TheDeepThingsOfGod
رفتن به کانال در Telegram
1 810
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
1 810
“እግዚአብሔር ግን ሳሙኤልን፦ ፊቱን የቁመቱንም ዘለግታ አትይ፤ ሰው እንዲያይ እግዚአብሔር አያይምና ናቅሁት፤ ሰው ፊትን ያያል፥ እግዚአብሔር ግን ልብን ያያል አለው።”
— 1ኛ ሳሙኤል 16፥7
1 810
የመንፈስ ቅዱስ ሕብረት
ሐዋሪያው ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ቤተክርስቲያን የጻፈውን መልእክቱን የጨረሰው --“የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ፣ የእግዚአብሔር ፍቅር፣ የመንፈስ ቅዱስም ኅብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን።” በማለት ነዉ።
— 2ኛ ቆሮንቶስ 13፥14
እኔ ዛሬ የምናገረው ስለመንፈስ ቅዱስ ሕብረት ነው።
መንፈስ ቅዱስን በተወሰነ ደረጃም ቢሆን ሁሉም ክርስቲያን ያዉቀዋል። ስለ መንፈስ ቅዱስ ሰልናገር ከእርሱ ጋር ስለምናደርገው ሕብረት ለመናገር መጀመሬ ለዚሁ ነዉ።
በብሉይ ኪዳን መንፈስ ቅዱስ ከተወሰኑ የተመረጡ ሰዎች ጋር ህብረት ያደርግ ነበር: እነዚህ ሰዎች ሙሉበሙሉ ማለት በሚቻል ደረጃ: እግዚአብሔር ለንግስና፤ ለክህነት ወይም ደግሞ ለነቢይነት የመረጣቸው ነበሩ። ህብረቱም ቢሆን ቀጣይና ዘላለማዊ አልነበረም/ the fellowship of the Spirit was on and off in the old testament/ ይህም የሆነው ከሰው የልብ ክፋት የተነሳ ነበር። “እግዚአብሔርም፦ መንፈሴ በሰው ላይ ለዘላለም አይኖርም፥ እርሱ ሥጋ ነውና፤ ዘመኖቹም መቶ ሀያ ዓመት ይሆናሉ አለ።”
— ዘፍጥረት 6፥3
“እግዚአብሔርም የሰው ክፉት በምድር ላይ እንደ በዛ፥ የልቡ አሳብ ምኞትም ሁልጊዜ ፈጽሞ ክፉ እንደ ሆነ አየ።”
— ዘፍጥረት 6፥5
በዚህ ምክንያት የእግዚአብሔር መንፈስ ለተለየ ዓለማ ከልሆነ ከሰዎች ጋር ህብረት አያደርግም ነበር: ነገር ግን በተወሰነ ደረጃም ቢሆን ሕብረት ነበር ይህንን ከንጉሡ ዳዊት ልመና መረዳት እንችላለን!
“ከፊትህ አትጣለኝ፥ ቅዱስ መንፈስህንም ከእኔ ላይ አትውሰድብኝ።”
— መዝሙር 51፥11
ንጉሡ ዳዊት ይህንን ልመና ያደረገበት ምክንያት አለው። የእግዚአብሔር መንፈስ በእርሱ ላይ ስሆን እና ትቶት ስሄድ ያለውን ልዩነት በግልጽ የተረዳው በመሆኑ ነዉ። ስለዚህ ሁልጊዜ መንፈስ ቅዱስ ከእርሱ ጋር እንድኖር በመፈለግ ይህንን ጸሎት አድርጓል!
ሕብረት ማለት ምን ማለት ነዉ? በብሉይ ኪዳን መንፈስ ቅዱስና ሰዎች ቀጣይና ዘላለማዊ አብሮ ነዋሪነት ስላልነበራቸው "ሕብረት" የሚለውን ቃል አናገኝም። መዝሙረ ዳዊት "በወንድሞች" መካከል መኖር ስላለበት ሕብረትና ስለበረከቱ ይናገራል: ከዚህ ያለፈ ከእግዚአብሔር ጋር ሕብረት ግን አናይም።
በአድስ ኪዳን ግን ሕብረት የሚለው ቃል በሰፊው ጥቅም ላይ ውሏል: መጀመሪያ ከጠቀስኩት የንባብ ክፍል "ሕብረት" የሚለው የግሪክ ቃል "κοινωνία" /koinonia/ የሚል ቃል ነዉ: ይህ ቃል በእንግሊዝኛው
fellowship, association, community, communion, joint participation, intercourse; የሚሉ ትርጉሞች አሉት። ሁሉም ቃላት፤ አብሮ ነዋሪነት፣ አብሮ ሰራተኝነትን፣ ተባባሪነትን፣ ተካፋይነትን የሚገልጹ ቃላት ናቸው።
መንፈስ ቅዱስ ከእኔ ጋር ሕብረት አለው ወይም እኔ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ሕብረት አለኝ ስንል: በቀጣይነት አብሮ ነዋሪ ነን፤ አብሮ ሰራተኛና ተባባሪ ነን፤ አንዳችንም የአንዳችን ተካፋይ ነን ማለት ነዉ።
1ኛ-ለዘላለም አብሮ ነዋሪ ነን!
“ብትወዱኝ ትእዛዜን ጠብቁ። እኔም አብን እለምናለሁ ለዘላለምም ከእናንተ ጋር እንዲኖር ሌላ አጽናኝ ይሰጣችኋል፤”
— ዮሐንስ 14፥15-16
ለዘላለም አብሮኝ ነዋሪ የሚለው ቃል ሁሉንም የሚገልጽ እንደሆነ አስባለሁ። ለምሳሌ ለዘላለም ባይሆንም ለዓመታት አብራችሁ የምትኖሯቸውን ወላጆቻችሁን፤ ወንድም እህቶቻችሁን አስቧቸው!? አብሮ ነዋሪ በመሆናችሁ ብቻ: አብሮ ሰረተኛ ተባባሪ፤ ናችሁ....ሌላው አንዳችሁ የአንዳችሁን አሰብ፣ አነጋገር ስሜት፣ አደራረግ... ወዘተ ትጋራላችሁ...ምክንያቱም አብሮ ነዋሪ በመሆናችሁ ነዉ።
ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ያላችሁ ሕብረትም ልክ እንደዚሁ ነዉ! መንፈስ ቅዱስ የክርስቶስን አሳብ ያከፍላችኋል!... አስተሳሰባችሁን አነጋገራችሁን፣ ድርጊታችሁን ሁሉ ይቀርጸዋል!.... እናንተም የምታስቡትን፣ የሚሰማችሁን ሕመማችሁን ደስታችሁን ሐዘናችሁን ሁሉ ታካፍሉታላችሁ...እርሱም ከእናንተ ወስዶ ይሸከመዋል! እርሱም ደስታውን ሐዘኑን ሁሉ ይነግራችኋል.... ሕብረት ማለት ይህ ነዉ።
JOIN
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች ፀጋና ሰላም ይብዛላችሁ እንደዚህ በለ እጅግ በሚያስጨንቅ እና ትልቅ ክህደት ባለበት ዘመን እውነተኛ የክርስቲያን ሕይወት መኖር የምንችለው ከእግዚአብሔር መንፈስና ቃል ጋር በግላችን ሕብረት ካለን ብቻ ነዉ።
የምህረት አምላክ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን አብዝቶ ይስጣችሁ! የቃሉን ደጅ ይክፈትላችሁ!
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ለትልቅ ነገ ተዘጋጅ/ተዘጋጂ እግዚአብሔር የከበረ እቅድ አለው።
“ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም።”
— ኤርምያስ 29፥11
1 810
ለ 58 ዓመታት መንፈስ ቅዱስ ለኢትዮጵያ የተናገራቸው 3 ነገሮች።
1-ኢትዮጵያዊያንን በዓለም ሁሉ እበትናለሁ ይህም የምሆነው መንግስቴን ለማስፋት ነዉ።
👉የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ሚስዮናዊት ትሆናለች።
👉አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ደግም የተወለደ ይሆናል።
👉ቤተክርስቲያንን ለክርስቶስ ዳግም ምጸት የሚያዘጋጅ ሪቫይቫል ከኢትዮጵያ ይነሳል።
2-ለጥቂት ጊዜ እጅግ ድቅድቅ ጨለማ ከፊትህ አለ: ከእግዚአብሔር ጋር ተጣበቅ።
3-ኢትዮጵያ ከፊቷ የከፍታ ዘመን አለ። በአስር ዓመት ውስጥ የ 500 ዓመት ሥራ የሚሰራበት ጊዜ አሁን ነዉ።
👉እነዚህ ትንቢቶች የሚፈጸሙበት ትውልድ ይህ ትውልድ እንደሆነ ያለጥርጥር አምናለሁ!
--ፓስተር በቀለ ወ/ኪዳን-- ከስተላለፉት መልእክት የወሰድኩት ነዉ። ሁላችሁም YouTube ላይ ተመልከቱት። ከባድ ነው ወንድሞቼ እና እህቶቼ ተዘጋጁ: እግዚአብሔር ወደተናገረው ከፍታ ያደርሰናል። ክብር ለስሙ ይሁን!🔥🔥🔥
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
በመንፈሳዊ ውጊያ ሁሉ የድል ቁልፍ!
💪💪🔥🔥💪💪🔥🔥💪💪🔥🔥
መቼም በየትኛውም ሁኔታና ጊዜ ከየትኛውም አይነት የሰይጣን ሀይል ጋር መዋጋት ስኖርባችሁ መርሳት የሌለባችሁ መሰረታዊ እውነት : ኢየሱስ በሞቱ እና በትንሳኤው በሰይጣን ለይ ፍጹም ፣ ዘላቂ ፣ የመጨረሻ እና የማይቀለበስ ድል መቀዳጀቱን ነዉ። ይህንን እውነት ለመለወጥ ሰይጣን ሊያደርግ የሚችለው ምንም ነገር የለም። ይህንን እውነት በመንፈሳችሁ መረዳት ከቻላችሁ በሰይጣን ለይ ፍጹም ድል በዘመናችሁ ሁሉ አላችሁ።
👇JOIN 👇 JOIN 👇JOIN 👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
#ለወንድሞች_ሁሉ!
...የሴቶችን ቀን በማስመልከት ይህንን ልበል...
እግዚአብሔር ሴትን ለመፍጠር የወንድን የጎድን(የጎን) አጥንት ነዉ የተጠቀመው! ግን ለምን? ለምን አጥንቱን ከእግር ወይም ከእጅ አልወሰደም? እግዚአብሔር ሄዋን አድርጎ የሰራትን አጥንት ከአዳም እግር ወስዶ ቢሆን ሴቶችን ወንዶች የሚፈልጉበት ለመድረስ ይጠቀሟቸው ነበር፤ ከአዳም እጅ ወስዶ ሰርቷት ቢሆን ደግሞ: ወንዶች የሚፈልጉትን ነገር ለማድረግ ወይም ለመያዝ ሴትን ይጠቀሙ ነበር። ነገር ግን እግዚአብሔር ከአዳም የወሰደው የጎድን አጥንቱን ነዉ: ምክንያቱም እጅ የሚጠበቅው ወይም የሚከልለው የአጥንት ክፍል ስለሆነ ነዉ። የአዳም እጅ የሚጠብቀውን የአጥንት ክፍል ወስዶ ነዉ ሄዋንን የሰራት። ስለዚህ ወንዶች ሴቶችን የመጠበቅ /የመከለል፤ ለሴቶች የመከላከል ሃላፊነት አለብን።
ወንዶች ያላችሁን ሃይል(እጅ) ሴቶችን ለመከላከል ተጠቀሙበት። በዚያ እጃችሁ ድሮ እንኳ ቢሆን የመታችኋት ሴት ከለች ይቅርታ ጠይቁ። እግዚአብሔር የሰጣችሁ እጅ የጎድን አጥንታችሁን እንድከልል ተደርጎ ነዉ የተሰራው።
#እህቶቻችሁን_ተከላከሉላቸው!
#ጠብቋቸው!
-Victor
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
March 8
ዛሬ የሴቶች ቀን ነዉ። በአምላካችን በእግዚአብሔር ፍቅር የምወዳችሁ እህቶች፤እጅግ ብዙ አምላካዊ ፍጹም ምክር እሰጣችሁ ነበር:... ነገር ግን ይህንን አንድ ነገር አትርሱ! በዘመናችሁ ሁሉ አጥብቃችሁ ያዙት: የሚያስመካችሁ ውበታችሁ ወይም የትኛውም አይነት ብቃታችሁ አይሁን፤ ትልቁ ሃብታችሁ እግዚአብሔርን መፍራት ይሁን! ይህንን ካደረጋችሁ ዘመናችሁን ሁሉ ምስጋናና መወደድ አይጎድልባችሁም!
“ውበት ሐሰት ነው፥ ደም ግባትም ከንቱ ነው፤ እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ግን እርስዋ ትመሰገናለች።”
— ምሳሌ 31፥30
ፀጋ ይብዛላችሁ!
የተወደዳችሁ ናችሁ!
የእግዚአብሔር ሴት ልጆች!
-Victor
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ፈተና ለምትፈተኑ ወዳጆቼ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ሆኖ ድል ይስጣችሁ!
“በዚያን ጊዜም መጻሕፍትን ያስተውሉ ዘንድ አእምሮአቸውን ከፈተላቸው፤”
— ሉቃስ 24፥45
#እወዳችኋለሁ😍
1 810
🔥TheDeepThingsOfTheSpirit🔥
ከመንፈስ ቅዱስና ከእግዚአብሔር ቃል ጋር ያላችሁ ሕብረት በየቀኑ ወደተሻለ ደረጃ ማደግ እንደለበት በማመን ወስኑ!
ጠዋት ከእንቅልፍ ስትነቁ መንፈስ ቅዱስን "ሕብረታችን ወደሌላ ደረጃ ከፍ እንድል እፈልጋለሁ: እባክህ አስጠጋኝ" በሉት።
እንደ አማኝ ከክርስቶስ ጋር የሚኖረን አንድነት ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በለን ሕብረት የሚወሰን ነዉ: ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ያላችሁ ሕብረት ከአንድ ደረጃ ወደሌላ ስሸጋገር ከክርስቶስ ጋር ያላችሁን አንድነት የበለጠ ማወቅ እና መግለጥ ትችላላችሁ!
መንፈስ ቅዱስ ኢየሱስን ከምንም በላይ በሕይወታችን እውነት የማድረግ ሃይል አለው። ስለዚህ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ያለን ሕብረት በየቀኑ በየሰዓቱ ማደግ አለበት።
የመንፈስ ቅዱስ መሪነትና አስተማሪነት ሃይሉም ለተወሰኑ ሰዎች ብቻ አይደለም ለሚያምኑ ሁሉ ነዉ።
የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ያላችሁ ሕብረት ወደ ላቀ ደረጃ እንዲያድግ በእግዚአብሔር ፍቅርና በኢየሱስ ክርስቶስ ፀጋ በርቱ!
👇👇👇👇👇join 👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ሉቃስ 5
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁷ ባረጀ አቁማዳም አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም፤ ቢደረግ ግን አዲሱ የወይን ጠጅ አቁማዳውን ያፈነዳል፥ እርሱም ይፈሳል አቁማዳውም ይጠፋል።
³⁸ አዲሱን የወይን ጠጅ ግን በአዲስ አቁማዳ ማኖር ይገባል፥ ሁለቱም ይጠባበቃሉ።
👉አድስ የወይን ጠጅ ሲፈላ እየጨመረ የመሄድ ባሕሪይ አለው።
👉አቁማዳ ወይን ለማፊላትና ለመያዝ ከፊየል ከቆዳ የሚሰሩት እቃ ነዉ። ቆዳ ደግሞ ስቆይ የመድረቅ ባሕርይ አለው። ስለዚህ አድስ የወይን ጠጅ በአሮጌ አቁማዳ ውስጥ ማድረግ ማስተዋል የጎደለው ተግባር ነዉ፤ የሚያደርገው ሰው ወይኑንም አቁማዳውንም ያጣል። ስለዚህ አድስ ወይን በአድስ አቁማዳ ወይም በታደሰ አቁማዳ ውስጥ ይደረጋል።
እግዚአብሔር አንዳንድ ጸሎቶቻችን ያልመለሰው እኛንም የጸሎት መልሳችንንም ማባከን ስለማይፈልግ ነዉ ብዬ አምናለሁ። ባልተለወጠ ማንነት ምንም ያህል ብንጸልይና ብንጾም የማንቀበላቸው የእግዚአብሔር በረከቶች አሉ። እግዚአብሔር አስተዋይ አጥማቂ ነዉ ወይኑንም አቁማዳውንም ማባከን አይፈልግም ስለዚህ አድስ ወይን ከመስጠቱ በፊት አቁማዳውን ያድስዋል!
ያልተመለሱ ጸሎቶቻችሁን አስቡ: እናም እራሳችሁን ተመልከቱ! ለእነዚያ ጸሎቶቻችሁ እግዚአብሔር መልስ ቢሰጥ: ተጠባብቃችሁ መኖር ትችላላችሁ? ወይኑና አቁማዳው አድስ ስሆኑ ተጠባብቀው ይኖራሉ ከልሆነ ግን ይጠፋሉ። በነገራችን ላይ አንዳንድ ሰዎችን ከእግዚአብሔር የለያቸው ድህነት ወይም ረሃብ አይደለም! ጸልያውና አልቅሰው ያገኙት በረከትና ጥጋብ ነዉ። እኛ ሳንሰራ ነገራችን ከተሰራ እኛም የተሰራልን ነገርም ተያይዘን የመጥፋት እድላችን ሰፊ ነዉ።
እግዚአብሔር ምንም ሰይሰራላችሁ፤ በእናንተ ተዓምራት ሰይሰራ፤ ቤት ሰይሰራላችሁ እናንተን ይስራችሁ! አሜን!
እግዚአብሔር በእኛ ከመስራቱ ቀድሞ እኛን መስራት ይወዳል! እሽ እንበለው! እንስማማ!
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
“ኃይልህንና ክብርህን አይ ዘንድ እንዲሁ በመቅደስ ውስጥ ተመለከትሁህ።”
— መዝሙር 63፥2
በእነዚህ የተወደዱ መቅደሶችህ ውስጥ ያየሁትን ሃይል በእኔም ሕይወት ለማየት እፈልጋለሁ! ጌታ ሆይ በድጋሚ አድርገው....አብዝተህ አድርገው! አድርገው! ሃይልህን አሁንም አድርገው!!
😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭
1 810
Who is next???
ቀጣዩ ማነው???.....
“ኃይልህንና ክብርህን አይ ዘንድ እንዲሁ በመቅደስ ውስጥ ተመለከትሁህ።”
— መዝሙር 63፥2
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
የዓለም ብርሃን ነህ/ሽ!
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ-- “በዓለም ሳለሁ የዓለም ብርሃን ነኝ።”
— ዮሐንስ 9፥5 አለ። እርሱ ዓለምን ትቶ ወደ አባቱ ቀኝ ከሄደ በኃላ: በዓለም ብርሃን የመሆንን ሕይወት ለእኛ ለምናምን ሰጥቶን ነዉ የሄደው--“እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ። በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሰወር አይቻላትም።”
— ማቴዎስ 5፥14
ነገር ግን ስለኢየሱስ ክርስቶስን ለመመስከር፤ ስለ እግዚአብሔር ቃል ለመናገር የምናፍርና የምንፈራ ከሆነ እንዴት ብርሃን መሆን እንችላለን? በተራሮች ላይ ቆመን በድፍረት እና በግልጽ እምነታችንን ለዓለም የማንናገር ከሆነ እንዴት ብርሃን መሆን እንችላለን?
ማቴዎስ 5
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁵ መብራትንም አብርተው ከዕንቅብ በታች አይደለም እንጂ በመቅረዙ ላይ ያኖሩታል በቤት ላሉት ሁሉም ያበራል።
¹⁶ መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ።
የማንሰብከው ወንጌል፤ የማንናገረው የእግዚአብሔር ቃል ለራሳችንም ለሌሎችም እንደማያበራ ከአልጋ በታች እንዳለ መብራት ነዉ። ነገር ግን ከደበቅንበን አውጥተን በመቅረዝ ላይ ስናስቀምጠው በቤቱ ውስጥ ላለ ሁሉ ያበራል!
ይህ ጊዜ የምናፍርበት የምንሸማቀቅበት ጊዜ አይደለም ለቅርቡም ለሩቁም ስለኢየሱስ ክርስቶስ የምንመሰክርበት ጊዜ ነዉ። ይህንን ስናደርግ የዓለም ብርሃን መሆናችንን በተግባር እንገልጣለን። ፀጋ ይብዛላችሁ!
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ሮሜ 6
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹³ ብልቶቻችሁንም የዓመፃ የጦር ዕቃ አድርጋችሁ ለኃጢአት አታቅርቡ፥ ነገር ግን ከሙታን ተለይታችሁ በሕይወት እንደምትኖሩ ራሳችሁን ለእግዚአብሔር አቅርቡ፥ ብልቶቻችሁንም የጽድቅ የጦር ዕቃ አድርጋችሁ ለእግዚአብሔር አቅርቡ።
¹⁴ ኃጢአት አይገዛችሁምና፤ ከጸጋ በታች እንጂ ከሕግ በታች አይደላችሁምና።
1 810
አያለሁ! እጠብቃለሁ! እፈልጋለሁ!
...መንፈስህ በሃይል ወርዶብኝ የነፍሳት ሸክም ከብዶብኝ....
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
