fa
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

رفتن به کانال در Telegram

📈 تحلیل کانال تلگرام የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

کانال የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 14 309 مشترک است و جایگاه 6 161 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 365 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 14 309 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 21 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 502 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 16 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 48.88% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 13.10% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 0 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 875 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 0 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

توضیحی برای کانال ارائه نشده است.

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 22 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

14 309
مشترکین
+1624 ساعت
+1117 روز
+50230 روز
آرشیو پست ها
የሰንበት ትምህርት ቤቶች አገልግሎት በጊዜያዊ ስሜት ሳይሆን በበቂ እውቀት፣ ትህትናና በተላበሰ መልኩ በቤተክርስቲያን አስተምህሮ ላይ ሊመሠረት ይገባል ሲሉ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ተናገሩ። (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) ታኅሣሥ 14/04/ 2017 ዓ.ም የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ከማኅበረ ቅዱሳን ወልድያ ማእከል ጋር በመተባበር ከሁሉም ወረዳዎች ለተውጣጡ የወረዳ አብያተ ክህነት  የሰንበት ትምህርት ክፍል ኀላፊዎችና የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አመራሮች ከታኅሣሥ 12-13 ቀን 2017 ዓ.ም ሥልጠና ሰጥቷል። የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ብርሃን ፍሥሐ ጌታነህ ለሠልጣኞች ባስተላለፉት መልእክት የሰንበት ትምህርት ቤቶችን ለማጠናከር ከጠቅላይ ቤተክህነት ጀምሮ ትኩረት መሰጠቱን ጠቅሰው አዲስ የተዘጋጀውን የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት መዋቅራዊ አደረጃጀትና ሥርዓተ ትምህርት በሀገረ ስብከቱ ተግባራዊ ማድረግ ተጀምሯል ብለዋል። ዋና ሥራ አስኪያጁ አክለውም የአሠልጣኞች ሥልጠና የወሰዱ መምህራን ሥርዓተ ትምህርቱን ለማስተግበር በየወረዳው ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና እየሰጡ መሆኑን ገልጸዋል። የሀገረ ስብከቱ የ10 ዓመት መሪ እቅድ እንዲሳካ የሰንበት ትምህርት ቤቶች የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ታስቦ የተዘጋጀ መርሐ ግብር መሆኑንም  ተናግረዋል። ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በሥልጠናው ማጠቃለያ "ለዘለዓለም የሚያበረታኝና የሚያጸናኝ ትምህርት ነው" የሚለውን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ኀይለቃል መነሻ አድርገው በሰጡት አባታዊ መመሪያና ቃለ ምእዳን መማር፣ መጠየቅ፣  ክርስትናን አውቆ በተግባር መኖርና ተለውጦ ሌሎችንም ለመለወጥ ማገልገል ይገባል ብለዋል። የሰንበት ትምህርት ቤቶች አገልግሎት በጊዜያዊ ስሜት ሳይሆን በበቂ እውቀት፣ ትህትናን በተላበሰ መልኩ  በቤተክርስቲያን አስተምህሮ ላይ ሊመሠረት ይገባል ያሉት ብፁዕነታቸው የሥልጠናው ተሳታፊዎች እራሳቸውን ለውጠው ብዙዎችን መለወጥ እንዲችሉ አሳስበዋል። መዝሙር ትምህርት ብቻ ሳይሆን ጸሎትም ነው፤ አሁን አሁን የምናየውና የምንሰማው መዝሙር ግን መንፈሰ እግዚአብሔር የራቀው በመሆኑ በሰንበት ትምህርት ቤቶች ዙርያ የሚታዩ ክፍቶች  ሊስተካከሉ እንደሚገባ  አባታዊ መመሪያ አስተላልፈዋል። "አንድነት" እግዚአብሔር ከእኛ ጋር እንዲሆን ቁልፍ መንገድ በመሆኑ የቤተክርስቲያኗ መዋቅር ተከብሮ ሰበካ ጉባኤያት የሰንበት ትምህርት ቤቶችን መከታተል፣ መደገፍና መቆጣጠር የሰንበት ትምህርት ቤቶች ደግሞ ለመዋቅር ተገዥ በመሆን ግደታቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል ብፁዕነታቸው። ለመርሐ ግብሩ መሳካት አስተዋጽኦ ያበረከቱንም አመስግነዋል። በሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት አተገባበር ላይ ግንዛቤ ለመፍጠርና የሀገረ ስብከቱን የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ለማቋቋም ታስቦ በተዘጋጀው በዚሁ መርሐ ግብር በሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት መዋቅራዊ አደረጃጀት፣መሪነት፣ በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት አተገባበር እንዲሁም በእቅድና ሪፖርት አዘገጃጀት ላይ ሥልጠና መሰጠቱን የሀገረ ስብከቱ የሰንበት ትምህርት ዋና ክፍል ኀላፊ መምህር ኤርምያስ አዳነ ተናግረዋል። በመርሐ ግብሩ የወልድያ መንበረ ንግሥት ኪዳነ ምሕረት መሠረተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤትና የወልድያ ከተማ አስተዳደር ሰንበት ትሞህርት ቤቶች አንድነት የአገልግሎት ልምዳቸን ለተሳታፊዎች አካፍለዋል። የሰሜን ወሎ መንበረ ጵጵስና ሀገረ ስብከት ቤተክህነት 11 አባላት ያሉት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ሥራ አስፈጻሚ ጉባኤና ሦስት አባላት ያሉት የአፈጻጸም ክትትልና ቁጥጥር ጉባኤ አባላት ተመርጠዋል። የሥራ አስፈጻሚና የቁጥጥር ጉባኤ አባላቱ ለቀጣይ 3 ዓመታት የሚያገለግሉ ሲሆን በብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ቡራኬ የአገልግሎት አደራ ተቀብለዋል። ዘገባው የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ነው። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"እጅህን ከአርያም ላክ!" መዝ 143(144)፡7 ዘመነ ስብከት ሰናይ ሌሊት! መልካም ዕለተ ሰንበት! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶ
"እጅህን ከአርያም ላክ!" መዝ 143(144)፡7 ዘመነ ስብከት ሰናይ ሌሊት! መልካም ዕለተ ሰንበት! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"ቅድስትና ያለ ነውር ትሆን ዘንድ ክብርት የሆነችን ቤተ ክርስቲያን ለራሱ እንዲያቀርብ ፈለገ።" ኤፌ 5፡27 ሰናይ ሌሊት! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (
"ቅድስትና ያለ ነውር ትሆን ዘንድ ክብርት የሆነችን ቤተ ክርስቲያን ለራሱ እንዲያቀርብ ፈለገ።" ኤፌ 5፡27 ሰናይ ሌሊት! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"ጻድቃን በበዙ ጊዜ ሕዝብ ደስ ይለዋል።" ምሳ 29፡2 ታኅሣሥ 9 የስማቸው ትርጓሜ የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ እስትንፋስ አንድም የክርስቶስ እስትንፋስ የሆነ ጻድቁ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ የተ
"ጻድቃን በበዙ ጊዜ ሕዝብ ደስ ይለዋል።" ምሳ 29፡2 ታኅሣሥ 9 የስማቸው ትርጓሜ የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ እስትንፋስ አንድም የክርስቶስ እስትንፋስ የሆነ ጻድቁ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ የተወለዱበት ዓመታዊ ክብረ በዓል ነው! ሰናይ ሌሊት! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት መዋቅራዊ አደረጃጀት እና የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ ግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና አካሄደ። (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) ታኅሣሥ 07/04/2016 ዓ.ም የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት በቅዱስ ሲኖዶስ መመርያ ሰጭነት በሁሉም ሀገረ ስብከት በትግበራ ላይ የሚገኘውን የሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ምንነትና አተገባበር እንዲሁም የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት መዋቅራዊ አደረጃጀት ዙሪያ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ በተላኩ መምህራን የግንዛቤ መስጫ መርሐ ግብር አካሄደ። ሥልጠናውን በሀገረ ስብከቱ ለሚገኙ ከ20 ወረዳ ቤተክህነት የተውጣጡ የሰንበት ትምህርት ቤት አመራሮችና መምህራን ተሳትፈዋል። ሥልጠናው በሀገረ ስብከቱ መንበረ ጵጵስና ከተማ አርባ ምንጭ በሚገኘው ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤልና ደብረ መንክራት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ከታኅሣሥ 5-6 ተከናውኗል። በመርሐ ግብሩ የጋሞና አካባቢው ዞኖች እና ጎፋና ባስኬቶ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ኅሩያን ገሪማ ጌታነህ እንዲሁ መምህር ዲያቆን ዐባይነህ ጸጋዬ የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች ክፍል ሓላፊና የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ሰብሳቢ ተገኝተዋል። የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ ቤተ ክርስቲያን ያለችበትን ወቅታዊ ፈተና በመረዳት ሰልጣኞች በሰለጠኑበት ሥልጠና ፍሬን ለማየት ጥበብና ብልሀት ጥንቃቄ ያሻል ብለዋል። መርሐ ግብሩ በሀገረ ስብከቱ የሚገኙ አጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በሥርዓተ ትምህርቱ ትግበራ የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የሚያስችል ግንዛቤ የፈጠረ ነው። ያሉት የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ኃሩያን ገሪማ ጌታነህ ሀገረ ስብከቱ ሰንበት ትምህርት ቤቶችን በማጠናከርና ሥርዓተ ትምህርቱን በመተግበር ዙርያ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ይህን የስልጠና መድረክ እንዲዘጋጅ ማድረጋቸውን ተናግረዋል። የሀገረ ስብከቱ የሰንበት ትምህርት ቤት ክፍል ሓላፊ መምህር ዲያቆን አባይነህ ፀጋዮም በበኩላቸው በተሰጠው ሥልጠና በመጠቀም የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት መዋቅር በማጠናከር ለሥርዓተ ትምህርቱ ትግበራ ጠንካራ ሥራ እንደሚሰሩ ተናግረዋል። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በዐዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ለ4ኛ ጊዜ በ2016 ዓ.ም በሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የምዘና ፈተና የወሰዱ የ4ኛ ፣ የ6ኛ እና የ10ኛ ክፍል ተማሪዎች ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ  በተገኙበት የእውቅና እና የቡራኬ መርሐ ግብር ተከናወነ። (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) ታኅሣሥ 06/04/2016 ዓ.ም በዐዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ለ4ኛ ጊዜ በ2016 ዓ.ም በሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የምዘና ፈተና የወሰዱ ቁጥራቸው ከ6200 በላይ የሚሆኑ የ4ኛ ፣ የ6ኛ እና የ10ኛ ክፍል ተማሪዎችን ዛሬ ታኅሣሥ 06 2017 ዓ.ም በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔ ዓለም ወመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ወአቡነ አረጋዊ ካቴድራል ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትሪያሪክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ፤ ብፁዕ አቡነ ሔኖክ የዐዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፤ ብፁዐን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፤ ሊቀ ማዕምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ የዐዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ሐላፊዎች ፤ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አመራሮች ፣ ተማሪዎችና የተማሪ ወላጆች  በተገኙበት የእውቅና እና የቡራኬ መርሐ ግብሩ ተከናውኗል። በመርሐ ግብሩም ብፁዕ አቡነ ሔኖክ የዐዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ " ልጅህን በሚሔድበት መንገድ ምራው በሸመገለ ጊዜ ከሱ ፈቀቅ አይልም" የሚል አምላካዊ ቃልን መነሻ በማድረግ አባታዊ ምክር አስተላልፈዋል። በቅዱስነታቸው መልካም ፈቃድ የዕለቱን ቃለ እግዚአብሔር ያስተላለፉት ብፁዕ አቡነ ፊሊጶስ የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሀገረ ስብከት እና የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ሊቀ ጳጳስ "ይህንን እዘዝና አስተምር በቃልም በተግባርም በእምነትም ለሚያምኑ ምሳሌ ሁን እንጂ ማንም ታናሽነትህን አይናቀው።(1ኛ ጢሞ 4÷12) መነሻ በማድረግ " ማንም ታናሽነታቹሁን አይናቀው የቤተ ክርስቲያን ተተኪ ናችሁ ብለዋል። ሊቀ ማዕምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ የዐዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅም "ሰንበት ተማሪዎች ዋነኛ የቤተ ክርስቲያን ተተኪ መሆናቸው ታውቆ ከፍተኛ ክትትልና ድጋፍ እየተደረገላቸው ይገኛል፤ ሰንበት ተማሪው ከበዓል አድማቂነት ወጥቶ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት የሚያውቅና የሚጠብቅ እንዲሆን እንረባረባለን በተጨማሪም በከተማው የሚገኙ ወጣቶች ሁሉ በሰንበት ት/ቤቶች እስኪታቀፉ እንሠራለን።" በማለት የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። በመቀጠልም ላዕከ ኄራን መንክር ግርማ የዐዲስ አባ ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ተ/ም/ሰብሳቢ " ሥርዓተ ትምህርቱ ነገ ሀገርና ቤተ ክርስቲያን ተስፋ የምትጥልባቸውን ሕጻናትና ወጣቶች በኹለት በኩል የተሳሉ ሰይፍ እንዲሆኑ የሚሠራ ወጥነት ያለውና ነው። ሁሉም ሰንበት ት/ቤቶች ሊተገብሩት ይገባል ብለዋል። የታተሙትንና ስርጭት ላይ የሚገኙትን ከ1ኛ እስከ 4ኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍትንም ሰንበት ትምህርት ቤቶች ገዝተው ይጠቀሙ ዘንድ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል። ቡፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ "በዚህ ዕድሜያቹ የቤተ ክርስቲያን ሕግና ሥርዓት በማወቃቹ ለቤተ ክርስቲያን ዘብ መቆም የምትችሉ የቤተ ክርስቲያን የጀርባ አጥንት ናችሁ በሃይማኖት ጽኑ" በማለት አባታዊ ቡራኬና ቃለ ምዕዳን ሰጥተዋል። በመጨረሻም ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተመራቂ ተማሪዎች የሜዳልያ ሽልማት ምዘናውን ላስፈተኑ 119 ሰንበት ትምህርት ቤቶች እንዲሁም ለመርሐ ግብሩ መሳካት አስተዋጽዖ ላበረከቱ አካላት ከቅዱስነታቸው እጅ ቡራኬ ተቀብለዋል። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"እግዚአብሔር አጥንቶቻቸውን ሁሉ ይጠብቃል፥ ከእነርሱም አንድ አይሰበርም።" መዝ 34፥20 የቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያኗ የከበረችበት፣የሥጋዋ የፈለሰበት፤ ከእርሷ ጋር የተገደሉ የሃያ ሰባት ደናግልም
"እግዚአብሔር አጥንቶቻቸውን ሁሉ ይጠብቃል፥ ከእነርሱም አንድ አይሰበርም።" መዝ 34፥20 የቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያኗ የከበረችበት፣የሥጋዋ የፈለሰበት፤ ከእርሷ ጋር የተገደሉ የሃያ ሰባት ደናግልም የሥጋቸው የፈለሰበት ታኅሣሥ ፮ ቀን በታላቅ ድምቀት ይከበራል፡ እንኳን አደረሳችሁ! መልካም ዕለተ ሰንበት! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

እንኳን ለእመቤታችን ወደ መቅደስ የገባችበ በዓል (በዓታ ለማርያም) በሰላም አደረሳችሁ! “በመከራዬ ጊዜ በአፌ የተናገርሁትን ከንፈሮቼም ያሉትን ስእለቴን ለአንተ እፈጽማለሁ።” መዝ 65፡14 መልካም
እንኳን ለእመቤታችን ወደ መቅደስ የገባችበ በዓል (በዓታ ለማርያም) በሰላም አደረሳችሁ! “በመከራዬ ጊዜ በአፌ የተናገርሁትን ከንፈሮቼም ያሉትን ስእለቴን ለአንተ እፈጽማለሁ።” መዝ 65፡14 መልካም በዓል! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"አየዋለሁ፥ አሁን ግን አይደለም፤ እመለከተዋለሁ፥ በቅርብ ግን አይደለም፤ ከያዕቆብ ኮከብ ይወጣል" ዘኁ 24፡17 ሰናይ ሌሊት! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ
"አየዋለሁ፥ አሁን ግን አይደለም፤ እመለከተዋለሁ፥ በቅርብ ግን አይደለም፤ ከያዕቆብ ኮከብ ይወጣል" ዘኁ 24፡17 ሰናይ ሌሊት! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok