fa
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

رفتن به کانال در Telegram

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

نمایش بیشتر
1 810
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
የሮሜ መጽሐፍ ጥናት ~ በወንጌል የተገኘው ጽድቅ እና ድህነት። ጥልቅ መንፈሳዊ ትምህርት! የእግዚአብሔር ቃል ፈጽሞ ይለውጣል። 👇👇👇ተቀላቀሉ👇👇👇 @TheDeepThingsOfGod @TheDee
የሮሜ መጽሐፍ ጥናት ~ በወንጌል የተገኘው ጽድቅ እና ድህነት። ጥልቅ መንፈሳዊ ትምህርት! የእግዚአብሔር ቃል ፈጽሞ ይለውጣል። 👇👇👇ተቀላቀሉ👇👇👇 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ሰላም የእግዚአብሔር ልጆች! ወዳጆቼ በተደጋጋሚ የሮሜ ጥናት እና ሌሎችም በዚህ ቻናል የምሰጠው አገልግሎት እንዲቀጥል ጠይቃችሁኛል! አንዳንዶቻችሁ ስትጸልዩልኝም እንደነበር አውቃለሁ ስለሁሉም አመሰግናለሁ! እጅግ በጣም አመሰግናለሁ! በዚህ ቻናል በኩል የምሰጠውን አገልግሎት እንደገና በብዙ ሃይል እና መረዳት እቀጥላለሁ። የእግዚአብሔር ልጆች በመንፈስ ቅዱስ ሃይል በርቱ! እግዚአብሔር በእናንተ ለማድረግ ያቀደውን መለወጥ የሚችል ምንም እና ማንም የለም! እወዳችኋለሁ!❤

አባት ሆይ😭 ከአገልግሎት በላይ ኢየሱስን እፈልገዋለሁ! ከብዙ ተከታዮች በላይ ኢየሱስን እፈልገዋለሁ! ተጽዕኖ ፈጣሪ ከመሆን በላይ ኢየሱስን እፈልገዋለሁ! ከመውደድ በላይ ኢየሱስን እፈልገዋለሁ! በዓለም ሁሉ እየዞሩ ከማገልገል በላይ ኢየሱስን እፈልገዋለሁ! ከማስተማር እና ተዓምራት ከማድረግ በላይ ኢየሱስን እፈልገዋለሁ! ታላቅ ሰው ከመሆን በላይ ኢየሱስን እፈልገዋለሁ! የእግዚአብሔር ሰው ከመባል በላይ ኢየሱስን እፈልገዋለሁ! ዘመኔን በብልጽግና መጨረስ ከምፈልገው በላይ ኢየሱስን እፈልገዋለሁ! ከሁሉም በላይ ኢየሱስ ያስፈልገኛል እኔም እፈልገዋለሁ!😭 ልሰማው፣ ለየው፣ ልመለከተው እና ልደስሰው እፈልጋለሁ! መንፈስ ቅዱስ እባክህ ኢየሱስን አሳየኝ😭

መንፈስ ቅዱስ ሆይ እባክህ እንደገና ኢየሱስን አሳየኝ😭

Consider the work of calvary a perfect work, perfect in every aspect perfect in every respect! ፍጹም፣ በሁሉም በኩል ፍጹም የሆነውን የቀራንዮ
Consider the work of calvary a perfect work, perfect in every aspect perfect in every respect! ፍጹም፣ በሁሉም በኩል ፍጹም የሆነውን የቀራንዮ ስራ ተመልከቱ።

ራሳችሁን ካዱና ጌታን ተከተሉ! ሰይጣን ወይም እስትንፋሱ በአፍንጫው ያለች የትኛውም ሰው እግዚአብሔር ለእናንተ ያለውን እቅድ መለወጥ አይችልም፣ ከእግዚአብሔር እቅድ ልያስቀራችሁ የሚችለው ብቸኛው አካል እራሳችሁ ናችሁ። @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ወዴት ነው እየሄዱ ያሉት? የዓለም የጤና ድርጅት (WHO) Global VAXPORR የተሰኘ በዓለም ሁሉ ተግባራዊ የሚደረግ ፓስፖርት እና Digital ID በማበልጸግ ላይ ነው። ይሄ ምን ትርጉም አለው
ወዴት ነው እየሄዱ ያሉት? የዓለም የጤና ድርጅት (WHO) Global VAXPORR የተሰኘ በዓለም ሁሉ ተግባራዊ የሚደረግ ፓስፖርት እና Digital ID በማበልጸግ ላይ ነው። ይሄ ምን ትርጉም አለው? ይሄንን ችግር ፈቺ ነው የተባለውን Digital ID እና ክትባት በሰውነቱ ውስጥ ያልተቀበለ የትኛውም ሰዉ ከቦታ ወደ ቦታ መዘዋወር እና ስራውን መስራት የማይችልበት ሁኔታ ይፈጠራል ማለት ነው፣ ይሄ ወዴት እያመራ ነው? 👇 ራእይ 13 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁷ የአውሬውም ስም ወይም የስሙ ቍጥር ያለው ምልክት የሌለበት ማንም ሊገዛ ወይም ሊሸጥ እንዳይችል ያደርጋል። ጥበብ በዚህ አለ። ተዘጋጁ! @TheDeepThingsOfGod

እንደ ሐዋሪያው ቅዱስ ጳውሎስ የማሰብ አቅም ያለው ሰው እስከ ዛሬ ድረስ አላየሁም ወደፊትም የሚገኝ አይመስለኝም። ሮሜ 5፥12-21 ድረስ ያለውን ለመረዳት ወራት ፈጅቶብኛል ነገር ግን አሁንም እንዳልያዝኩት ይሰማኛል። የጥበብና የመገለጥ መንፈስ የሆንከው መንፈስ ቅዱስ ሆይ እባክህ እርዳኝ።

አዳም እንዴት የኢየሱስ አምሳል ይሆናል? መጽሐፍ ቅዱስ አዳም የኢየሱስ ክርስቶስ አምሳል (Pattern) እንደሆነ በግልጽ ቃል ይናገራል። እንዴት? አዳም ከእግዚአብሔር አንድ ትዕዛዝ ነበር የተቀበለው፥ ይህም ትዕዛዝ "አትብላ" የሚል ተጻራሪ ትዕዛዝ ነበር። ነገር ግን አዳም ይህችን አንድ ትዕዛዝ በመተላለፉ ኃጢአት ወደ ዓለም ገባ፣ ሞትም በኃጢአት በኩል። አዳም በሰራው ያለመታዘዝ ስራ እንደ አዳም ሕግን በመጣስ ኃጢአት ባልሰሩት የእርሱ ልጆች ሁሉ ላይ እስከ ሙሴ ድረስ ሞት ንጉስ ሆነ። እንዴት ነው እስከ ሙሴ ድረስ የነበሩት የአዳም ልጆች(እስከ ሙሴ ድረስ የነበሩ ሰዎች ሁሉ) እንደ አዳም ሕግን በመጣስ ኃጢአት አልሰሩም ማለት የምንችለው? እያልን ያለው "ኃጢአት አልሰሩም አይደለም" ነገር ግን እንደ አዳም ትዕዛዝን በመተላለፍ ኃጢአት አልሰሩም ነው። እንዴት? ምክንያቱም አዳም ትዕዛዝ ተሰጥቶት ነበረ፥ ከአዳም በኋላ እስከ ሙሴ ድረስ ግን ለሰዎች የተሰጠ አንድም ትዕዛዝ አልነበረም፥ ሕግ ወይም ትዕዛዝ በሌለበት ደግሞ ኃጢአት አይቆጠርም። ይህ ማለት ከአዳም በኋላ እስከ ሙሴ ድረስ እግዚአብሔር ኃጢአትን አይቆጥርም ነበር ማለት ነው፣ ይህ ማለት ግን ከአዳም በኋላ እስከ ሙሴ ድረስ በዓለም ኃጢአት አልነበረም ማለት አይደለም። ኃጢአት በአዳም በኩል ወደ ዓለም ስለገባ በዓለም ነበር ነገር ግን ምንም አይነት ትዕዛዝ ወይም ሕግ ስላልነበረ አይቆጠርም ነበር። ይሁን እንጂ እንደ አዳም ትዕዛዝን በመተላለፍ ኃጢአት ባልሰሩት ሁሉ ላይ እስከ ሙሴ ድረስ ሞት ነገሰ። አሁን አዳም እንዴት የኢየሱስ ምሳሌ እንደሆነ ግልጽ እንደሚሆንላችሁ አምናለሁ። 1- ለአዳም አንድ ትዕዛዝ እንደተሰጠው ለኢየሱስ አንድ ትዕዛዝ ነው የተሰጠው፣ አዳም ባለመታዘዝ ኃጢአት ወደ ዓለም እንዲገባ፣ በኃጢአት ሞት ወደ ሰዎች ሁሉ ያመጣ ቢሆንም ኢየሱስ ግን በመታዘዝ ጽድቅ ወደ ዓለም እንዲገባ፣ ይህንን የፀጋ ስጦታና የእግዚአብሔር ጽድቅ የሚቀበሉ በሕይወት እንዲነግሱ አድርጓል። 2-በአዳም አንድ ያለመታዘዝ ስራ እንደ አዳም ትዕዛዝን በመጣስ ኃጢአት ባልሰሩት ሁሉ ላይ ሞት እንደ ነገሰ፣ በኢየሱስ አንድ የጽድቅ ስራ ምንም የጽድቅ ስራ ባልሰሩት ሁሉ ላይ ጽድቅ በፀጋ ይነግሳል፣ እነርሱም በሕይወት ይነግሳሉ። ከሮሜ መጽሐፍ ጥናት ከሰባተኛው ደረጃ ትምህርት የተወሰደ---ሮሜ 5፥12-14---። ወንድሞቼና እህቶቼ በዚህ ክፍል ሐዋሪያው ቅዱስ ጳውሎስ ለመረዳት የሚያስቸግር አመክንዮ(Logic) በመጠቀም በአዳም እና በኢየሱስ መካከል ያለውን ምስስሎሽ ያስረዳል፣ ለመረዳት አስቸጋሪ ከሆነባችሁ ተስፋ አትቁረጡ በጸሎት እና በዝግታ ደጋግማችሁ ተመልከቱ፥ የእግዚአብሔር ፀጋ ከመንፈሳችሁ ጋር ይሁን። @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

Let us prepare by his grace!❤ በፀጋው እንዘጋጅ! ኢየሱስ ክርስቶስ የተዘጋጁትን ለመውሰድ ተመልሶ ይመጣል።
Let us prepare by his grace!❤ በፀጋው እንዘጋጅ! ኢየሱስ ክርስቶስ የተዘጋጁትን ለመውሰድ ተመልሶ ይመጣል።

አቃቂ በሰቃ መከነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ላይ ከአምስት መቶ የሚበልጡ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ጥቃት አድርሰው እንደዚህ አድርገዋል ትልቅ ዋጋ አሏቸው ያሏቸውን መገልገያ እቃዎች ዘርፈው እና የተ
+5
አቃቂ በሰቃ መከነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ላይ ከአምስት መቶ የሚበልጡ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ጥቃት አድርሰው እንደዚህ አድርገዋል ትልቅ ዋጋ አሏቸው ያሏቸውን መገልገያ እቃዎች ዘርፈው እና የተረፈውን አውድመው ሄደዋል። መሰብሰብያ አዳራሽና መገልገያ እቃዎች ማውደም ይቻል ይሆናል ቅዱሳንን ግን ማስቆም ወንጌልን ማጥፋት አይቻልም። በጣም የሚገርመው ጾም ላይ ነን እያሉ የክርስቶስ ቤተክርስቲያንን ለማፍረስ መንቀሳቀስ እቃ ማውደም ፍጹም ተገላቢጦሽ ነው። አጋንንታዊ እና ስጋዊ እንቅስቃሴ ነው፥ ነገር ግን ቤተክርስቲያን እንደ ጠንካራ ዓለት ናት የሚወድቁበት ሁሉ ይደቃሉ የምትወድቅባቸውን ሁሉ ደግሞ ትፈጫለች። በቅርቡ በዚህ ስፍራ ላይ ቤተክርስቲያን ከበፊቱ በርትታ ትጸናለች!

👇👇👇👇👇👇👇 ከ እኛ በፊት ብዙ አሉ 👇👇👇 https://t.me/Jesus_kingdom https://t.me/Jesus_kingdom https://t.me/Jesus_kingdom

ቀደምት ሐዋሪያት አባቶች ዓለምን እንዳወኩ እና እንደገለባበጡ ቅዱሱ መጽሐፍ ይነግረናል አሁን ግን ዓለም ቤተክርስቲያንን እያወከች እና እየገለባበጠች ነው። ያጣነው ነገር እንዳለ ግልጽ ነው! ቀደምት ቅዱሳን ሐዋሪያት የነበራቸው ነገር ግን እኛ ያጣነው ነገር እንዳለ ግልጽ ነው። መዝሙር 7 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁶ እግዚአብሔር ሆይ፤ በመዓትህ ተነሥ፤ በቍጣ በተነሡብኝ ላይ ተነሥ፤ አምላኬ ሆይ፤ ንቃ፤ ትእዛዝም አስተላልፍ! ⁷ የሕዝቦች ጉባኤ ይክበብህ፤ አንተም ከላይ ሆነህ ግዛቸው፤ ⁸ እግዚአብሔር በሕዝቦች ላይ ይፈርዳል። @TheDeepThingsOfGod

#አሁንም #አልረፈደም ከማን ጋር በቅርበት እንደምትቆዩ በጥንቃቄ ምረጡ፥ የሕልውና ጉዳይ ነው። “ከጠቢባን ጋር የሚሄድ ጠቢብ ይሆናል፤ የሰነፎች ባልንጀራ ግን ክፉ መከራን ይቀበላል።” — ምሳሌ 13፥
#አሁንም #አልረፈደም ከማን ጋር በቅርበት እንደምትቆዩ በጥንቃቄ ምረጡ፥ የሕልውና ጉዳይ ነው። “ከጠቢባን ጋር የሚሄድ ጠቢብ ይሆናል፤ የሰነፎች ባልንጀራ ግን ክፉ መከራን ይቀበላል።” — ምሳሌ 13፥20 @TheDeepThingsOfGod

Pastor Benny Hinn sings "As the Deer"😭 This song is full of anointing🙌 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

አልረፈደም! ገና ማለዳ ነው! ያለፈውን ድላችሁንም ሽንፈታችሁንም እርሱ! ትላንትን እርሱ! የሰይጣንን ኩነኔ አትስሙ! እንደገና ከእግዚአብሔር ጋር ጀምሩ! አልረፈደም! እመኑኝ እግዚአብሔር የተናገራችሁን ሁሉ አንድም ሳይቀር ይፈጽመዋል እናንተም ከእርሱ ጋር ትሰራላችሁ።

ቀበሮ የቱንም ያህል እንቅልፋም ቢሆን በአንበሳ መንገድ ላይ የመተኛትን ስህተት አይሰራም። በአንበሳ መንገድ ላይ መተኛት ማለት በአንበሳ ሆድ ውስጥ መንቃት ማለት እንደሆነ ጠንቅቆ ያውቀዋል።😂 የይሁዳ አንበሳ የሆነው የኢየሱስ ክርስቶስ ወንድሞችና እህቶች እናንተም አንበሳ ናችሁ፥ እግዚአብሔር ወዳዘጋጀላችሁ ግብ በሚወስዳችሁ መንገድ ላይ የተኛ የትኛውም ማሰብ የተሳነው ቀበሮ አጋንንት፥ ጠንቋይ፥ ሟርተኛ፥ የሰይጣን ኤጀንት የሆነ ሰው... ትልቅ ስህተት እንደሰራ አሳዩት። ማንም እና ምንም ከግባችሁ እንዲያስቀራችሁ አትፈቀዱለት! መልካም የውጊያ ቀን! @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

እራሳችሁን ለኢየሱስ ክርስቶስ አሳልፋችሁ ስትሰጡ ክርስትናን ያለ ትግል መኖር ትጀምራላችሁ። If you surrender to Jesus Christ, you can live Christianity without struggle. To surrender means: to stop resisting the Grace of God, to give up on your natural strength and to submit to the authority of the Lord.

ሚስጥር! “ስለ ወንዶችና ስለ ሴቶች ልጆቻቸው የሕዝቡ ሁሉ ልብ ተቈጥቶ ነበርና ሕዝቡ ሊወግሩት ስለ ተናገሩ ዳዊት እጅግ ተጨነቀ፤ ዳዊት ግን በአምላኩ በእግዚአብሔር ልቡን አበረታ።” — 1ኛ ሳሙኤል 30፥6 ከላይ ያለው የመጽሐፍ ክፍል በአንድ ወቅት ንጉሥ ዳዊት ዙሪያው ላይ እየተፈጠሩ በሉ ነገሮች እንዴት እንደተጨነቀ ይነግረናል፥ ነገር ግን በእንደዚህ አይነት መጨነቅ የነበረው ዳዊት ወዲያው እራሱን እንዳበረታ እናያለን። ይሄ እንዴት ይሆናል? እጅግ የተጨነቀ ሰው እንዴት እራሱን መበርታት ይችላል? ሚስጥሩ ይሄ ነው: ዳዊት የቱንም ያህል ቢጨነቅ የማይጨነቅ ክፍል አለው፥ የቱንም ያህል ወደታች ቢወድቅ የማይወድቅ እና ሁልጊዜ ከፍ እንዳለ የሚኖር ክፍል አለው፥ የተጨነቀዉን እና ወደታች ዝቅ የሚለውን ዳዊትን ማበረታታት የሚችል ክፍል አለው። ይሄንን ክፍሉን ጠንቅቆ ያውቀዋል እናም በእንደዚህ አይነት ጊዜ የተጨነቀውን የራሱን ክፍል ለመበረታታት ይጠቀምበታል። ተወዳጆች እናንተም ይሄንን ክፍላችሁን እንድታገኙ እመክራችኋለሁ፥ የማይጨነቀውን እናንተን! ይሄም በክርስቶስ ኢየሱስ ያላችሁ ማንነት ነው። "ዳዊት ግን በአምላኩ በእግዚአብሔር ልቡን አበረታ"። ይሄንን ስታውቁ በምንም አይነት ሁኔታ ውስጥ ብትሆኑ እራሳችሁን ለማበረታታት እና ለመቀጠል ሃይል ይኖራችኋል። #በክርስቶስ#እራሳችሁን#አግኙ #እራሳችሁን#አበረቱ #ተባርካችኋል! @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

PowerfulSecret! “And David was greatly distressed; for the people spake of stoning him, because the soul of all the people was grieved, every man for his sons and for his daughters: but David encouraged himself in the LORD his God.” — 1 Samuel 30፥6 (KJV) The scripture above tells us how king David was distressed at some point because of his surrounding, but immediately in the midst of all his distress, he encouraged himself! Oh, wow! How can a distressed Man encourage himself? This is the Secret: No matter how down he drops he has part of him that will never go down, part of him that will never get distressed, part of him that can encourage the discouraged and the distressed! He knows it, and in times like this he uses that part to encourage part of him that gets distressed. Beloveds find the part of you that never gets discouraged, which is your identity in God. When you find it, no matter the surrounding and your condition, you will still have power to encourage yourself! Find who you are in Christ! #YouAreBlessed! #YouAreVictor! #YouAreHisMember #YouArePriestlyKing #YouAreHisElect #YouAlwaysWin! #EncourageYourself!