fa
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

رفتن به کانال در Telegram

📈 تحلیل کانال تلگرام የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

کانال የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 14 477 مشترک است و جایگاه 6 026 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 324 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 14 477 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 29 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 526 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 12 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 38.31% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 10.22% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 5 538 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 477 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 33 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

توضیحی برای کانال ارائه نشده است.

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 30 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

14 477
مشترکین
+1224 ساعت
+1357 روز
+52630 روز
آرشیو پست ها
የብፁዕ አቡነ ባስልዮስ እና የብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) ሥርዓተ ቀብር እሑድ መጋቢት 17 ቀን 2015 ዓ.ም በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እንደሚፈጸም የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ
+1
የብፁዕ አቡነ ባስልዮስ እና የብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) ሥርዓተ ቀብር እሑድ መጋቢት 17 ቀን 2015 ዓ.ም በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እንደሚፈጸም የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ( ዶ/ር ) ገለጹ፡፡

ዛሬ ምሽት 2፡00 ላይ በEOTC TV ፈለገ ጥበብ የቴሌቭዥን መርሐ ግብር ላይ ይጠብቁን! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmU
ዛሬ ምሽት 2፡00 ላይ በEOTC TV ፈለገ ጥበብ የቴሌቭዥን መርሐ ግብር ላይ ይጠብቁን! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg ✍️ Facebook 👇 http://facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/

ዛሬ ምሽት 2፡00 ላይ በEOTC TV ፈለገ ጥበብ የቴሌቭዥን መርሐ ግብር ላይ ይጠብቁን! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg                      ✍️ Facebook 👇 http://facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/

ደብረ ዘይት ደብረ ዘይት የተራራ ስም ሲሆን የወይራ ዛፍ በብዛት የሚገኝበት ተራራ ስለሆነ ደብረ ዘይት ተብሏል፡፡ (ደብር ማለት ተራራ ማለት ነው) ይህ ዕለት ለምን ይህንን ስያሜ አገኘ? ይህ ዕለት የጌታችን ዳግም መምጣት የሚታሰብበት ዕለት ሲሆን ይህንን ስያሜ ያገኘው ጌታችን በዚህ ተራራ ላይ ነገረ ምጽአቱን ስላስተማረበት ነው፡፡ ማቴ 24÷1-36፡፡ እንዲሁም ይህ ተራራ ከኢየሩሳሌም በስተምስራቅ በጥቂት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ ሲሆን ጌታችን ሲያርግ በዚህ ተራራ ላይ ደቀመዛሙርቱ እያዩት አርጓል፡፡ ሉቃ 24፡50፡፡ ዳግመኛም ለፍርድ ሲመጣ በዚሁ ተራራ ላይ ይገለጣል፡፡ ዘካ 14፡4 ዕለቱ ምን ይታሰብበታል? ዕለቱ የክርስቶስ ሁለተኛ መምጣት (ዳግም ምጽአት) የሚታሰብበት ነው፡፡ ሁለተኛ ሲመጣ ዓለምን ለማዳን ወይም መከራ ለመቀበል ሳይሆን ለፍርድ ነው፡፡ በመጀመሪያ ሲመጣ ብዙ መከራ ባጸኑበት ጊዜ ሁሉንም በዝምታ ነው የተቀበለው፡፡ ሲገረፍ፣ ሲቸነከር፣ ሲሰደብ፣ ምራቅ ሲተፋበት ሁሉ ዝም ነው ያለው፡፡ ኢሳ 53፡7 “በሸላቾቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ እንዲሁ አፉን አልከፈተም” እንዲል፡፡ አሁን ግን ሲመጣ ዝም አይልም ይናገራል፡፡ እንዲህም ይላል፦ ጻድቃንን እናንተ ያባቴ ብሩካን ወደእኔ ኑ፡፡ ኃጥአንን እናንተ ርጉማን ከእኔ ወግዱ ይላቸዋል፡፡ በዳግም ምጽአቱ ሲመጣ ዝም እንደማይል ቅዱስ ዳዊት እንዲህ ብሎ አረጋግጦልናል፡፡ “እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም እሳት በፊቱ ይነዳል” ብሎናል፡፡ የዕለቱ ስያሜ የፍርድ ቀን እንደመሆኑ በዚያን ቀን ፍርድ ብቻ ይሰጣል፡፡ ያን ጊዜ ልመና /ምልጃ/ አይኖርም፡፡ አምላካችን ለፍርድ መቼ ይመጣል? ይሄ ጥያቄ የሐዋርያትም ጥያቄ ነበረ ግን ክርስቶስ ይህንን ከአባት ከእግዚአብሔር /ከሥላሴ/ በቀር ማንም አያውቀውም ብሎ ነው መስል የሰጣቸው፡፡ ነገር ግን የሚመጣበትን ዕለቱን ባይነግራቸውም የመምጫው ጊዜ ሲደርስ የሚሆኑትን ምልክቶች ነግሯቸዋል፡፡ እንዲህም አላቸው፡፡ እኔ መምጫዬ ሲደርስ፦ − ብዙዎች እኔ ክርስቶስ ነኝ እያሉ በስሜ ይመጣሉ − የጦርነትን ወሬ በስፋት ትሰማላችሁ − ሕዝብ በሕዝብ ላይ መንግስትም በመንግስት ላይ ይነሳል − ረሃብ፣ ድርቅ፣ ቸነፈር፣ የምድር መናወጥ ይሆናል − በስሜ የሚያምኑ ለመከራ ተላልፈው ይሰጣሉ፣ ይገደላሉ፣ በአሕዛብ የተጠሉ ይሆናሉ − ሐሰተኞች ነብያት ይነሳሉ ብዙዎችንም ያስታሉ − ምስክር ይሆን ዘንድ ወንጌል በአሕዛብ መካከል ይሰበልካል − የረከሰ ተግባር በመቅደሱ ሲፈጸም ታያላችሁ፡፡ ይህንን ካያችሁ መምጫዬ እንደደረሰ እወቁ፡፡ አላቸው፡፡ ከነዚህ መካከል የቀረ ወይም ያልተፈጸመ ምን አለ? ሁሉም ተፈጽሟል፡፡ የምንጠብቀው አንድ ነገር ቢኖር የእርሱን መምጣት ብቻ ነው፡፡ ሲመጣ ምን ይከናወናል? ትንሳኤ ሙታን ሁለት አይነት ነው የክብር ትንሳኤ እና የውርደት ትንሳኤ፡፡ “በመቃብር ያሉ ሁሉ ድምጹን የሚሰሙበት ሰዓት ይመጣል መልካም ያደረጉ ለሕይወት ትንሳኤ ክፉም ያደረጉ ለፍርድ ትንሳኤ ይወጣሉና፡፡” ጌታችንም ለፍርድ ሲመጣ በጎች የተባሉ ጻድቃንን በቀኝ ፍየል የተባሉ ኃጥአንን በግራ ያቆማቸዋል፡፡ በዘውትር ጸሎታችን ማጠቃለያ ላይ “ያድነን ዘንድ በአባቱ ምስጋና ከቅዱሳን መላእክቶቹ ጋር በመጣ ጊዜ ጻድቃንን በቀኙ ኃጥአንን በግራ ባቆመ ጊዜ እኛን ከሰማእቱ እስጢፋኖስ ከመጥምቁ ዮሐንስ እና ከሁሉ ቅዱሳን ከሰማእታት ጋር ያቀመን ዘንድ ለምኝልን እንላለን፡፡” በግ እና ፍየል ተብለው የተመሰሉ ጻድቃንና ኃጥአነ ናቸው፡፡ ፍየል ላቷን ወደላይ በማድረግ ኃፍረተ ሥጋዋን አትሸፍንም ኃጥአንም ኃጢአታቸውን በንስሐ አይሸፍኑም፡፡ በጎች ግን ኃፍረተ ሥጋቸውን በላታቸው ይሸፍናሉ ጻድቃንም ሐጢአታቸውን በንስሐ ይሸፍናሉ፡፡ ፍየሎች ሲሰማሩ በየቦታው እንደሚበታተኑ ሁሉ ኃጥአንም በየኃጢአት ሥፍራው ሁሉ ተበታትነው ይገኛሉና፡፡ በጎች ግን በተሰማሩበት በአንድነት ይንቀሳቀሳሉ ጻድቃንም በአንድነት በቤተክርስቲያን ተሰብስበው የመገኘታቸው ምሳሌ ነው፡፡ ፍየሎች ሲታሰሩና ሲያዙ መጮህን ያበዛሉ (አንዳንዴ እንደሰው አይነት ድምጽ ሁሉ እያወጡ ይጮሀሉ) ኃጥአንም በመከራ ጊዜ ያጉረመርማሉ ያማርራሉም፡፡ በጎች ግን ሲታሰሩና ሲጎተቱ በዝምታ ይነዳሉ፡፡ በበግ የተመሰለ ክርስቶስም “በሸላቾቹ ፊት ዝም እንደሚል በግ ተነዳ” እንዲል መጽሐፍ፡፡ ልክ እንዲሁ ጻድቃንም መከራ በደረሰባቸው ጊዜ እንደጌታቸው በዝምታ ታግሰው የማለፋቸው ምሳሌ፡፡ ስለዚህ ምን ማድረግ ይጠበቅብናል? ቀኒቱን እና ሰአቱን አናውቃትምና ተዘጋጅተን መኖር ይጠበቅብናል፡፡ በማቴ 25፡1-13 እንደምናነበው ሙሽራ ሊቀበሉ የወጡ 10 ቆነጃጅት ነበሩ፡፡ አምስቱ ልባሞች አምስቱ ሰነፎች ነበሩ፡፡ ልባሞቹ መብራት እና ዘይት ይዘው ነበረ ሰነፎቹ ግን መብራት ብቻ ነበራቸው፡፡ መብራት ሃይማኖት ነው ዘይቱ ደግሞ ምግባር፡፡ ሙሽራው ክርስቶስ ነው፡፡ አስሩም በአንድነት ሆነው ሲጠብቁት ሙሽራው ዘገየባቸው እና ተኙ፡፡ እኩለ ሌሊት በሆነ ጊዜ ሙሽራው መጣ ተነሱ ሲባል ዘይት የሌላቸው መራታቸውን ማብራት አቃታቸው፡፡ ዘይት የያዙት ግን ወዲያውኑ አብርተው ተቀበሉት፡፡ አምስቱ ዘይት ፍለጋ ሲሄዱ ሙሽራው ገብቶ አዳራሹ ተዘጋ፡፡ ሙሽራውን ሲጠብቁ የነበሩ ቆነጃጅት ሙሽራው ሲዘገይ ተኙ ያለው የሞት ምሳሌ ነው፡፡ እኩለ ሌሊት ሲሆን ሙሽራው መጣ የተባለው ደግሞ የክርስቶስን ዳግም ምጽአት ነው፡፡ ክርስቶስ ሲመጣ መብራት /ሃይማኖት/ ይዘው ዘይት /ምግባር/ ያልያዙ ነበሩ፡፡ ሃይማኖት ይዘን ምግባር ሳይኖረን ከመጣ ወደአዳራሹ ወደ መንግስተ ሰማያት መግባት አይቻልም ሙሽራው ደጁን ይዘጋብናል፡፡ ስለዚህ አሁን ዘይት የተባለ ንስሐ፣ ዘይት የተባለ ቁርባን፣ ዘይት የተባእ ቅድስናን መያዝ ያስፈልጋል፡፡ እንደኖህ ዘመን ገና ነው እያልን ስንቀልድ ድንገት ጥፋት መጥቶ እንዳንወሰድ ራሳችንን ለቅድስና እናዘጋጅ፡፡

፨፨፨፨ ጾምን አትጹሟት ፨፨፨፨፨ መቼስ በቤተክርስቲያን ውስጥ ግሩም የመንፈሳዊነት ለዛ እንዲሰማን ከሚያደርጉ ነገሮች ዋነኛው ጾም ነው። ያለ ጾም ክርስቲያናዊ ትሩፋቶችን ማሰብ ከባድ ነው አይቻልምም ። ጾም ምግባር ናት በአምላክ ተተግብራ የተሰጠች የምግባራት ሁሉ ቅመም ነች። እንዲህ አሁን እንዳለንበት ያለ የጾመ ጊዜያት ሲመጡ ደግሞ ነፍሳችን ሐሴትን ታደርጋለች በአምላኳም ደስ ይላታል። ጾም ማለት መከልከል ነው ከምግበ ሥጋ ለተወሰኑ ጊዜያት መከልከል እንዲሁም  የነፍስን ፍላጎት እና ቅድስና ከሚያደፈርሱ የኃጥያት ምግቦች መከልከል (ከሃጥያት መራቅ)። አዘውትረን የምንጠቀማቸውን ነገሮች እንተዋለን (ignore)  እናደርጋለን ክርስቲያናዊ ትሩፋቶች ላይ እናተኩራለን ።እዚህ ጋር ማስተዋል ያለብን እኛ አጽዋማትን ብቻ ጠብቀን የምናቆማቸውን ነገሮች ዘወትር በኑሯቸው ሁሉ ያቆሟቸው እና የዘውትር ጿሚዎች የሆኑ  ክቡራን አበው እና እማት የሞሉበት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንደምንኖር ማስተዋል አለብን ።የእኛም ጾም ሞገስ የሚያገኘው ከእነርሱ ጾም ጋር ተደምሮ እግዚአብሔር ጋር ሲደርስ ነው ። የኛ መከልከል ነገ የሚፈርስ ነው የእነርሱ መከልከል ግን የዘውትር ነው ።እኛ የበሬ ስጋ ባንበላ አብስሉኝ ቀቅሉኝ የማይለውን የሰው ስጋ ሐሜት በተባለ  ቢላ እየቆረጥን እንበላለን እነርሱ ግን ለዚህ እንኳን በማያመች ቦታ ላይ በብሕትውና (በብቸኝነት) ንግግራቸውን ከአምላክ ጋር ብቻ አድርገው  በምድር ላይ ሳሉ ፍጹም የመላእክትን ግብር ተላብሰው ይኖራሉ  ሰለሆነም በአጽዋማት ወቅት አምላካችን ሆይ የእነዚህን አባቶች እና እናቶች የጾም ጽናት ስጠን የጾማቸው ሞገስ ለእኛም ጾም ሞገስ ትሁናት ብለን መማጸን ትልቅ ብልህነት ነው። ምንም እንኳን ጾም መከልከል ቢሆንም ጾምን እራሱን  የሚርቁ ላለመጾም አንድ ሁለት ብለው ምክንያት የሚደረድሩ ሰዎችን ሳይ ግን እነዚህማ ጾምን እራሷን ይጾሟታል ለማለት ተገደድኩ  ጾምን መራቃቸው ቢደንቀኝ ነው ጾምን አትጹሟት ብዬ በርዕሴ መምከሬ ። አበው እንዲህ ይሉናል "ጾምን አትሽሿት (አትጹሟት) እርሷ ክርስቶስን ለምሰል የምናደርገውን መንገድ ታጸናለችና "  ከዚህ ምስጢር አንጻር ጾምን ስንፈትሻት ምንኛ ድንቅ ናት ።ለካስ እኛ የሰው ልጆች ክርስቶስን እንመስለው ዘንድ የተፈጠርን ነን።ቅዱሳን ክርስቶስን ከመሰሉ በኋላ እናንተ ደግሞ እኛን ምሰሉ ብለው ማስተማራቸው  ለዚህ አይደለምን። ጾም የማልጾመው ጌታዬ ስለጾመልኝ ነው ብሎ ከትሩፋት መራቅ ምንኛ ሞኝነት ነው ?በእውነት አምላካችን ጾምን የጾመው  እኛ እንዳንጾም ነውን? ይህ እንዴት ያለ  ክርስቶስን ካለማወቅ የመጣ የአዕምሮ ስንኩፍነት ነው? አምላካች ሰው ሆኖ የተገለጠው ወደፊት በክርስቲያኖች የሚፈጸሙ ምግባራትን አከናውኖ ወይም እርሱ ፈጽሞ እኛን ከትሩፋት ውጪ ለማድረግ ሳይሆን አስቀድሞ በተሰራ በደል ካሳ ሆኖ እራሱን ለራሱ ሊያቀርብ ነው እንጂ ።በመስቀል ላይ ከፈጸመው  ዘላለማዊ የማዳን ስራው እና ከሌሎች መለኮትነቱን ከሚገልጹ ተግባሮቹ ውጪ  አምላካችን በመዋዕለ ሥጋዌው ያከናወናቸው ምግባራት ሁሉ እኛ ተከታዮቹ እንድንፈጽማቸው የተሰጡ ትምህርቶች ናቸው ።በቃል ከመናገር  በመምህራን ከማሰበክ በተግባር ማስተማር ይጸናልና ክርስቶስ ጾምን በተግባር አስተምሮናል ። አንዳንዶች ግን ጾምን ለምን ይጾሟታል? (ሁሌም የሚያውከኝ ጥያቄ) ........የመጀመሪያው ምክንያታቸው ካመንኩኝ ይበቃኛል ወይም እምነት ብቻ   የሚለው  ጥራዝ ነጠቅ እውቀታቸው ነው ።እስኪ ይህችን ሃሳብ ሰከን ብለን እንመርምራት  ......በእውኑ ሰለጾም ጥቅም ማመን ብቻ የጽድቅ መንገድ ይሆናልን  ???? ከየት መጥቶ  እንዴትስ ማመን ብቻ ምግባርን አካቶ ትሩፋት ይሆናል? ።  ይህ ማለት እኮ አንድ ሰው  ምግብ መብላት ባሰበ ቁጥር እንደበላ ይቆጠርለታል እንደማለት ነው አልያም አንድ ሰው ምግብ መብላት ጥቅም እንዳለው ካመነ ብቻ እንደበላ ይቆጠርለታል እንደማለት ነው (ይህማ ለደሀ ሀገራት ምንኛ መልካም ነበር ህዝቡን እመን  እንደበላህ ይቆጠርልሃል እያልክ ማስተኛት ብቻ)   ። ወይም ደግሞ ስለጾም ጥቅም ማሰባቸው ብቻ ከጾም በረከት ያሳትፋቸዋል ማለት ሊሆን ነው..........  ስለዚህ እኔ የዚህን የጾም መንፈስ ከዚህ አርቁልኝ  ወደማለት ትልቅ ድፍረት ያደርሳቸዋል" እምነት ብቻ" በሚል   በሽታ የተጠቁ  ህመምተኞች። (እግዚአብሔር ከመድኀኒቱ ያቅርባችሁ)!!!!!!! ከላይ እንደጠቀስነው ሰዎቹ ጾም ጠላታቸው ነው  !!!!ለዚህም የዳረጋቸው እምነት ብቻ   የሚለው  እሾሃማ አዙሪት ነው ።ግና ከዚህኛው በበለጠ በደንብ ጾምን ወደመጥላት ያደረሳቸው በሽታ ወዲህ ነው .......ክርስትናን ከምግባር  ለይቶ ማየት  ።  ይህ ደግሞ ውሃ መጠጣትን ከውሃ ለይቶ እንደማየት ነው ። ክርስትና እራሷ ምግባር ናት ። ክርስትና ውስጥ በእምነት ብቻ የሚባል ትምሕርት የለም ።መጽሐፍ ያለምግባር እምነት የሞተች ናት እንዲል። ለጾም እና ለምግባራት ካላቸው ጥላቻ አንጻር ሰይጣንም ሳይቀናባቸው አይቀርም  (ኸረ እሱስ ለበረከት ባይሆንም ይጾማል)። ወዳጄ ክርስትና በክርስቶስ መስመር መጓዝ ነው ። "የተጠራችሁለት ለዚህ ነውና ክርስቶስ ደግሞ ፍለጋውን እንድትከተሉ ምሳሌ ትቶላችሁ ስለ እናንተ መከራን ተቀብሏልና "(1ጴጥ 2:21)  እንዲል መንግስተ ሰማያት በመዝናናት  የምትገኝ ሳትሆን የምግባር ውጤት ነች። "ወደ እግዚአብሔር መንግስት በብዙ ድካምና መከራ እንገባ ዘንድ አለን "(ሐዋ 14:22) የሚለውን ቃል ስታነቡ ስለምትቸኩሉ ዘላችሁት ይሆን ወይስ እንዴት ተረድታችሁት ይሆን ። እኛ ግን እንዲህ እናምናለን ጾም ታላቂቷ ክርስቲያናዊ ምግባር ነች ።ለመልካም ነገርም ታነሳሳለች "ወመንቅሒት ላዕለ ኩሉ ገድል ውዱስ " እንዲል ማር ይስሐቅ ። ቅዱስ ጳውሎስን እስኪ እንጠይቀው  "ክቡር አባታችን ጳውሎስ ሆይ የእግዚአብሔር ጸጋና በረከት እንዲሁም መንግስት  እንዴት ትገኛለች  ????"  ቅዱስ  የሆነው የቤተ/ክ መብራትም እንዲህ ይመልስልናል  "በድካምና በጥረት ብዙ ጊዜም እንቅልፍ በማጣት በራብና በጥም ብዙ ጊዜም በመጦም  ...."   (2ቆሮ 11:27)  ብሎ ይመልስልናል  ።  ይህንንስ እንዴት ተረድተውት ይሆን በእውነት እነርሱ ከቅዱስ ጳውሎስ በላይ ጌታን አውቀውት ነውን እርሱ እንጹም እያለ "ሳንጾም እንድናለን " የሚሉት  ።ለእንደዚህ አይነት ነፍስ ዋይታ አለባት እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስ ትዕዛዝ ተቀብለን  እንጾማለን ።እናም ስንጠቀልለው  በጾም ሕይወት ተመስጦ በምግባር አጊጦ  አምላክን መጠበቅ ብልህነት ነው ። ከዚህ ውጪ ግን ጾምን የምትከለከሉ ሰዎች ያለምግባር ድኅነት የለምና  ጾምን አትጹሟት  እንላለን  ። ዲ/ን ፍጹም እማኝነህ

አዘዘ።  ጌታችን ኢየሱስ ነጋዴውች በቤተ መቅደሱ ውስጥ ሲነግዱና ትርፍ ሲያጋብሱ አይቶ እጅግ ተቆጣ በጅራፍ እየነዳ አወጣቸው። ለደቀ መዛሙርቱ ጌታችን ገንዘብ ለዋጮችን ከቤተ መቅደስ ማስወጣት መሲህ መሆኑን ሌላው ምልክት ነበር። ነጋዴዎችን ከነበጎቻቸው ማስወጣት ይመጣል ብለው የሚጠብቁት መሲህ ብቻ ያደርገዋል የሚል እምነት ነበር ብለው ያስቡ ነበር። በዚኽም ነቢዩ ቅዱስ ዳዊት "የቤትህ ቅናት በላኝ" የሚለው መፈጸሙን አወቁ።  “የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉት አላቸው”   ደቀ መዛሙርቱ የነቢዩን ትንቢት መፈጸሙን ቢያውቁም አይሁድ ግን ትንቢቱን ባለማስተዋላቸው ይህንን ለምን እንዳደረገ ምልክት ጠየቁ። ጌታ ቤተ መቅደሱን ሲያጸዳ ካህናቱም ደነገጡ ማንም ሊናግረው አልደፈረም። በዙሪያው ጸጥታ ሰፈነ የቤተ መቅደሱ ዙርያ ከንግድ ነጻ ሆነ። እግዚአብሔር ለሙሴ በመገለጥ ተራራው እንደ ተቀደሰ ሁሉ አሁንም ቤተ መቅደሱን ባረከው።  በአገልግሎቱ መጀመሪያ ቤተ መቅደሱን እንዳጸዳ ከሦስት ዓመት በኋላ ጊዜም ከመስቀል በፊት ይህንን ድርጊት ፈጽሞታል። መ/ር ንዋይ ካሳሁን

ምኩራብ “ቤተ መቅደሱን አፀዳ” ዮሐ.፪፡፲፭ ምኩራብ የአይሁድ የጸሎት ቤተ ነው። ቤተ መቅደሳቸው አንድ ቦታ ኢየሩሳሌም ሲሆን ምኩራባት ግን በየቦታው ተሰርተው ነበር። በምኩራብ የሰንበት በዓል ይከበራል፡ ጸሎት ይጸለያል። የዓመት በዓላት እና መስዋዕት የሚሰዋው ግን በቤተ መቅደስ ብቻ ነበር። ምኩራብ መሥራት የተጀመረው ናቡከደነጾር መቅደሱን አፍርሶ አይሁዳውያንን ከኢየሩሳሌም ወደ ባቢሎን በወሰዳቸው ጊዜ በተለያዩ ስፍራዎች የማምለኪያ ስፍራን መሥራት ጀመሩ። በጌታችን ትምህርት ጊዜ ብዙ ምኩራባት ነበሩ። ሐዋርያትም ለስብከት በወጡ ጊዜ ወደ ምኩራብ በመሔድ ያስተምሩ ነበር።” የነፃ ወጪዎች ከተባለችው ምኵራብም ከቀሬናና ከእስክንድርያም ሰዎች ከኪልቅያና ከእስያም ከነበሩት አንዳንዶቹ ተነሥተው እስጢፋኖስን ይከራከሩት ነበር” ሐዋ.፱ አስር ሰዎች ራሳቸውን የቻሉ ከሆኑ ምኩራብ መስራት ይችሉ ነበር። በምኩራብ ውስጥ የሙሴና የነቢያት መጽሐፍት ይነበባሉ። አንባቢው ከፍ ባለ ቦታ ቆሞ ያነባል። "ሕግና ነቢያትም ከተነበቡ በኋላ የምኵራቡ አለቆች፦ ወንድሞች ሆይ፥ ሕዝብን የሚመክር ቃል እንዳላችሁ ተናገሩ ብለው ላኩባቸው” ምኩራብ ለቤተ መቅደሱ መዳረሻ ሲሆን በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለተመሠረተችው ቤተ ክርስቲያን ሞግዚት ሆና ነበር ያገለገለችው።  ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቃና ዘገሊላ ባሕር በስተ ሰሜን ወደ ምትገኘው ወደ ቅፍርናሆም ከተማ ሄደ። በየዓመቱ በርካታ አይሁዳውያን የፋሲካን በዓል ለማክበር ወደ ኢየስሩሳሌም ይሄዳሉ “ወላጆቹም በያመቱ በፋሲካ በዓል ወደ ኢየሩሳሌም ይወጡ ነበር” ሉቃ.፪፡፵፩ ጌታችን ከተጠመቀ በኋላ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር የፋሲካን በዓል ለማክበር ወደ ኢየሩሳሌም ሔደ። በዚኽም የፋሲካ ሳምንት ብዙ ሰዎች ከፍልስጥኤም ልዩ ልዩ ክፍሎች ከሩቅም ከቅርብም ሳይቀር መጥተው ነበር። የቤተ መቅደሱ አካባቢ ሁኔታ ቤተ መቅደስ ዓላማው የእግዚአብሔርን ቃል ማስተማር፡ ለኃጢአተኛው መስዋዕት ማቅረብ ሲሆን፤  ሲጠቀለል ሊመጣ ላለው መሲህ ሕዝቡን ማዘጋጀት ነው። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለፋሲካ በዓል ኢየሩሳሌም እንደደረሰ ነጋዴዎች ለመስዋዕት የሚቀርቡ እንስሳት በቤተ መቅደሱ ቅጥር ጊቢ ውስጥ ሲሸጡ ተመለከተ። ለአምልኮ ወደ ቤተ መቅደስ የሚጸጡትን ገንዘብ በዚያው በቤተ መቅደሱ ውስጥ ነበር። “በመቅደስም በሬዎችንና በጎችን ርግቦችንም የሚሸጡትን ገንዘብ ለዋጮችንም ተቀምጠው አገኘ” ይላል ዮሐ.፪፡፲፬ ሰዎች ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ የሆነውን መስዋዕት ይዘው ሊመጡ አልቻሉም ነበር። እንዲህ ላሉት ሰዎች እንዲመች ተብሎ ከቤተ መቅደሱ ውጭ ባሉት አደባባዮች እንስሳት ይሸጡ ነበር። ለምስዋዕት የሚቀርቡትን ለመግዛት ሰዎች ተሰብስበው ነበር። በተጨማሪም የውጭ ሀገር ገንዘቦች በቤተ መቅደሱ ቅንስናሽ ገንዘቦች ይመነዘሩ ነበር። ምናልባትም የሮም የግሪክ መገበያያይ ገንዘቦች ይመጣሉ። ምክንያቱም ከነዚህ ሀገራት የመጡ ብዙ ሕዝቦች ይኖሩ ነበር። በወቅቱ ሀገሪቱ በሮማ ቅኝ ግዢ ስር ውድቃ ነበር። በተጨማሪም እያንዳንዱ አይሁድ የነስፍ ቤዛ የሚሆን በዓመት አንድ ብር ይከፍል ነበር። በዚህ መልኩ የተሰበሰበው ገንዘብ ለመቅደሱ አገልግሎት ይውል ነበር። “አንተ የእስራኤልን ልጆች ቍጥር ተቀብለህ፥ በቈጠርሃቸው ጊዜ መቅሰፍት እንዳይሆንባቸው፥ በቈጠርሃቸው ጊዜ ከእነርሱ ሰው ሁሉ እንደ ቍጥራቸው መጠን የነፍሱን ቤዛ ለእግዚአብሔር ይስጥ….የማስተስረያውንም ገንዘብ ከእስራኤል ልጆች ወስደህ ለመገናኛው ድንኳን ማገልገያ ታደርገዋለህ፤ በእግዚአብሔርም ፊት ለነፍሳችሁ ቤዛ እንዲሆን ለእስራኤል ልጆች መታሰቢያ ይሁን” ይላል።  ዘጸ.፴፡፲፪ በዚኽ ምክንያት በቤተ መቅደሱ የሚቀመጥ ብዙ ገንዘብ ነበር። ወደ ቤተ መቅደስ ለመግባት ደግሞ ሁሉም አይነት የውጭ ሀገር ምንዛሬዎች ለአገልግሎት ወደ ሚውለው የገንዘብ አይነት ወደ “ሼኬል” ወደ ተባለው ቅንስናች ገንዘብ መቀየር ይኖርበታል። ይህ የገንዘብ መዘርዘር ለምዝበራና ለስግብግብነት አመቺ ሁኔታ በመፍጠሩ አስከፊ ድርጊት ሆነ። የገንዘብ ምንዛሬው ለካህናቱ የገቢ ምንጭ ሆነ።  በሬዎችና እንሳሳት ለምን ወደ ቤተ መቅደስ መጡ "መስዋዕት ካላቀረቡ እግዚአብሔር ልጆቻቸውን እና መሬታቸውን አይባርክም" ብለው እንዲያምኑ ምእመናኑን ያስተምሯቸው ነበር። በዚህ አኳኋን ከእንስሳቱ ሽያጭ ብዙ ገንዘብ ይገባ ነበር። ነጋዴዎቹን ካህናቱ በመመሳጠር ሕዝቡን በመዝረፍ ራሳቸውን አበለጸጉ። በተለይም ለፋሲካ በዓል ብዙ መስዋዕቶች ይቀርቡ ስለነበር በቤተ መቅደስ የሚካሔደው ሽያጭ ከፍተኛ ነበር። በዚኽ ጊዜ የሚፈጠረው የእንስሳት ጩኽት፤ የነጋዴዎች ጫጫታ ቦታውን የተቀደሰ የእግዚአብሔር ቤት ከመሆን ፈንታ ግርግር የሚበዛባት የከብት ገብይት ስፍራ አስመሰለው። የዋጋ ክርክር፤ የከብት የበግ የርግብ ጩኽት፤ የሳንቲም ፍጭት፤ የቁጣ ክርክር ሁሉ ይሰማ ነበር። ከትርምሱ የተነሳ ወደ ቤተ መቅደስ የሚመጣው ሕዝብ ይታወካል መጥቶም ምንም የቅድስና ስራ ሳይሰራ ይመለሳል። ዛሬም ከገንዘብ አምጡ ውጭ የቤተ ክርስቲያንን ዋና መልእክት የዘነጉ ቀላል አይደሉም። በቤተ መቅደሱ የሚነገሩ የነቢያት የትንቢት መጽሐፍት ተዋጡ። ስለ ቤተ መቅደስ አገልግሎት ትጋት ነበራቸው  ነገር ግን የገንዘብ ፍቅር የሕሊናቸውን ሚዛን አዛባው። እግዚአብሔር ከሰጣችው አገልግሎት በእጅጉ ራቁ።  እግዚአብሔር በሲና ተራራራ ላይ በመውረዱ ቦታው የተቀደሰ ነበር። ሙሴ ጫማውን እንዲያወልቅ ተነገረው። የተራራውን አካባቢ ዙሪያ ድንበር ከልሎ እንዲቀድሰው አዘዘ።  ወደ ተራራርው እንዳይቀርቡም በማስጠንቀቂያ ተናገረ። “በሦስተኛው ቀን ሕዝቡ ሁሉ ሲያዩ እግዚአብሔር በሲና ተራራ ላይ ይወርዳልና ለሦስተኛው ቀን ይዘጋጁ።ወሰንም ለሕዝቡ በዙሪያው አድርግላቸው፦ ወደ ተራራው እንዳትወጡ ጫፉንም እንዳትነኩ ተጠንቀቁ፤ ተራራውንም የነካ ፈጽሞ ይሞታል የማንም እጅ አይንካ፤ ነገር ግን የሚነካው ሁሉ ይወገራል፥ ወይም በፍላጻ ይወጋል፤ እንስሳ ወይም ሰው ቢሆን አይድንም በላቸው።” ብሎ ነበር  ዘጸ. ፲፱፡፲፪  በዚኹ መጠን የቤተ መቅደሱ ክልል መከበር ነበረበት እንስሳትም እንኳ መድረስ የለባቸውም ከተፈቀደው ተግባር እና ክልል ውጭ። ነገር ግን በትርፍ ፍላጎት ውጣ ውረድ ይህ ሁሉ ተዘነጋ። ካህናቱና አለቆቹ በሕዝቡ መካከል የእግዚአብሔር እንደራሴ እንዲሆኑ ተመርጠው ነበር። ነገር ግን በቤተ መቅደሱ ዙሪያ የሚደረገውን አስጸያፊ ነገር ማስቆም ግን ተሳናቸው። በታማኝንነት እግዚአብሔርን ማገልገል ለሕዝቡ ምሳሌ መሆን ነበረባቸው። ነገር ግን ስለ ግል ጉዳያቸው  ተጨነቁ ንፉግነት ልባቸውን አደነደነው። ዛሬ በቅድስና በፍቅር ለሕዝቡ ምሳሌ የሚሆን አገልጋይ የታጣበት ለገንዘብ ብቻ የተቆመበት ጊዜ ነው። ለምዕመናኑ ችግር መንፈሳዊነት እድገት ግድ የለሽ ሆነዋል። በገፈፋም ይሁን በዘረፋ የሕዝብ ገንዘብ ላይ ብቻ ዘምተዋል። ርግብ ርግብ በብሉይ ኪዳን የድሆች መስዋዕት ነበር። “ስለ ሠራው ኃጢአት ለበደል መሥዋዕት ጠቦትን ለማምጣት ገንዘቡ ያልበቃ እንደ ሆነ፥ ሁለት ዋኖሶች ወይም ሁለት የርግብ ግልገሎች፥ አንዱን ለኃጢአት መሥዋዕት ሁለተኛውንም ለሚቃጠል መሥዋዕት፥ ለእግዚአብሔር ያቀርባል” ይላል ዘሌ.፭፡፯ በዚህ መሰረት ጌታችንን ወደ ቤተ መቅደስ በስምንተኛው ቀን በወሰዱት ጊዜ የርግብ መስዋዕት አቀረቡ። ስለሆነም በቤተ መቅደስ ዙርያ ርግቦች የተገኙት ለዚህ ነበር። ጌታ “ርግብ ሻጪዎችንም፦ ይህን ከዚህ ውሰዱ” ያለው ርግብ ጅራፍ አይችሉምና በቃል

✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg ✍️ Facebook 👇 http://facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram
✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg                              ✍️ Facebook 👇 http://facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ✞✞ አስራ ስምንት ቀረህ...✞✞         ዕረፍቱ ለቅዱስ አቡፋና ★★★ ሕይወቱ ✔ይህ የከበረ አባት በዘመኑ ስለእግዚአብሔር ፍቅር የዚህን ዓለም ክፉ ስራ በመናቅ ከቶ ብርሃን በሌለበት ዋሻ ውስጥ በፈቃዱ የሚኖር ሆኖ በየሁለት ቀን ይጾማል የሚበላውም የሚጠጣውም በመስፈርያ ተለክቶ ነው በሌሊትና በመዓልት አምስት መቶ ጊዜ እየጸለየ የሚኖር አባት ነው፡፡ በተጨማሪ በከበረች በአርባ ጾም ከሦስት ቀኖች በላይ ሳይበላ ይፈፅም ነበረ፡፡ ✔ አባ አቡፋና መላ ተጋድሎውን የፈጸመው ለሰውነቱ ረፍትን ሳይሰጣት በመቆም ነበር ተቀምጦም አያውቅም ሲበላም ሲያንቀላፋም የራሱ ረፍትን ላለመስጠት ግድግዳ ተጠግቶ ነው በዚህም ትጋቱ እግሮቹ እንደ ዝሆን እግር እስከሚሆኑ ድረስ ይጋደል ነበር፡፡ ያደረጋቸው ተዓምራት " እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ በእኔ የሚያምን እኔ የማደርገውን ሥራ እርሱ ደግሞ ያደርጋል፤ ከዚህም የሚበልጥ ያደርጋል" ዮሐንስ ወንጌል ፲፬÷፲፪ ✞ በሦስት እንጀራ ሃያ ሰው ያጠገበ ነው፡፡ ✔ በአንዲት እለት ወንድሞች ሊጎበኙት ወደ እርሱ መጡ የሚያቀርብላቸው እንጀራን አጣ ሦስት እንጀራን በአገኘ ግዜ ለሃያ ሰዎች አቀረበላቸው እነርሱም በልተው ጠገቡ ተአምራትንም እያደረገ በሽተኞችን እየፈወሰ ኖረ፡፡ ✞ እንደ ኤልሳዕ ምሳር በውኃ ላይ አንሳፎአል ✔ በዋሻው ደጃፍ የውኃ ምንጭ ነበረ ምሳርንም ወረወረበት ምሳሩም ነብይ ኤልሳዕ እንዳደረገው በውኃ ላይ ተንሳፈፈ፡፡ ✞ በቆቡ ሙት አስነስቷል፡፡ ✔ በአንዲትም ዕለት ሦስት መቶ የወርቅ ዲናር የያዘ እንግዳ በአንድ ቄስ ቤት አደረ በተኛ ግዜ ስለ ገንዘቡ ቄሱ ገደለውና ወስዶ ከአንድ መነኩሴ ደጅ ጣለው፡፡ ለቅዱስ አቡፋናም በነገሩት ግዜ ከሟቹ ላይ እንዲጥሉበት ቆቡን ሰጣቸው ሲጥሉበትም ሟቹ ተነሳ ስለ ገንዘቡ ቄሱ እንደገደለው ነገራቸው እጅግም አደነቁ፡፡ ✔ በሌላም ቀን አንድ ሰው ቡራኬ ሊቀበል ልጁን ይዞ ወደ እርሱ ሲመጣ ልጁ በጉዞ ላይ ሳለ ሞተ ልጁንም ተሸክሞ ወደ ቅዱስ አቡፋና ሔደ በፊቱም ሰግዶ ተባርኮ ተመለሰ ያን ግዜ የሞተው ብላቴና ተነስቶ አባቱን ተከተለው፡፡ ✞✞ አስራ ስምንት ቀረህ✞✞ ✔ ይህ መልእክት ለቅዱስ አቡፋና በጸሎት ላይ ሳለ የመጣለት መልእክት ነው፡፡ የከበረ አቡፋናም አስራ ስምንት ዕለታት እንደሆኑ አስቦ እነዚህ እለቶች እስኪፈፀሙ በጾም በጸሎት በንስሐ በመትጋት ቆመ፡፡ ይህም ቀን ባለፈ ግዜ አስራ ስምንት የተባሉ ሱባኤዎች ናቸው ብሎ ይህንንም በጾም በጸሎት በሱባኤ በመቆም አሳለፈ፡፡ ይህም ባለፈ ግዜ አይ አስራ ስምንት ወሮች ቢሆኑስ ብሎ ይህንንም በመቆም ሳያጓድል አሳለፈ፡፡ ነገር ግን ዳግመኛ ወደርሱ እንዲህ የሚል ቃል መጣ "አቡፋና ሆይ አስራ ስምንት አመት ናትና ጽና በርታ አለህ እግዚአብሔር" አለው በዚያንም ግዜ ፈጽሞ ግዜው ሩቅ ነው ሳይል በጾም በጸሎት በተጋድሎ ጸና፡፡  ከቆመ ደምሮ አስራ ስምንቱ ዓመት በተፈፀመ ግዜ ዕረፍቱን አውቆ ቅዱስ ቁርባንን ተቀበለ ወደ መኖርያውም ሄዶ ራሱን ዘንበል አድርጎ ነፍሱን በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ፡፡ ♠♠ መልእክት ☞ ለእኛ የምንሞትበት ቀን ተለክቶ ተሰፍሮ ቢነገረን ቀሪውን ሕይወታችንን ምን በማድረግ እናሳልፍ ይሆን? እንደ ኖህ ዘመን ሕዝቦች ግዜው ገና ነው እያልን ያላየነውን በማየት ያልሰራነውን በመስራት በኃጢአት ላይ ኃጢአት እናበዛ ይሆን? ወይንስ እንደ ቅዱስ አቡፋና ተዘጋጅተን እንጠብቃለን? ✔ እግዚአብሔር ለምን ይመስለናል እለተ ሞታችንን የሰወረብን? 1- ሁልግዜ ሟች መሆናችንን እያሰብን ተዘጋጅተን እንድንኖር 2- ለእኛ አስቦ ስለሚወደን፡፡ ማለት እለተ ሞታችንን ብናውቅ ኖሮ የቀሩንን ቀናት እያሰብን በሰቀቀን በኖርን ነበርና፡፡ 3- የበለጠ እንዳናሳዝነው፡፡ ማለት የቀረንን እያሰብን የሄን ያህል ግዜ ይቀረኛል ግዜው ገና ነው እያልን እንደ ኖህ ዘመን ሕዝቦች በኃጢአት ላይ ኃጢአት እንዳናበዛ፡፡ ስለዚህ ሁልጊዜ እለተ ሞታችንን እያሰብን እንኑር ያለን የመኖር እድል እንድንበት ዘንድ የተሰጠን ቀን ዛሬ መሆኑን በልባችን ሰሌዳ እንጻፍና ወደ እግዚአብሔር ተመልሰን በጾም በጸሎት በንስሐ በስጋወ ደሙ እንትጋ፡፡ ይህንንም ትጋት እግዚአብሔር ለሁላችን ያድለን የአባ አቡፋና በረከቱ ከእኛ ጋር ትኑር፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር፡፡ የካቲት 25 የዕረፍታቸው መታሰቢያ ነው፡፡

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ✞✞ አስራ ስምንት ቀረህ...✞✞         ዕረፍቱ ለቅዱስ አቡፋና ★★★ ሕይወቱ ✔ይህ የከበረ አባት በዘመኑ ስለእግዚአብሔር ፍቅር የዚህን ዓለም ክፉ ስራ በመናቅ ከቶ ብርሃን በሌለበት ዋሻ ውስጥ በፈቃዱ የሚኖር ሆኖ በየሁለት ቀን ይጾማል የሚበላውም የሚጠጣውም በመስፈርያ ተለክቶ ነው በሌሊትና በመዓልት አምስት መቶ ጊዜ እየጸለየ የሚኖር አባት ነው፡፡ በተጨማሪ በከበረች በአርባ ጾም ከሦስት ቀኖች በላይ ሳይበላ ይፈፅም ነበረ፡፡ ✔ አባ አቡፋና መላ ተጋድሎውን የፈጸመው ለሰውነቱ ረፍትን ሳይሰጣት በመቆም ነበር ተቀምጦም አያውቅም ሲበላም ሲያንቀላፋም የራሱ ረፍትን ላለመስጠት ግድግዳ ተጠግቶ ነው በዚህም ትጋቱ እግሮቹ እንደ ዝሆን እግር እስከሚሆኑ ድረስ ይጋደል ነበር፡፡ ያደረጋቸው ተዓምራት " እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ በእኔ የሚያምን እኔ የማደርገውን ሥራ እርሱ ደግሞ ያደርጋል፤ ከዚህም የሚበልጥ ያደርጋል" ዮሐንስ ወንጌል ፲፬÷፲፪ ✞ በሦስት እንጀራ ሃያ ሰው ያጠገበ ነው፡፡ ✔ በአንዲት እለት ወንድሞች ሊጎበኙት ወደ እርሱ መጡ የሚያቀርብላቸው እንጀራን አጣ ሦስት እንጀራን በአገኘ ግዜ ለሃያ ሰዎች አቀረበላቸው እነርሱም በልተው ጠገቡ ተአምራትንም እያደረገ በሽተኞችን እየፈወሰ ኖረ፡፡ ✞ እንደ ኤልሳዕ ምሳር በውኃ ላይ አንሳፎአል ✔ በዋሻው ደጃፍ የውኃ ምንጭ ነበረ ምሳርንም ወረወረበት ምሳሩም ነብይ ኤልሳዕ እንዳደረገው በውኃ ላይ ተንሳፈፈ፡፡ ✞ በቆቡ ሙት አስነስቷል፡፡ ✔ በአንዲትም ዕለት ሦስት መቶ የወርቅ ዲናር የያዘ እንግዳ በአንድ ቄስ ቤት አደረ በተኛ ግዜ ስለ ገንዘቡ ቄሱ ገደለውና ወስዶ ከአንድ መነኩሴ ደጅ ጣለው፡፡ ለቅዱስ አቡፋናም በነገሩት ግዜ ከሟቹ ላይ እንዲጥሉበት ቆቡን ሰጣቸው ሲጥሉበትም ሟቹ ተነሳ ስለ ገንዘቡ ቄሱ እንደገደለው ነገራቸው እጅግም አደነቁ፡፡ ✔ በሌላም ቀን አንድ ሰው ቡራኬ ሊቀበል ልጁን ይዞ ወደ እርሱ ሲመጣ ልጁ በጉዞ ላይ ሳለ ሞተ ልጁንም ተሸክሞ ወደ ቅዱስ አቡፋና ሔደ በፊቱም ሰግዶ ተባርኮ ተመለሰ ያን ግዜ የሞተው ብላቴና ተነስቶ አባቱን ተከተለው፡፡ ✞✞ አስራ ስምንት ቀረህ✞✞ ✔ ይህ መልእክት ለቅዱስ አቡፋና በጸሎት ላይ ሳለ የመጣለት መልእክት ነው፡፡ የከበረ አቡፋናም አስራ ስምንት ዕለታት እንደሆኑ አስቦ እነዚህ እለቶች እስኪፈፀሙ በጾም በጸሎት በንስሐ በመትጋት ቆመ፡፡ ይህም ቀን ባለፈ ግዜ አስራ ስምንት የተባሉ ሱባኤዎች ናቸው ብሎ ይህንንም በጾም በጸሎት በሱባኤ በመቆም አሳለፈ፡፡ ይህም ባለፈ ግዜ አይ አስራ ስምንት ወሮች ቢሆኑስ ብሎ ይህንንም በመቆም ሳያጓድል አሳለፈ፡፡ ነገር ግን ዳግመኛ ወደርሱ እንዲህ የሚል ቃል መጣ "አቡፋና ሆይ አስራ ስምንት አመት ናትና ጽና በርታ አለህ እግዚአብሔር" አለው በዚያንም ግዜ ፈጽሞ ግዜው ሩቅ ነው ሳይል በጾም በጸሎት በተጋድሎ ጸና፡፡  ከቆመ ደምሮ አስራ ስምንቱ ዓመት በተፈፀመ ግዜ ዕረፍቱን አውቆ ቅዱስ ቁርባንን ተቀበለ ወደ መኖርያውም ሄዶ ራሱን ዘንበል አድርጎ ነፍሱን በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ፡፡ ♠♠ መልእክት ☞ ለእኛ የምንሞትበት ቀን ተለክቶ ተሰፍሮ ቢነገረን ቀሪውን ሕይወታችንን ምን በማድረግ እናሳልፍ ይሆን? እንደ ኖህ ዘመን ሕዝቦች ግዜው ገና ነው እያልን ያላየነውን በማየት ያልሰራነውን በመስራት በኃጢአት ላይ ኃጢአት እናበዛ ይሆን? ወይንስ እንደ ቅዱስ አቡፋና ተዘጋጅተን እንጠብቃለን? ✔ እግዚአብሔር ለምን ይመስለናል እለተ ሞታችንን የሰወረብን? 1- ሁልግዜ ሟች መሆናችንን እያሰብን ተዘጋጅተን እንድንኖር 2- ለእኛ አስቦ ስለሚወደን፡፡ ማለት እለተ ሞታችንን ብናውቅ ኖሮ የቀሩንን ቀናት እያሰብን በሰቀቀን በኖርን ነበርና፡፡ 3- የበለጠ እንዳናሳዝነው፡፡ ማለት የቀረንን እያሰብን የሄን ያህል ግዜ ይቀረኛል ግዜው ገና ነው እያልን እንደ ኖህ ዘመን ሕዝቦች በኃጢአት ላይ ኃጢአት እንዳናበዛ፡፡ ስለዚህ ሁልጊዜ እለተ ሞታችንን እያሰብን እንኑር ያለን የመኖር እድል እንድንበት ዘንድ የተሰጠን ቀን ዛሬ መሆኑን በልባችን ሰሌዳ እንጻፍና ወደ እግዚአብሔር ተመልሰን በጾም በጸሎት በንስሐ በስጋወ ደሙ እንትጋ፡፡ ይህንንም ትጋት እግዚአብሔር ለሁላችን ያድለን የአባ አቡፋና በረከቱ ከእኛ ጋር ትኑር፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር፡፡ የካቲት 25 የዕረፍታቸው መታሰቢያ ነው፡፡

በተፈጠረው ግርግር መነሻት የታሰሩ ምእመናንን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ እየጠየቅን ይህ የማይሆን ከሆነ ግን ቤተ ክርስቲያን መብቷን ለማስከበር ወደ ቀጣይ እርምጃዎች የምትገባ መሆኑን በአክብሮት እያሳወቅን ይህንንም ድርጊት ተከታትሎ የሚያሳውቅ እና የሚያስፈጽም የሕግ ባለሙያዎች ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደሥራ እንዲገባ የሚደረግም መሆኑን ጭምር እናሳስባለን፡፡ በዚህ ሕገ ወጥ ድርጊት የሊቀ ሰማዕቱን የቅዱስ ጊዮርጊስ ክብረ በዓል ለማክበር በመምጣት ህይወቱን ላጣው ልጃችን እግዚአብሔር ነፍሱን በአብርሃም፣ በያዕቆብና በይስሐቅ እቅፍ ያኑር፣ ለቤተሰቦቹም መጽናናትን ያድልልን እያልን ቀላልም ሆነ ከባድ የአካል ጉዳት የደረሰባችሁ የቤተ ክርስቲን የጭንቅ ቀን ልጆች ደማችሁን እና መከራችሁን እንደ ሰማእታት ዋጋ ይቆጥርላችሁ ዘንድ ጸሎታችን ነው፡፡ እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ የካቲት ፳፬ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም አዲስ አበባ፣ኢትዮጵያ

"የካቲት 23 ቀን 2015 ዓ.ም በተከበረው የቅዱስ ጊዮርጊስ ክብረ በዓል በቤተ ክርስቲያን ላይ የአድዋ የድል በዓልን አስታኮ በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች የተፈፀመው እጅግ አሳዛኝ ድርጊት ቤተክርስቲያን ሰምታና አይታ በዝምታና በሀዘን ብቻ  የምታልፈው ጉዳይ አልሆነም"...ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሙሉ መግለጫው እንደሚከተለው ቀርቧል፦ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን በየካቲት ፳፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን  በመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ላይ በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች አማካኝነት የተፈጸመውን ሕገ ወጥ ድርጊት አስመልክቶ ከአዲስ አበባ ሀገረ ሰብከት የተሰጠ መግለጫ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከሀገራችን ኢትዮጵያ ሀገረ መንግሥት ምሥረታ ጀምሮ ያለችና መንግሥትን ያጸናች፣ የራሳቸው የጽሑፍ ቋንቋ ካላቸው ጥቂት ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ አንዷ እንድትሆን ፊደል ቀርፃ ያስተማረች፣ መንግሥት የአረንጓዴ አሻራን መርሐግብር ከማስጀመሩ ከሺህ ዓመታት በፊት የአካባቢ ጥበቃን ስትሠራ የኖረችና አሁንም በየአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት፣ ገዳማትና አድባራት የአካባቢ ጥበቃ ሥራን የምትሠራ፣ ዘመናዊ ትምህርት ከመጀመሩ ከሺህ ዓመታት በፊት ሥርዓተ ትምህርት ቀርፃ ያስተማረችና የሀገር መሪዎችን፣ የስነ ህንፃ ባለሙያዎችን፣ የመድኃኒት አዋቂዎችንና ተመራማሪዎችን ያፈራች ቤተ ክርስቲያን ከመሆኗም በላይ ተቋም መሥርታ ለዘመናት የተቋምን ምንነት ያስተማረች ራሷ ሀገር የሆነች ናት፡፡ በተለይም ደግሞ መላው የአፍሪካ ሀገራት በቅኝ ግዛት በተያዙበት፣ አውሮፓውያን ኢትዮጵያንም ለመቀራመት ተስማምተው በፋሺስቱ የኢጣልያ መንግሥት አማካኝነት ሀገራችንን በወረረበት ጊዜ የንጉሱን የክተት አዋጅ ተከትሎ ሕዝቡ ለነፃነቱ እንዲዋደቅ የሀገር ፍቅር ለምእመኗ ያስተማረች በመሆኑ እና የንጉሱም ጥሪ ሀገራዊ ብቻ ሳይሆን ሃይማኖትን የመጠበቅ ጥሪም የነበረ በመሆኑ ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ንጉሱን እንዲከተል ከማድረጓም በላይ ታቦተ ቅዱስ ጊዮርጊስን በካህናቱ አጅባ የጦር ግንባር ድረስ በመዝመት፣ ምእመኑን እና ህዝቡን በማጽናናትና ፀሎተ ፍትሀት በማድረግ በዓድዋ ጦርነት ኢትዮጵያ ሀገራችን ድል እንድትቀዳጅና ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም የነፃነት አርማ እንድትሆን በማድረግ ትልቁን የታሪክ ድርሻ እንደምትወስድ የታወቀ ሀቅ ነው፡፡ ከዚህ የድል በዓል በኋላም ኢትዮጵያ በነፃነት በቆየችባቸው ዓመታት ሁሉ ይህን የአድዋ የድል በዓል ቤተ ክርስቲያን የሰማእቱን ቅዱስ ጊዮርጊስ ታቦተ ሕግ ከመንበረ ክብሩ ወጥቶ ህዝቡን በመባረክ፣ ካህናቱና ምእመናኑ በታላቅ ምሥጋና እና መዝሙር በመላ ሀገሪቱ ስታከብረው የኖረች፤ ወደፊትም እየፈጸመች የምትጸናበት አኩሪ ታሪኳ ነው፡፡  ይሁን እንጂ ይህ በዓል ላለፉት ጥቂት ዓመታት የድል በዓል መሆኑ ቀርቶ የጠብና የጥላቻ በዓል እየሆነ መምጣቱ ቤተ ክርስቲያንን በእጅጉ ያሳዘነ ተግባር ሆኗል፡፡ በተለይም ትላንት የካቲት ፳፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም በተከበረው የቅዱስ ጊዮርጊስ ክብረ በዓል በቤተ ክርስቲያን ላይ የአድዋ የድል በዓልን አስታኮ በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች የተፈፀመው እጅግ አሳዛኝ ድርጊትን ግን ቤተ ክርስቲያን ሰምታና አይታ በዝምታና በሀዘን ብቻ  የምታልፈው ጉዳይ አልሆነም፡፡   በየካቲት ፳፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም የቅዱስ ጊዮርጊስ ክብረ በዓል ለማክበር ሕዝቡ ከየቤቱ ተሰባስቦ ከጠዋቱ ፫፡፲፭ ላይ ታቦተ ሕጉ ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ የጆርጅያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት ከመንበረ ክብሩ ወጥቶ ዑደት ካደረገና ሕዝቡን ባርኮ በዐውደ ምህረቱ ላይ ከቆመ በኋላ ሊቃውንቱ ያሬዳዊ ወረብ በማቅረብ ላይ እንዳሉ ከመንግሥት የጸጥታ መዋቅር የቤተ ክርስቲያኒቱን ተቋማዊ ልዕልናን ተላልፈው በሰሜን በኩል ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ቅጥር ግቢ ፪ ጊዜ በተኮሱት አስለቃሽ ጭስ ምክንያት የንግሥ በዓሉ በመረበሹ በዓሉ ተቋርጦ ከጠዋቱ ፬ ሰዓት ላይ ታቦተ ሕጉ ወደ መንበሩ ተመልሷል፡፡ በዚህም ምክንያት እስከአሁን በደረሰን መረጃ መሠረት በቤተ ክርስቲያን ቅጥር ከፍተኛ ረብሻ በመፈጠሩ ምክንያት ፩ ምእመን በተተኮሰው አስለቃሽ ጭስ ታፍነው ሕይወታቸውን ማጣታቸውን፣ አገልጋይ ካህናት አባቶች፣ ምእመናን እና ምእመናት ከፍተኛ የሆነ አካላዊ እና ሥነ ልቡናዊ ጉዳት ደርሶባቸዋል፤ ከ፲፭ ያላነሱ የሰንበት ትምህርት ቤት አገልጋይ ተማሪዎች በደረሰባቸው ጉዳት ምክንያት ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል፡፡  ይህ ድርጊት ከተፈፀመ በኋላም መንግሥት የቤተ ክርስቲያኒቱን ክብርና ልዕልና በመዳፈር በቤተ ክርስቲያን ላይ ይህን በደል የፈፀሙ የጸጥታ መዋቅር አካላትን ለሕግ ያቀርባል፣ እንደ መንግሥት ኃላፊነቱን ይወጣል ብለን ብንጠብቅም የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ቢሮ በዓሉን አስመልክቶ በዕለቱ ባወጣው መግለጫ ችግሩን የፈጠሩት አካላት ‹‹የአደባባይ በዓሉን ለመረበሽ ሲያቅታቸው በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የሚደረገውን ኃይማኖታዊ በዓል ለመረበሽ ሞክረዋል፡፡ የጸጥታ መዋቅሩ ችግሩን ለመቆጣጠር በወሰደው እርምጃ ጉዳቱን ለመቀነስ ችሏል›› ሲል የችግሩን ሁኔታ ገልጧል፡፡ በዚህ መግለጫውም ላይ አሁንም ችግሩ የሌሎች ቡድኖች እንደሆነና የቤተ ክርስቲያኒቱን በዓል የረበሸው የእነዚህ አካላት እንቅስቃሴ ነው በማለት የሰጠው መግለጫ በቦታው ላይ ከነበረው እውነታ በእጅጉ የራቀ እና ድርጊቱ የተወሰኑ ግለሰቦች ሳይሆን የመንግሥት እውቅና ያለው መሆኑን እንዲሁም መንግሥት ችግሩን ለማረም እና መፍታት ፍላጎት የሌለው መሆኑን እንድንረዳ አድርጎናል፡፡ የቤተ ክርስቲያን በዓል እንዲረበሽ እና ምእመናን ህይወታቸውን እንዲያጡ እንዲሁም እንዲጎዱ ያደረገው ከመንግሥት የጸጥታ መዋቅር የተተኮሰው አስለቃሽ ጭስ እና ጥይት መሆኑ ለሁሉም የታወቀ ሆኖ እያለ ጉዳዩን ወደ ሌላ አካል ለማላከክ የተሄደበትን ርቀት ቤተ ክርስቲያን በፍፁም የምትቀበለው አይሆንም፡፡ የመንግሥት የፀጥታ አካል በቤተ ክርስቲያን ቅጥር ግቢ አስለቃሽ ጭስ በመተኮስ ምእመናን ላይ ጉዳት ሲያደርስ እና የቤተ ክርስቲያንን ክብር ሲያጎድፍ ይህ የመጀመሪያው አይደለም፡፡ በጥር ፩ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም በቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን በተሰበሰቡ ምእመናን ላይ በቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ አስለቃሽ ጭስ በመተኮስ ብዙምእመናን እንዲጎዱ የተደረገ ሲሆን በጊዜው መንግሥት ይህን ድርጊት በፈጸሙ አካላት ላይ እርምጃ ከመውሰድ ይልቅ ልክ እንደአሁኑ ችግሩ የሕገ ወጦች ነው በማለት ለድርጊቱ እውቅና ሰጥቶት አልፏል፡፡ በዚህ ድርጊት መንግሥት በጸጥታ መዋቅሩ ውስጥ ያሉ እና መንግሥትንና ሕዝብን እንዲሁም ተገቢ ያልሆነ ያለመግባባት የሚያባብሱትን ግለሰቦች እና አመራሮች ለይቶ እርምት ከመውሰድ ይልቅ ሕዝብና መንግሥትን ሆድና ጀርባ የሚያደርግ ተግባሩን አስፋፍቶ ቀጥሏል፡፡ በመሆኑም መንግሥት ለዘመናት የኖረች እና ከግማሽ የሀገሪቱ ህዝብ በላይ የያዘችን ቤተ ክርስቲያን ክብርና ልዕልና በሚዳፈር መልኩ በተፈጸመው ሕገ ወጥ ተግባር ላይ የተሳተፉ እና ይህን ድርጊት የፈጸሙ የጸጥታ አካላትና እንዲፈፀም ያዘዙ የመንግሥት ኃላፊዎችን በ፲፭ ቀናት ጊዜ ውስጥ ለይቶ በሕግ እንዲጠየቁ እንዲያደርግ እና ይህንንም ለቤተ ክርስቲያኒቱም ሆነ ለሕዝበ ክርስቲያኑ በግልጽ እንዲያሳውቅ እንዲሁም በተለመደው የሀሰት ውንጀላ በዓላችንን በማክበር ላይ እያሉ የመንግሥት የፀጥታ አካላት በፈፀሙት ሕገ ወጥ ተግባር ምክንያት

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፲ኛ ዓመት በዓለ ሲመት ዛሬ ተከብሯል። የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይ
+2
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፲ኛ ዓመት በዓለ ሲመት ዛሬ ተከብሯል። የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖትን 10ኛ ዓመት በዓለ ሢመት ዛሬ የካቲት 24 ቀን 2015 ዓ/ም  በመንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተከብሯል። በትላንትናው ዕለትም ፲ኛ ዓመት በዓለ ሢመት በማስመልከት ዜና መዋዕል ዘብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክና ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ የተሰኙ መጽሐፍት ተመርቀዋል። መጽሐፍቱ የቅዱስነታቸውን የሕይወት ታሪክ፣ ባለፉት ፲ ዓመታት በሀገር ውስጥና በውጪ ሀገራት ያከናወኗቸውን ዋና ዋና ሥራዎችን፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎችን፣ ቤተ ክርስቲያን ባለፉት ፲ ዓመታት በስኬት ያከናወነቻቸው ዋና ዋና ተግባራት እና የገጠሟትን ተግዳሮቶች ተከትሎ በቅዱስ ፓትርያርኩ የተላለፉ መልዕክታትን አጠቃሎ የያዘ መሆኑ ተገልጿል። መጻሕፍቱን በውጪው ዓለም የሚገኙ ምዕመናን  በቀላሉ አግኝተው ማንበብ ይችሉ ዘንድም በቤተ ክርስቲያን ድረ ገጽ https://www.eotceth.org  ላይ እንዲጫን መደረጉን የኢኦተቤ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ አሳውቋል። ፎቶ: ተሚማ