥርዓት ሲሆን በሌላ በኩል የነበረው አቀባበል ደግሞ እጅግ የሚያሳዝን ነበር፡፡ ሥርዓተ ኦሪትን፣ ትንቢተ ነቢያትን በሚገባ እንከተላለን ይሉ የነበሩ ጸሐፍት ፈሪሳውያን መምህር ሆይ ደቀ መዛሙርትህን ገሥጻቸውÂ አሉት፡፡
🌿ጌታችንም መልሶ እነዚህ ዝም ቢሉ ድንጋዮች ይጮኻሉÂ ሲል መልሶላቸዋል፡፡ ቅናት አቅላቸውን ያሳታቸው ፈሪሳውያንም የዋህ የሆነው ሕዝብ ምስጋና ወደ ጥላቻ እንዲለወጥ አድርገዋል፡፡ ከሁሉ የሚያሳዝነው በዕለተ ሆሳዕና እሑድ ዘንባባ ይዘው የዘመሩለትን ጌታ ዓርብ ይሰቀል ዘንድ ይገባልÂ ብለዋል፡፡
🌿መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ጀርባ ላይ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ገባ፡፡ በዚህም በነቢዩ ዘካርያስ እንዲህ ተብሎ የተነገረው ትንቢት ተፈጸመ፡፡እነሆ ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው፤ ትሑትም ሆኖ በአህያም፣ በአህያዪቱ ግልገል በውርንጫዪቱ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል፡፡Â ዘካ.9፡9፤ ማቴ.21፡4፤ ማር.11፡1-10፤ሉቃ.19፡28-40፤ ዮሐ.12፤15፡፡
🌿ጌታችን በአህያ ጀርባ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም መግባቱ የሰላም ንጉሥ መሆኑን ያመለክታል፡፡ እስራኤል ዘመነ ምሕረት ሲሆንላቸው አባቶቻቸው በአህያ ጀርባ ተቀምጠው ይታዩ ነበር፡፡ ጌታም እውነተኛ የኅሊና ሰላም ይዤላችሁ መጣሁ ሲለን በአህያ ጀርባ ወደ ቤተ መቅደስ ሕይወታችን ተጉዟል፡፡
🌿መላእክት በዕለተ ልደቱ በሰማይ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይገባዋል በምድር ሰላም ለሰው ሁሉ ይሁንÂ /ሉቃ.2፡13/ እያሉ የዘመሩለት የሰላም ባለቤት ነው፡፡ በመዋዕለ ትምህርቱም ሰላሜን እሰጣችኋለሁÂ /ዮሐ.14፡27/ ብሎ እንዳስተማረ ያን ሰላም የሚሰጥበትን ዕለት መቅረቡን ለማመልከት ነው፡፡ በሌላ በኩልም በአህያ ጀርባ መቀመጡ ኅቡዕ ምሥጢር አለው፡፡
🌿በአህያ ጀርባ የተቀመጠ ሰው ሌላውን አሳድዶ አይዝም፣ እርሱም ሮጦ አያመልጥም፡፡ በዚህም ጌታችን በእምነት ለሚፈልጉት የሚገኝ ቅርብ ሲሆን በእምነት ለማይፈልጉት ግን የማይገኝ መሆኑን አስተምሯል፡፡ ስለዚህ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች ፀሐይ ዕድሜያችን ሳትጠልቅ በእምነት እንፈልገው፡፡ አሞጽ4፡፡ የአህያን ጀርባ ያልናቀ ጌታችን ትሑት ሰብእና እና የተሰበረ ልቡና ወዳለው ሰው ዘወትር ይጓዛል፣ የተዋረደውንና የተሰበረውን ልብ አይንቅም፡፡ ኢሳ.66፡2፤ መዝ.50፡17፡፡
🌿ለታሰሩት መፈታትን ሊሰብክ ሰው የሆነ ጌታችን ከማሰሪያዋ በተፈታች አህያ እንደተቀመጠ ሁሉ ከኃጢአት እስራት በተፈታ ሕይወት ዛሬም ያድራል፤ የኅሊና ሰላምን ይሰጣል፡፡ ስለዚህ ንስሐ ገብተን ጌታችንን ሆሳዕና በአርያም እያልን ልናመሰግነው ይገባል፡፡
ምንጭ፡ ሐመር ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ፣ መጋቢት/ሚያዝያ 1996 ዓ.ም | 282 |
| 4 | بدون متن... | 173 |
| 5 | 🌾ዐቢይ ጾም ሰባተኛ ሳምንት🌾
(ኒቆዲሞስ የእስራኤል መምህር)
(ዮሐ. ፫፥፭)
🌾ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለኒቆዲሞስ ምሥጢረ ጥምቀትን በገለጸለት ጊዜ ሲደናገር አይቶ «አንተ የእስራኤል መምህር ስትኾን ይህን አታውቅምን?» ብሎታል፡፡ ይህ ጥያቄ የሚጠቁመን ኒቆዲሞስ አለቅነትን ከመምህርነት የያዘ፤ በአይሁዳውያን ዘንድ የታፈረና የተከበረ ሰው እንደ ነበረ ነው።
🌾መምህርቢኾንም ‹‹የሚቀረኝ ያላወቅሁት፣ ያልጠነቀቅሁት ብዙ ነገር አለ›› በማለት የመምህርነቱን ካባ አውልቆ፣ የተማሪነትን ዳባ ለብሶ ከክርስቶስ ሊማር መጣ፡፡ እስኪ ሙሉውን ቃለ ንባብ አብረን እናንብብ :-
"ከፈሪሳውያንም ወገን የአይሁድ አለቃ የሆነ ኒቆዲሞስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፤ እርሱም በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ፦ መምህር ሆይ፥ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ከሆነ በቀር አንተ የምታደርጋቸውን እነዚህን ምልክቶች ሊያደርግ የሚችል የለምና መምህር ሆነህ ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደ መጣህ እናውቃለን አለው። ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው።
🌾ኒቆዲሞስም፦ ሰው ከሸመገለ በኋላ እንዴት ሊወለድ ይችላል? ሁለተኛ ወደ እናቱ ማኅፀን ገብቶ ይወለድ ዘንድ ይችላልን? አለው።ኢየሱስም መለሰ፥ እንዲህ ሲል፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም።
🌾ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው፥ ከመንፈስም የተወለደ መንፈስ ነው።ዳግመኛ ልትወለዱ ያስፈልጋችኋል ስላልሁህ አታድንቅ። ነፋስ ወደሚወደው ይነፍሳል፥ ድምፁንም ትሰማለህ፥ ነገር ግን ከወዴት እንደ መጣ ወዴትም እንዲሄድ አታውቅም፤ ከመንፈስ የተወለደ ሁሉ እንዲሁ ነው። ኒቆዲሞስ መልሶ፦ ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል? አለው።
🌾ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፦ አንተ የእስራኤል መምህር ስትሆን ይህን አታውቅምን? እውነት እውነት እልሃለሁ፥ የምናውቀውን እንናገራለን ያየነውንም እንመሰክራለን፥ ምስክራችንንም አትቀበሉትም።ስለ ምድራዊ ነገር በነገርኋችሁ ጊዜ ካላመናችሁ፥ ስለ ሰማያዊ ነገር ብነግራችሁ እንዴት ታምናላችሁ?"(ዮሐ ፫÷ ፩-፲፪)
🌾ከኒቆድሞስ ሕይወት ብዙ እንማራለን ። አጠር አድርገን ስንመለከት ። የኒቆዲሞስ በሌሊት ገስግሶ መምጣት ለምሥጢረ ጥምቀት ትምህርት መገለጥ ምክንያት ነው ። የአይሁድ መምህር የነበረው ኒቆዲሞስ በሌሊት ገስግሶ ብዙ ምስጢር እንደተገለጠለት ሁሉ ።
🌾ዛሬም በቤተ ክርስቲያን ተገኝተን በቅዳሴው፣ በኪዳኑ፣ በሰዓታቱ፣ በማኅሌቱ ብንሳተፍ ረቂቅ የኾነው ሰማያዊ ምሥጢር ይገለጥልናል፡፡
➡እንደ ኒቆዲሞስ ራሳችንን ዝቅ አድርገን በምሥጢራት በመሳተፍ ለታላቅ ክብር እንበቃ ዘንድ የአምላካችን የልዑል እግዚአብሔር ቅዱስ ፈቃዱ ይኹንልን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር🙏 | 684 |
| 6 | بدون متن... | 215 |
| 7 | 🌾መኑ ውእቱ ገብር ኄር🌾
🌾ታማኝ አገልጋይ ማነው🌾? (ማቴ.24፥45)
🌾በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስያሜ የዐቢይ ጾም ስድስተኛው እሑድ ወይም ሳምንት ገብር ኄር ይባላል፡፡ ሰያሜውን የሰጠውም ኢትዮጵያዊ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ነው፡፡ ጾመ ድጓ በተባለው ከአምስቱ መጻሕፍቶቹ አንዱ በሆነው ጾመ ድጓ መጽሐፍ ሳምንቱን የዐቢይ ጾም ሳምንታት ስያሜዎች ከነሥርዓተ ማኅሌቱ አዘጋጅቷል፡፡ ስለዚህ በስድስተኛው የዐቢይ ጾም ሳምንት ከዋዜማው ቅዳሜ ጀምሮ በቤተ ክርስቲያን፡- የሚዘመረው ዝማሬ፣ የሚሰበከው ስብከት፣ የሚሰጠው ትምህርት ገብርኄርን የሚያወሳ ነው ማለት ስለ ታማኝ አገልጋይ ነው፡፡
➡በማቴ.25፥14-25 የተገለጸውና በዕለቱ የሚነበበው ወንጌልም የሚነግረን ይህን ነው፡፡
“አንድ ባዕለ ጸጋ ሰው ባሪያዎችን ጠርቶ ለአንዱ አምስት መክሊት ሰጠው፣ ሁለት መክሊት የሰጠውም አለ፣ አንድ መክሊትም የሰጠው አለ፡፡ ከዚህ በኋላ ወደሩቅ አገር ሄደ፡፡
#አምስት_መክሊት የተቀበለውም ወጥቶ ወርዶ ሌላ አምስት አትርፎ አስር አደረገ፡፡
#ሁለት_መክሊት የተቀበለውም አትርፎ አራት አደረገ፡፡ አንድ የተቀበለው ግን ሄዶ መሬቱን ቆፍሮ በሻሽ ጠቅልሎ የጌታውን መክሊት ቀበራት፡፡
➡ከብዙ ጊዜ በኋላ ጌታቸው መጥቶ ተቆጣጠራቸው፡፡ አምስት መክሊት የተቀበለው ቀርቦ ጌታዬ አምስት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር እነሆ አምስት አተረፍኩ አለው፡፡ “ገብርኄር ወምዕመን ዘበሁድ ምዕምነ ኮንከ ዲበ ብዙህ እሰይመከ ባዕ ውስተ ፍስሐሁ ለእግዚእከ” “አንተ ታማኝ ባሪያ በጥቂቱ ታምነሃል በብዙ እሾምሃለሁ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ” አለው፡፡
➡ሁለት የተቀበለውም ቀርቦ ጌታዬ ሁለት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር እነሆ ወጥቼ ወርጄ ሌላ ሁለት አትርፌ አራት አድርጌአለሁ፡፡ “አንተ ታማኝ በጎ አገልጋይ በጥቂቱ ታምነሃል በብዙ እሾምሃለሁ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ” አለው፡፡
#አንድ_መክሊት የተቀበለው ግን ቀርቦ “ጌታዬ አንተ ክፉና ጨካኝ ካልዘራህበት የምታጭድ ካልበተንህበት የምትሰበስብ እንደሆንክ ስለአወቅሁ መሬቱን ቆፍሬ ቀበርኋት እነኋት መክሊትህ” አለው፡፡ “አንተ ሰነፍ ባሪያ መክሊቴን በጊዜ ልትሰጠኝ በተገባህ ነበር እኔም ወጥቶ ወርዶ ለሚያተርፍ በሰጠሁት ነበር”፡፡
➡ንዑ የዚህን ሀኬተኛ መክሊት ውሰዱና አስር መክሊት ላለው ስጡት፡፡ ላለው ይሰጡታል ይጨመርለታል ለሌለው ግን ያለውን ይቀሙታል፡፡ ንዑ ይህን ሰነፍና ሃኬተኛ ባሪያ እጅ እግሩን አሥራችሁ ጽኑዕ ጨለማ ወደአለበት ውሰዱት ጩኸትና ጥርስ ማፋጨት ወዳለበት ጨምሩት” አለ ማቴ.25፥14-25፡፡
🌾ባዕለ ጸጋ የተባለው ጌታ ነው፡፡ መክሊት የተባለው ልዩ ልዩ የአገልግሎት ጸጋ ነው፡፡ ያተረፉት በሚገባ በታማኝነት ያገለገሉ ቅዱሳን ሰዎች ናቸው መክሊቱን የቀበረው ደግሞ በታማኝነት በተሰጠው ጸጋ ማገልገል ሲገባው ያላገለገለ ነው፡፡ ጌታቸው ሊቆጣጠራቸው መጣ ማለት በዕለተ ምጽአት ለሁሉም በአገለገለው አገልግሎት ዋጋ ለመስጠት እንደሚመጣ ያሳየናል፡፡
🌾ያገለገሉትን ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አላቸው ማለት ታማኝ አገልጋዮች መንግሥተ ሰማያትን ይወርሳሉና፡፡ ሰነፎች ደግሞ ጥርስ ማፋጨት ስቃይ ጽኑዕ ጨለማ ባለበት ሲዖል መግባታቸውን የሚያሳይ ነው፡፡
🌾ከላይ ያነሳነው የቅዱስ ወንጌል ቃል፡- “ታማኝ አገልጋይ ማነው”? ይህ እያንዳንዱ በአርዓያ እግዚአብሔር የተፈጠረ የሰው ልጅ ጥያቄ ነው የዚህን አምላካዊ ጥያቄ መልስ መስጠት ከሰው ልጆች ይጠበቃል፡፡
➡መልካም አገልግሎት አገልግለን መንግሥቱን እንድንወርስ “ገብርኄር” እንድንባል አምላካችን ይርዳን፡፡
🌾ወስብሐት ለእግዚአብሔር | 1 525 |
| 8 | بدون متن... | 255 |
| 9 | 🌾አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም🌾
🌾መጋቢት ሠላሳ በዚች ቀን ከእግዚአብሔር ዘንድ ስለተሰጠው ስለ ክብሩ ልዕልና ለከበረ መልአክ ለገብርኤል የወልደ እግዚአብሔርን ሰው የመሆኑን ዜና ለምትወልደው ለድንግል ማርያም እንዲአበስራት የተገባው ስለሆነ በዓሉን ልናከብር ይገባል።
🌾ስለዚህ በዚች በከበረች ታላቅ ፀጋ በዚህ መልአክ እጅ እግዚአብሔር ይቅር ብሎናልና ፈፅሞ ልናከብረው ይገባናል፤ እርሱም ደግሞ ስለ ክርስቶስ መምጣትና ለዓለም ድኅነት መገደሉን ለኢየሩሳሌምም መዳኛዋ መሆኑን ስለ ወገኖቹ ከምርኮ መመለስ ሲጸልይ ለዳንኤል የነገረው ሱባዔዎችንም የወሰነለትና በሱባዔዎቹም መጨረሻ ንጹሀን የሚነጹበት የክብር ባለቤት ክርስቶስ ይመጣል ይገድሉታልም ለኢየሩሳሌምም መደኛዋ ይሆናታል ያለው ይህ መልአክ ነው።
➡ከዚያ በኋላም ለእስራኤል ልጆች የሚደረጉ መስዋእቶችና ቁርባኖች ይሻራሉ፤ የክብር ባለቤት ጌታችን ስለ ዓለሙ ሁሉ ድኅነት ለእመቤታችን ማርያም ከእርስዋ መወለዱን ይነግራት ዘንድ የተገባው አድርጎታልና ስለዚህ ሁልጊዜ የበዓሉን መታሰቢያ ልናደርግ ይገባናል፤ ጌታ ከጠላታችን ሰይጣን እጅ ያድነን ዘንድ ስለ እኛ እንዲማልድ በበጎ ስራ ሁሉ እንዲረዳን እንለምነው ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን። | 1 302 |
| 10 | بدون متن... | 255 |
| 11 | 🌾ጥንተ ስቅለት🌾
🌾ለዓለም ሁሉ ድኅነት መድኃኒዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ መጋቢት በ፳፯ኛው ቀን በመስቀል ላይ ተሰቀለ፡፡ በክርስቶስ ክርስቲያን የተባልን ልጆቹም ይህን እናዘክር ዘንድ ዓይን ልቡናችንን ወደ ቀራንዮ እናንሣ!
🌾በዮሐንስ ወንጌል ላይ እንደተጻፈው አይሁድ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ሊይዙት ወደ ጌቴሴማኒ በመጡ ጊዜ ‹‹ማንን ትፈለጋላችሁ?›› ቢላቸው ‹‹የናዝሬቱን ኢየሱስን እንፈልጋለን›› ሲሉት ‹‹እኔ ነኝ›› ቢላቸው ከአንደበቱ የወጣውን መለኮታዊ ቃል ብቻ መቋቋም አቅቷቸው መሬት ላይ ወድቀው ተዘርረዋል፡፡ (ዮሐ.፲፰፥፩) የጌታችን ሞቱ በፍጹም ፈቃዱ እንደሆነም በዚህ እንረዳለን::
➡ስለዚህም የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም ትዕግሥት አንክሮ ይገባል! ዓለምን በመዳፉ የያዘ አምላክ በአይሁድ እጅ እንደሌባ ተያዘ፤ ሠራዊተ መላእክት ለምሥጋና በፊቱ የሚቆሙለት መድኃኔዓለም እርሱ ሊፈረድበት በፍርድ ዐደባባይ ቆመ፡፡ በእስራት ያሉትን የሚፈታ እርሱ በብረት ችንካር ተቸነከረ፡፡ ሰማይን በከዋክብት ምድርም በአበባ ያስጌጠ እርሱ ግን የእሾህ አክሊል በራሱ ላይ ደፋ፡፡ ዓለሙን ሁሉ በቸርነቱ የሚመግብ እርሱ ‹‹ተጠማሁ›› አለ፡፡
➡አይሁድ በምቀኝነት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ለመስቀል ከያዙት በኋላ እሾህ ያለው አክሊል ሠርተው ከፍላት አግብተው በጉጠት አንስተው ‹ኢየሱስ ናዝራዊ ንጉሥ ነህ ዘውድ ይገባሃል› ብለው በራሱ ላይ ደፉበት፡፡ እራሳቸው እንደ መሮ፣ ወርዳቸው እንደ ሞረድ ዐራት ማዕዘን አሠርተው ቁመታቸውን ክንድ ከስንዝር፣ ስለታቸውን እንደ ወስፌ አድርገው ችንካር ሠርተው በስቁረት አግብተው በጌታችን በራሱ ላይ ቢመቱበት ሥጋ ለሥጋ ገብቶ መሐል ልቡን ወጋው፡፡
🌾አክሊለ ሦኩን በራሱ ላይ አድርገው ሲያበቁ ከቤት ወደ ዐደባባይ እያመላለሱ ‹‹ንጉሥ ሆይ!…›› እያሉ ምራቃቸውን እየተፉበት ተዘባበቱበት፡፡ መስቀል አሸክመው ከሊቶስጥራ እስከ ቀራኒዮ ድረስ እያዳፉ ሲወስዱት በምድር ላይ ጣሉት፡፡ ከኋላ ያሉት ‹‹ፍጠን›› እያሉ ገፍትረው ይጥሉታል፤ ከፊት ያሉት ደግሞ ‹‹ምን ያስቸኩልሃል?›› እያሉ መልሰው ገፍትረው ይጥሉታል፡፡
➡ከዚህ በኋላ ክፉዎች አይሁድ ቁመታቸውን ክንድ ከስንዝር ስለታቸው ደግሞ እንደ ወስፌ የሆኑ አምስት ችንካሮችን ሠርተው ሳዶር በሚባለው ችንካር ቀኝ እጁን፣ በአላዶር ግራ እጁን፣ በዳናት ሁለት እግሮቹን፣ በአዴራ መሐል ልቡንና በሮዳስ ደረቱን ቸንክረው የአዳም ራስ ቅል ባለበት ቀራኒዮ ዐደባባይ ላይ ሰቅለውታል፡፡
🌾የኋሊትም አስረው አፍንጫውን ደጋግመው ቢመቱት ደሙ በመሬት ላይ እንደ ውኃ ፈሰሰ፡፡ ከጌቴሴማኒ እስከ ሐና ቤት ድረስ አስረው የፊተኞቹ ሲጎትቱት የኋለኞቹ እየለቀቁት የኋለኞቹም በተራቸው ሲጎትቱት የፊተኞቹ ይለቁታል፤ እንዲህ እያደረጉ ከመሬት ጋር እያጋጩ አሠቃዩት፡፡ ሳውል በእግሩ ሲረግጠው ጌታችን ‹‹መመለስህ ላይቀር ለምን ትረግጠኛለህ?›› ቢለው ስለዚህ ንግግርህ ብሎ ሳውል አስገረፈው፡፡ በሁለት ግንዶች መካከል አድርገው ከግንዱ ጋር አጋጩት፡፡ በእጃቸው ሲመቱት እጃቸውን ስላመማቸው ድንጋይ ጨብጠው ፊቱን ጸፉት፡፡
➡በሽመል ደብድበውታል፡፡ በጲላጦስ ዐደባባይም የጌታችንን ፂሙን ነጭተውታል፡፡ ጲላጦስ እንደ ሕጋቸው ገርፈው እንዲለቁት ቢያዝም ክፉዎች አይሁድ ግን ጌታችንን ሲገርፉት ‹‹አሠቃቂ ግርፋቱን ዓይተን ልባችን እንዳይራራ›› ብለው ሰንጠረዥ ገበጣ ሠርተው ሲጫወቱ አንዱ ተነሥቶ ይገርፍና ሲደክመው ‹‹ቆጠራችሁን?›› ብሎ ይጠይቃል፡፡ ‹‹አልቆጠርንም›› ሲሉት ከድካሙ የተነሣ ‹‹እኔው ልግረፍ እንደገና እኔው ልቁጠር›› ብሎ ትቶት ሲቀመጥ ሌላኛው ይነሣና እንደዛኛው ሁሉ በተራው ይገርፈዋል፡፡
➡ሁሉም እንዲህ እያደረጉ ጌታችንን ሥጋው አልቆ አጥንቱ እንደበረዶ ነጭ ሆኖ እስኪታይ ድረስ ፮፲፻፮፻፷፮ (ስድስት ሺህ ስድስት መቶ ስድሳ ስድስት) ጊዜ ጽኑ ግርፋትን ገረፉት፡፡ በእነዚህ ሁሉ ግርፋቱ ወቅት ሥጋው ተቆርሶ መሬት ላይ ወድቋል፡፡
🌾የዓለም መድኃኒት የማዳኑ ምሥጢር ምንኛ ድንቅ ነው!!! ለዚህ ባሕርይው አንክሮ ይገባል!!!
🌾አምላካችን እግዚአብሔር በአንድ ልጁ በጌታችን በመድኃታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መከራ መስቀል፣ ሞትና ትንሣኤ ከሞተ ነፍስ ይታደገን ዘንድ ፍቃዱ ይሁንልን፤ አሜን!!! | 1 144 |
| 12 | بدون متن... | 277 |
| 13 | 🌾መፃጉዕ🌾
(የዓብይ ፆም ፬ኛ ሳምንት)
🌾“መጻጉ” ማለት በሽተኛ ማለት ነው፡፡ አምላካችን በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ በዚህች ምድር ሲመላለስ ከደዌ ዳኛ ከአልጋ ቁራኛ የገላገላቸው መኾኑን የሚያሰረዱ የምስክርነት ቃሎች የሚሰሙበትን ጊዜ ቅዱስ ያሬድ “መጻጉ” በማለት ጠርቶታል፡፡
(ዮሐ_5፣5_9)
"በዚያም ከሠላሳ ስምንት ዓመት ጀምሮ የታመመ አንድ ሰው ነበረ ኢየሱስ ይህን ሰው ተኝቶ ባየ ጊዜ፥እስከ አሁን ብዙ ዘመን እንዲሁ እንደ ነበረ ዐውቆ፦ልትድን ትወዳለህን አለው።
"ድውዩም፦ጌታ ሆይ፥ውሃው በተናወጠ ጊዜ
በመጠመቂያዪቱ ውስጥ የሚያኖረኝ ሰው የለኝም፥ነገር ግን፥እኔ ስመጣ ሳለኹ ሌላው ቀድሞኝ ይወርዳል ብሎ መለሰለት።
"ኢየሱስ፦ተነሣና ዐልጋህን ተሸክመህ ሒድ አለው።
ወዲያውም ሰውዬው ዳነ ዐልጋውንም ተሸክሞ ሔደ። | 792 |
| 14 | https://youtu.be/y2_9e6hKdF4?si=sGHgElbmm84EcocM | 246 |
| 15 | بدون متن... | 279 |
| 16 | #ምኩራብ
(የአብይ ፆም 3ኛው ሳምንት)
🌾ምኩራብ ማለት ለአምልኮትና ለትምህርት ለህብረተሰቡ አገልግሎት የሚሰጥ የአይሁድ ቤተ ጸሎት ነው። ጌታ በመዋዕለ ስብከቱ በእስራኤል ሀገር ብዙ ምኩራቦች ስለነበሩ እየገባ ወንጌልን አስተምሮባቸዋል። በዚህም “ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ ወመሀረ ቃለ ሃይማኖት” እንዲል ቅዱስ ያሬድ ኢየሱስ ወደ አይሁድ ምኩራብ ገብቶ የሃይማኖት ቃልን አስተማረ። ከሚለው የቅዱስ ያሬድ ዜማ ሥያሜውን አግኝቷል።
🌾በምኩራብ ጸሎትና ትምህርት ይፈጸምበታል። መሥዋዕት ግን አይከናወንም። መሥዋዕት ግን በታላቁ ቤተ መቅደስ በኢየሩሳሌም ብቻ ይፈጸም ነበር። በዚህ ሳምንት የሚነገረው ታሪክ ጌታ ቤተ መቅደሱን የገበያ ማዕከል አድርገው ሸቀጥ ዘርግተው በጉን ላሙን ርግቡን እየሸጡ አገኛቸው። በዚህ ተቆጥቶ በጉን ላሙን ርግቡን ከምኩራብ አስወጥቶ ሸቀጣቸውንና መደርደሪያቸውን እንዲሁም ወርቅና ብራቸውን በነፋስ በተነባቸው ይላል።
🌾በዚህ ሁኔታ ከቤተ መቅደስ አስወጥቶ ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች እናንተ ግን የሽፍቶችና የወንበዴዎች ዋሻ አደረጋችኋት በማለት ወቅሷቸዋል። “አሰስሉ ወአውፅኡ ዘንተ እምዝየ ወኢትረስዩ ቤተ አቡየ ቤተ ምሥያጥ” እንዲል ዮሐ. 2፥16፤ ማቴ. 21፥13። ይህን ተአምር በማሳየት ቤተ ጸሎት የተቀደሰ ከገበያ የተለየ መሆኑን አስተምሮበታል።
🌾በሰንበተ ምኩራብ ጌታ ወደ ቤተ መቅደስ ገብቶ ለዋጮችን ማስወጣቱ ወርቅና ብሩን በነፋስ መበተኑ ላሞችን በጎችን በጅራፍ መግረፉ ቤተ መቅደሱን ማንጻቱ ወዘተ ይነገራል።
መልካም ሰንበት ይሁንልን። | 811 |
| 17 | "መጋቢት 10 #መስቀለ_ክርስቶስ
"መርሕ በፍኖት ሞገሶሙ ለጻድቃን ክርስቶስ።
"ዝንቱ መስቀል☦ ለአዳም ዘአግብኦ ውስተ ገነት።
"መሪ ነው ለመንገድ ሞገሳቸው ለጻድቃን ክርስቶስ።
"ይህ መስቀል☦ ነው ለአዳም የመለሰው ወደ ገነት።
"እንኳን አደረሳችሁ። | 251 |
| 18 | بدون متن... | 263 |
| 19 | " #ሰው እየገደሉ ወደሚበሉ #ሰዎች #ክርስቶስን ለመሰበክ የሄደው #ሐዋርያ ዐረፈ።
🌾አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም መጋቢት 8 ሰውን ወደሚበሉ ሰዎች አገር ሄዶ ወንጌልን ይሰብክ ዘንድ ዕጣ የደረሰውና በእዚያም ሰው በላዎቹ ዐይኖቹን አውልቀው አሥረውት ሳለ 30ኛው ቀን ሳይፈጸም ጌታችን በተአምራት ያዳነው አስቀድሞም በከሃዲውና ጌታችንን በሸጠው በይሁዳ ምትክ የተተካው ሐዋርያው ቅዱስ ማትያስ ዕረፍቱ ነው፡፡
🌾ቅዱስ ማትያስ ሐዋርያ፡- ማትያስ ማለት ‹‹ምትክ›› ማለት ነው፡፡ በአስቆሮቱ ይሁዳ ምትክ የተተካው ሐዋርያ ነው፡፡ ሐዋ 1፡15-27፡፡ አስቀድሞ ግን ቁጥሩ ከ72ቱ አርድእት ነበር፡፡ ሰውን ወደሚበሉ ሰዎች አገር ሄዶ ወንጌልን ይሰብክ ዘንድ ዕጣ ደረሰው፡፡ ይህችም ሀገር እስኩቴስ የተባለች ሩሲያ እንደሆነች የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ጸሐፊዎች ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡
➡ማትያስም እነዚህ ሰውን የሚበሉ ሰዎች አገራቸው እንደደረሰ ዐይኑን አውልቀው አሠሩት፡፡ ምግባቸውም የመጻተኛ ሰው ሥጋ ነው፡፡ በልማዳቸው መሠረት መጻተኛን ሰው ገና እንደያዙት ዐይኖቹን ዐውልቀው በእሥር ቤት ያኖሩታል፡፡ እስከ 30 ቀንም ድረስ ሳር እያበሉ ያስቀምጡትና በ30ኛው ቀን አውጥተው አርደው ይበሉታል፡፡
➡ሐዋርያው ማትያስንም ዐይኖቹን አውልቀው አስረውት ሳለ 30ኛው ቀን ሳይፈጸም ጌታችን ሐዋርያው እንድርያስን ወደ እርሱ ላከለት፡፡ ዐይኑንም ፈወሰለት፡፡ እንድርያስም በተዘጋው በር በተአምራት ገብቶ እሥር ቤቱ ውስጥ ያሉ እሥረኞችን በስውር አውጥቶ ከከተማው ውጭ ካስቀመጣቸው በኋላ ሁለቱ ሐዋርያት ግን ተመልሰው ሰውን ለሚበሉት ሰዎች ተገለጡላቸው፡፡ ይዘውም በአንገታቸው ገመድ አግብተው ለ3 ቀን በሀገራቸው ጎዳናዎች ላይ ሁሉ ጎተቱዋቸው፡፡
➡ሁለቱም ሐዋርያት በጸሎታቸው ከእሥር ቤቱ ምሰሶ ሥር ውኃ አፈለቁና ውኃው ሀገራቸውን ሁሉ እስኪያጥለቀልቅና ሰዎቹንም እስከ አንገታቸው ድረስ እስከሚደርስ ሞላ፡፡ ሁሉም በተጨነቁ ጊዜ ሁለቱ ሐዋርያት በፊታቸው ተገለጡና ‹‹በጌታችን እመኑ ትድናላችሁ›› በማለት ወንጌልን ሰብከውላቸው አሳመኗቸው፡፡ ምሥጢራትንም ሁሉ ገለጡላቸው፡፡ ደግሞም የአራዊት ጠባይን ከሰዎቹ ያርቅላቸው ዘንድ ወደ ጌታችን ከጸለዩ በኋላ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠመቋቸው፡፡
➡ያ የአውሬነት ጠባያቸውም ጠፍቶላቸው የዋህ፣ ቅንና ሩኅሩኆቸ ሆኑ፡፡ ሐዋርያትም ሃይማኖትን እያስተማሯቸው 30 ቀን አብረዋቸው ከተቀመጡ በኋላ አገልጋይ ኤጲስ ቆጶሳትን፣ ካህናትንና ዲያቆናትን ሾመውላቸው ሄዱ፡፡
🌾ማትያስም ወደ ደማስቆ ገብቶ ወንጌልን በመስበክ ብዙዎችን አሳመነ፡፡ ያላመኑ ክፉዎች ግን ይዘው በጽኑ ሥቃይ አሠቃዩት፡፡ አስረው በብረት አልጋ ላይ አስተኝተው ከሥሩ 6 ቀን ሙሉ እሳት አንድደው አቃጠሉት፡፡ ሊያዩትም በመጡ ጊዜ እንደፀሐይ እያበራ አገኙት፡፡ እሳቱ ሥጋውንም ሆነ ልብሱን የራሱንም ፀጉር ምንም አልነካውም ነበር፡፡
➡በዚህም እጅግ ተደንቀው ዳግመኛም 24 ቀን እስኪፈጸም ድረስ ከብረት አልጋው ሥር እሳት አነደዱ፡፡ አሁንም ያለምንም ጉዳት ፍጹም ጤነኛ ሆኖ ቢያገኙት እጅግ ተደንቀው ‹‹በማትያስ አምላክ እናምናለን›› ብለው በጌታችን አምነዋል፡፡
➡እርሱም አስተምሮ ካጠመቃቸው በኋላ አገልጋዮችን ሾመላቸው፡፡ ከዚያም ተነሥቶ ስሟ ፊላዎን ወደሚባል ከአይሁድ አገሮች ወደ አንዲቱ ሄዶ በዚያም ካስተማረ በኋላ መጋቢት 8 ቀን በጎ ዕረፍትን ዐረፈ፡፡
ከሥጋውም ብዙ አስደናቂ ተአምራት ተገለጡ፡፡
🌾የሐዋርያው የቅዱስ ማትያስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን! አሜን🙏 | 553 |
| 20 | بدون متن... | 142 |
