cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

URIM🔥

የዚህ ዘመን ቅሬታዎች፣የሀገራችን መድሀኒቶች፣እውነተኛ ክርስቲያኖች፣እግዚአብሄር በሚሰራበት ቀን ገንዘቦቹ ነን። ክርስቲያን ለሆነ ሁሉ የተከፈተ URIM ሁሉን ለወንጌል ብቻ😍 Subscribe Our YouTube Channel 👇👇👇👇👇 https://youtube.com/@URIMAGAPE?si=JnGurbjzh0clS2B_ @Urim7

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
3 246
مشترکین
+2124 ساؚت
+887 عوز
+34830 عوز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

ክፍል ስድስት አንድ ብቻ እውነተኛ ወንጌል አለ!! በሞባይል ምርቶች ውስጥ የትክክለኛውን ብራንድ የሚመስሉ ሀይ ኮፒ ተብለው የሚጠሩ ምርቶች አሉ ፡፡ እነዚህ ምርቶች በመመሳሰል ደረጃ የሚጠጋጉ ቢመስሉም ነገር ግን የዋናውን ብራድ አይነት ሊሆኑ አይችሉም ፡፡ የክርስትና ወንጌል አንድ ነው አይነቱም እጅግ ከሌሎቹ የተለየ ነው ፡፡ ኢየሱስ ሲናገር እንዲህ ብሎ ነበር። ‹‹ሰላምን እተውላችኋለሁ፥ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም። ልባችሁ አይታወክ አይፍራም።›› ዮሃ 14፡27 ሁለት ሰላሞች ቀርበዋል ነገር ግን ተመሳሳይነት በስም ደረጃ ቢኖራቸውም በአይነትና በምንጭ ይለያያሉ ። 🔸አንደኛው አለም የሚሰጠው ሰላም ሲሆን 🔸 ሁለተኛው ደግሞ ኢየሱስ የሚሰጠው ነው ፡፡ 🔸 አንደኛው እውነተኛው ኢየሱስ የሚሰጠው ሲሆን 🔸ሁለተኛው አለም የምትሰጠው ሰላም መሳይ ሰላም ነው ፡፡ መመሳሰል እንጂ አንድ አይነትነት የለበትም ፡፡ በወንጌልም እንዲሁ ነው እውነተኛ አንድ ወንጌል አለ ውሸተኛ ልዩ ወንጌል ደግሞ በገላቲያ እንደተገኘው አለ ፡፡ ( ስለ ወንጌል ምንነት በቀጣይ በሰፊው መጣበታለሁ ) ወንጌል በአጭሩ ስለ ማን እንደሆነ መፅሀፍ እንዲህ ብሎ ይነግረናል ‹‹ይህም ወንጌል በሥጋ ከዳዊት ዘር ስለ ተወለደ እንደ ቅድስና መንፈስ ግን ከሙታን መነሣት የተነሣ በኃይል የእግዚአብሔር ልጅ ሆኖ ስለ ተገለጠ #ስለ_ልጁ ነው፤ እርሱም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።›› እውነተኛው ወንጌል ይሄ ሆኖ ሳለ ሰዎች አማራጭ መንገድ በመፈለግ ሊባዝኑ ይችላሉ ፡፡ እንደ ገላቲያ ሰዎች !! በገላቲያ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተፈጠውን ጉደይ አስመልክቶ ጳውሎስ እንዲህ ይፅፋል ፡፡ ‹‹በክርስቶስ ጸጋ እናንተን ከጠራችሁ ከእርሱ ወደ ልዩ ወንጌል እንዲህ ፈጥናችሁ እንዴት እንዳለፋችሁ እደነቃለሁ፤እርሱ ግን ሌላ ወንጌል አይደለም፤ የሚያናውጡአችሁ የክርስቶስንም ወንጌል ሊያጣምሙ የሚወዱ አንዳንዶች አሉ እንጂ።ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ፥ ከሰበክንላችሁ ወንጌል የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ፥ የተረገመይሁን።አስቀድመን እንዳልን እንዲሁ አሁን ሁለተኛ እላለሁ፥ ከተቀበላችሁት የተለየውን ማንም ቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን።›› #የጳውሎስ_መደነቅ ጳውሎስ የገላቲያ ሰዎችን እንደሚደነቅባቸው ይነግራቸዋል ፡፡ይህ መደነቅ ስለ ሰሩት መልካም ነገር ስላሳዩት ትጋት ሳይሆን ስላቃዊ ወይም አሉታዊ በሆነ መንገድ የተደነቀበትን መናገሩ ነው ፡፡ እንዴት ከክርስቶስ ውጪ ሌላ ፈለጋችሁ ? በክርስቶስ የጠራችሁን ትታችሁ ወደ ሌላ ወንጌል ለመሄድ እንዴት አሰባችሁ? በሚል ነው የሚደነቅባቸው ፡፡ እውነት ነው ከሱ ከእግዚአብሔር ውጪ እንመኝ ብንል እንኳ ምን የሚያስመኝ ነገር አለ ፡፡ እንኳን ወደ ውጭ ወደ ራስ ማይት ራሱ ከባድ ነው ፡፡ ሁሉ ተስፋ የሚያስቆርጥ ጭጋግ ነው ፡፡ ተስፋ የሚያለመልም እውነተኛ እርሱ እግዚአብሄር ነው ፡፡ ይህ አምላክ በክርስቶስ ጠርቶናል ሌላ ምን ያሻናል? ይህ ወንጌል እውነተኛ ወንጌል አንድ ብቻ ነው ፡፡ ተከታይም ቀዳሚም የለውም …… ‹‹በክርስቶስ ጸጋ እናንተን ከጠራችሁ ከእርሱ ወደ ልዩ ወንጌል እንዲህ ፈጥናችሁ እንዴት እንዳለፋችሁ እደነቃለሁ›› ሁለት አይነት ነገሮች በእዚህ ክፍል እናስተውላለን አንዱን እንመልከት 🔸1ኛ በክርስቶስ ፀጋ እናንተን ከጠራችሁ ከእርሱ ( በክርስቶስ ፀጋ የጠራችሁ እርሱን ትታችሁ አ.መ.ት ) አማኞች የተጠሩ ናቸው ፡፡ የተጠሩት በክርስቶስ ፀጋ ነው ፡፡ ሳይጠራ የመጣ አማኝ የለም ፡፡ይህ በተለያዩ የቅዱሳት መፅሐፍት ምስክርነት የፀና እውነት ነው ፡፡ ይህ ጥሪ በተላያየ መንገድ ተገልጧል ፡፡ የዕብራውያን መፅሐፍ ፀሐፊ እንዲህ ይላል ፡፡ ‹‹ስለዚህ፥ ከሰማያዊው ጥሪ ተካፋዮች የሆናችሁ ቅዱሳን ወንድሞች ሆይ፥ የሃይማኖታችንን ሐዋርያና ሊቀ ካህናት ኢየሱስ ክርስቶስን ተመልከቱ፤›› ዕብ 3፡1 ስለዚህ ቅዱሳን አማኞች ሁሉ እንደተጠሩት እንደዚሁ የገላቲያ ሰዎችም ተጠርተዋል ፡፡ምናልባት እዚህ ጋር ማንሳት ያለብን አንድ ነጥብ የዳኑት አማኞች ተጠርተው ሲሆን ያልዳኑት ግን ሳይጠሩ ቀርተው አለመሆኑን ማወቅ ያስፈልጋል ፡፡ የንጉስን ጥሪ ችላ ያሉ አልፈልግም ብለው ከእዚህ ጥሪ ይልቅ የራሰቸው ድግስ ያስቀደሙ በስራቸው የተማመኑ ከእዚህ ጥሪ ይልቅ እንደ ገላቲያ ሰዎች ወደ ጎን የተመለከቱ እነዚህ ከጥሪው ድግስ ያልተቋደሱ ተላሎች ናቸው ፡፡ አብ ሲደግስ ልጁን ቤዛ ሲያደርግ ጳውሎስ እንዲህ ነበር የፃፈው ፡፡ ‹‹አንድ እግዚአብሔር አለና፥ በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም #ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤ #ራሱንም_ለሁሉ_ቤዛ_ሰጠ፥ ይህም በገዛ ዘመኑ ምስክርነቱ ነበረ፤›› 1ኛ ጢሞ 2፡5-6 ታዲያ ይህን የአብ ስጦታ ያልተቀበሉ ሊቀበሉ ካለቸው ቁጣ በላይ ምን የሚያስፈራ ቁጣ አለ? እውነተኛ ወንጌል እርሱ ግን መትረፊያ ነው ፡፡በወንጌል የተሰበከው መዳን ከእግዚአብሄር የሆነ ለሰዎች የመጨራሻ የዘላለም ህይወት መፍትሔ ነው ፡፡ ሁሉ ሐጢያት ስለሰሩ ለእነርሱ የሚሆን መፍትሔ በወንጌል ጥሪ ውስጥ ተቀምጧል ፡፡ የገላታያ ሰዎች ይህንን ጥሪ ሰምተው በክርስቶስ አምነው የሚኖሩ እውነተኛ አማኞች ነበሩ ፡፡ ይህም በፍሬያቸው ተገልጧል ፡፡ ጳውሎስም ይህንን በቀጣይ ምዕራፎች ላይ መስክሮላቸዋል፡፡ ምን ዋጋ አለው የስሕተት አስተማሪዎእ አይናቸውን ከዋና ጉዳያቸው ላይ አንስተው ወደ ልዩ ወንጌል እንዲያተኩሩ አደረጓቸው አንጂ ፡፡ ይህ ትልቅ ህመም ነው ፡፡ በተለይም እንደ ጳውሎስ አይነት ለሆነ እውነተኛ አገልጋል ፡፡ ለዛ ነው ጳውሎስ ምጥ ይዞኛል የሚለው ፡፡ ‹‹ልጆቼ ሆይ፥ ክርስቶስ በእናንተ እስኪሣል ድረስ ዳግመኛ ስለ እናንተ ምጥ ይዞኛል።›› ገላ 4፡19 ከኢየሱስ ውጪ አማራጭ የለንም ብቸኛ ማረፊያ መደላደያ እርሱ ነው ፡፡ እርሱ ቢደገፉት ምቹ ነው ቢጠጉት ያማረ ነው፡፡ ቢሰማሩበት ለምለም ነው ፡፡ ቢኖሩበት እረፍት ነው ፡፡ በክርስቶስ ላይ ተደላድሎ መኖር ይሁንልን አሜን ይቀጥላል ..... ✍️ Girum Difek 🔥@Urim7🔥 🔥@Urim7🔥
نمایش همه...
❤ 3
Photo unavailableShow in Telegram
የክርስትያን መዝሙር ይፈልጋሉ??
نمایش همه...
🥰🥰አዎ🥰🥰
🤮🤮አይ🤮🤮
Photo unavailableShow in Telegram
የማንን መዝሙር ይፈልጋሉ???
نمایش همه...
❤️❤️ዮሐንስ ግርማ💙💙
❤️❤️እንደለ ወ/ግዮርግስ💙💙
❤️❤️ታምራት ሃይሌ💙💙
❤️❤️ደዊት ጌታቸው💙💙
❤️❤️መስከረም ጌቱ💙💙
❤️❤️ተስፋዬ ጋብሶ💙💙
❤️❤️ይትበረክ ተምሩ💙💙
❤️❤️አድሱ ወርቁ💙💙
❤️❤️ደንኤል ዐ/ሚካኤል💙💙
❤️❤️ቤተልሔም ተዘራ💙💙
❤️❤️ሰለሞን(ኦሮምኛ)💙💙
❤️❤️በብ💙💙
❤️❤️ደረጄ ከበደ💙💙
❤️❤️መስፍን ጉቱ💙💙
❤️❤️ሰላም ደስታ💙💙
❤️❤️ሻወዬ ደምጤ💙💙
❤️❤️ሊሊ(ቃልክዳን)💙💙
❤️❤️ይትበረክ አለሙ💙💙
📌📌ሁሉንም📍አንድ📍ላይ📌📌
በ ጥቅት ግዜ ውስጥ በ ሺዎች ማግኛ መንገድ ነው ➺ Above  ➣  1k+ subscribers ➺ Above  ➣  2k+ subscribers ➺ Above  ➣  5k+ subscribers ➺ Above  ➣  10k+ subscribers በላይ subscribers ያላችሁ አነግሩን 👍 ➨ @FreePromoETH 👈 ማሳሰብያ መንፈሳዊ ያልሆነ ቻናል ❌አንቀበልም❌
نمایش همه...
📡የምትወዱትን ከቲቪ ቻናሎች ዉስጥ መርጣችሁ ሙሉውን ፕሮግራም መከታተል ትችላላችሁ የምትወዱትን ቻናል ምረጡ ቀጥሎም የሚመጣላቹ መንፈሳዊ ቻናል ተቀላቀ 📲Wave ለመግባት  👉 @FreePromoETH 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
نمایش همه...
📡 Marcil  ቲቪ 📡
📡 Christ Army  ቲቪ 📡
📡 CJ  ቲቪ 📡
📡 Presence  ቲቪ 📡
📡 Heaven  ቲቪ 📡
📡  JPS  ቲቪ 📡
📡 Christ Mission ቲቪ 📡
📡 Holy  ቲቪ 📡
📡 JW  ቲቪ 📡
📡 Bethel  ቲቪ 📡
📡 Arara ቲቪ 📡
📡 ሌሎችን ለማግኘት 📡
Photo unavailableShow in Telegram
የማንን መዝሙር ይፈልጋሉ???
نمایش همه...
💙💙ዮሐንስ ግርማ❤️❤️
💙💙እንደለ ወ/ግዮርግስ❤️❤️
💙💙ታምራት ሃይሌ❤️❤️
💙💙ደዊት ጌተቸው❤️❤️
💙💙መስከረም ጌቱ❤️❤️
💙💙ታስፋዬ ገብሶ❤️❤️
💙💙ይትበረክ ተምሩ❤️❤️
💙💙አድሱ ወርቁ❤️❤️
💙💙ደንኤል አ/ሚከኤል❤️❤️
💙💙ቤተልሔም ተዘራ❤️❤️
💙💙ሰለሞን(ኦሮምፋ)❤️❤️
💙💙በብ❤️❤️
💙💙ደረጄ ከበደ❤️❤️
💙💙መስፍን ጉቱ❤️❤️
💙💙ሰላም ደስታ❤️❤️
💙💙ሸወዬ ደምጤ❤️❤️
💙💙ሊሊ(ቃል ክደን)❤️❤️
💙💙ይትበረክ አለሙ❤️❤️
📌📌ሁሉንም 📍አንድ📍 ላይ ለመግኛት📌📌
ለምትወዱት ሰው ላኩለት በዚህ ህያው ቃል ባርኩት😍 “ሁሉን የሚችል አምላክም ለብዙ ሕዝብ ጉባኤ እንድትሆን ይባርክህ፥ ያፍራህ፥ ያብዛህ፤” — ዘፍጥረት 28፥3 🔥@Urim7🔥 🔥@Urim7🔥
نمایش همه...
👍 1❤ 1🤩 1
Photo unavailableShow in Telegram
የክርስትያን መዝሙር ይፈልጋሉ??
نمایش همه...
🥰🥰አዎ🥰🥰
🤮🤮አይ🤮🤮
🎤ከወንድ ዘማሪዎች ውስጥ ማንን ታደንቃላቹ ? በመዝሙሮቹ የተባረካቹ እና የምትወዱትን ዘማሪ ምረጡ ቀጥሎም የሚመጣላቹ መንፈሳዊ ቻናል ተቀላቀ 📲Wave ለመግባት 👉 @FreePromoETH 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
نمایش همه...
🥰 ዮሴፍ በቀለ 🥰
🥰 ሸዋዬ ዳምጤ 🥰
🥰 ዳዊት ጌታቸው 🥰
🥰 ተስፋዬ ጋቢሶ 🥰
🥰 ተመስገን ማርቆስ 🥰
🥰 ይድነቃቸው ተካ 🥰
🥰 ታምራት ሀይሌ 🥰
🥰 ዮሐንስ ግርማ 🥰
🥰አሰግድ አበበ 🥰
አገኘው ይደግ 🥰
🥰 መስፍን ጉቱ 🥰
🥰 ተከስተ ገትነት 🥰
🥰 ኤፍሬም አለሙ 🥰
🥰ቴዲ ታደሰ 🥰
🥰 አስፋው መለሰ 🥰
🥰በረከት ተስፋዬ 🥰
🥰 አውታሩ ከበደ  🥰
🔰ሁሉንም በአንድ ለማግኘት 🔰
🔔ይ🀄️ላ🀄️ላሉን🔔
ሕመም ማስታገሻ የሰው ነፍስ ሕመሙን ይታገሣል፤ የተቀጠቀጠን መንፈስ ግን ማን ያጠንክረዋል?” ምሳ 18á14 በማለዳ ከቤት ወጥቼ የመኪናዬን ሞተር እያሞቅሁ ሼር ላለመፍታት የሬዲዮኑን መክፈቻ ተጫንሁ፡፡ የነካሁት የዜና ጣቢያ ነበርና ዜናው በዝርዝር ቀጠለ። ጋዜጠኞቹ የአሜሪካንን የጤና ቢሮ በጭንቀት በነሰገው ርዕሰ ጉዳይ ላይ በስፋት ይወያያሉ። ወሬው የሥርጭቱ ስፋትና የጉዳቱ ጥልቀት እረፍት ስለሚነሳው የአደንዛዥ ዕጽ ጥገኝነት ጉዳይ ነው። ይህ የብዙዎችን ሕይወት እየቀጠፈና የበርካቶችን ኑሮ እያመሰቃቀለ ያለው አደንዛዥ ዕጽ ከኮሎምቢያ ወይም ከሜከሲኮ በስውር የሚገባና በአሜሪካ ጎዳናዎች የሚቸበቸብ ሳይሆን በሕጋዊ መንገድ በየሆሰፒታሉ በተመሠከረላቸው ሐኪሞች ለሕሙማን በመድኃኒት መልክ የሚታዘዝ ነው። ስሙ ኦፒዮይድ ይባላል። የሕመም ማስታግሻ ነው። በተከታታይ ከተወሰደ በማይበጠሰ የሱስ ገመድ ይተበትባል፤ መጠኑ ከፍ ካለ ደግሞ ወላጁ እስከ ወዲያኛው ያሸልባል። በ2015 ብቻ ይህንን እንከብል አብዝተው በመውሰድ 85,495 አሜሪካውያን ለሞት ተዳርገዋል። በቅርቡ "ሕመም ይሰማኛል" ብለው ሆስፒታል ለሄዱ 100 ሚሊዮን አሜሪካውያን ሐኪሞቹ 259 ሚሊዮን እፒዮኢድ እንዳዘዙና የመድኃኒት መደብሮች እንደቸበቸቧቸው መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ ይህ የኪኒን ቁጥር 323,148,587 ለሆነው መላው የአሜሪካ ሕዝብ በነፍስ ወከፍ እንድ እንድ ጠርሙሰ ይደርሳል። “በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ” እንዲሉ ችግሩን ከድጡ ወደ ማጡ የሚወሰደው ጉዳይ የዕጽ ጥገኝነቱን በአፒዮይድ የተለማመዱ ሰዎች መድኃኒቱ ለለሚወደድባቸው ሄሮይን የተባለ በዋጋ አራት እጥፍ የሚያንሰ በእደንዛዥነቱ ግን በብዙ እጥፍ የሚብስ ሕገ-ወጥ አደንዛዥ ዕጽ ፍለጋ በየሥርቻው ለመንከራተት መዳረጋቸው ነው። ይህ እንዴት ሊሆን ቻለ? ከተባለ መልሱ የአሜሪካ ሕዝብ ከጊዜ ወደ ጊዜ ሕመምን የመታገሰ አቅሙ እየመነመነ ሰለመጣና ለትንሽ ለትልቁ ሕመም ማለታገሻ ስለሚፈልግ ነው። የሕመም ስሜት ደረጃ አለው። እንዳንዱ ጥርሰ ነክሶ ማለፍ ግድ ይላል። አሜሪካን የገነቧት አባቶች ይህ ሕመም ማስታገሻ አልነበራቸውም። ሕመምን የመታገለና የማላለፍ እቅማቸው ግን ከፍተኛ ነበር። áŠĽá‹áŠá‰ľ ከክርስትና ሕይወታችን ጋር እ አዛምደን እንየው። ኢየሱስ ክርስቶስ በምድር ኑሮው የሕማም ሰው ነበር። መከራ እንደሚጠብቃቸው አስረግጦ ተናግሯል። ሐዋርያቱም ይህንኑ በኑሯቸው፣ በትምሕርታቸውና በብዕራቸው አጽንተውልናል። ጌታ ሲስቀል በእንዳንድ በጎ አድራጊዎች ከእሞት፣ከወይን ጠጅና ከክርቤ የተዘጋጀ ሕመም ማስታገሻ ቀርቦለት ነበር፤ ነገር ግን ቀመሰው እንጂ ሊጠጣው ፈቃደኛ አልነበረም። ያንን ያደረገው ሾለ ኃጢአታችን የሚቀበለውን መከራ እንደ ክብር ስለቆጠረው ሳይሰማው በማደንዝዣ ተሰውሮ እንዲያልፍ አልፈለገም ። ስቃይ በሥጋ ሕመም ብቻ የሚገለጥ አይደለም፤ ዘርፈ ብዙ ነው። እንዲያውም የነፍስ ሥቃይ ከሥጋው በብዙ እጥፍ ይበረታል። ጌታ ኢየሱስም በመስቀል ላይ ያሳለፈው ስቃይ የሥጋ ብቻ እልነበረም። በገዛ ወዳጆቹ የመሸጥና የመካድ ስቃይ፣በቅርብ ተከታዮቹ የመተውና በጭንቅ ሰዓት ለብቻ የመቅረት ሕመም፣ የመናቅ፣ á‹¨áˆ˜á‰°á‹á‰ľ ዘግናኝ ሰሜት በጸጋ አስተናግዷል። ነገር ግን አላማውን ስለሚያውቅ፤ ለማን እንደ ሆነ ሰለሚረዳ፣ ለጥቂት ጊዜ መሆኑን ስለሚገነዘብና ከስቃዩ ጀርባ ያለውን ደስታ ስለሚያይ ከስቃዩ ለመዳን ጥረት አላደረገም፡፡ በዘመናችን የክርስትና ሕይወት አውድማ ላይ እንደ ጥንቱ ሾለ እውነት፣ ሾለ ጽድቅ፣ ሾለ ወንጌል፣ ሾለ ፍቅር ዋጋ መከፈልና መከራን መቀበል እንደ ጦር እየተፈራ፣ እየተጠላና ኋላ ቀርነት ተደርጎ እየተቆጠረ መጥቷል። ከስቃይና ከመከራ እንዲያድናቸው እንጂ ጌታ፤ ጌታ ሰለሆነ የሚያመልኩት ቁጥር እየመነመነ ነው። እንዲህ አይነቶቹ መከራ የመጣባቸው ቀን ጀርባቸውን ሊሰጡ የተዘጋጁ የጉባኤ አድማቂዎች ናቸው። የደላን ቀን ጣፋጭ ምሥጋና አቅርበን የከፋን ቀን በምሬት እንጉርጉሮ ቅኝት የምንቀይር ቤቱ ይቁጠረን። ታዲያ ለምን ይሆን ሾለ ሌላው ሕመምን መታገሥ የተሳነን? የመንፈሳችን መድክምና መላላት ነው። መንፈሳችን ሲጠነከር የሥጋችንን ሕመም መታገስ አንቸገርም። መንፈሳችን በኃጢአትና በዓለማዊ ምኞት ከተቀጠቀጠ ግን ማስታገሻ ፍለጋ በውጭ ለመንከራተት እንገደዳለን እንጂ ሾለ እውነት መገፋትን፣ መናቅን፣ መተውን፣ በሐሰት መወንጀልን፣ ለብቻ መቅረትን መታገሰ እንችልም። ታዲያ መፍትሄው ምንድነው? መንፈሳችን ጠንካራ እንዲሆን የእግዚአብሔርን ቃል ሳናሰልሰ መመገብ፣ የተመገብነው ከእኛ ጋር ተዋህዶ እንዲጠቅመን በቀንና በሌሊት ማሰላሰል፥ የተረዳነውን እውነት ሼል ላይ ማዋል ነው። ሌላው መንፈስን የሚያጠነከረው ዘወትር ሳይታከቱ በጸሎት መጽናት ነው። ያኔ በጊዜውም አለ ጊዜውም ጸንተን እንቆማሰን። ሕመምን እንታገሳሰን። ጸሎት ጌታ ሆይ- በጸጋህ ከኃጢአትና በኃጢአት ምክንያት ከሚያመጣው ዘላለማዊ ፍርድና ኩነኔ አድነኸኛል። ዘላለማዊ ክብርና ዕረፍት ከፈቱ እንደሚጠብቀኝ አውቃለሁ። ሆኖም በምድር ኑሮዬ ሾለ ወንጌል፣ ሾለ አውኅትና ሾለ ፍቅር በጽናት እንድቆም፣ መከራን አንድካፈል' ስቃይን እንድታግስ ትፈልጋለህ። እባከህ መንፈሴን በጸጋህ አጠንክረህ የውስጥንም ሆነ የውጭ ጊዜያዊ ሥቃይ አስተምረኝ። 🔥@Urim7🔥 🔥@Urim7🔥
نمایش همه...
❤ 2👍 1