fa
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

رفتن به کانال در Telegram

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

نمایش بیشتر
1 810
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
2ኛ ጢሞቴዎስ 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²² ከክፉ የጎልማሳነት ምኞት ግን ሽሽ፥ በንጹሕም ልብ ጌታን ከሚጠሩ ጋር ጽድቅን እምነትን ፍቅርን ሰላምን አጥብቀህ ተከተል። ²³ ነገር ግን ጠብን እንዲያመጣ አውቀህ ከሰነፎችና ካልተማሩ ምርመራ ራቅ፤ ²⁴ የጌታም ባሪያ ለሰው ሁሉ ገር ለማስተማርም የሚበቃ ለትዕግሥትም የሚጸና ሊሆን እንጂ ሊጣላ አይገባውም። ²⁵-²⁶ ደግሞም፦ ምናልባት እግዚአብሔር እውነትን ያውቁ ዘንድ ንስሐን ይሰጣቸዋልና ፈቃዱን ለማድረግ በዲያብሎስ ሕያዋን ሆነው ከተያዙበት ወጥመድ ወጥተው፥ ወደ አእምሮ ይመለሳሉ ብሎ የሚቃወሙትን በየዋህነት ይቅጣ።

የዓለም ምስኪን ሰው። (The most miserable man.) የዓለም ምስኪን ሰው!!!...ከክብራቸው እየሩሳሌምና ከእርስታቸው እስራኤል ተነቅለው ወደ ባብሎን ተማርከው የተወሰዱ እስራኤላውያን፣ ወይም ልጆቿን ላይመለሱ ያጣቻቸው ራሔል፤ ከሰው ሁሉ ተወግዘው በካታኮምብ ዋሻዎች ውስጥ እንደ አይጥ የኖሩ የሰምርኔስ ዘመን ውድ ክርስቲያኖች ወይም በጨካኙ ሂትለር በግፍ የተጨፈጨፉ አይሁዶች እንኳ የዚህን ሰው ያህል ሚስኪን እንዳልሆኑ አምናለሁ! ይህ ሰው ከሰዎች ሁሉ ይልቅ ምስኪን ነዉ! ከሰዎች ሁሉ በላይ ሃዘንተኛ እና ምንም ምቾት የማይሰጠው ሰው ነዉ። ይህ ሰው ማን እንደሆነ ታውቃላችሁ? የማያምን ሰው አይደለም! ክርስቲያን! ምን አይነት ክርስትያን? "ኢየሱስ ክርስቶስን ለዚህኛው ሕይወት ብቻ ተስፋ የሚያደርግ ክርስቲያን!" ኢየሱስ ክርስቶስን ለትዳር፤ ለቤት፤ ለመኪና፤ ለስጋዊ ፈውስ፤ ለበለጠግነት፤ ለትልቅነት፤ ለዝና... ወዘተ...ለዚህኛው ሕይወት #ብቻ ኢየሱስ ክርስቶስን ተስፋ ያደረገ ክርስቲያን ከሰዎች ሁሉ ይልቅ ሞኝ! ሃዘንተኛ እና ምንም ምቾት የማይሰጠው ሰው ነዉ። “በዚች ሕይወት ብቻ ክርስቶስን ተስፋ ያደረግን ከሆነ፥ #ከሰው_ሁሉ_ይልቅ_ምስኪኖች_ነን።” — 1ኛ ቆሮንቶስ 15፥19 ኢየሱስ ክርስቶስን ለዚህ ሕይወት ተስፋ አድርገዋለሁ! ነገር ግን ለዚህ ሕይወት ብቻ አይደለም!!! ከዚህ ሕይወት በለፈ: ለመለኮታዊ ባሕሪይ፤ ለዘላለማዊ ባለጠግነት፤ ለመንፈሳዊ ሃይል፤ በሚመጣው ዓለም ለሚገኝ አክሊልና ስልጣን፤ ለመንፈሳዊ ገዥነት.... ተስፋ አደርገዋለሁ! በጣም የሚደንቀው ይህ በዚህኛውም ሆነ በሚመጣው ዓለም ትርፍ ያለው ነዉ። ዘላለማዊና ዘላቂ ነዉ። Victor 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ልዑል መኖሪያዬ -ዘማሪት ዘርፌ ከበደ።

አይገርምም! ኢየሱስ ክርስቶስ የመረጣቸው ደቀመዛሙርት በኃላ ዓለምን ያወኩ እና የዓለምን ታሪክን የለወጡ ሰዎች የዚህን ዓለም እውቀት የተማሩ አልነበሩም! የስነ መለኮት ምሁራንም አልነበሩም! ባለጠጎችም አልነበሩም! ወይም ጠቢባን እና አስተዋዮችም አልነበሩም! ከንጉሳውያን ቤተሰብም አልነበሩም!...ኢየሱስ የፈለገው ባዶነታቸውን ብቻ ነበር። እነዚህ ማሃይሞች/ያልተማሩ (ሐዋሪያት 4:13) ተብለው የተጠሩ: ኢየሱስ አለማወቃቸውን ፣ባዶነታቸውን ተጠቀመው!!! በመንፈስ ቅዱስ ባዶነታቸውን ሞልቶት ዓለምን አወከባቸው! (ሐዋሪያት 17:6) ኢየሱስ እንድሰራብህ/ሽ ምንም መሆን አይጠበቅብህም/ሽም "ተከተለኝ" የሚለውን ድምፅ "እሽ እከተልሃለሁ!" ማለት ብቻ ነዉ። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

አንብቡና ለምትወዷቸው አጋሩ! የወንድሞች እና የእህቶች ሕይወታቸው ይሰራ.....

#እውነት ነጻ ያወጣል! “ስለዚህ #የክርስቶስን_ነገር_መጀመሪያ_የሚናገረውን_ቃል ትተን ወደ ፍጻሜ እንሂድ፤ መሠረትን ደግመን አንመሥርት፥ እርሱም #ከሞተ_ሥራ_ንስሐና #በእግዚአብሔር_እምነት፥ ስለ #ጥምቀቶችና #እጆችንም_ስለ_መጫን ስለ #ሙታንም_ትንሣኤ ስለ #ዘላለም_ፍርድም ትምህርት ነው።” — ዕብራውያን 6፥1-2 በዚህ የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ ውስጥ ብቻ የተጠቀሱ መሰረታዊ እና የመጀመሪያ ተብለው የተጠሩ የእውነት ትምህርቶች:- 1-ያክርስቶስን ነገር መጀመሪያ የሚናገር ቃል። 2-ከሞተ ስራ ንስሐ የማድረግ አስተምሮ። 3-በእግዚአብሔር ስለ ማመን። 4-የጥምቀቶች አስተምህሮ ። 5-እጆችን የመጫን ትምህርት። 6-የሙታን ትንሳኤ። 7-ስለ ዘላለም ፍርድ የለ አስተምህሮ። እነዚህ የእውነት አስተምህሮዎች በክርስትና እምነት መሰረታዊ እና የመጀመሪያ ትምህርቶች ናቸው። እያንዳንዱ ክርስቲያን እነዚህን ትምህርቶች ማወቅ ብቻ ሰይሆን ለማያምኑ ሰዎች ለማስረዳት እንኳ የበቃ መሆን አለበት: አሁን ያለው ሁኔታ ግን ከዚህ የተለየ ነዉ። ጥያቄ ልጠይቃችሁ: ስንቶቻችን እነዚህን የመጀመሪያና መሰረታዊ አስተምህሮዎች በትክክል ተረድተናል? ስንቶቻችንስ ለማያምኑ ማስረዳት እንችላለን??? ቀጥሎ ያለውን የምለው በፍጹም በትምክህት አይደለም ቤተክርስቲያንን እወዳለሁ! (don't get me wrong) በምንም አይነት የእውነት እውቀት ደረጃ ላይ ያሉ ወንድሞችንና እህቶችን እወዳለሁ! ስለዚህ በንጹሕ ልብ ነዉ የማወራው:- አሁን ባለችው ቤተክርስቲያን ውስጥ እጅግ ብዙዎች እንዴት ጥሩ ትዳር መገንባት እንዳለባቸው ያውቃሉ! እንዴት በእምነት ቃል ከችግር መውጣት እንዳለባቸው ያውቃሉ፤ እንዴት መሪ መሆን እንደሚቻል ያውቃሉ... ወዘተ...እነዚህ ሁሉ ማወቅ በጣም ጥሩ ነዉ! ደግሞም ማወቅ ይኖርብናል: ነገር ግን አብዛኛው የቤተክርስቲያን አባል(member) ስለ ክርስቶስ የሚናገረውን የመጀመሪያ ቃል አያውቅም! አብዛኛው ሰው ከላይ የተጠቀሱትን የመጀመሪያ እውነቶች: ለማያምኑ ማስረዳት አይችልም! ይህ በጣም የሚያሳዝን ነዉ። እኔ ነገሩን እንደዚህ ነዉ የማየው: አሻዋ ላይ ቤት እንደማነጽ! የእግዚአብሔር ልጆች መሰረቱ ላይ አጥልቀን ስር እንስደድ ከዛም በኃላ ማነጽ እንችላለን። ግንበኛ(architect) ባልሆንም አንድ ነገር ማየት እችላለሁ የየትኛውም አይነት ሕንጻ ርዝመት፤ ክብደት፤ ጥራትና ቀጣይነት በመሰረቱ ይወሰናል። መሰረት ከሚፈቅደው በላይ ማነጽ አንችልም። ከደረግንም ለጥፋት ነዉ የሚሆንው: ስለዚህ መሰረቱን እናግኘው: በእርሱም ስር እንስደድ ሌላው ሁሉ ደረጃ በደረጃ የሚሰራ ይሆናል። ፀጋ ይብዛላችሁ። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

በአንዳች አትጨነቁ! Be careful for nothing! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

እግዚአብሔር እንዴት ትልቅና ድንቅ ነዉ???

“ምሥጢሩ ለአምላካችን ለእግዚአብሔር ነው፤ የተገለጠው ግን የዚህን ሕግ ቃሎች ሁሉ እናደርግ ዘንድ ለእኛ ለዘላለምም ለልጆቻችን ነው።” — ዘዳግም 29፥29 ምንም ያሕል መንፈሳዊ ብንሆን እውቀትንም ሁሉ ብናውቅ: ረቂቅ ጥበብንም ብናገኝ: ማስተዋልንም አብዝተን ብናተረፍ አንዳንድ ነገሮች ሚስጢር እንደሆኑ ይቆያሉ: በእምነት ብቻ "አሜን" ብለን የምንቀበላቸው መንፈሳዊ ሚስጥራት አሉ። በተለይ ደግሞ በዚህኛው ዓለም ስንኖር የቱንም ያህል መንፈሳዊ ደረጃችንን ብንጨምር በአእምሮ የማንረዳቸው ነገር ግን ፈጽሞ መካድ የማንችላቸው በእምነት ብቻ ልንቀበላቸው የሚገቡ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሚስጢራት አሉ። ከእነዚህ አንዱ "ምስጥረ-ሥላሴ" ነዉ። ይህ ሚስጢር እግዚአብሔር አንድ ነገር ግን ከአንድ በላይ: ሦስት ማንነቶች መሆኑ ነዉ። ሦስት ማንነቶች(persons) በቅዱሳት መጽሐፍት እንደተገለጠው አባት፣ ልጅ እና ቅዱስ መንፈስ ናቸው። ይሄንን ሚስጢር በሰዎች ቃላት ለመግለጽ እንኳ ያዳግታል። ቅዱሳት መጽሐፍት ግን በምንም አይነት መንገድ ከሌላ ምንጭ ልናገኘው የማንችለውን እውነትና እውቀት ይሰጡናል። በተለይ ደግሞ ስለ እግዚአብሔር ባሕሪይ/Nature/። ሰዎች ይህንን ሚስጢር ለመረዳት እና ለማስረዳት በሚያደርጉት ጥረት ውስጥ አብዛኛውን ጊዜ ስህተት ውስጥ ይወድቃሉ። በጣም የሚገርመው ከነቢያትም ሆነ ከሐዋሪያት ይህንን ሚስጢር ለማስረዳት መልእክት የጻፈ አንድም አለመኖሩ ነዉ: በመንፈስ ቅዱስ እንደተገለጠላቸው ልክ እንደዚያው አምላክ አንድ ነዉ ብለዋል: ደግሞም ሦስት የተለያዩ አካላት (distinct persons) ነገር ግን አሁንም ፈጽሞ አንድ የሆኑ እንደሆኑ ገልጸዋል። ምን እንላለን "አሜን" ነዉ። መጽሐፍ ቅዱስ “እምነትም ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የሚያስረግጥ፥ የማናየውንም ነገር የሚያስረዳ ነው።” — ዕብራውያን 11፥1 ይለናል። ይህ የእምነት ትርጉም ሰይሆን ተግባር/function/ ነዉ። እምነት የመጀመሪያ "ተስፋን ያስረግጣል" ወይም የወደፊቱ ላይ ዛሬ ያስቆማችኋል ማለት ነዉ። ሌላው ደግሞ እምነት "የማናየውን ያስረዳል" ይህ ማለት እንደ ሚስጥረ-ሥላሴ ያሉ መንፈሳዊ ነገሮችን በሥጋም ሆነ በነፍስ አይናችን ልናያቸው የማንችላቸውን መንፈሳዊ እውነቶች ለመንፈሳችን የማስገንዘብ ተግባር ወይም ውጤት አለው ማለት ነዉ። በእምነት ብቻ ነዉ መንፈሳዊ ምስጢራትን መረዳት የምንችለው። #መጽሐፍ_ቅዱስ። #እምነት። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

Bishop David oyodepo... #Love! #ስሙት_እና_ተለማመዱ! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

እግዚአብሔር የሚሰጣችሁ ራዕይ ለማንም ከሚሰጠው ራዕይ የተለየ ስለሆነ ስኬታችሁን ከማንም ስኬት ጋር አታነጻጽሩ! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

The steadfast love......😍😍😍 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

በሕይወታችሁ የመንፈስ ቅዱስ ሪቫይቫል እንድጀምር ስትጸልዩ እግዚአብሔር ውስጣችሁ ለመንፈስ ቅዱስና ለሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ አፒታይት ይፈጥራል። መንፈሳችሁ ውስጥ የተፈጠረውን አፒታይት መጠበቅና ማሳደግ ስትችሉ እና የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ በመንፈስ ቅዱስ ስገለጥላችሁ ሪቫይቫል በሕይወታችሁ ይጀምራል። ሪቫይቫል በሕይወታችሁ ስጀምር ሁሉም ሰው የሐዋሪያት ሥራ መጽሐፍን ከእናንተ ሕይወት እና አገልግሎት ያነበዋል። 👇👇👇👇JOIN 👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

መጽሐፍ ቅዱስን ከዘፍጥረት እስከ ራዕይ አንድም ጊዜ አንብባችሁ ያልጨረሳችሁ ነገር ግን ሌሎች ብዙ መጽሐፍት አንብባችሁ የጨረሳችሁ ክርስቲያን ወንድሞቼና እህቶች ምን እላለሁ እግዚአብሔር ምህረት ያብዛላችሁ!🙄 በሰይጣን ሽንገላ ተታላችሁ ይሆን? የእግዚአብሔርን ምክር ትታችሁ የስጋ ለባሽን ምክር ለምን ትወዳላችሁ!? አረ ንቁ! ሰይጣን እንዲሸነግላችሁ አትፍቀዱ። ቢያንስ ሃያ ሰባቱን የአዲስ ኪዳን መጽሐፍት ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ በማንበብ ራሳችሁን አስለምዱ። ፀጋ ይብዛላችሁ!😍 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ማርቆስ 16 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁵ እንዲህም አላቸው፤“ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ፤ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ፤ ¹⁶ ያመነ የተጠመቀ ይድናል፤ ያላመነ ግን ይፈረድበታል። ¹⁷ የሚያምኑትን እነዚህ ምልክቶች ይከተሏቸዋል፤ በስሜ አጋንንትን ያወጣሉ፤ በአዲስ ልሳንም ይናገራሉ፤ ¹⁸ እባቦችን በእጃቸው ይይዛሉ፤ የሚገድል መርዝ ቢጠጡ እንኳ አይጐዳቸውም፤ እጃቸውንም በሕመምተኞች ላይ ይጭናሉ፤ እነርሱም ይፈወሳሉ።” ¹⁹ ጌታ ኢየሱስ ይህን ከተናገራቸው በኋላ ወደ ሰማይ ዐረገ፤ በእግዚአብሔርም ቀኝ ተቀመጠ። ²⁰ ከዚያም ደቀ መዛሙርቱ ወጥተው፣ በየስፍራው ሁሉ ሰበኩ፤ ጌታም ከእነርሱ ጋር ይሠራ ነበር፤ ትምህርታቸውንም ተከትለው በሚፈጸሙ ምልክቶች ቃሉን ያጸና ነበር። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ትልቅ ጅማሮ ነው! እግዚአብሔር በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን የሚሰራው ትልቅ ሥራ አለ። የካውንስሉ የመጀመሪያ የምስረታ ዓመት። ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን!
+5
ትልቅ ጅማሮ ነው! እግዚአብሔር በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን የሚሰራው ትልቅ ሥራ አለ። የካውንስሉ የመጀመሪያ የምስረታ ዓመት። ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን!

ታዋቂነት፤ ስም፤ ዝና እና ሃብት ራሃባቻው ያልሆኑ ሰዎች አሉ! እንዚህን ነገሮች ሁሉ በአጭር ጊዜ ለማግኘት ብዙ Advantage ያላቸው ነገር ግን ስለአንድ ነገር ሁሉንም እንደ ጉዳት የቆጠሩ ሰዎች አሉ! “አዎን፥ በእውነት ከሁሉ ይልቅ ስለሚበልጥ ስለ ክርስቶስ ኢየሱስ ስለ ጌታዬ እውቀት ነገር ሁሉ ጉዳት እንዲሆን እቈጥራለሁ፤...” — ፊልጵስዩስ 3፥8-9 ኢየሱስ ክርስቶስን ለማወቅ ጥልቅ ፍላጎትና ትልቅ ትጋት ያላችሁ የእግዚአብሔር ልጆች ከዚህም የተነሳ ሌላውን እንደ ጉዳት የምትቆጥሩና በእግዚአብሔር ቃል እየተፈተናችሁ የቆያችሁ ከመናፍስት አባት እግዚአብሔር የተነገረላችሁ ቃል ይመጣል በዚያን ጊዜ ንጉስ ልኮ ያስፈታችኋል! ተፈትናችሁ የጠራችሁ በምትሆኑበት ጊዜ በምድሩና በለው፤ በቤቱም ሁሉ ላይ ይሾማችኋል! ከራሱም ቀጥሎ ያከብራችኋል። #የእግዚአብሔር_ቃል_ስፈትናችሁ_አትዛሉ! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

Child of God say Amen to the blessings Of God over your life! #የአሮን_በረከት! ዘኍልቁ 6 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²⁴ እግዚአብሔር ይባርክህ፥ ይጠብቅህም፤ ²⁵ እግዚአብሔር ፊቱን ያብራልህ፥ ይራራልህም፤ ²⁶ እግዚአብሔር ፊቱን ወደ አንተ ያንሣ፥ ሰላምንም ይስጥህ። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ሕይወት መንፈሳዊ ነዉ።/Life is spiritual./ ....አስተውሉ ፊተኛው አዳምና ረዳቱ የነበረችው ሔዋን በእግዚአብሔር ኤደን በገን የነበሩበት ጊዜ በሕይወት የነበሩበት ጊዜ ነበር: ከጨርቅ ወይም ከቆዳ የተሰራ ልብስ አይለብሱም ነበር ነገር ግን እራቁትነት አይሰማቸውም ነበር፤ በዚያ ስራ ነበር ድካም ግን አልነበረም፤ ይመሽና ይነጋም ነበር ፍርሃት እና ሃዘን ግን አልነበረም! ምክንያቱም የሕይወት ምንጭ ከሆነው መንፈስ ጋር ተስማምተው የነበሩበት ጊዜ ስለነበር ነዉ። የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ በተላለፉ ጊዜ ግን ወድያው እራቁቱነት፤ ፍርሃት፤ የበደለኝነት ስሜት በኃላም ድካም፤ ላብ፤ ስቃይ፤ ሕመም መጡባቸው! ምክንያቱም የሕይወት ምንጭ ከሆነው መንፈስ ባለመታዘዝ ስለተለያዩ እና ስለሞቱ ነው። የሕይወት ምንጭ እግዚአብሔር ነዉ። እግዚአብሔር ደግሞ መንፈስ ነዉ። ከእግዚአብሔር የተለየ ሕይወትን እየኖረ አይደለም! በድካም በላብ እና በስቃይ ነው የሚኖረው: የሕይወት ምንጭ ከሆነው መንፈስ የተስማማ ግን በሕይወት ይኖራል። አያችሁ ሕይወት መንፈሳዊ ነዉ:እውነተኛ እረፍት፤ ሐሴት ፤ጤንነት ፤ ነጻነት፤ ስኬት ሁሉ መንፈሳዊ ነዉ። መንፈስ ቅዱስ ያልረዳው ስጋ ለባሽ ሕይወትን መኖር አይችልም: ምክንያቱም ሕይወት መንፈሳዊ ነዉ። ሰው ሕይወትን መኖር የሚጀምረው ከእግዚአብሔር ጋር ሲሆን ነዉ። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ታዋቂነት፤ ስም፤ ዝና እና ሃብት ራሃባቻው ያልሆኑ ሰዎች አሉ! እንዚህን ነገሮች ሁሉ በአጭር ጊዜ ለማግኘት ብዙ Advantage ያላቸው ነገር ግን ስለአንድ ነገር ሁሉንም እንደ ጉዳት የቆጠሩ ሰዎች አሉ! “አዎን፥ በእውነት ከሁሉ ይልቅ ስለሚበልጥ ስለ ክርስቶስ ኢየሱስ ስለ ጌታዬ እውቀት ነገር ሁሉ ጉዳት እንዲሆን እቈጥራለሁ፤...” — ፊልጵስዩስ 3፥8-9 ኢየሱስ ክርስቶስን ለማወቅ ጥልቅ ፍላጎትና ትልቅ ትጋት ያላችሁ የእግዚአብሔር ልጆች ከዚህም የተነሳ ሌላውን እንደ ጉዳት የምትቆጥሩና በእግዚአብሔር ቃል እየተፈተናችሁ የቆያችሁ ከመናፍስት አባት እግዚአብሔር የተነገረላችሁ ቃል ይመጣል በዚያን ጊዜ ንጉስ ልኮ ያስፈታችኋል! ተፈትናችሁ የጠራችሁ በምትሆኑበት ጊዜ በምድሩና በለው፤ በቤቱም ሁሉ ላይ ይሾማችኋል! ከራሱም ቀጥሎ ያከብራችኋል። #የእግዚአብሔር_ቃል_ስፈትናችሁ_አትዛሉ! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit