የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
رفتن به کانال در Telegram
نمایش بیشتر
📈 تحلیل کانال تلگرام የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
کانال የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 843 مشترک است و جایگاه 5 321 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 154 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 843 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 02 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 562 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 10 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 37.65% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 10.49% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 5 962 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 1 661 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 44 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
توضیحی برای کانال ارائه نشده است.
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 03 سپتامبر, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کردهاند.
15 843
مشترکین
+1024 ساعت
+657 روز
+56230 روز
آرشیو پست ها
"#ቤተ_ክርስቲያን_በዚህ_መልክ አስተምራ ያስመረቀቻችሁ በሌላኛው የሕይወት ገጽ የተማራችሁትን የዓለማዊ ትምህርትና እውቀት እንድትተው ሳይሆን ከመንፈሳዊ ትምህርቱ ጋር አጣጥማችሁና አቀናጅታትሁ ቤተ ክርስቲያን እንድታተርፍባችሁ ነው።" ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት በሥርዓተ ትምህርት መሠረት ያስተማራቸው 11,885 ተማሪዎች ጥቅምት 30/2018 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ ለ5ኛ ጊዜ አስመርቋል።
መርሐ ግብሩ ሕያውን የእግዚአብሔር ቃልና ግሩም ግብሩን እንዲሁም ወርኃ ጽጌን የሚገልጹ ዝማሬዎች ፣ ኪነ ጥበብ፣ ሥነ ጽሑፍ እና ስብከት እንዲሁም በብፁዓን አባቶች ትምህርተ ወንጌል ተሰጥቶበታል።
በዕለቱ የተመረቁ ተማሪዎች ከ164 ገዳማት እና አድባራት የተውጣጡ የሀገረ ስብከቱን ምዘና ወስደው ወደ ቀጣይ ክፍል የተዘዋወሩ 11,885 የሰንበት ት/ቤት የ4ኛ፣ የ8ኛ እና የ10ኛ ክፍል ተማሪዎች መሆናቸውን ላዕከ ኄራን መንክር ግርማ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶችን አድነት ተቀዳሚ ምክትል ሰብሰቢ ገልጸዋል።
ተማሪዎቹ በ8 የትምህርት ዘርፎች የተከፋፈለውን ሥርዐተ ትምህርት መሠረት በማድረግ በየገዳማቱና አድባራቱ ባሉ ሰንበት ት/ቤቶች ቅዳሜና እሑድ ትምርታቸውን የተከታተሉ መሆናቸውን አስታውሰዋል።
አክውለም "በዚሁ ሁሉ የቤተ ክርስቲያን ተልእኮ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ድጋፉና የኔባይነቱ በእጅጉ የሚያስመሰግን ሲሆን የዛሬውን የምርቃት መርሐ ግብር አስፈላጊ በሆነው በጀት በማገዝና የሥርዐተ ትምህርቱ መጻሕፍትን አጥቢያዎች ለየሰንበት ትምህርት ቤቱ እንዲገዙ ከማድረግና የምዝና ፈተና በሚሰጥበትም ወቅት ከብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ ጀምሮ በየቦታው በመዘዋወር ምልክታና ክትትል በማድረገቸው በእጅጉ ኮርተናል በልጅነት ልብም እናመሰግናለን" ብለዋል።
በመርሐ ግብሩ ለ160 ሰንበት ትምህርት ቤቶችና ከፍተኛ ነጥብ ላስመዘገቡ ተመራቂዎች፣ ሰንበት ት/ቤቶች እና ክፍለ ከተሞች ከአባቶች እጅ ቡራኬና ሽልማት ሲቀበሉ የጀሞ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት የዋንጫ ተሸላሚ።
በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሐላፊ የሆኑት መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወ/ትንሣኤ ተመራቂ ተማሪዎቹ ትምህርቱን በአግባቡ እንዲከታተሉ ዘወትር በመማርና በማንበብ እንዲተጉና ለቤተ ክርስቲያን ጠበቃ ሆነው እንዲቆሙ አሳስበዋል።
በምርቃት መርሐ ግብሩ አባታዊ መልእክት ያስተላለፉት ብፁዕ አቁነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባና የሀዲያ ስልጤ አህገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ባዩት መልካም ቤተ ክርስቲያናዊ ትልቅ ተግባር ተደንቀው የእግዚአብሔር መንግሥት ወንጌል በትውልድ እንዲጸና የተቀበሉትንም የእምነትና የእውቀት ቤተ ክርስቲያናዊ አደራቸውን እንዲጠብቁ ተመራቂዎችን አሳስበዋል።
ብፁዕነታቸው"ቤተ ክርስቲያን በዚህ መልክ አስተምራ ያስመረቀቻችሁ በሌላኛው የሕይወት ገጽ የተማራችሁትን የዓለማዊ ትምህርትና እውቀት እንድትተው ሳይሆን ከመንፈሳዊ ትምህርቱ ጋር አጣጥማችሁና አቀናጅታትሁ ቤተ ክርስቲያን እንድታተርፍባችሁ ነው።" ብለዋል።
ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ "በዚህ ሁሉ አገልግሎት ለሚታይ ቤተ ክርስቲያናዊ ስኬት በማድረስ ረገድ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የመንበረ ፓትርያክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደረጃ መምሪያ የበላይ ሊቀ ጳጳስ ሊመሰግኑ ይገባል የሀገረ ስብከቱ ዋና ክፍልና የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት መሪዎችና አስተባባሪዎችንም በእጅጉ እናመስግናልን" ብለዋል።
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ "አባቶቻችን የተረፋቸውን ሳይሆን ያላቸውን ሳይቀር ሳይሰስቱ ሰጥተው ያስረከቡንን ቤተ ክርስቲያን በእምነትና በእውቀት በመታዘዝ የተማርነውን ለሕይወት ዋጋ ማድረግ ይገባለናል" በማለት ለተመራቂዎች መልእክት አስተላላፈዋል።
በምርቃት መርሐ ግብሩ ላይ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባና የሀድያ ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ቀሌምጦስ የመንበረ ፓትርያርክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ምሕረት አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ፣ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ከፍተኛ የሥራ ሓላፊዎችና ሠራተኞች፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሥራ ሓላፊዎችና ሠራተኞች፣ የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ ሊቃነ መናብርት፣ የሰንበት ት/ቤት አመራሮች፣ መዘምራንና ጥሪ የተደረገላቸው በርካታ እንግዶች ተገኝቷል።
ዘገባው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ነው።
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
👉 Website
🎓🎓🎓 የተማሪዎች ምርቃት #4_ቀን_ቀረው 🎓🎓🎓
" ኅየንተ አበውኪ ተወልዱ ለኪ ደቂቅ "
{"በአባቶችሽ ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ"} (መዝ 44:16)
በ2017 ዓ.ም በሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ሥርዓተ ትምህርት መሠረት ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ እና በሀገረ ስብከት በብሔራዊ ደረጃ ምዘና ተደርጎላቸው ያለፉ #የ4ኛ , #የ8ኛ እና #የ10ኛ ክፍል #ከ11_000 በላይ ተማሪዎች ብጹዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ፤ አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፤ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ፤ የተመራቂ ተማሪ ወላጆች እንዲሁም ምዕመናን/ት በተገኙበት የምርቃት መርሐ ግብር ይከናወናል!!!
🎓🗓 #ጥቅምት_30_2018_ዓ_ም
🎓 🕰 #ከቀኑ_5_30_ጀምሮ
🎓 🏢 #በሚሊኒየም_አዳራሽ
አይቀርም!!! ኑ ተማሪዎቻችን በጋራ እንመርቅ!!!
የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት
🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓
የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የ2017 ዓ.ም 2ተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን አከናወነ።
የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የ2017 ዓ.ም 2ተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤን በሀገረ ስብከቱ የመሰብሰቢያ አዳራሽ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ፣ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሳሕል ቀሲስ ነጋሽ ሀብተወልድ፣ የሀገረ ስብከቱ የስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊ መጋቢ ሐዲስ አባ ኃይለ ገብርኤል ተስፋ፣ የሀገረ ስብከቱ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሐላፊ ሊቀ ካህናት ቀሲስ ሻውል ታዬ ፣ የሀገረ ስብከቱ እና ወረዳዎች አንድነት የሥራ አመራሮች ፣ ሰባኪያነ ወንጌል እና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ጥቅምት 23/2018 ተካሂዷል።
ጠቅላላ ጉባኤውም በጠዋት እና ከሰዓት መርሐ ግብር የተካሄደ ሲሆን የጠዋቱ መርሐ ግብር በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ጸሎተ ቡራኬ የተከፈተ ሲሆን የናዝሬት ደብረ ይድራስ ቅዱስ ጊዮርጊስ ፈለገ ሰማዕት ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት ዝማሬ አቅርበዋል። ብፁዕነታቸው ለጠቅላላ ጉባኤው ተሳታፊዎች አባታዊ መመሪያ በመስጠት ወጣቱ ዘመኑን ዋጀቶ እንዲያገለግል መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
የአንድነቱ የ2017 የሥራ ሪፓርት በአንድነቱ ጸሐፊ ወጣት ከተማ ደረጀ በኩል የቀረበ ሲሆን ከጠቅላላ ጉባኤውም በሪፓርቱ ዙሪያ ለተነሱ ጥያቄዎች ከሥራ አመራሩ ግብረ መልስ ተሰጥቶበት ሪፖርቱ በጠቅላላ ጉባኤው ጸድቋል። ከዚህ በመቀጠልም ከሀገረ ስብከቱ ከሚገኙ የወረዳዎች የተሻለ አፈፃፀም ያሳየውን የመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ያለውን ተሞክሮ በተወካዩ በኩል ለጠቅላላ ጉባኤው አቅርቧል።
በከሰዓቱ መርሐ ግብር ለጠቅላላ ጉባኤ አባላት ስድስት የመወያያ አጀንዳዎች ተሰጥቶ በቡድን በመሆን እንዲወያዩ ተደርጓል። የውይይቱ ሪፓርት ማጠቃለያም በጠቅላላ ጉባኤው ውሳኔዎች ውስጥ ተካተዋል፡፡
በመቀጠል በአንድነቱ ተቀዳሚ ም/ሰብሳቢ መ/ር ዓለምአንተ አበጀ የ2018 ዓ.ም ስልታው ዕቅድ ቀርቦ በቀረበው ዕቅድ ላይ ውይይት ተደርጎ በጠቅላላ ጉባኤው ፀድቋል። በማስከተል የሀገረ ስብከቱ አንድነት የጎደሉ የሥራ አመራር እና የሥራ አስፈጻሚ እጩ ቀርበው በጠቅላላ ጉባኤው ፀድቀዋል።
በዕለቱ የቀድሞው የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ማደራጃ ክፍል ሐላፊ ለነበሩት ለመጋቤ ሐዲስ ቆሞስ አባ ኃይለ ገብርኤል ተስፋ የሽኝት እና አሁን የማደራጃው ሐላፊ በመሆን እያገለገሉ ላሉት ለሊቀ ካህናት ቀሲስ ሻዉል ታዬ የእንኳን ደህና መጣችሁ የስጦታ መርሐ ግብር ከአንድነቱ ሥራ አመራር በብፁዕነታቸው አማካኝነት ተከናውኗል።
በመጨረሻም የጠቅላላ ጉባኤው ቃለ ጉባኤ እና የተወሰኑ ውሳኔዎች ተነቦ በጋራ ድምፅ ጸድቆ የማጠቃለያ ሀሳብ በማደራጃው ሐላፊ ሊቀ ካህናት ቀ/ሻውል ታዬ የቀረበ ቀርቦ በሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ የማሳረጊያ መልእክት አቅርበው አባታዊ መመሪያ ሰጥተው መርሐ ግብሩ ፍፃሜውን አግኝቷል፡፡
መረጃው የሀገረ ስብከቱ አንድነት ሚዲያ እና ህዝብ ግንኙነት ክፍል ነው፡፡
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
👉 Website
Repost from የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትቤቶች አንድነት ጥቅምት 30/2018ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ የሚያካሂደውን የምርቃት እና የጉባኤ መርሐግብር ዝግጅት ማጠናዘቀቁን የአንድነቱ የመረሐ ግብር አዘጋጅ አብይ ኮሚቴ አስታወቀ።
በእለቱ ከ164ገዳማት እና አድባራት የተውጣጡ የሀገረ ስብከቱን ምዘና ወስደው ወደ ቀጣይ ክፍል የተዘዋወሩ ከ11,800 በላይ የሰንበት ት/ቤት ተማሪዎች በብጹእ ወቅዱስ ፖትሪያሪኩ እና ብጹአን አባቶች ቡራኬ እንደሚመረቁ ኮሚቴው አሳውቋል።
መርሐግብሩ በሁለት ክፍል የተከፈለ ሲሆን የመጀመርያው ክፍል ጉባኤ ሲሆን ከቀኑ 6:00እስከ9:00 በዝማሬ፣በኪነጥበብ እና በቃለእግዚአብሔር የሚከናወን ሲሆን ፣
ሁለተኛው ክፍል የምርቃት መርሐግብር ሲሆን በመርሐግብሩም ተመራቂዎች ከብጹአን አባቶችቡራኬ ይቀበላሉ በውጤታቸው ከፍተኛ ነጥብ ያመጡ ተማሪዎች እና ሰንበት ት/ቤቶች ከአባቶች እጅ ሽልማት ይቀበላሉ በሁለተኛውም ምእራፍ በተመራቂዎች ዝማሬ እና በብጹአን አባቶች ትምህርት እና ቃለ ምእዳን እንደሚሰጥ የተገለጸ ሲሆን በእለቱ ሁሉም ሰንበት ት/ቤቶች ተመራቂ ተማሪዎች ነጭ ልብሳቸውን ለብሰው ከጠዋቱ 5:00 ሚሊኒየም አዳራሽ እንዲደርሱ ያሳሰበ ሲሆን ካለው የቦታ ጥበት አኳያ ተማሪዎች አመቺ ቦታ ለማግኘት በቅድሚያ ተገኝተው ቦታቸውን እንዲይዙ አሳስቧል ፣ ወላጆች ምእመናን የገዳማት እና አድባራት አስተዳዳሪዎች የሰበካ ጉባኤ ምክትል ሊቃነመናብርት፣ የሰንበት ት/ቤት አመራሮች መዘምራን ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ከ5:30ጀምሮ ወደ አዳራሹ መግባት እንደሚችሉ እና ጉባኤው ከቀኑ6:00 በጸሎተ ወንጌል እንደሚጀመር ኮሚቴው አብራርቷል።
በመጨረሻም በዚህ ጉባኤ ምእመናን በነጻ መሳተፍ እንደሚችሉ ያሳወቀ ሲሆን ለጉባኤው የሚያስፈልጉ ቅድመዝግጅት መጠናቀቁን እና መርሐግብሩን ለማከናወን እለቱን በጉጉት እየጠበቅን ነው ሲል አብይ ኮሚቴው በመግለጫው አብራርቷል።
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የምርቃት አብይ ኮሚቴ።
#አስቸኳይ_መልዕክት
የመጻሕፍት ሥርጭትን በተመለከተ ለሁሉም ሀገረ ስብከት
እንደሚታወቀው ከ1-7ኛ ክፍል በአማርኛ እንዲሁ ከ1-4ኛ ክፍል በአፋን ኦሮሞ መማርያ መጻሕፍት ታትመው ለየሀገረ ስብከቱ ስናሰራጭ መቆየታችን ይታወቃል።
ከእነዚህ መጻሕፍት መካከል ከ1ኛ እስከ 4ኛ ክፍል የአማርኛ መጻሕፍት በአሁኑ ሰዓት ሙሉ ለሙሉ ተሽጠው ያለቁ መሆኑን እየገለጽን ከ1-4ኛ ክፍል መጻሕፍት ለኹለተኛ ሕትመት ፍላጎታችሁን ከአሁኑ እንድታሳውቁ፤ እንዲሁ ከ5ኛ እስከ 7ኛ ክፍል እና ከ1-4 የኦሮምኛ መጻሕፍት በሥርጭት ላይ ሲሆኑ ነገር ግን ያለው ብዛት ጥቂት በመሆኑ ሀገረ ስብከቶች በመጻሕፍት ግዥ ያላችሁን ፍላጎት አስቀድማችሁ በመላክ ቅድሚያ እንድታገኙ ስንል እናሳስባለን።
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
👉 Website
የአንድነት ገዳማት ኅብረቱ መተዳደሪያ ደንብ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሕግ አገልግሎት መምሪያ በኩል ታይቶና ተመርምሮ እንዲቀርብ፣
በአጠቃላይ በአንድነት ገዳማት ኅብረት የቀረበው የገዳማውያንና ገዳማውያት ማረፊያ እና የገቢ ማስገኛ ሁለገብ ሕንጻ ግንባታ የትግበራ ዕቅድ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በኩል በዘርፉ ባለሙያዎች ታይቶና ተገምግሞ ከባለሙያ አስተያየቶችና የውሳኔ ሐሳብ ጋር ተጠንቶ ለግንቦት 2018 ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ እንዲቀርብ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ወስኗል፡፡
9.በበዓላት አከባበር፣ በመንፈሳዊ አገልግሎት አፈጻጸም ዙሪያ የሚታዩ ግድፈቶች፣ ያልተገቡ እንቅስቃሴዎችና ከሥርዓት የወጡ የአገልግሎት አፈጻጸሞች መታረም ስላለባቸው በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በሚሰየሙ ሊቃውንትና ባለሙያዎች ለመመሪያና ለማስተማሪያ የሚሆን ሰነድ ተዘጋጅቶ እንዲቀርብ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ተገቢውን ውሳኔ ያስተላለፈ መሆኑን እየገለጽን ያለጠባሳ የሚያድኑ ሐኪሞች፣ ያለቅሬታ የሚያስታርቁ ሽማግሌዎች በነበሩባትና ባሉባት ሀገር ተመካክሮ ችግርን አለመፍታት ተገቢ አይደለምና ሀገራችንን እንወዳለን፣ ሕዝባችንን እናከብራለን የምትሉ፣ የዜጎችን ደኅንነት የማስጠበቅ ኃላፊነት ያለባችሁ ሁሉ ክቡር የሆነው የሰው ልጅ ሕይወት በከንቱ እንዳይጠፋ፣ አካሉ እንዳይጐድል የሀገር ልማትና መልካም ገጽታ እንዳይበላሽ ጠላት መባባሉ ቀርቶ፣ የጦር መሣሪያ ትግል ተወግዶ፣ በእኩልነትና በመስማማት ሰላማዊ የችግር አፈታት መንገድን ተከትላችሁ በውይይትና በጥበብ ልዩነቶችን በመፍታት የተሟላ ሀገራዊ ሰላም እንዲሰፍን ታደርጉ ዘንድ ቅዱስ ሲኖዶስ ከአደራ ጭምር ሐዋርያዊ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡
በመጨረሻም የሀገራችን ኢትዮጵያና የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን ሕልውና ስለማይነጣጠሉ፣ ሀገራችን በሉአላዊነቷ እንድትቀጥል የቤተ ክርስቲያናችን የአንድነት መዋቅሯ የበለጠ ተጠናክሮ፣ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮዋ ሰፍቶ፣ ለትውልድ እንድትሻገር፣ ሕዝባችን ደኅንነቱና ሰላሙ ተጠብቆ እንዲኖር ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ጀምሮ ሁሉም የቤተ ክርስቲያናችን መምህራን፣ ካህናትና ሕዝባውያን፣ መነኰሳትና መነኰሳይያት በሙሉ በፍቅርና በአንድነት ዘወትር በመጸለይ ዘመኑ ከደረሰበት አሠራርና ጥበብ በላቀ ሁኔታ ከፍ ብለን ትውልዱን ለመዋጀት እንድንችል የበኩላችሁን እንድትወጡ በማሳሰብ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ዓመታዊ ስብሰባውን አጠናቋል፡፡
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ
አሜን!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም
ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
ምንጭ ኢኦተቤክ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
1.ሁለንተናዊ ሰላምና መረጋጋት የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሃይማኖታዊ መሠረቷ፥ የሥርዓተ ቅዳሴዋና የምሥጢራት አገልግሎቷ አካል፣ የመንፈሳዊና ማኅበራዊ ሥምሪቷ ማእከላዊ ዐምድ በመሆኑ በግንቦት 2017 ዓ.ም. ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የተሠየመው የሀገራዊ ሰላምና የቤተ ክርስቲያን አንድነት ኮሚቴ ሥራውን አጠናክሮ እንዲቀጥል፤ የደረሰበትንም ውጤት ለግንቦት 2018 ዓ.ም ምልዓተ ጉባኤ እንዲያቀርብ ቅዱስ ሲኖዶስ ጥብቅ መመሪያን አስተላልፏል
2.በትግራይ አህጉረ ስብከት የሚገኘው ሕዝበ ክርስቲያን ሕዝባችንና ወገናችን ስለሆነ አብያተ ክርስቲያናቱና ገዳማቱም የቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ ሀብቶች በመሆናቸው፣ አህጉረ ስብከቱም የተደራጁት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በመሆኑ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሕግና ቀኖና ተጠብቆ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልና ተከብሮ፣ የመዋቅር ግንኙነቱን ወደ ቀደመ ቦታው እንዲመለስ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የሰላም፣ የአንድነትና የይቅርታ በር ክፍት መሆኑን ከመግለጽ ጋር ቅዱስ ሲኖዶስ በክልሉ ለሚገኙት አባቶች፣ ካህናትና ምእመናን ያልተቋረጠ የሰላም ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡
የቀድሞዎቹ ቅዱሳን አባቶቻችን ዋጋ ከፍለው፣ ቀኖናዊ ሥርዓቷንና ክብሯን ጠብቀውና አስጠብቀው ፣ አንድነቷን አጽንተው ያወረሱንን አሐቲ ቤተ ክርስቲያን የቀደመ ሉዓላዊ ክብሯ እንደተጠበቀ ለመጭው ትውልድ ማስተላለፍ የበለጠ ዋጋ ያሰጣልና ቀደም ሲል ለዚሁ ጉዳይ የተሠየመው ኮሚቴ ሥራውን አጠናክሮ እንዲቀጥል፣ ሊቃውንቱ፣ ካህናቱና መላው ሕዝባችንም የቤተ ክርስቲያንን አንድነት ለማጠናከር በሚደረገው ጥረት ሁሉ የበኩላችሁን እንድትወጡ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በአጽንኦት ያሳስባል፡፡
3.ቅዱስ ሲኖዶስ አባት እንዲመደብላቸው ጥያቄ ባቀረቡ አህጉረ ስብከት ዙሪያ የውሳኔ ሐሳብ የሚያቀርቡ ብፁዓን አባቶችን በመሰየምና ተገቢውን ውይይት በማድረግ፡
ሀ) ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ የኢሉ አባቦራ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የምዕራብ ወለጋ ሀገረ ስብከትን ደርበው እንዲመሩ፣
ለ) ብፁዕ አቡነ ቶማስ የአዊና መተከል አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ የምሥራቅ ጎጃምን ሀገረ ስብከት ደርበው እንዲመሩ፣
ሐ) ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የደቡብ ወሎና ከሚሴ አህጉረ ስብከትን ደርበው እንዲመሩ፣
መ) ብፁዕ አቡነ ኒቆዲሞስ የምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ጳጳስ የምሥራቅ ወለጋና ሆሮ-ጉድሩ ወለጋ አህጉረ ስብከትን ደርበው እንዲመሩ
ሠ) በተጨማሪም የሸካ ዞን ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ተብሎ ራሱን ችሎ በሀገረ ስብከት ደረጃ እንዲቋቋም፣ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል ሀገረ ስብከቱን እንዲያደራጁና እንዲመሩ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
4.ነባሩና ጥንታዊው የቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ገድል እንደተጠበቀ ሆኖ ገድለ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በሚል ያለአግባብ በአንድ ግለሰብ ተዘጋጅቶ እየተሠራጨ ያለው መጽሐፍ በሊቃውንት ጉባኤ ተመርምሮ ያለበት ግድፈትና የስሕተት ትምህርት በሙሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሰ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን አስተምህሮ የማይወክል ሆኖ በመገኘቱ ተወግዟል፤
በውስጡ የያዛቸውም የተሳሳቱ ትምህርቶች በሙሉ ተቀባይነት ስለሌላቸው መጽሐፉ ለጥናትና ምርምርም ሆነ ለማጣቀሻ አገልግሎት እንዳይውል፣ በሥርጭት ላይ የዋለው መጽሐፍ እንዲታገድና በድጋሚም እንዳይታተም፣ ለየአህጉረ ስብከቱ ሠርኩላር እንዲተላለፍ፣ የአፈጻጸም ክትትል እንዲደረግና አጠቃላይ ሁኔታው በሊቃውንት ጉባኤ በኩል በሚዲያ እንዲገለጽ፣ የአስተምህሮ ስሕተትን በማካተት አሳትመው ያሰራጩት ግለሰብ በቋሚ ሲኖዶስ ተጠርተው እንዲጠየቁና የፈጸሙትን ስሕተት ዐውቀው ወደፊት ተመሳሳይ ስሕተት እንዳይፈጽሙ ጥብቅ መመሪያ እንዲሰጣቸው፣
መጽሐፉ እንዲመረመር ያደረገው የደብረ ሊባኖስ አንድነት ገዳምና የገዳሙ የቅኔ መምህር መጋቤ ምሥጢር አባ ክንፈሚካኤል ወልደ ገብርኤል የምስጋና ደብዳቤ እንዲጻፍላቸው ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
5.በሰሜን ካሊፎርኒያ ኔቫዳና አሪዞና ሀገረ ስብከት የኆኅተ ሰማይ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ወቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም መንፈሳዊ ኮሌጅና የአብነት ምስክር ጉባኤ ቤት ለማቋቋም በጠየቀው መሠረት እንዲፈቀድ ሆኖ የትምህርት አሰጣጥ ፖሊሲውና ሥርዓተ ትምህርቱ፣ የሰው ኃይል አደረጃጀቱና መዋቅራዊ ተጠሪነቱ ተዘጋጅቶ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ተጠንቶ ከውሳኔ ሐሳብ ጋር ለግንቦት 2018 ርክበ ካህናት ምልዓተ ጉባኤ እንዲቀርብ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤
6.በምዕራብና በመካከለኛው ካናዳ የሚገኙት ሁለቱ አህጉረ ስብከት ከአሁን በፊት በ2017 ዓ.ም. በተሰጠው ውሳኔ መሠረት ያለ ጣልቃ ገብነት በየራሳቸው እንዲተዳደሩና የኤድመንተንና አካባቢው ሀገረ ስብከት የመካከለኛው ካናዳ ኤድመንተንና አካባቢው ሀገረ ስብከት በሚል ሥያሜ እንዲስተካከል ምልዓተ ጉባኤው ወስኗል፡፡
7.በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ በአረርቲ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በዓል ለማክበር ሄደው አዲሱን ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን በመጐብኘት ላይ እያሉ አደጋ በደረሰባቸው ምዕመናን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የተሰማውን ሐዘን እየገለጸ እግዚአብሔር አምላካች ላረፉት ወገኖቻችን ዕረፍተ ነፍስ እንዲሰጥልን ከመጸለይ ጋር አካላዊ ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች ለማሳከምና የተጎጂ ቤተሰቦችን ለመርዳት የገንዘብ ድጋፍ እንዲደረግ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ ለወደፊቱም በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ዙሪያ በሚገነቡ ሕንጻ ግንባታዎች አደጋ ከመድረሱ በፊት ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ ቅዱስ ሲኖዶስ በአጽንዖት ያሳስባል፤
8.በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ ገዳማት ያሉት መነኰሳትና መነኰሳይያት ለአገልግሎትና ጉዳይ ለማስፈጸም ወደ አዲስ አበባ ሲመጡ ክብራቸውና ገዳማዊ ሕይወታቸው ተጠብቆ ጉዳያቸውን እስከሚፈጽሙ ድረስ የገዳማት ኅብረቱ ባቀረበው ጥያቄ መሠረት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በኩል ማረፊያ የሚሆን ቦታ እንዲዘጋጅላቸው፣
የቅዱስ ሲኖዶስ መደበኛ ምልዓተ ጉባኤ መጠናቀቁን አስመልክቶ መግለጫ ተሰጠ
ጥቅምት ፲፯/፳፻፲፰ ዓ.ም
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ የሚመራው፣ የሐዋርያት መንበር ወራሽ የሆነው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ
“ወይኩን ጉባኤ ሊቃነ ኤጴስ ቆጶሳት ወኤጲስ ቆጶሳት ክልዔተ ጊዜ በበዓመት ወይትናገሩ በእንተ ግብረ አብያተ ክርስቲያናቲሆሙ ወያሰስሉ ዕቅፍታተ …
የሊቃነ ጳጳሳትና የጳጳሳት ምልዓተ ጉባኤ በዓመት ሁለት ጊዜ ይሁን ስለአብያተ ክርስቲያናት የሚገባውን ሁሉ ይነጋገሩ የሐዋርያዊ ተልእኮ መሰናክሎችንም ሁሉ ያስወግዱ” ተብሎ በመጀመሪያው የሐዋርያት ቀኖና፣ በሁለተኛው ቀሌምንጦስ በተደነገገው መሠረት ምልዓተ ጉባኤው ከጥቅምት 11 - ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ስለ ቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊና የምጣኔ ሀብት ዕድገት፣ ስለ ሀገር ሰላምና አንድነት፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደርና ሐዋርያዊ ተልእኮ መስፋፋት ስለ ሰው ልጅ ሁሉ ደኅንነት ሰፊ ውይይት አድርጓል፡፡
ወቅቱን ያማከሉና ዘላቂ የቤተ ክርስቲያንን ተቋማዊ ሕልውና የሚያረጋግጡ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልናንን የሚያስጠብቁ፣ ለምእመናን ደኅንነትና ለአገልጋዮች ሕይወት በሚጠቅሙ፣ መንሳፈዊ አስተዳደርንና ማኅበራዊ ጉዳዮችን መሠረት ባደረጉ አጀንዳዎች ላይ በመንፈስ ቅዱስ አንድነት በመወያየት ለቤተ ክርስቲያናችንና ለሀገራችን ጠቃሚ የሆኑ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡
በዚሁ መሠረት፡-
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ የመጀመሪያ ቀን ውሎው በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ውሳኔ ሰጠ።
የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት በሰጠው ዕለታዊ መግለጫ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዓመት ሁለት ጊዜ የሚከናወነው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ የጥቅምት ወር ምልዓተ ጉባዔውን ጥቅምት 11 ቀን በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በመክፈቻ ጸሎት መጀመሩን አስታውሷል።
የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤትን በመወከል መግለጫውን የሰጡት መምህር ዳንኤል ሰይፈሚካኤል ምልዓተ ጉባዔው ዛሬ ጥቅምት 12 ቀን የመጀመሪያ ቀን ጉባዔውን ያከናወነ ሲሆን 16 አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ማጽደቁን ገልጸዋል።
በጠዋቱ ውሎ 7 ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን አጀንዳ እንዲቀርጹ ውሳኔ ያሳለፈ ሲሆን እነዚህም ሊቃነ ጳጳሳት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ፣ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል ፣ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ፣ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል፣ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ፣ ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል እና ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ናቸው ፡፡ ኮሚቴው በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ በሰብሳቢነት በብፁዕ አቡነ ዲዎስቆሮስ በአስረጂነት ተሰብስቧል።
ምልዓተ ጉባኤው በከሰዓቱ ውሎም ከ16ቱ አጀንዳዎች በ4ቱ ላይ ውሳኔ የሰጠ መስጠቱን ያስታወቀ ሲሆን እነዚህም ውሳኔዎች፦
1 ቅዱስነታቸው በጠዋቱ የመክፈቻ ጸሎት ያስተላለፉት መልዕክት በቀጣይ የሥራ መመሪያ አድርጎ ምልዓተ ጉባዔው አጽድቋል፡፡
2 ከጥቅምት 4-10 በነበረው የሰበካ መንፈሳዊ ዓለም ዓቀፍ ጉባኤ የነበሩ የቡድን ውይይቶች በቃለ ጉባኤ ቀርቦ ቃለ ጉባዔውን ምልዓተ ጉባዔው የ2018 ዓ.ም የሥራ መመሪያ አድርጎ አፅድቋል፡፡
3 ሀገራዊ ሰላምን አስመልክቶ ምልዓተ ጉባዔው በግንቦት ወር ተወያይቶ ሊቃነ ጳጳሳትን የያዘ ኮሚቴ ያዋቀረ ሲሆን ኮሚቴው የተሰጠውን ኃላፊነት አጠንክሮ እንዲቀጥል ተወያይቶ አጽድቋል፡፡
4 በትግራይ የተፈጠረው ወቅታዊ ክፍፍልን አስመልክቶ የተወያየ ሲሆን በውይይቱም ሕዝቡ ሕዝባችን አብያተ ክርስቲያናቱም የቤተክርስቲያን ሀብት እንደመሆናቸው ቀደም ብሎ የተዋቀረው የሰላም ኮሚቴ ሥራውን አጠንክሮ እንዲቀጥል በምልዓተ ጉባኤው ወስኗል፡፡
ጉባዔው በነገው ዕለትም ቀጥሎ በቀሪዎቹ 12 አጀንዳዎች ላይ ውይይት ያደርጋል፡፡
Repost from የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ የመጀመሪያ ቀን ውሎው በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ውሳኔ ሰጠ።
የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት በሰጠው ዕለታዊ መግለጫ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዓመት ሁለት ጊዜ የሚከናወነው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ የጥቅምት ወር ምልዓተ ጉባዔውን ጥቅምት 11 ቀን በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በመክፈቻ ጸሎት መጀመሩን አስታውሷል።
የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤትን በመወከል መግለጫውን የሰጡት መምህር ዳንኤል ሰይፈሚካኤል ምልዓተ ጉባዔው ዛሬ ጥቅምት 12 ቀን የመጀመሪያ ቀን ጉባዔውን ያከናወነ ሲሆን 16 አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ማጽደቁን ገልጸዋል።
በጠዋቱ ውሎ 7 ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን አጀንዳ እንዲቀርጹ ውሳኔ ያሳለፈ ሲሆን እነዚህም ሊቃነ ጳጳሳት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ፣ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል ፣ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ፣ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል፣ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ፣ ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል እና ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ናቸው ፡፡ ኮሚቴው በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ በሰብሳቢነት በብፁዕ አቡነ ዲዎስቆሮስ በአስረጂነት ተሰብስቧል።
ምልዓተ ጉባኤው በከሰዓቱ ውሎም ከ16ቱ አጀንዳዎች በ4ቱ ላይ ውሳኔ የሰጠ መስጠቱን ያስታወቀ ሲሆን እነዚህም ውሳኔዎች፦
1 ቅዱስነታቸው በጠዋቱ የመክፈቻ ጸሎት ያስተላለፉት መልዕክት በቀጣይ የሥራ መመሪያ አድርጎ ምልዓተ ጉባዔው አጽድቋል፡፡
2 ከጥቅምት 4-10 በነበረው የሰበካ መንፈሳዊ ዓለም ዓቀፍ ጉባኤ የነበሩ የቡድን ውይይቶች በቃለ ጉባኤ ቀርቦ ቃለ ጉባዔውን ምልዓተ ጉባዔው የ2018 ዓ.ም የሥራ መመሪያ አድርጎ አፅድቋል፡፡
3 ሀገራዊ ሰላምን አስመልክቶ ምልዓተ ጉባዔው በግንቦት ወር ተወያይቶ ሊቃነ ጳጳሳትን የያዘ ኮሚቴ ያዋቀረ ሲሆን ኮሚቴው የተሰጠውን ኃላፊነት አጠንክሮ እንዲቀጥል ተወያይቶ አጽድቋል፡፡
4 በትግራይ የተፈጠረው ወቅታዊ ክፍፍልን አስመልክቶ የተወያየ ሲሆን በውይይቱም ሕዝቡ ሕዝባችን አብያተ ክርስቲያናቱም የቤተክርስቲያን ሀብት እንደመሆናቸው ቀደም ብሎ የተዋቀረው የሰላም ኮሚቴ ሥራውን አጠንክሮ እንዲቀጥል በምልዓተ ጉባኤው ወስኗል፡፡
ጉባዔው በነገው ዕለትም ቀጥሎ በቀሪዎቹ 12 አጀንዳዎች ላይ ውይይት ያደርጋል፡፡
• ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
በጐዶሎው ዓለም የምትኖር ቤተ ክርስቲያን ጉድለቷን ለመሙላት ብዙ መሥዋዕትነት ከፍላለች፤ ቤተ ክርስቲያን ለቀጣዩ ትውልድ መሸጋገርና የጐደለባትን ለመሙላት ስትል ከቅዱሳን ሐዋርያት አንሥቶ እስካለንበት ዘመን ድረስ ብዙና የብዙ ብዙ አበው ካህናትን፣ ሊቃውንትንና ምእመናንን ከደም ጠብታ፣ እስከ ቁስ ስጦታ ገብራለች፡፡
አሁን በምድር ላይ ያለችው ቤተ ክርስቲያን የዚህ ሁሉ ውጤት ናት፤ ቤተ ክርስቲያን እንደ ሌላው ጊዜ ሁሉ ዛሬም የጐደለባት ብዙ ነገር አለ፤ በተቻለ መጠን እርሱን ለሟሟላት መጣርና በተሻለ ሁኔታ ወደፊት ማሻገር ደግሞ የዚህ ጉባኤ ተቀዳሚ ተግባር ነው፡፡ በዚህ ረገድ ይህ ጉባኤ ብቻው አይደለም፤ በብዙ ሚሊዮኖች የሚቈጠሩ የእግዚአብሔር ልጆች ድምፁን ለመስማት ከዙሪያው ሆነው በጉጉት ይጠብቃሉ፡፡ እነኝህ የእግዚአብሔር ልጆች ለመስማት ብቻ ሳይሆን ድምፁን ሰምተው ለመታዘዝም የተዘጋጁ ናቸው፣ ከሁሉ በላይ ደግሞ “ሁለትም ሦስትም ሆናችሁ በስሜ በተሰበሰባችሁበት እኔ በመካከላችሁ እገኛለሁ” በማለት ጉባኤውን የመሠረተው አምላክ ከዚህ ጉባኤ መካከል አለ፡፡
በመሆኑም ይህ ጉባኤ የተወሰን አባቶች ብቻ ሳንሆን ብዙ ሰማውያንና ምድራውያን ባለድርሻ ያሉበት፣ መንፈስ ቅዱስም በመንፈስ የሚመራው እንደሆነ የማይታበል ነው፡፡ ከዚህ አንጻር ጉባኤው በምድር ያለችውን የእግዚአብሔር መንግሥት በበላይነት የሚመራ ነውና፣ ያለበት ኃላፊነት ከባድና እጅግ የላቀ ነው፡፡ ጉባኤው ኃላፊነቱን በአግባቡ ሲወጣ የሚሰጠው ሽልማት ታላቅ እንደሆነ ሁሉ፣ ኃላፊነቱን በትክክል ካልተወጣ ደግሞ ተጠያቂነቱ በዚያው ልክ ከባድ ነው፤ ብዙ ከተሰጠው ብዙ ይፈለጋል ተብሎአልና፡፡
• ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
እኛ በአገልግሎትና በመሪነት በምንገኝበት በዚህ ዘመን ቤተ ክርስቲያን የጐደሉባት ነገሮች ብዙ ናቸው፤ ከሁሉ በላይ በውስጣችን የአንድነት ጐድለት በስፋት ይታያል፤ ለተሰየምንለት መለኮታዊ ተልእኮ አንድ ሐሳብ፣ አንድ ቃል፣ አንድ ልብ ሆነን መሰለፍ ያለመቻል ክፍተት እየተንጸባረቀ ነው፡፡ የዘመኑን ጥበብና ስልት ያልተከተለ ሐዋርያዊ ተልእኮአችንና አስተዳደራችንም ምእመናንን አላረካም፤ ክፍተቱ የሚድያ ቀለብ ከመሆንም አልፎ በጎቻችን በሌሎች እንዲዘረፉ ትልቅ በር እየከፈተ ነው፡፡ በእነዚህ ዓበይት ጉዳዮች እና በመሳሰሉት ጉድለቶቻች ላይ ፈጣን፣ ቈራጥና አዋጭ የሆነ ሥራ ካልሰራን ለወደፊት የቤተ ክርስቲያንን ህልውና ጥያቄ ውስጥ መክተቱ አይቀሬ ነው፡፡
• ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
ቤተ ክርስቲያናችን በተጠቀሱት ችግሮች ተከባ ባለችበት ሁኔታ የሀገራችን ሰላም መቀዛቀዝ ደግሞ ሌላው ተጨማሪ ጉድለትን እያስከተለብን ነው፡፡ አማንያን የመንፈስና የሥነ ልቡና ሰላም ከማጣታቸውም በላይ አካላቸው ለሞትና ለጉዳት፤ ሃብታቸው ለዝርፊያና ለውድመት እየተዳረገ ነው፡፡ ይኽም ሁሉ ሆኖ ፍትሕን እያገኙ አይደለም፤ አብያተ ክርስቲያናትም በምእመናን ፍልሰት እየተዘጉም እየተቃጠሉም ነው፡፡
ከዚህም ሌላ የሌለን ነገር እንዳለ አስመስሎ ከየአቅጣጫው የሚወረወረው የባዕዳን ስም የማጥፋት ዘመቻ፣ የቤተ ክርስቲያኗን እምነት ከመንቀፍና ከማብጠልጠል በላይ አልፎ የቅዱሳንን ቅዱስ ሥዕል በአደባባይ እስከ መቅደድ ተደርሶአል፤ በቤተ ክርስቲያናችን ህልውና ላይ በዓላማ የተነሡ አካላት የላኳቸው እንዳሉ በሚመስል መልኩ በስመ ተሐድሶ የሚደረገው እንቅስቃሴ የኛው መለያ የሆነውን ንዋየ ቅድሳትና ልብሰ ተክህኖ፣ መዝሙርና ሥርዓተ አምልኮ በመጠቀም ቤተ ክርስቲያናችንን በአደባባይ እየተዳፈረ ይገኛል፡፡
ይህ አላስፈላጊ ተግባር የሀገሪቱን ዜጎች በእኩልነት የሚያስተዳድረውን ሕገ መንግሥት በቀጥታ የሚፃረር ድርጊት ነው፤ ሆኖም በሕግ የሚጠይቅና የሚያስቆም አካል አልተገኘም፤ እኛም ዝምታን የመረጥን መስለናል፡፡ ነገር ግን መፍትሔው ዝምታ ሳይሆን በሕግ አግባብ ነገሩን ለመፍታት መንቀሳቀስ እንደሆነ ሁሉም ሊገነዘበው ይገባል፡፡
• ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
በዘመናችን እየተከሠተ ያለው ችግር ስንዘረዝር ውለን ብናድር መናገሩ በራሱ መፍትሔ ሊያመጣልን አይችልም፤ ጉባኤው ከዚህ በላይ መናገር እንደሚችልም እንገነዘባለን፤ ነገር ግን ለዚህ ሁሉ ችግር ዘላቂ መፍትሔ ሊያመጣ የሚችል መደላድል ይህ ጉባኤ በዚህ ስብሰባ ሊተልም ይገባል ብለን ከአደራ ጋር ማሳሰብ እንወዳለን፡፡ በሌላ በኩል በሀገራችን ያለው ያለመረጋጋት በሕዝባችን አጠቃላይ ሥነ ልቡና በሀገሪቱ አንድነትና ዕድገት የሚያስከትለውን ጫና በቀላሉ የሚታይ አይሆንም፤ የሕዝቡ ሥነ ልቡና ከተጐዳ የነገው ዕድል ጤናማ ይሆናል ተብሎ አይታሰብም፡፡
ችግሩ እየታየ ያለው በዋናነት በሀገራችን ፖለቲከኞች በመሆኑ ነገሩ የተወሳሰበና የተራዘመ እንዲሆን አድርጎታል፤ በመሆኑም ይህ የርስ በርስ ግጭት ቆሞ ችግሮች በውይይትና በድርድር በመፍታት የወንድማማች እልቂት የሚያስቆም የሰላምና የዕርቅ ዕድል ቅድሚያ እንዲሰጠው ጉባኤው የበኩሉን ጥረት ማድረግ ይገባዋል፡፡ የነገው ትውልድ ልማታዊ ተስፋ እውን ሊሆን የሚችለው ሰላምና አንድነት ሲኖር ነውና መንግሥት፣ ተፎካካሪ ፖለቲከኞችና ነፍጥ ያነሡ ወገኖች ሁሉ ለሰላም መስፈንና ለልማት ዕድገት መረጋገጥ ሲባል ወደ መግባባት እንዲመጡ በእግዚአብሔር ስም አባታዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
በመጨረሻም
ዓመታዊውና ቀኖናዊው የቅዱስ ሲኖዶስ ዓቢይ ጉባኤ በዛሬው ዕለት በጸሎት የተከፈተ መሆኑን ለሕዝበ ክርስቲያኑ በእግዚአብሔር ስም እናበስራለን፡፡
እግዚአብሔር የተባረከና የተቀደሰ ጉባኤ ያድርግልን፤
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ አሜን፡፡
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ጥቅምት ፲፪ ቀን ፳፻፲8 ዓመተ ምሕረት
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
