fa
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

رفتن به کانال در Telegram

📈 تحلیل کانال تلگرام የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

کانال የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 14 296 مشترک است و جایگاه 6 167 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 365 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 14 296 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 20 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 492 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 16 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 52.64% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 13.12% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 7 523 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 875 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 29 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

توضیحی برای کانال ارائه نشده است.

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 21 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

14 296
مشترکین
+1624 ساعت
+1157 روز
+49230 روز
آرشیو پست ها
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን ! አንድነታችን ለቤተክርስቲያናችን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የጠቅላላ ጉባኤ የአቋም መግለጫ 1 በአንድነቱ የቀረበውን ዕቅድ ያፀደቅን ሲሆን ሁላችንም ለተግባራዊነቱ እንተጋለን ፡፡ 2 የሰ/ት/ቤትን ዝማሬን በተመለከተ ጉባኤው ተወያይቶ ባፀደቀው መሰረት ሁሉም ሰ/ት/ቤት የሚጠቀምበትን ልብሰ ስብሀት የካህናት በተለይም የዲያቆናት  አክሊል የሆነና ተመሳሳይ የሆነ ከዚህ በኋላ የትኛውም ሰ/ት/ቤት እንዳይጠቀም፡፡ የልብሰ ስብሐትና የአክሊል ዓይነት ተወስኖ በመመሪያ እስኪወርድ ድረስ ከካህናትና ከዲያቆናት አልባሳትና አክሊል ውጪ ሰ/ት/ቤቶች ባላቸው ልብሰ ስብሐት እየተጠቀሙ እንዲቆዩ ተስማምተናል፡፡ 3 አዘማመርን በተመለከተ ያሬዳዊ ዜማን የጣሰ ወደ ጭፈራ ያደላ አዘማመር እንዲቆም ይህንንም ለማስፈፀም ከክፍለ ከተማ አንድነት ክትትል እንዲያደርግ ተስማምተናል፡፡ 4 የአጫበር ስም እየተተገበረ ያለ አዘማመርን በተመለከተ የዘርፉ ሊቃውንትን ጨምሮ ብዙአባቶችን እና ምዕመናንን ያሳዘነ ጉዳይ በመሆኑ በሊቃውንት ተጠንቶ በቅድስት ቤተክርስቲያን ውሳኔ ተላልፎ እስኪተገበር ድረስ ሁሉም ሰንበት ትምህርት ቤት የአጫበር ስም የሚደረግ ዝማሬን እንዲያቆሙ፡፡ 5 ከላይ በተጠቀሱት የአለባበስና አዘማመር ጉዳይ በሀገረ ስብከት መመሪያ እንዲተላለፍ እና ሰበካ ጉባኤያት ቁጥጥር እንዲያደር ተስማምተናል፡፡ 6 የ2018ዓ/ም የአጥቢያ የሰ/ት/ቤት የአመራር ምርጫ ለማስፈፀም ጉባኤው የተስማማ ሲሆን የምርጫ ወቅቱ እስከሚደርስ ድረስ አሁን ያለ ሁሉም  አመራር በአዲስ እያደራጀ እንዲቆይ እና ምንም አይነት የሰንበት ትምህርት ቤት አመራር ምርጫ እንዳይካሄድ እና የተለየ ችግር ያለባቸው ሰ/ት/ቤቶች ብቻ ክክፍለ ከተማ አንድነቱ ጋር እየተወያዩ አደራጅ ጊዜያዊ ኮሚቴ እንዲያቋቁሙ ተስማምተናል ፡፡ 7  የሰንበት ትምህርት ቤቶችን መረጃ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ዘመኑን በዋጀ መልኩ ለማራጀት በአንድነቱ በተዘጋጀው ፖርታል እንድንጠቀም የራሳቸው ዳታ ቤዝ ያላቸው ሰ/ት/ቤቶች ከሀገረ ስብከቱ አንድነት ዳታ ቤዝ ጋር እንዲያናብቡ እና በየደረጃው የሚያድገውን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ሁሉም ሰ/ት/ቤቶች ሀዋርያዊ አገልግሎታችንን ለመፈፀም በጋራ ለመስራት ተስማምተናል፡፡  የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉 Website

በሥርዓተ ትምህርቱ መሠረት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ለነበሩት የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሰንበት ተማሪዎች የማጠቃለያ ፈተና ተሰጠ። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) ሐምሌ 27 2017 ዓ.ም የሰ/ት/ቤቶች
+4
በሥርዓተ ትምህርቱ መሠረት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ለነበሩት የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሰንበት ተማሪዎች የማጠቃለያ ፈተና ተሰጠ። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) ሐምሌ 27 2017 ዓ.ም የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምርያ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት በትግበራ ላይ በሚገኘው ሥርዓተ ትምህርት መሠረት ለተማሩ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በዛሬው ዕለት በ5 የተለያዩ የመፈተኛ ማዕከላት የማጠቃለያ ፈተና ሰጥቷል። ለምዘና የቀረቡ የየአጥቢያው ሰንበት ተማሪዎች በ2015 ዓ.ም በሀገረ ስብከት ደረጃ የሚዘጋጀውን የ10ኛ ክፍል ፈተና የወሰዱና ከክፍል ክፍል ተሸጋግረው ለዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ፈተና የደረሱ ተማሪዎች ሲሆኑ በ3 ሀገረ ስብከት ማለትም አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ፣ ሸገር ሀገረ ስብከት እና ጉራጌ ሀገረ ስብከት ላይ የሚገኙ 15 አጥቢያ ሰንበት ት/ቤቶች ምዘናውን ወሰደዋል። ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት 12 አጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች ምዘናውን የወሰዱ ሲሆን ከሸገር ሀገረ ስብከት አንድ እንዲሁም ከጉራጌ ሀገረ ስብከት ደግሞ 2 አጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች በጠቅላላም 268 ተማሪዎች የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል የማጠቃለያ ምዘናን ወስደዋል። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉 Website

ለ4ኛ እና ለ8ኛ ክፍል የሰ/ት/ቤት ተማሪዎች አኅጉረ ስብከት አቀፍ የሚኒስትሪ ፈተና ለመስጠት ዝግጅት ማጠናቀቁን የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት አስታወቀ፡፡ በመንበረ ጵጵስና ፤ በቢሾፍቱና አካባቢው ፤ በዱግዳ ፣ በአዳሚ ቱሉ ጅዶ ኮምቦልቻ ፣ በፈንታሌ እና በቦሰት ወረዳ ቤተ ክህነት ስር የሚገኙና የ4ኛ እና የ8ኛ ክፍል የሰ/ት/ቤት ትምህርቶችን ሲማሩ ለቆዩ ተማሪዎች በ27/11/2017 ዓ.ም ፈተናውን ለመስጠት ዝግጅቱን ማጠናቀቁን የምሥራቅ ሸዋ ሀ/ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መላከ ሳሕል ቀሲስ ነጋሽ ሀብተወልድ በቀን 24/11/2017 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል፡፡ የሀ/ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ በ6ቱ ወረዳ ቤተ ክህነት በተመረጡ የፈተና ጣቢያዎች በሚሰጠው ፈተና ፤ የወረዳ ቤተክህነት ሥራ አስኪያጆች ፤ የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች በቦታው በመገኘት በጸሎት እንዲስጀምሩም መመሪያ አስተላልፈዋል፡፡ የፈተና ዝግጅትን አስመልክቶ የምሥራቅ ሸዋ ሀ/ስብከት የሰ/ት/ቤቶች ክፍል ኃላፊ ሊቀ ካህናት ቀሲስ ሻውል ታዬ በሰጡት ተጨማሪ ማብራሪያ ፈተናው የተዘጋጀው ለሁሉም የትምህርት ዓይነቶች ለየብቻቸው በአማርኛ እና በአፋን ኦሮሞ ቋንቋዎች መሆኑን ገልጸው ፤ ሥርዓተ ትምህርቱ በተደራጀ ሁኔታ መተግበሩ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ልጆች ያለው ጠቀሜታ ዘርፈ ብዙ በመሆኑ የሀ/ስብከቱ አንድነት ወደፊትም በሥርዓተ ትምህርቱ ትግበራ ላይ በስፋት እንደሚሠራ ጠቁመዋል፡፡ ፈተናው ከጠዋቱ 2፡30 እስከ ቀኑ 11፡00 ሰዓት ድረስ የምሳ ሰዓትን ሳይጨምር የሚሰጥ መሆኑም በመግለጫው ተገልጿል፡፡ የሀ/ስብከቱ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት በበኩሉ አስፈላጊውን መመሪያ በመስጠት፤ ክትትል በማድረግና ለሥርዓተ ትምህርቱ ትግበራና ለፈተና ዝግጅት የሚያስፈልጉ ልዩ ልዩ ወጪዎችን በመሸፈን በብጹዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ መመሪያ ሰጭነት ሀ/ስብከቱ እያደረገ ላለው እገዛ ከፍተኛ ምሥጋና አቅርቧል፡፡ በተጨማሪም ትምህቱን በማስተማር ፣ ለፈተናው ጥያቄ በማዘጋጀት ፣ በትርጉም ሥራ እና በአጠቃላይ ሥርዓተ ትምህርቱን በልዩ ልዩ መንገዶች እየደገፉ ለሚገኙ አካላት ምሥጋና ቀርቧል፡፡ መረጃው የምሥራቅ ሸዋ ሀ/ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ነው፡፡ (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉 Website

የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ሐምሌ 26/2017 ዓ.ም እና ሐምሌ 27/2017 ዓ.ም  የ11ኛ ዓመት  2ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ይካሄዳል፡፡ የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ከሌላው ጊዜ ተጠናክሮ መንፈሳዊ አገልግሎት እየሰጠ እንዳለ ይታወቃል፡፡ በዚህም ጠቅለለ ጉባዔው የ2018 ዓ.ም እቅድ ማጽደቅ ፣ በተመረጡ እና ወቅታዊ በሆኑ የአገልግሎት አጀንዳዎች ላይ ውይይቶች ማድረግ ፤ እንዲሁም  የ2017 ዓ.ም የሥራ አፈጻጸምን መለስ ብሎ ለማየትና በጥንካሬው ለመቀጠልና ከድክመቱ ለመማር ይረዳ ዘንድ 11ኛ ዓመት  2ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ለማድረግ በሰፊ ዝግጅት ላይ ይገኛል። በጉባኤው ላይም ሊቃነ ጳጳሳት ፣ የሀገረ ስብከቱ ስራ አስኪያጅ  የጉባኤው መደበኛ አባል የሆኑ  የየሰንበት ት/ቤቶች ስራ አመራሮች እና አንድነቱን ሲያገግሉ የነበሩ የቀድሞ አመራሮች እንዲሁም በተጋባዥ  እንግድነት የየክፍለ ከተማው ስራ አስኪያጆች ፣ የአድባራት እና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ፣ የየሰበካ ጉባኤው ምክትል ሊቃነ መናብርት ፣ የማኅበራት ተወካዮች ይገኛሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ  ከሰንበት ት/ቤቶች እንድነት ጽሕፈት ቤት ያገኝነው መረጃ ያመለክታል። ጉባዔው ለሁለት ቀናት የሚቆይ ሲሆን ቅዳሜ ማለትም በ26/11/2017 ዓ/ም  ከቀኑ 8፡00 _ 12፡ 00 ሰዓት በተያዘለት መርሓግብር መሰረት የየሰንበት ት/ቤቶች ሥራ አመራሮች በሙሉ  እና ተጋባዥ እንግዶች የሚገኙ ሲሆን እሑድ ማለትም 27/11/2017 ዓ/ም ከጠዋቱ 3፡00_ 12፡00 ሰዓት የየሰንበት ት/ቤቶች ጽ/ቤት አመራሮች በተመረጡ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይቶች እና የውሳኔ ሃሳቦች እንደሚሰጡ ይጠበቃል በተለይም አሁን ላይ እየታዩ ያሉ የሰንበት ት/ቤት የአዘማመር ጉዳዮች እና አዲሱን መዋቅር ትግበራን ተከትሎ  ቀጣይ ዓመት የሚደረገው አጠቃላይ የገዳማት እና አድባራት ሰንበት ት/ቤት የሥራ አመራር ምርጫን በተመለከተ ሰፊ ውይይት ይደረግበታል ተብሎ  ይጠበቃል  ። በመሆኑም የየሰንበት ት/ቤቶች የሥራ አመራሮች በሙሉ በተጠቀሰው ቀን በመገኘት  የውይይቱ አካል እንዲሆኑ እና በየሰንበት ት/ቤቶች ተግባራዊ በሚሆኑ ጉዳዮች ላይ ሐሳባቸውን እንዲሰጡ  አንድነቱ በጥብቅ አሳስቧል። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉 Website

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የሁሉም መዋቅር በጠቅላላ ጉባኤ ውይይት አቅጣጫ መሠረት ስልታዊ ዕቅድ እስከ ዋና ተግባር የያዘውን በድረገጻችን ላይ ከታች በተቀመጠው ማስፈንጠሪያ (link) ገብታችሁ የምታገኙ ሲሆን እንደ መዋቅራችሁ አግባብና እንደ አገልግሎቱ ስፋት ዝርዝር ተግባራትን የማዘጋጀት እና ተጨማሪ አካባቢያዊ ሁኔታዎችን በማካተት የሚተገበር ሲሆን በየደረጃው ያለው የስንበት ት/ቤቶች አመራር በሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ድረ ገጽ በመግባት ስልክ ቁጥር ወይም ኢሜይሉን በማስገባት መጠቅም የሚችል ይሆናል፡፡ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/የ2018-2021-ስልታዊ-እቅድ/ 👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆 (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉 Website

ሦስተኛው የአህጉረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና የምርቃት መርሐ ግብር ተከናወነ። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) ሐምሌ 21 / 11 / 2017 ዓ.ም ሦስተኛው የአህጉረ ስብከቶች የሰ/ት/ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና የምርቃት መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ ተከናውኗል። በምረቃ መርሐ ግብሩ ላይም ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅና የሸገር ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ የምስካየ ኅዙናን ገዳም የበላይ ጠባቂ እና የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ ሰብሳቢ ፣ ብፁዕ አቡነ ኤጲፋኒዮስ የምሥራቅ ጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ በርናባስ የዋግህምራ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወልደ ትንሣኤ የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሐላፊ ፣ ዲ.ን ስንታየሁ ምስጋናው የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ተ/ም/ሰብሳቢ ፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ሓላፊዎች ፣ መምህራነ ወንጌል ፣ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የሥራ አመራር አባላት ተገኝተዋል። ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ባስተላለፉት መልእክት "ጌታችን በመዋዕለ ሥጋዌው ለ3 ዓመት ከ3 ወር ሐዋርያትን ከተለያየ ግብርና ክፍል መርጦ ካስተማራቸው በኋላ ሂዱና አስተምሩ በሀገር ሁሉ ቋንቋ አስተምሩ ብሎ እንዳዘዛቸውና አልጫ የሆነውን ዓለም በማስተማር እንዳጣፈጡ ሁሉ እናንተም በተማራችሁት ትምህርት ሄዳችሁ እንድታስተምሩ ፣ እንድታሰለጥኑ ፣ ፍሬ እንድታፈሩ" በማለት አባታዊ ምክርና ቃለ ቡራኬ ሰጥተዋል። ብፁዕ አቡነ ኤጲፋንዮስ የምሥራቅ ጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስም እንዲሁ "ከእግዚአብሔር የተላከ ከእግዚአብሔር የተመረጠ የአምላኩ የእግዚአብሔርን ቃል ይናገራል" በሚል ኃይለ ቃል ተነስተው እርሱን ለማገልገል የሚጠራ ማንኛውም አገልጋይ የእግዚአብሔርን ዓላማ ፣ ሐሳብ የእርሱን ዕቅድና እርሱ ለሰው ያለውን አምላካዊ ጥበብ ፣ መግቦት በፍጥረቱም ላይ እንዴት እንደሚሠራና ጥልቅ የሆነውን ፍቅሩን ሁሉ ይናገራል። ብለው ወደ መጣችሁበት ስንቃችሁን ያዛችሁ በመሄድ በሚገባ አገልግሎታችሁን እንድትፈጽሙ ይሁን በማለት አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈው ቋጭተዋል። በዕለቱ ሌላኛውን አባታዊ መልእክት ያስተላለፉት ብፁዕ አቡነ በርናባስ የዋግህምራ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስም እንዲሁ "በአባቶች ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ" የሚለውን የልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት ቃል መነሻ አድርገው እናንተም በአባቶቻችሁ ፈንታ የተተካችሁ እንደመሆናችሁ አባቶቻችሁን መስላችሁ ቤተ ክርስቲያንን ልታገለግሉ ይገባል በማለት ለተመራቂ መምህራን የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሐላፊ መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወልደ ትንሣኤ "መጻሕፍት እግዚአብሔርን ወደ ማድነቅ ልብህን ይመሩታልና" በሚል ኃይለ ቃል በመነሣት የማደራጃ መምሪያውን መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ተ/ም/ሰብሳቢ ዲያቆን ስንታየሁ ምስጋናው በሥልጠናው ጊዜ አጠቃላይ የተከወኑ ተግባራትና በቀጣይ እንዲሠሩ የሚፈለጉ ጉዳዮች ላይ ገለጻ አድርገዋል። ሠልጣኝ መምህራኑም የነበራቸውን የ15 ቀን ቆይታ የተመለከተ ዘገባ እና አቋማቸውንም እንዲሁ በተወካያቸው በኩል አቅርበው ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እጅ የዕውቅና የምስክር ወረቀታቸውን ተቀብለው የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል። ሥልጠናው ከሐምሌ 7 እስከ ሐምሌ 20 ቀን ድረስ በተከታታይ ለ15 ቀናት የተሰጠ ሲሆን በሥልጠናውም ላይ ከ30 አህጉረ ስብከት የተወጣጡ 209 መምህራን ተከታትለው አጠናቅቀዋል። ከነዚህም መካከል 106 ቀሳውስትና ዲያቆናት እንዲሁም 8 ሴቶች ይገኙበታል። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉 Website

ሦስተኛው የአህጉረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና የምርቃት መርሐ ግብር ተከናወነ። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) ሐምሌ 21 / 11 / 2017 ዓ.ም ሦስተኛው የአህጉረ ስብከቶች የሰ/ት/ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና የምርቃት መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ ተከናውኗል። በምረቃ መርሐ ግብሩ ላይም ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅና የሸገር ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ የምስካየ ኅዙናን ገዳም የበላይ ጠባቂ እና የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ ሰብሳቢ ፣ ብፁዕ አቡነ ኤጲፋኒዮስ የምሥራቅ ጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ በርናባስ የዋግህምራ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወልደ ትንሣኤ የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሐላፊ ፣ ዲ.ን ስንታየሁ ምስጋናው የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ተ/ም/ሰብሳቢ ፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ሓላፊዎች ፣ መምህራነ ወንጌል ፣ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የሥራ አመራር አባላት ተገኝተዋል። ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ባስተላለፉት መልእክት "ጌታችን በመዋዕለ ሥጋዌው ለ3 ዓመት ከ3 ወር ሐዋርያትን ከተለያየ ግብርና ክፍል መርጦ ካስተማራቸው በኋላ ሂዱና አስተምሩ በሀገር ሁሉ ቋንቋ አስተምሩ ብሎ እንዳዘዛቸውና አልጫ የሆነውን ዓለም በማስተማር እንዳጣፈጡ ሁሉ እናንተም በተማራችሁት ትምህርት ሄዳችሁ እንድታስተምሩ ፣ እንድታሰለጥኑ ፣ ፍሬ እንድታፈሩ" በማለት አባታዊ ምክርና ቃለ ቡራኬ ሰጥተዋል። ብፁዕ አቡነ ኤጲፋንዮስ የምሥራቅ ጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስም እንዲሁ "ከእግዚአብሔር የተላከ ከእግዚአብሔር የተመረጠ የአምላኩ የእግዚአብሔርን ቃል ይናገራል" በሚል ኃይለ ቃል ተነስተው እርሱን ለማገልገል የሚጠራ ማንኛውም አገልጋይ የእግዚአብሔርን ዓላማ ፣ ሐሳብ የእርሱን ዕቅድና እርሱ ለሰው ያለውን አምላካዊ ጥበብ ፣ መግቦት በፍጥረቱም ላይ እንዴት እንደሚሠራና ጥልቅ የሆነውን ፍቅሩን ሁሉ ይናገራል። ብለው ወደ መጣችሁበት ስንቃችሁን ያዛችሁ በመሄድ በሚገባ አገልግሎታችሁን እንድትፈጽሙ ይሁን በማለት አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈው ቋጭተዋል። በዕለቱ ሌላኛውን አባታዊ መልእክት ያስተላለፉት ብፁዕ አቡነ በርናባስ የዋግህምራ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስም እንዲሁ "በአባቶች ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ" የሚለውን የልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት ቃል መነሻ አድርገው እናንተም በአባቶቻችሁ ፈንታ የተተካችሁ እንደመሆናችሁ አባቶቻችሁን መስላችሁ ቤተ ክርስቲያንን ልታገለግሉ ይገባል በማለት ለተመራቂ መምህራን የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሐላፊ መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወልደ ትንሣኤ "መጻሕፍት እግዚአብሔርን ወደ ማድነቅ ልብህን ይመሩታልና" በሚል ኃይለ ቃል በመነሣት የማደራጃ መምሪያውን መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ተ/ም/ሰብሳቢ ዲያቆን ስንታየሁ ምስጋናው በሥልጠናው ጊዜ አጠቃላይ የተከወኑ ተግባራትና በቀጣይ እንዲሠሩ የሚፈለጉ ጉዳዮች ላይ ገለጻ አድርገዋል። ሠልጣኝ መምህራኑም የነበራቸውን የ15 ቀን ቆይታ የተመለከተ ዘገባ እና አቋማቸውንም እንዲሁ በተወካያቸው በኩል አቅርበው ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እጅ የዕውቅና የምስክር ወረቀታቸውን ተቀብለው የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል። ሥልጠናው ከሐምሌ 7 እስከ ሐምሌ 20 ቀን ድረስ በተከታታይ ለ15 ቀናት የተሰጠ ሲሆን በሥልጠናውም ላይ ከ30 አህጉረ ስብከት የተወጣጡ 209 መምህራን ተከታትለው አጠናቅቀዋል። ከነዚህም መካከል 106 ቀሳውስትና ዲያቆናት እንዲሁም 8 ሴቶች ይገኙበታል። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉 Website

ሦስተኛው የአህጉረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና የምርቃት መርሐ ግብር ተከናወነ። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) ሐምሌ 21 / 11 / 2017 ዓ.ም ሦስተኛው የአህጉረ ስብከቶች የሰ/ት/ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና የምርቃት መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ ተከናውኗል። በምረቃ መርሐ ግብሩ ላይም ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅና የሸገር ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ የምስካየ ኅዙናን ገዳም የበላይ ጠባቂ እና የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ ሰብሳቢ ፣ ብፁዕ አቡነ ኤጲፋኒዮስ የምሥራቅ ጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ በርናባስ የዋግህምራ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወልደ ትንሣኤ የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሐላፊ ፣ ዲ.ን ስንታየሁ ምስጋናው የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ተ/ም/ሰብሳቢ ፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ሓላፊዎች ፣ መምህራነ ወንጌል ፣ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የሥራ አመራር አባላት ተገኝተዋል። ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ባስተላለፉት መልእክት "ጌታችን በመዋዕለ ሥጋዌው ለ3 ዓመት ከ3 ወር ሐዋርያትን ከተለያየ ግብርና ክፍል መርጦ ካስተማራቸው በኋላ ሂዱና አስተምሩ በሀገር ሁሉ ቋንቋ አስተምሩ ብሎ እንዳዘዛቸውና አልጫ የሆነውን ዓለም በማስተማር እንዳጣፈጡ ሁሉ እናንተም በተማራችሁት ትምህርት ሄዳችሁ እንድታስተምሩ ፣ እንድታሰለጥኑ ፣ ፍሬ እንድታፈሩ" በማለት አባታዊ ምክርና ቃለ ቡራኬ ሰጥተዋል። ብፁዕ አቡነ ኤጲፋንዮስ የምሥራቅ ጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስም እንዲሁ "ከእግዚአብሔር የተላከ ከእግዚአብሔር የተመረጠ የአምላኩ የእግዚአብሔርን ቃል ይናገራል" በሚል ኃይለ ቃል ተነስተው እርሱን ለማገልገል የሚጠራ ማንኛውም አገልጋይ የእግዚአብሔርን ዓላማ ፣ ሐሳብ የእርሱን ዕቅድና እርሱ ለሰው ያለውን አምላካዊ ጥበብ ፣ መግቦት በፍጥረቱም ላይ እንዴት እንደሚሠራና ጥልቅ የሆነውን ፍቅሩን ሁሉ ይናገራል። ብለው ወደ መጣችሁበት ስንቃችሁን ያዛችሁ በመሄድ በሚገባ አገልግሎታችሁን እንድትፈጽሙ ይሁን በማለት አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈው ቋጭተዋል። በዕለቱ ሌላኛውን አባታዊ መልእክት ያስተላለፉት ብፁዕ አቡነ በርናባስ የዋግህምራ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስም እንዲሁ "በአባቶች ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ" የሚለውን የልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት ቃል መነሻ አድርገው እናንተም በአባቶቻችሁ ፈንታ የተተካችሁ እንደመሆናችሁ አባቶቻችሁን መስላችሁ ቤተ ክርስቲያንን ልታገለግሉ ይገባል በማለት ለተመራቂ መምህራን የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሐላፊ መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወልደ ትንሣኤ "መጻሕፍት እግዚአብሔርን ወደ ማድነቅ ልብህን ይመሩታልና" በሚል ኃይለ ቃል በመነሣት የማደራጃ መምሪያውን መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ተ/ም/ሰብሳቢ ዲያቆን ስንታየሁ ምስጋናው በሥልጠናው ጊዜ አጠቃላይ የተከወኑ ተግባራትና በቀጣይ እንዲሠሩ የሚፈለጉ ጉዳዮች ላይ ገለጻ አድርገዋል። ሠልጣኝ መምህራኑም የነበራቸውን የ15 ቀን ቆይታ የተመለከተ ዘገባ እና አቋማቸውንም እንዲሁ በተወካያቸው በኩል አቅርበው ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እጅ የዕውቅና የምስክር ወረቀታቸውን ተቀብለው የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል። ሥልጠናው ከሐምሌ 7 እስከ ሐምሌ 20 ቀን ድረስ በተከታታይ ለ15 ቀናት የተሰጠ ሲሆን በሥልጠናውም ላይ ከ30 አህጉረ ስብከት የተወጣጡ 209 መምህራን ተከታትለው አጠናቅቀዋል። ከነዚህም መካከል 106 ቀሳውስትና ዲያቆናት እንዲሁም 8 ሴቶች ይገኙበታል። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉 Website

"የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።" መዝ 33(34) ፡ 7 እንኳን ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ! ሐምሌ 19 በዚህች ዕለት ቅዱስ ገብርኤል
"የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።" መዝ 33(34) ፡ 7 እንኳን ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ! ሐምሌ 19 በዚህች ዕለት ቅዱስ ገብርኤል ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስን እና እናቱን ቅድስት እየሉጣን ከእሳት ያደነበት ዕለት ነው! መልካም በዓል! (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉 Website

ብፁዕ አቡነ ቀለሜንጦስ የክረምት የመምህራን አሰልጣኞች ሥልጠና እየወሰዱ ያሉ መምህራንን ጎበኙ። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) ሐምሌ 18/11/2017ዓ.ም በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በሰን
+1
ብፁዕ አቡነ ቀለሜንጦስ የክረምት የመምህራን አሰልጣኞች ሥልጠና እየወሰዱ ያሉ መምህራንን ጎበኙ። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) ሐምሌ 18/11/2017ዓ.ም በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት አዘጋጅነት በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩንቨርስቲ እየተሰጠ የሚገኘው የክረምት የመምህራን የአሰልጣኞች ስልጠና ላይ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ እና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀለሜንጦስ በመገኘት አባታዊ መልዕክት አስተላልፈዋል። ብፁዕነታቸው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለልጁ ለጢሞቴዎስ የተናገረውን "ለወንድሞችህ ይህንን አስተምራቸው" የሚለውን ኃይለ ቃል መነሻ አድርገው አባታዊ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ልጄ ሆይ ጆሮህን ለመምህራን ስጥ እንደተባለ ከመምህራን እግር ስር ቁጭ ብለው የሚማሩት ቃለ እግዚአብሔር ለሕይወታች ስንቅ ነውና ቅዱስ ጢሞቴዎስን አብነት አድርጎ በሕይወት መተርጎም ይገባል የተማርነውንም ለወንድሞች ማስረዳት መንገር ይገባል ብለዋል። በመጨረሻም ሰልጣኞች በተከታታይ በቀንም በማታም እየተሰጣቸው ያለውን ሥልጠና በሚገባ ተከታትለው በየሀገረ ስብከታቸው ሲመለሱ በትኩረት ሊሰሩ ለሌሎችም ሊያጋሩ እንደሚገባ አባታዊ መልዕክት አስተላልፈዋል። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉 Website