fa
Feedback
Estifanos Getahun

Estifanos Getahun

رفتن به کانال در Telegram
1 079
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-47 روز
-1730 روز
آرشیو پست ها
photo content
+2

ዛሬ 26 ሺህ ቤቶችን ለአገራችን የመጀመሪያ በሆነ የግንባታ ቴክሎጂ በላፍቶ ሳይት ስራ አስጀምረናል። በዚህ ዓመት ከያዝናቸው ዋነኛ እቅዶች መካከል ቀዳሚው ለከተማችን ነዋሪዎች የቤት አቅርቦትን ተደራሽ ማድረግ ነው። በመሆኑም በዚህ ዓመት ከ100 ሺህ በላይ ቤቶችን ለመገንባት አቅደን በርካታ ተግባራትን እያከናወንን ሲሆን፣ እቅዳችንን በጥራትና በፍጥነትን እውን ለማድረግ ለአገራችን የመጀመሪያ የሆነውን Cold-Formed Steel (CFS) የግንባታ ቴክኖሎጂን መጠቀም አንድ አማራጭ አድርገን ዛሬ ስራ አስጀምረናል። ይህ ቴክኖሎጂ በሌላው ዓለም የተለመደ ሲሆን፣ ቤቶችንም ሆነ ህንፃዎችን በፋብሪካ ውስጥ የሚገጣጠሙ ብረቶችን በመጠቀም ወለልን፣ ግድግዳና ጣሪያን ጨምሮ ሁሉንም ክፍል በፍጥነትና በጥራት ማምረት የሚያስችል አሰራር ነው። የዚህን የቴክኖሎጂ ፋብሪካ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለከተማ የተከልን ሲሆን፣ በፈጠራና ፍጥነት መርህ ግንባታን ከሳይት ወደ ፋብሪካ በመቀየር የግንባታ ፍጥነትን በማሳደግ፣ ወጪን በመቀነስና ጥራትን በማሻሻል አንጻር ተመራጭ ነው። አስተዳደራችን እንደወትሮው የነዋሪውን ጥያቄ ለመመለስ እና ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥ በጠንካራ የፕሮጀክት ማኔጅመንት፣ ዲስፕሊን እና በ24/7 የስራ መርሃ ግብር ፕሮጀክቱ በጥራትና በፍጥነት ተጠናቅቆ ለታለመለት አላማ እንዲውል ያደርጋል። ይህን ከከተማችን አልፎ ለአገር ጠቃሚ የሆነ ቴክኖሎጂን ወደ አገር ይዘዉ የመጡትን የሌጋሲ ሆም ድርጅት ባለቤት ኢንጂነር ያሬድ አፈወርቅን በራሴና በከተማ አስተዳደሩ ስም አመሰግናለሁ ። ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ ክቦርት ከንቲባ አዴ አዳነች አቤቤ

photo content
+6

photo content
+9

photo content
+9

በአንድ መድረክ አራት ሽልማቶችን ያሸነፈው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ***** የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ አየር መንገዶች ማህበር (AFRAA) 57ኛ አመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ በአራት ዘርፎች አሸናፊ ሆኗል። ማህበሩ በአንጎላ ሉዋንዳ ባዘጋጀው ዓመታዊ የእውቅና መድረክ ላይ ነው ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ሽልማቶቹን ያበረከተው።   በዚህም አየር መንገዱ በዓለም አቀፍ ስራዎች ትርፋማነት የ2024 ምርጥ አየር መንገድ እውቅናን ሲያገኝ፤ አፍሪካን በአየር ትራንስፖርት በማገናኘት የላቀ አገልግሎት በመስጠትም ማሸነፍ ችሏል፡፡ አየር መንገዱ ለአፍሪካ አቪዬሽን ኢንዱስትሪ እድገት ላበረከተው ከፍተኛ አስተዋጽኦ፤ የላቀ አገልግሎት በመስጠት ዘርፍም አሸንፏል። እንዲሁም የአፍሪካ ህብረት በአህጉሪቱ ነፃ የአየር ትራንስፖርት እውን ለማድረግ ለያዘው ፕሮጀክት የላቀ አስተዋጽኦ በማድረጉም አየር መንገዱ ተሸላሚ መሆን ችሏል። በአፍሪካ ከ60 በላይ በዓለም ከ145 በላይ መዳረሻዎች ያሉት የኢትዮጵያ አየር መንገድ፤ አፍሪካን በአየር ትራንስፖርት በመገናኘት የአንበሳውን ድርሻ ይዟል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያገኘው እውቅና የፓን አፍሪካን እሴቶች መጠናከር የሰጠውን ትኩረት ከማሳየቱም በላይ የተቋሙ ሰራተኞች ቁርጠኝነትና ትጋት ውጤት መሆኑን የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መሥፍን ጣሰው ገልፀዋል። አየር መንገዱ ለቀጠናዊ ትስስርና እንዲሁም ለዘርፉ እድገት እያደረገ ያለውን አስተዋፅኦ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቋልአስታውቋል።

photo content
+5

Baay’isuu: Muuxannoowwan gaggaarii fi milkaahinoota argaman karaa qindaa’een babal’isuu;

photo content

"ሚናን ለይቶ ለመፍትሔ መቆም ሰላምን ያረጋግጣል" ምክትል ርእሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ.ር)

photo content

የሁለት ሰዎችን ህይወት አጥፍቶ የተሰወረን ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፡፡ *** አዲስ አበባ፤ ህዳር 23 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፡- የወንጀል ድርጊቱ የተፈጸመው ህዳር 04 እና 05 ቀን 2018 ዓ/ም በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 06 ልዩ ቦታው 23 ቀበሌ መዝናናኛ ክበብ አካባቢ ነው፡፡ ተከሳሽ እሱ ያውቃል ቢያዝን ከባለቤቱ ከወ/ሮ ሐመልማል አለምነህ ጋር በትዳር ተጣምረው መኖር ከጀመሩ አራት ወራትን አስቆጥረዋል፡፡ ተከሳሽ ከባለቤቱ ጋር በኪራይ ከሚኖሩበት ቤት ህዳር 04 ቀን 2018 ዓ/ም ከጠዋቱ 4፡00 ሠዓት ሲሆን ከሌላ ወንድ ጋር ስልክ ትደዋወያለሽ በሚል ቂም በቀል በመነሳሳት ሟችን አንገቷን በማነቅ ህይወቷ እንዲያልፍ በማድረግ በር ዘግቶባት ከአካባቢው ለጊዜው ይሰወራል፡፡ ተከሳሹ በዚሁ ብቻ አላባቃም ከአንድ ቀን በኋላ ህዳር 05 ቀን 2018 ዓ/ም ባለቤቱን ከገደለበት መኖሪያ ግቢ ተመልሶ በመምጣት ከእዚህ ቀደም ከባለቤቱ ጋር በሚፈጠረው ፀብ ያሸማግል የነበረን አለባቸው አየለ የተባለን ጎረቤቱን በሟች ባለቤቱ ይጠረጥረው ነበርና መሳሪያ በመተኮስ በስምንት ጥይት ህይወቱ እንዲያልፍ በማድረግ ከአካባቢው ሊሰወርም ችሏል፡፡ የወንጀሉ መፈፀም መረጃ የደረሰው የአዲስ አበባ ፖሊስ የወንጀል ምርመራና ክትትል ክፍሉ የወንጀል ስፍራው ላይ በመገኘት የሟች አለባቸው አየለን አስከሬን በማንሳትና ከአካባቢው በሰበሰበው መረጃ መነሻነት የሟች መኖሪያ ቤት ሲከፈት የሐመልማል አለምነህ አስከሬን ሊገኝም ችሏል፡፡ ፖሊስ ከወንጀሉ መፈፀም በመነሳት ተገቢውን የሰውና የኤሌክትሮኒክስ መረጃዎችን በመከታተል ተጠርጣሪውን ህዳር 18 ቀን 2018 ዓ/ም ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሰሜን ሸዋ ዞን ሞላሌ ከተማ ከተደበቀበት መኖሪያ ቤት የግድያ ወንጀሉን ከፈፀመበት መሳሪያ ጋር በቁጥጥር ስር ሊያውልም ችሏል፡፡

photo content
+9

እንኳን ደስ አለን! በእግር ኳስ ስፖርት የጀመርነው ፕሮጀክት ፍሬ በማፍራት ላይ ነው። ዛሬ በመዲናችን አዲስ አበባ ሲካሄድ በነበረው የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ አገራት ከ17 ዓመት በታች ውድድር፣ ብሔራዊ ቡድባችን የኬንያ አቻውን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት በመርታት ከ 22 ዓመታት በኋላ ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፍ ችሏል። ይህ ድል የእግር ኳስ ስፖርት ወዳድ ለሆነው ህዝባችን የዘመናት ቁጭት በቅርቡ መልስ እንደሚያገኝ ያሳየ ነው። ቀይ ቀበሮዎቹ ያስመዘገቡት ውጤት ለዘርፉ የሰጠነው ትኩረት ውጤት እያፈራ መሆኑን ማሳያ ነው። በራሴና በከተማ አስተዳደሩ ስም መላው የቡድኑ አባላትን፣ የኢትዮዽያን ሕዝብ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እወዳለሁ። ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ! via - ክብርት ከንቲባ አዴ አዳነች አቤቤ

photo content
+3

ኢትዮጵያ ከ22 ዓመት በኋላ ለአፍሪካ ዋንጫ አለፈች ከ17 ዓመት በታች የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ኬንያን በማሸነፍ ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፉን አረጋግጧል። ዛሬ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተደረገው የደረጃ ጨዋታ የኢትዮጵያ ወጣት ቡድን የኬንያ አቻውን 3 ለ 0 በማሸነፍ ነው ከሁለት አስርት ዓመታት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ የተመለሰው። ዳዊት ካሳው ቢኒያም አብርሃ እና ብሩክ እይላቸው የኢትዮጵያን ግቦች አስቆጥረዋል። ወጣቱ አጥቂ ዳዊት ካሳው በአጠቃላይ ስምንት ግቦችን በማስቆጠር  ውድድሩን አጠናቋል። በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት ሲካሄድ የቆየው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የሴካፋ ውድድር ዛሬ ፍጻሜውን የሚያገኝ ሲሆን ዩጋንዳ እና ታንዛኒያ ለዋንጫ የሚጫወቱ ይሆናል።

photo content

ስድስቱ 100 % እንዲሳኩ የሚጠበቁ ተግባራት 🎉🎉🎉

photo content

“አንድ አማፂ ስልጣን የያዘበትን እለት ማክበር ነውር ነው” - ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥ