TheDeepThingsOfGod
رفتن به کانال در Telegram
1 810
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
1 810
“እኛ ግን በጸሎትና በቃሉ አገልግሎት እንተጋለን።”
— ሐዋርያት 6፥4
ወዳጆቼ በጸሎትና በቃሉ አገልግሎት መትጋት ይኖርብናል!
1 810
የተወደዳችሁ የእግዚአብሔርን እውነት ስለ ክርስቶስ ኢየሱስ ከተሰጡት ከመጀመሪያዎቹ ትምህርቶች ጀምረን ፍጹም እስከሆኑት ትምህርቶች ድረስ በጥንቃቄ ከልተማርን፣ ካላስተማርን እና ካልተቀበልን የኢትዮጵያም፣ የአፍሪካም ቤተክርስቲያን የአውሮፓ እና የአሜሪካ አብያተክርስቲያናት የደረሰባቸው አደጋ ይደርስባታል።
አስተውሉ: በአንድ ወቅት የአውሮፓም የአሜሪካም አብያተክርስቲያናት በመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች የደመቁ ነበሩ ነገር ግን ቤት የቱንም ያህል በስጦታዎች የተዋበ ቢሆን እንኳ መሰረት ከሌለው መውደቁ አይቀሬ ነው።
ወደ እግዚአብሔር ቃል በትህትና እንመለስ! ሁሉም የሚከተለው የእግዚአብሔርን ቃል ነው።
እግዚአብሔር በዓለም ሁሉ ዙሪያ ያሉ የክርስቶስ አብያተክርስቲያናትን በምህረቱ ይጎብኝ! አሜን!
@TheDeepThingsOfGod
@TheDeepThingsOfGod
1 810
የተወደዳችሁ አንድ ጥያቄ ልጠይቃችሁ!
የውሃ ጥምቀት ትርጉሙ ምንድነው? በአንድ አማኝ ሕይወት ውስጥ የሚፈጥረው መንፈሳዊ ተጽዕኖስ ምንድነው?
ተወዳጆች አመሰግናችኋለሁ!🥰
1 810
ለኃጢአት እንደሞትን እራሳችንን እንቁጠር!
አንድ ሰው እጅግ በጣም ብልሹ የሆነ ሰው አስቡ፣ ቤተክርስቲያን የሚሄዱ ሰዎች እንኳ የማይታገሱት አይነት ሰው ነው። መጠጥ ይጠጣል፣ ሲጋራ ያጨሰል፣ ለባለቤቱ መልካም አይደለም፣ ልጆቹን ይራገማል። እናም ባለቤቱና ልጆቹ ጌታን ኢየሱስን ተቀብለው በአካባቢያቸው ያለ አጥቢያ ቤተክርስቲያን ተቀላቀሉ። እሁድ ቀን ወደ ቤተክርስቲያን ለመሄድ ከቤታቸው በር ስወጡ እንደተለመደው ወንበሩ ላይ ወደኃላ ተደግፎ ተቀምጧል በእጁም የሚያጨሰውን ሲጋራ ይዟል ከፊቱ ባለው ጠረቤዛ ላይም መጠጥ አስቀምጧል፣ በእጁ ላይ በለው ስልክ የማይገባ ምስል ይመለከታል፥ ልጆቹን እና ባለቤቱን ስመለከት እየዛተ እና እየተገዘተ መሳደብና መረገም ጀመረ፣ እነርሱም ፈጥነው ወጥተው ሄዱ። እጅግ በጣም መልካም ጊዜ ከቤተክርስቲያን ጋር ካሳለፉ በኋላ ወደቤታቸው ተመለሱ፣ ከፊት በለው በር ወደውስጥ ሲገቡ እንደተለመደው ዛቻውን፣ ስድቡን እና እርግማኑን እየጠበቁ ነበር፥ ነገር ግን ከወትሮው ፈጽሞ በተለየ መልኩ ሰውዬው ዝም ብሏል፣ እየተሳደበም እየዛተም አልነበረም፣ በጣቶቹ ውስጥ ተጠምዶ የነበረው ሲጋራ እዚያው ማስቀመጫ ውስጥ እየጨሰ ነው ሰውዬው ግን እያጨሰ አልነበረም፣ መጠጡ በእቃው ውስጥ እንዳለ ነው እርሱ ግን እየጠጣ አይደለም፣ በስልኩ ይመለከት የነበረውን አስጸያፊ ምስል እንኳ እየተመለከተ አልነበረም። ለምን? ምክንያቱም ባለቤቱና ልጆቹ ከቤት ወጥተው ከሄዱ በኋላ ሰውዬው የልብ ምቱ በድንገት ቆሞ ስለነበር ወዲያው ሞተ። አሁን ለመጠጥና ለሲጋራ ሞቷል፣ ለመራገም እና ለመሳደብ ሞቷል፣ የማይገቡ ተንቀሳቃሽ ምስሎች ለማየት ሞቷል። ኃጢአት ከዚህ በኋላ አይስበውም እናም ኃጢአት ከእርሱ ውስጥ ምንም አይነት ምላሽ ማግኘት አይችልም እርሱም ለኃጢአት ምላሽ መስጠት አይችልም። ሞቷል።
“እንዲሁም እናንተ ደግሞ ለኃጢአት እንደ ሞታችሁ፥ ግን በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን ሆናችሁ ለእግዚአብሔር ሕያዋን እንደ ሆናችሁ ራሳችሁን ቁጠሩ።”
— ሮሜ 6፥11
👇👇👇ተቀላቀሉ👇👇👇
@TheDeepThingsOfGod
@TheDeepThingsOfGod
1 810
ሮሜ 6፥1-2 ~ መግቢያ
እግዚአብሔር ለአሮጌው ሰው ያዘጋጀው መፍትሔ- የሞት ፍርድ!
ፀጋ እንዲበዛ በኃጢአት መኖር አለብን ወይ?
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfGod
@TheDeepThingsOfGod
1 810
አንድ መንፈሳዊ ሚስጥር ላካፍላችሁ!
ሰዎች በተለይም ክርስቲያኖች አብዛኛውን ጊዜ የሚሰሩት ስህተት ሰይጣንን ተጠያቂ ማድረግ ነው። በአገልግሎት፣ በትምህርት፣ በቢዝነስ፣ ከሰዎች ጋር በለ ግንኙነት እና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ ለሚደርስብን እክል ወይም በሕይወታችን ወደፊት ለመሄድ ስንቸገር፣ ለውጦች እየፈለግን የምንፈልጋቸውን ለውጦች ግን ማየት ስያቅተን ሰይጣንን ተጠያቂ ማድረግ የተለመደ ነው፣ የሆነ ቦታ ለመድረስ እየፈለግን ነገር ግን ካለንበት ወደፊት ጠጋ ማለት ሲሳነን ሰይጣን የከለከለኝ ስንል ብዙ ጊዜ እንደመጣለን። ይሄ ፈጽሞ ስህተት ነው፣ ወዳጆች ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀሉ በእኛም ምትክ በሰይጣን ለይ ፍጹም ፣ ዘላቂ ፣ የመጨረሻ እና የማይቀለበስ ድል ተቀዳጅቷል! ይህ ድል የክርስቲያኖችም ነው። ይሄ ማለት ሰይጣን እጁን አጣምሮ ይቀመጣል ማለት አይደለም፣ ነገር ግን የቱንም ያህል ቢዋጋ የተሸነፈ ነው። ስለዚህ ክርስቲያን በሕይወቱ ለሚከሰቱ መጥፎ ነገሮች ሁሉ ሰይጣንን ተጠያቂ ማድረጉ ለተሸነፈ ጠላት እውቅና (Credit) እንደመስጠት ያለ ሞኝነት ነው፤ እንደዚህ ያለው አስተሳሰብ ሰይጣንን የሚያከብር እና ኢየሱስ ክርስቶስ በሰይጣንና በጨለማ ሃይላት ሁሉ ላይ የተቀዳጀውን ድል የሚያኮስስ ነው።
ታዲያ ማነው ተጠያቂ? ወደፊት ላለመሄዴ፣ አንድ ቦታ ለመቆሜ ወይም ለመጥፎ ነገሮች ማነው ተጠያቂ? እራሴው ነኝ! በውስጤ ያለው አሮጌው ሰው ነው። ለዚህ ነው መጽሐፍ ቅዱስ በኤፌሶን 4፥22 ላይ -“አሮጌውን ሰው አስወግዱ፥” የሚለን። አሮጌው ሰው የሰይጣን አቻ ነው፣ ምንአልባትም የከፋ ይሆናል፣ ሰው ለሰይጣን ጥቃት እንኳ የሚጋለጠው በአሮጌው ሰው ምክንያት ነውና።
የዕብራውያን መልእክት ጸሓፊ ክርስቲያኖችን እንደዚህ በማለት የተናገረውም በዚሁ ምክንያት ነው---“እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፥ እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና።” — ዕብራውያን 12፥1-2--- በዚህ ጥቅስ ውስጥ የተሰመራውን ተመልከቱ፣ ኃጢአት የሚለው ቃል የሚገልጸው የግብር ኃጢአትን ብቻ አይደለም ነገር ግን በውስጣችን ያለውን አሮጌውን ሰው ነው፣ ይህ ሰው ኃጢአተኛ ተፈጥሮ ያለው ሰው ነው። በግልጽ እንደምናነበው ይህንን አሮጌ ሰው ይህ ክፍል "ሸክም" እና "ቶሎ የሚከብ ወይም በቀላሉ ተብትቦ የሚይዝ" ይለዋል። ወዳጆቼ ክርስቲያኖች ወደፊት እንዳንሮጥ ሸክም እና በቀላሉ ተብትቦ የሚይዝ እና ያለንበት የሚያስቆም ጠላት የሆነብን ሰይጣን ሰይሆን በእኛ ያለው አሮጌ ሰው ነው። መጽሐፍ ቅዱስ "አስወግዱት" ነው የሚለን። ይህንን አሮጌ ሰው ከስወገዳችሁ ሰይጣን በእናንተ አንዳች የለውም!
ወደ ግባችሁ ለመድረስ ሸክም የሚሆንባችሁን እና በቀላሉ ተብትቦ በፊታችሁ ከተዘጋጀው የከበረ ሩጫ የሚያስቆማችሁን አሮጌውን ሰው አስወግዱት! ፀጋ ይብዛላችሁ!
ተወዳጆች ሌሎችም መንፈሳዊ መልእክቶች ለማግኘት ቻናሌን ተቀላቀሉ👇
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfGod
@TheDeepThingsOfGod
1 810
የጌታዬ ድል የእኔም የባሪያው ድል ነው!🔥
ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀሉ በሰይጣን ላይ የተቀዳጀው ፍጹም፣ ዘላቂና የማይቀለበስ ድል በእርሱ የሚያምኑ ሰዎችም ሁሉ የተቀዳጁት ድል ነው።
ወዳጆቼ ሰይጣን ለዘላለም ተሸንፏል!😁
@TheDeepThingsOfGod
@TheDeepThingsOfGod
1 810
መታዘዝ- ዓመጻን መጥላት ነው~ አለመታዘዝ - ዓመጽ ነው።
የመጀመሪያው ኃጢአት/Original Sin/ ዓመጽ (አለመታዘዝ) ነበር። ለዚህ ነው እግዚአብሔር ከሰዎች የሚፈልገው አንዱ ትልቅ ነገር ሰዎች ዓመጻን እንዲጠሉ ወይም እንዲታዘዙ ነው---“እሺ ብትሉ ለእኔም ብትታዘዙ፥ የምድርን በረከት ትበላላችሁ፤”
— ኢሳይያስ 1፥19
ፊተኛው አዳም በመጀመሪያ ምድርን እንዲገዛ እግዚአብሔር ሰጥቶ ነበር ነገር ግን ከእግዚአብሔር ከተቀበለው ምድርን የመገዛት ስልጣንና ሃይል የተለያየው አመጸኛ /የማይታዘዝ/ ከሆነ በኋላ ነው።
በእስራኤል ታሪክ ውስጥ በእግዚአብሔር ተቀብተው እግዚአብሔርን እና ሕዝቡን ለማገልገል የተነሱ መሳፍንትም ነገስታትም የእግዚአብሔርን ቅባት ያጡበት ትልቁ ምክንያት አመጽ/አለመታዘዝ/ ነበር።
የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስም በዚህ መታዘዝ ወይም ዓመጻን በመጥላቱ ምክንያት ነው እግዚአብሔር የቀባው: እንዲህ ተብሎ ተጽፏልና “ጽድቅን ወደድህ ዓመፅንም ጠላህ፤ ስለዚህ እግዚአብሔር አምላክህ ከጓደኞችህ ይልቅ በደስታ ዘይት ቀባህ ይላል።”
— ዕብራውያን 1፥9
ከወዳጆቻችሁ ሁሉ በላይ እግዚአብሔር እንዲቀባችሁ ከፈለጋችሁ ከመጸለይ እኩል መታዘዝን ተማሩ! ዓመጻን ተጸየፉ።
@TheDeepThingsOfGod
1 810
ለጥያቄ የተሰጠ መልስ!
የውርስ ኃጢአት ማለት ምን ማለት ነው? ኃጢአትስ ይወረሳል እንዴ?
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfGod
@TheDeepThingsOfGod
1 810
ሰላም የተወደዳችሁ!
ጥያቄ ልጠይቃችሁ: ብዙ ጊዜ ሰዎች የውርስ ኃጢአት እያሉ ሲናገሩ ሰምታችኋል! የውርስ ኃጢአት ማለት ምን ማለት ነው?
መልሳችሁን Comment አድርጉ ወይም በ inboxላክልኝ?
ፀጋ ይብዛላችሁ!
1 810
ለምን ሰዎች ሁሉ ይሞታሉ? ዓለም በጥበቧ መቼም መልስና መፍትሔ መስጠት የማትችለው ጥያቄ ነው። ሞት መንፈሳዊ እንጂ ሳይንሳዊ መፍትሔ የለውም።
ሞት ወደ ሰዎች ሁሉ የደረሰበት መንገድ ኃጢአት ይባላል። ከኃጢአት ሃይል ነጻ ያልወጣ ሰው ከሞት ወጥመድ ማምለጥ አይቻለውም። ከኃጢአት ሃይል ደግሞ ነጻ መውጣት የሚቻለው እውነትን ወይም ኢየሱስ ክርስቶስን፣ ያስተማረውን እና ያደረገውን በማወቅና አምኖ በመቀበል ነው።
አንድ ጊዜ በኃጢአት ምክንያት ከሞተ በኃላ በሦስተኛው ቀን ከሙታን የተነሳውና ለዘላለም ሕያው የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እርሱን መቀበልና በስሙም ማመን ሰዎች በሕይወት ዘመናቸው ማድረግ የሚችሉት እግዚአብሔርም ከሰዎች የሚፈልገው ታላቅ ስራ ነው።
“በእኔ የሚኖር፣ የሚያምንብኝም ከቶ አይሞትም፤ ይህን ታምኛለሽን?””
— ዮሐንስ 11፥26 (አዲሱ መ.ት)
@TheDeepThingsOfGod
1 810
የሮሜ ጥናት 5፥12-21
በአዳምና በኢየሱስ ክርስቶስ መካከል ያለው ልዩነት እና ተመሳሳይነት በንጽጽር ~ ደረጃ ሰባት
ለጥያቄ @GFI777
@TheDeepThingsOfGod
@TheDeepThingsOfGod
@TheDeepThingsOfGod
1 810
እግዚአብሔርን ማወቅ ቅድሚያ የምትሰጠው ጉዳይ ይሁን!
Make knowing God your priority!
“በመንገድህ ሁሉ እርሱን ዕወቅ፤ እርሱም ጐዳናህን ቀና ያደርገዋል።”
— ምሳሌ 3፥6 (አዲሱ መ.ት)
“In all your ways know, recognize, and acknowledge Him, and He will direct and make straight and plain your paths.”
— Prov 3፥6 (AMP)
1 810
ግጥም ...😍
#ድል_በድል
(ድ)ል የተደረገ: እድለኛ
(ል)ቤ ነበረ: እምቢተኛ
(በ)ፍቅር የዳነ: ህመምተኛ
(ድ)ግስ ነጋሪ: ሆነ ተረኛ
(ል)ዑል የማረከው:ምርኮኛ!!
.
.
.
ራእይ 19 (Revelation)
9፤ እርሱም፡— ወደ በጉ ሰርግ እራት የተጠሩ ብፁዓን ናቸው፡ ብለህ ጻፍ፡ አለኝ። ደግሞም፡— ይህ የእግዚአብሔር እውነተኛ ቃል ነው፡ አለኝ።
@TheDeepThingsOfGod
@TheDeepThingsOfGod
@TheDeepThingsOfGod
