cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe

﷽ | Muslim | Theology | Comparative Religion | Philosophy | Student | Teacher |

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
13 729
مشترکین
+1924 ساعت
+1387 روز
+54230 روز
آرشیو پست ها
እየመሸ ስለነበር ወደ ቤቴ ለመመለስ በጥድፊያ ላይ ነበርኩ፣ ድንገት መንገድ ላይ የተወሰኑ ፕሮቴስታንቶች ተሰባስበው ፓምፍሌት እየሰጡ ነበር። ሊሰጡኝ መፈለጋቸውን አስተውየ ከአንዳቸው ተቀበልኩና ጉዞየን ቀጠልኩ። አስር ሜትር አካባቢ እንደሄድኩ ሰዎች ሰብሰብ ብለው ያዳምጣሉ። ከፕሮቴስታንቶቹ መካከል ከአንዱ ጋር የሚወያይ ሙስሊም ነው። በጣም ብቸኩልም ቀረብ ብየ ቢያንስ 1 ደቂቃ ለማደመጥ ወሰንኩ። ፕሮቴስታንቱ በደህንነት ትምህርቱ ወቅት የሰማትን ቃል ደጋግሞ ያስተጋባል። ሙስሊሙ ልጅ መጠነኛም ቢሆን የንጽጽር ትምህርቶች እንደደረሱት በሚያስታውቅ መልኩ ለፕሮቴስታንቱ የሚጠይቃቸው ጥያቄዎች ልጁን ግራ እንዳጋቡት ከፊቱ ያስታውቃል። አማራጭ ያጣው ፕሮቴስታንቱ ልጅ ዝምታን መርጦ ማዳመጥ ጀመረ። እሰብካለሁ ብሎ የወጣው ልጅ ተሰባኪ ሆነ፥ ውስጤን የማላቀው ደስታ እየተሰማኝ እኔም ጉዞየን ቀጠልኩ። እዚህ መንደር ስለሚሽነሪው አስጊ ስራዎች በዝርዝር ተነግሯል። ለቅሶ ደጋግመን አውርተናል፣ ሰምተናል። በዚህ ምክንያት ላለፉት አመታት ብዙው ሰው በእልህ ተሞልቶ የአቅሙን ተፍጨርጭሯል። አንዳንዶቻችን ተስፋ ቆርተን ትተነውም ይሆናል። ግን በብዙ አመታት ትግል ውስጥም ቢሆን የሆነ ቦታ ላይ ፍሬዎች መኖራቸው ግን ምንም ጥርጥር የሌለው ጉዳይ ነው። አንዳንዱን ፍሬ አሏህ ፈቅዶልን ልናየው እንችላለን፣ አንዳንዱን ደግሞ ሳናየው ሞት ሊቀድመን ይችላል። ግን መቸም በአሏህ ላይ የምንተማመነውና የማንጠራጠረው ነገር ኢንሻአላህ ነገ ከዛሬ የተሻለ እንደሚሆን ነው..! ___ https://t.me/Yahyanuhe
نمایش همه...
120👍 53🏆 11
Photo unavailableShow in Telegram
ከሞትክ በኋላ ሰዎች በምን ያህል ፍጥነት እንደሚረሱህ ብታውቅ ኖሮ አሏህን እንጂ ማንንም ለማስደሰት አትኖርም ነበር። آه لو علمت السرعة التي ينساك الناس بها بعد موتك، فلن تعيش حياتك لإرضاء أحد سوى اللّٰه.
نمایش همه...
👍 53😢 21😱 2
አንዳንድ ወገኖቻችን፦ “እስልምና ትክክለኛ ሀይማኖት ከሆነ እንዴት ሁሉም ነብያት አረቦች ሊሆኑ ቻሉ? እኛ፦ ከ124,000 ነብያት ውስጥ አረብ መሆናቸው የተነገረን 4 ብቻ ናቸውኮ (ሁድ፣ ሷልህ፣ ሹዐይብ፣ ሙሐመድ "ﷺ" ‎منهم أربعة من العرب: هود، وصالح، وشعيب، ونبيك يا أبا ذر). ይኸው ወገናችን፦ “ግን እኮ ሁሉም አረብኛ እንተናገሩ ነው በቁርአን ውስጥ በአረብኛ የተጠቀሰው” እኛ፦ ኧረ ተው! ቁርአን ውስጥኮ የጉንዳኗ 🐜 ንግግር ሳይቀር በአረብኛ ተጠቅሷል፣ ታዲያ ጉንዷኗ አረብ ናት ማለት ነው? 😒🤦🏻‍♂️ يَا أَيُّهَا النَّمْلُ ادْخُلُوا مَسَاكِنَكُمْ “..እናንተ ጉንዳኖች ሆይ! ወደ መኖሪያዎቻችሁ ግቡ..” (Qur’an 27:18). #ትርጉም ___ https://t.me/Yahyanuhe
نمایش همه...
👍 50 9🤩 8🏆 2
የመጽሀፍ ቅዱስ ግጭቶች - 31 https://vm.tiktok.com/ZMMYaxUPx/
نمایش همه...
👍 16🎉 3
Photo unavailableShow in Telegram
በወር ከመቶ ብር ጀምሮ በመነያት የሒዳያ ኢስላማዊ ማዕከል አባል በመሆን የዳዕዋው አካል ይሁኑ፦ https://bit.ly/4aGr93u በቴሌግራም በኩል ሊያገኙን ከፈለጉ፦ @Hidayaislamiccenter
نمایش همه...
👍 29 13
📌 ሪፖርት የመጽሀፍ ወቅፉን በተመለከተ ... ስቲሮት የተሰኘውን መጽሀፍ ለተለያዩ መርከዞች ለመስጠት የ190 ኮፒ መጽሀፍ የሚሸፍን ከተገኘ በሚል ያቀረብኩትን ጥያቄ አስመልክቶ ከአንድ ኮፒ አቅም ጀምሮ ሙሉውን እስከሸፈነ አንድ ወንድም ድረስ ደስ የሚል ተሳትፎ የነበረበት ነበር። በዚህም መሠረት የመጽሀፉ ሙሉው ብር ማለትም 19,000 ብር የተሟላ ሲሆን በዚህም መሠረት ለሚከተሉት ቦታዎች እስካሁን ተልከዋል፦ ◾️ አዲስ አበባ ለሚገኝና ከ90 በላይ ከተለያዩ አካባቢዎች መጥተው ትምህርት ለሚወስዱበት አንድ መርከዝ ለሁሉም መድረስ ባይችልም በጋራ እንዲጠቀሙበት 50 ኮፒ ገደማ አድርሰናል ◾️ በተመሳሳይ አዲስ አበባ ለሚገኝና ከደቡብ የሀገራችን ክፍል ለመጡ ተማሪዎች ትምህርት ለሚሰጥ አንድ መርከዝ ቃል የገባንላቸው ሲሆን በሚቀጥለው ሳምንት በአሏህ ﷻ ፍቃድ እናደርስላቸዋለን። ◾️ ደቡብ ለሚገኙ የሀድያና የከንባታ ተወላጅ የእራሴ ተማሪዎች በአካል እንዲያደርሱ በተመሳሳይ ለነሱም ሰጥቻለሁ። ◾️ ሸይኹ ለሚፈልጉት መርከዝ እንዲሰጡ ተጨማሪ መጽሀፍትን በማከል በፈለጉት ሰአት ሲጠይቁኝ እንዲወስዱ አማካይ ቦታ አስቀምጨላቸዋለሁ። ◾️ ከአማራ ክልል ጥያቄ ካቀረቡ ሁለት መርከዞች መካከል አንደኛው መድረሳ የወሰዱ ሲሆን ከደቡብ ወሎ የጠየቁኝ ወንድሞች ያገኙብኝ አድራሻ ስለጠፋብኝ ማግኘት አልቻልኩም፥ በዚህ አጋጣሚ ይህንን ፖስት ስታዩት አናግሩኝ። ◾️ በግል ወቅፍ ካደረጉ በኃላ ለራሳቸውም ኮፒ ለፈለጉ ወንድሞች በስማቸው በማስቀመጥ እንዲወስዱ ተመቻችቷል። 📌 የገባው ብር ከመጽሀፉ ዋጋ በላይ ስለነበር ተጨማሪ መጽሀፍትን በመግዛት ከላይ ለተዘረዘሩ ቦታዎችም ልኬያለሁ። በዚህም መሠረት አጠቃላይ 400 መጽሀፍትን በግዥ የጨመርኩ ሲሆን ከስቲሮት በተጨማሪ እነዚህም አብረው ተልከዋል። 📌 ከተገዙ ተጨማሪ መጽሀፍት ውስጥ አሁንም ጠይቃችሁኝ ያልተላኩ በርካታ መጽሀፍ ስላሉ ወንድም ሙስጠፋን በዚህ ስልክ በመደወልና የመርከዛችሁን አድራሻ በማሳወቅ የተቀመጠላችሁን መጽሀፍ መውሰድ ትችላላችሁ፦ +251911265565 ◾️ በመጨረሻም በዚህ ኸይር ስራ ላይ የተባበራችሁ ሁሉ አሏህ መልካም ምንዳውን ይክፈላችሁ እያልኩ በኒያችሁ ልክ አሏህ እንዲመነዳችሁ ዱዓየ ነው። እኔን ማግኘት ከፈለጉ በቴሌግራም አድራሻየ በኩል ያገኙኛል፦ t.me/Yahyanuhe1
نمایش همه...
👍 26
2👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
የመጽሀፍ ቅዱስ ግጭቶች #30 https://vm.tiktok.com/ZMMNHYYFD/
نمایش همه...
👍 12
Photo unavailableShow in Telegram
የወንድማችን የሸይኽ ሰዒድ አሊ ጀውሀርን ሙሉ የቁርአን ንባብ የያዘ አፕልኬሽን ይፋ ተደርጓል። አፑ ካልተሳሳትኩ ፍሪ ይመስለኛልና ዳውንሎድ በማድረግ አድምጡት፣ በግሌ ጭኘው የተወሰኑ ሱራውችን አዳምጫለሁ፣ ማሻአላህ ደስ የሚል ስራ ነው። አሏህ የኸይር ስራ ሚዛኑ ላይ ያድርግለት..! https://play.google.com/store/apps/details?id=com.hexlabs.quran
نمایش همه...
👍 36🥰 8👏 2🔥 1
Photo unavailableShow in Telegram
የመጽሀፍ ቅዱስ ግጭቶች #29 https://vm.tiktok.com/ZMMNdUfBy/
نمایش همه...
👍 7 2
ቤቲንግ ወይንም ቁማር ከከተማው አልፎ በገጠሩ በኩልም ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ የሚገኝ የኡማችን አንዱ ጠንቅ ሁኗል። አንዳንድ የክፍለ ሀገር ከተሞች ላይ ስያሜውን ለክርክር እንዲመች ቁማርን "ቀመር" በሚል አግባቢ ቃል እየሰየሙ እንደሚጠቀሙት አንዳንድ ወንድሞች ነግረውናል። በዚህ በኩል ሰፊ ስራ ከኡለሞችና ከዱዓቶች ይጠበቃል። በዚህ ትውልድ ገዳይ ተግባር ውስጥ የሚሳተፉ ወንድሞችንም መምከርና ማስተማር የሁላችንም ሀላፊነት ነው።
نمایش همه...
👍 69 20
ከሒዳያ መስራቾች መካከል የሆነው የወንድማችን ሙስጠፋ ሙደሲር የቲክቶክ አካውንት ነው። ለላይቭ ትምህርቶች በቪዲዮ ለመግባት 1,000 ሰው ስለሚያስፈልገው ፎሎው በማድረግ 1,000 እንሙላለት። ጠቃሚ ቪዲዮዎችንም በሒደት መልቀቅ ስለሚጀምር ከቪዲዮዎቹ እንጠቀማለን፦ https://www.tiktok.com/@mudesirmustefa?_t=8kCQr9JdDqX&_r=1
نمایش همه...
👍 30 2
ከሒዳያ መስራቾች መካከል የሆነው የወንድማችን ሙስጠፋ ሙደሲር የቲክቶክ አካውንት ነው። ለላይቭ ትምህርቶች በቪዲዮ ለመግባት 1,000 ሰው ስለሚያስፈልገው ፎሎው በማድረግ 1,000 እንሙላለት። ጠቃሚ ቪዲዮዎችንም በሒደት መልቀቅ ስለሚጀምር ከቪዲዮዎቹ እንጠቀማለን፦ https://www.tiktok.com/@mudesirmustefa?_t=8kCQr9JdDqX&_r=1
نمایش همه...
ቦረናን እንደ ሀድያ “True generosity comes without strings attached” ቦረና ተርቧል፣ ድጋፍም ይሻል። ከምንም በላይ የተቸገረ ወገንን ለመርዳት መንቀሳቀስ መልካምና የሚበረታታ ተግባር ነው። እርዳታን ፖለቲካዊ ማድረግ እንደሚወገዘው ሁሉ ግን በራበው ሰው ላይም "ወንጌል መስራት" ሰሚ ባይኖረውም ሊወገዝ ይገባል። ፕሮፌሰር ጆን ማርክ "Models of muslim evangalizing" በሚለው ፔፐሩ ከሚገልጻቸው የማክፈሪያ መንገዶች አንዱ "Institutional Model" ሲል የሚጠራው መንገድ አንዱ ነው። የሞዴሉ አተገባበር በአጭሩ እንደሚከተለው ነው፦ ሰውን እንዲሁ "ወንጌልን ተቀበል" እያሉ መወትወት ያን ያህል ፍሬ አያስገኝም። ታዲያ ምን ይሻላል?የተሻለው አካሔድ ሙስሊም በሚበዛባቸው አካባቢ የተለያዩ ተቋማትን በመገንባት ለነዚህ አገልግሎቶች የሚመጣውን ሙስሊም አጋጣሚውን ተጠቅሞ ማክፈር የሚል ነው። ለዚህም የእርዳታ ድርጅት፣ ሆስፒታል፣ የትምህርት ተቋማት ወዘተ ተመራጭ ማዕከላት ናቸው። ... የመሠረተ ክርስቶስ ቸርች ለቦረና ወገኖቻችን ድጋፍ ማድረጓን በግሌ ልቃወመው የምችለው አይደለም። ለቦረና ህዝብ ሙስሊሙ ወገናቸው በተሻለ ሊያደርገው የሚገባውን ቀድመው ማድረግ ችለዋል። ግን ደግሞ ካለፈ ተሞክሯችን እንደምናውቀው ከነዚህ እርዳታዎች ጀርባ ያሉ የእጅ ጥምዘዛዎችንም መከታተልና በትክክልም እርዳታዎች "እርዳታ ብቻ" መሆናቸውን ማረጋገጥ አለብን። ይህ በህጉም ይከለከላል፣ የተራበን ሰው ለማብላት ሌላ ሞቲቭ ይዞ መሄድ አይፈቀድም። የእርዳታ ድርጅቶች የሀይማኖት ጫናን መሠረት እንዲያደርጉ ፈጽሞ አይፈቀድም። ◾️ ለኛ፦ ሁሌም መሠል ነገራትን መናገር ለተናጋሪው ብቻ ሳይሆን ለሰሚውም እንደሚያሰለች እገምታለሁ። ግን አሁንም አረፈደም ከሚል ቀና ግምት መናገሩና መወያየቱ ከተቻለም የአቅምን አበርክቶ ህዝባችንን ከዱንያም ከኤኼራም ፈተና ማዳን የሁላችንም ኃላፊነት ነው። በተለይ በተቋም በኩል ያላችሁ ሰዎች ብዙ ኃላፊነት እንናንተው ጋር መውደቁ አይቀርም። ልብ በሉ፦ አንዳንድ ኩፍሮች በበደል ስር አድርገው ዱንያችንን ሊያበላሹ ይችላሉ፣ አንዳንድ ኩፍሮች ደግሞ ዱንያችንን ሰጥተው አኼራችንን ሊያሳጡን ይችላሉ። የአኼራው የከፋና አደገኛ ነው። ◾️ ሰጭዎችም ይህንን አባባል አትዘንጉት፦ "True generosity comes without strings attached, freely given from the heart with no expectation of reciprocity or ulterior motives." ቁርዓን ሰውን ስለሚያበሉ ደጋጎች በሚገርም መልኩ ይነግረናል። ስራቸው ሁሉ ጌታቸው ዘንድ ምንዳን ከማግኘት እንጅ በምትኩ ምስጋናም ሆነ የተለየ ክፍያን ፈልገው አይደለም፦ إِنَّمَا نُطْعِمُكُمْ لِوَجْهِ اللَّهِ لَا نُرِيدُ مِنكُمْ جَزَاءً وَلَا شُكُورًا «የምናበላችሁ ለአላህ ውዴታ ብቻ ነው፡፡ ከእናንተ ዋጋንም ማመስገንንም አንፈልግም፡፡ [ አል-ደህር - 9 ]
نمایش همه...
👍 57 10🔥 1
Photo unavailableShow in Telegram
👍 2
አንድ እዚህ መንደር የሚታወቅና በብዙ ሰው ዘንድ "የሚከበር" ጸሀፊ አለ፣ እምነቱ ፕሮቴስታንት ቢሆንም ስለእምነቱ አብዝቶ የሚጽፍ ሰው ግን አይደለም። ግለሰቡ የአንድ የማቀው ፋብሪካ ባለቤት ከመሆኑም በተጨማሪ በተለያዩ ሜንስትሪም ሚዲያዎች ማህበረሰብን ስለማረቅ በሚያስተጋባቸው ሀሳቦቹ ብዙው ሰው (ሙስሊሙን ጨምሮ) እንደበጎ አሳቢ አይቶ ያደንቀዋል። ሌላም ግን የማይታወቅ ማንነት አለው። ቁርአንና ነብዩ ሙሐመድ "ﷺ" የሚሰደቡባቸው የፕሮቴስታንት ሰባኪ ፖስቶች ላይም ያለምንም መሸማቀቅ Love teact ሲሰጥ ታገኙታላችሁ። መጀመሪያ አካባቢ ካለው ማንነት አንጻር በስህተት ያደረገው መስሎኝ ኡዝር ሰጥቸው አውቃለሁ። ሲደጋገም ግን እራሱ ፈልጎት እንደሆነ ገባኝ። አስፈላጊ አይደለም ብየ ስላመንኩ እንጅ ሜንሽን ባደርገው ብዙ ሰው ባለማመን እንደሚከራከረኝ አቃለሁ። ይህ እንግዲህ በአደባባይ ያየነው እውነታ ነው፣ ከጀርባ ያለውን ደግሞ አሏህ ያውቃል። ለማንኛውም የሚሽነሪውን ቡድን ደብል ፌስ ማሳያ ነውና ትምህርት ውሰዱበት..!
نمایش همه...
👍 56
نمایش همه...
👍 9
نمایش همه...
👍 16
01:54
Video unavailableShow in Telegram
👍 25 6👏 1
ምእመናን ግን በጀነት ስላሉ ከዚያ ቀን ስቃይ ተቤዥተዋል። ከእነዚያ ከካዱት ግን ቤዛ አይወሰድም፥ ለእነዚያም ለበደሉት ከሐድያን በምድር ያለው ሁሉ መላውም ከእርሱ ጋር መሰሉም ቢኖራቸው ኖሮ በትንሣኤ ቀን ከቅጣቱ ክፋት የተነሳ በእርሱ ነፍሶቻቸውን በተቤዡበት ነበር፦ 57፥15 «ዛሬም ከእናንተ ቤዛ አይወስድም፥ ከእነዚያ ከካዱትም አይወሰድም፡፡ መኖሪያችሁ እሳት ናት፥ እርሷ ተገቢያችሁ ናት፡፡ ምን ትከፋም መመለሻ!» ይሏቸዋል፡፡ فَالْيَوْمَ لَا يُؤْخَذُ مِنكُمْ فِدْيَةٌ وَلَا مِنَ الَّذِينَ كَفَرُوا ۚ مَأْوَاكُمُ النَّارُ ۖ هِيَ مَوْلَاكُمْ ۖ وَبِئْسَ الْمَصِيرُ 39፥47 ለእነዚያም ለበደሉት በምድር ያለው ሁሉ መላውም ከእርሱ ጋር መሰሉም ቢኖራቸው ኖሮ በትንሣኤ ቀን ከቅጣቱ ክፋት የተነሳ በእርሱ ነፍሶቻቸውን በተቤዡበት ነበር፡፡ وَلَوْ أَنَّ لِلَّذِينَ ظَلَمُوا مَا فِي الْأَرْضِ جَمِيعًا وَمِثْلَهُ مَعَهُ لَافْتَدَوْا بِهِ مِن سُوءِ الْعَذَابِ يَوْمَ الْقِيَامَةِ ይህቺ የካፊር ነፍስ ከነፍስ ምንንም ቤዛ የማይያዝበትን ቀን ተጠንቀቁ! እንግዲህ ቤዛ፣ ምልጃ፣ ወዳጅነት የሌለበት ቀን የተባለው ከዐውድ እና አጠቃላይ ከቁርኣን መልእክት አንጻር ለከሓዲ በዳዮች ብቻ ነው። የፍርዱ ቀን ሁሉም ነቢይ ለኡመቱ ወደ አላህ ምልጃ ያረጋል፥ የነቢያችን”ﷺ” ምልጃ በትንሳኤ ቀን የሚያገኘው ከልቡ ወይም ከነፍሱ፦ “ከአሏህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም” ያለ ሰው ነው፦ ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 1, ሐዲስ 402 አነሥ ኢብኑ ማሊክ እንደዘገበው የአሏህ ነቢይም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "ሁሉም ነቢይ ለኡመቱ ወደ አላህ ጸሎት ያረጋል፥ በትንሳኤ ቀን የእኔ ጸሎት ለኡመቴ ምልጃ ነው*። عَنْ قَتَادَةَ، حَدَّثَنَا أَنَسُ بْنُ مَالِكٍ، أَنَّ نَبِيَّ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ لِكُلِّ نَبِيٍّ دَعْوَةٌ دَعَاهَا لأُمَّتِهِ وَإِنِّي اخْتَبَأْتُ دَعْوَتِي شَفَاعَةً لأُمَّتِي يَوْمَ الْقِيَامَةِ ‏”‏ ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 3, ሐዲስ 41 አቢ ሁረይራ እንደተረከው፦ *”እኔም፦ የአሏህ መልእክተኛ”ﷺ” ሆይ! በትንሳኤ ቀን ማነው እድለኛ ሰው የእርስዎን ምልጃ የሚያገኘው? አልኩኝ፤ የአላህ መልእክተኛም”ﷺ”፦ “አቢ ሁረይራ ሆይ! ንግግር ለመማር የአንተን ቆይታ ዐውቃለው፤ እንደማስበው ስለዚህ ጉዳይ ከአንተ በፊት ማንም አልጠየቀኝም። በትንሳኤ ቀን የእኔን ምልጃ የሚያገኝ እድለኛ ሰው ከልቡ ወይም ከነፍሱ፦ “ከአሏህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም” ያለ ነው"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، أَنَّهُ قَالَ قِيلَ يَا رَسُولَ اللَّهِ، مَنْ أَسْعَدُ النَّاسِ بِشَفَاعَتِكَ يَوْمَ الْقِيَامَةِ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ لَقَدْ ظَنَنْتُ يَا أَبَا هُرَيْرَةَ أَنْ لاَ يَسْأَلَنِي عَنْ هَذَا الْحَدِيثِ أَحَدٌ أَوَّلُ مِنْكَ، لِمَا رَأَيْتُ مِنْ حِرْصِكَ عَلَى الْحَدِيثِ، أَسْعَدُ النَّاسِ بِشَفَاعَتِي يَوْمَ الْقِيَامَةِ مَنْ قَالَ لاَ إِلَهَ إِلاَّ اللَّهُ، خَالِصًا مِنْ قَلْبِهِ أَوْ نَفْسِهِ ‏”‌‏.‏ ✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
نمایش همه...
وَلَقَدْ خَلَقْنَا الْإِنسَانَ وَنَعْلَمُ مَا تُوَسْوِسُ بِهِ نَفْسُهُ ۖ وَنَحْنُ أَقْرَبُ إِلَيْهِ مِنْ حَبْلِ الْوَرِيدِ (ሱረቱ ቃፍ - 16) ሰውንም ነፍሱ (በሐሳቡ) የምታጫውተውን የምናውቅ ስንኾን በእርግጥ ፈጠርነው፤ እኛም ከደም ጋኑ ጅማት ይበልጥ ወደርሱ ቅርብ ነን፡፡ @slmatawahi
نمایش همه...
54:50
Video unavailableShow in Telegram
ኢስላምና ሙስሊሞችን ለምን ይነካካሉ? | ኡስታዝ አህመድ አደም | ሀዲስ | Ustaz ahmed adem | hadis ሸገር ሲቲ Sheger @QesesTube
نمایش همه...
ምልጃ የሌለበት ቀን በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 2፥254 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ውስጥ ቤዛ፣ ወዳጅነትም፣ ምልጃም የሌለበት ቀን ከመምጣቱ በፊት ከሰጠናችሁ ነገር ለግሱ፡፡ ከሓዲዎችም በዳዮቹ እነርሱ ናቸው፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا أَنفِقُوا مِمَّا رَزَقْنَاكُم مِّن قَبْلِ أَن يَأْتِيَ يَوْمٌ لَّا بَيْعٌ فِيهِ وَلَا خُلَّةٌ وَلَا شَفَاعَةٌ ۗ وَالْكَافِرُونَ هُمُ الظَّالِمُونَ "ምልጃ" ሥስት ማንነቶችን ያቅፋል፥ እነርሱም፦ ፨አንደኛው የሚማለደው ተማላጅ፣ ፨ሁለተኛው የሚማልደው አማላጅ እና ፨ሦስተኛ የሚማለድለት ተመላጅ ናቸው። አሏህ የሁሉም ነገር ፈጣሪና አስተናባሪ በመሆኑ የሚማለድ ተማላጅ ነው፥ በአሏህ ፈቃድ የሚያማልዱት አማላጆች ደግሞ መላእክት፣ ነቢያት እና ሰማዕታት ናቸው፦ 2፥255 ያ እርሱ ዘንድ በፈቃዱ ቢኾን እንጅ የሚያማልድ ማነው? مَن ذَا الَّذِي يَشْفَعُ عِندَهُ إِلَّا بِإِذْنِهِ 21፥28 በፊታቸው ያለውንና በኋላቸው ያለውንም ሁሉ ያውቃል፡፡ ለወደደውም ሰው እንጅ ለሌላው አያማልዱም፡፡ እነርሱም እርሱን ከመፍራታቸው የተነሳ ተጨናቂዎች ናቸው፡፡ يَعْلَمُ مَا بَيْنَ أَيْدِيهِمْ وَمَا خَلْفَهُمْ وَلَا يَشْفَعُونَ إِلَّا لِمَنِ ارْتَضَىٰ وَهُم مِّنْ خَشْيَتِهِ مُشْفِقُونَ "ለወደደውም ሰው እንጅ ለሌላው አያማልዱም" የሚለው ይሰመርበት! ዐውደ ንባቡ ስለ መላእክት እያወራ እንደሆነ አንባቢ ልብ ይለዋል። የሚማለድላቸው ተመላጆች ደግሞ አሏህ ዘንድ ቃል ኪዳን የያዙት አማንያን ናቸው፦ 34፥23 ምልጃም እርሱ ለፈቀደለት ሰው ብቻ ቢሆን እንጂ እርሱ ዘንድ ምንም አትጠቅምም*፡፡ وَلَا تَنفَعُ الشَّفَاعَةُ عِندَهُ إِلَّا لِمَنْ أَذِنَ لَهُ 19፥87 *አልረሕማን ዘንድ ቃል ኪዳንን የያዘ ሰው ቢኾን እንጂ ማማለድን አይችሉም*፡፡ لَّا يَمْلِكُونَ الشَّفَاعَةَ إِلَّا مَنِ اتَّخَذَ عِندَ الرَّحْمَـٰنِ عَهْدًا 20፥109 በዚያ ቀን ለእርሱ አልረሕማን የፈቀደለትን እና ለእርሱም ቃልን የወደደለትን ሰው ቢኾን እንጅ ምልጃ አንድንም አትጠቅምም፡፡ يَوْمَئِذٍ لَّا تَنفَعُ الشَّفَاعَةُ إِلَّا مَنْ أَذِنَ لَهُ الرَّحْمَـٰنُ وَرَضِيَ لَهُ قَوْلًا "በዚያ ቀን" የሚለው የፍርዱ ቀን ሲሆን በዚያን ቀን አሏህ የፈቀደላቸው መላእክት፣ ነቢያት እና ሰማዕታት ለምዕመናን ያማልዳሉ። ነገር ግን ለኩፋሮች ምንም ወዳጅ እና ተሰሚ አማላጅ የላቸውም፦ 40፥18 ለበዳዮች ምንም ወዳጅ እና ተሰሚ አማላጅ የላቸውም፡፡ مَا لِلظَّالِمِينَ مِنْ حَمِيمٍ وَلَا شَفِيعٍ يُطَاع 2፥254 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ውስጥ ቤዛ፣ ወዳጅነትም፣ ምልጃም የሌለበት ቀን ከመምጣቱ በፊት ከሰጠናችሁ ነገር ለግሱ፡፡ ከሓዲዎችም በዳዮቹ እነርሱ ናቸው፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا أَنفِقُوا مِمَّا رَزَقْنَاكُم مِّن قَبْلِ أَن يَأْتِيَ يَوْمٌ لَّا بَيْعٌ فِيهِ وَلَا خُلَّةٌ وَلَا شَفَاعَةٌ ۗ وَالْكَافِرُونَ هُمُ الظَّالِمُونَ "ቤዛ፣ ወዳጅነትም፣ ምልጃም የሌለበት ቀን" የፍርዱ ቀን ሲሆን ቤዛ፣ ወዳጅነትም፣ ምልጃም የሌለው ለኩፋሮች ስለሆነ ዐውዱ ላይ "ከሓዲዎችም በዳዮቹ እነርሱ ናቸው" በማለት ይናገራል። ያ የፍርዱ ቀን እነርሱም ከአሏህ እርዳታ የማይረዱበትን እና ምልጃን የማይቀበሉባት ቀን ነው፦ 2፥48 ነፍስም ከነፍስ ምንንም የማትመነዳበትን፣ ከእርሷም ምልጃን የማይቀበሉባትን፣ ከእርሷም ቤዛ የማይያዝበትን፣ እነርሱም የማይረዱበትን ቀን ተጠንቀቁ፡፡ وَاتَّقُوا يَوْمًا لَّا تَجْزِي نَفْسٌ عَن نَّفْسٍ شَيْئًا وَلَا يُقْبَلُ مِنْهَا شَفَاعَةٌ وَلَا يُؤْخَذُ مِنْهَا عَدْلٌ وَلَا هُمْ يُنصَرُونَ "የማይቀበሉ" ተብሎ በሦስተኛ መደብ በግስ መደብ የተጠቀሱት እና "እነርሱ" ተብሎ በሦስተኛ መደብ በስም መደብ የተጠቀሱት በዳዮቹ ከሓዲዎች እንጂ ምእመናንን አይጨምርም፥ በፍርዱ ቀን አሏህ የፈቀደለትን እና ለእርሱም ቃልን የወደደለትን ሙእሚን ቢኾን እንጅ ለከሓዲ ምልጃ አንድንም አትጠቅምም። ኩፋሮች የትንሳኤ ቀን፦ "በሰቀር ውስጥ ምን አገባችሁ? ተብለው ሲጠየቁ፦ "ከሰጋጆቹ አልነበርንም፣ ለድኾችም የምናበላ አልነበርንም፣ ከዘባራቂዎቹም ጋር እንዘባርቅ ነበርን፣ በፍርዱ ቀንም እናስተባብል ነበርን" ይላሉ። የአማላጆችም ምልጃ አትጠቅማቸውም፦ 74፥48 የአማላጆችም ምልጃ አትጠቅማቸውም፡፡ فَمَا تَنفَعُهُمْ شَفَاعَةُ الشَّافِعِينَ "ወዳጅነትም የሌለበት ቀን" የተባለው አሁንም ለኩፋሮች እንጂ ለሙእሚን በፍጹም አይደለም። "ሑላህ" خُلَّة ማለት "ወዳጅነት" ማለት ሲሆን "ኻሊል" خَلِيل ማለት ደግሞ "ወዳጅ" ማለት ነው፥ በዚያ ቀን ኩፋሮች አንዱ ለሌላው ጠላት ነው፦ 43፥67 ወዳጆች በዚያ ቀን ከፊላቸው ለከፊሉ ጠላት ነው፡፡ አላህን ፈሪዎች ብቻ ሲቀሩ፡፡ الْأَخِلَّاءُ يَوْمَئِذٍ بَعْضُهُمْ لِبَعْضٍ عَدُوٌّ إِلَّا الْمُتَّقِينَ "ወዳጆች" ለሚለው የገባው ቃል "አኺላእ" أَخِلَّاء ሲሆን "ኻሊል" خَلِيل ለሚለው ብዙ ቁጥር ነው፥ "አላህን ፈሪዎች ብቻ ሲቀሩ" የሚለው ይሰመርበት! አሏህን ፈሪዎች ምእመናንማ ከእነዚያ አላህ በእነርሱ ላይ ከለገሳቸው ከነቢያት፣ ከጻድቃንም፣ ከሰማዕታትም፣ ከመልካሞቹ ጋር ይወዳጃሉ፡፡ የእነዚያም ወዳጅነት አማረ፦ 4፥69 አላህን እና መልክተኛውንም የሚታዘዝ ሰው እነዚያ ከእነዚያ አላህ በእነርሱ ላይ ከለገሳቸው ከነቢያት፣ ከጻድቃንም፣ ከሰማዕታትም፣ ከመልካሞቹ ጋር ይኾናሉ፡፡ የእነዚያም ጓደኝነት አማረ፡፡ وَمَن يُطِعِ اللَّهَ وَالرَّسُولَ فَأُولَـٰئِكَ مَعَ الَّذِينَ أَنْعَمَ اللَّهُ عَلَيْهِم مِّنَ النَّبِيِّينَ وَالصِّدِّيقِينَ وَالشُّهَدَاءِ وَالصَّالِحِينَ ۚ وَحَسُنَ أُولَـٰئِكَ رَفِيقًا ስለዚህ "ምልጃም የሌለበት ቀን" የተባለው "ወዳጅነትም የሌለበት ቀን" በተባለበት ዐውድ ከሆነ እና ለምእመናን ምልጃ ሆነ ወዳጅነት ካላቸው ምልጃ እና ወዳጅነት የሌለበት ቀን ለኩፋሮች ነው፥ የፍርዱ ቀን ለኩፋሮች ቤዛ የሌለበት ቀን ነው። ሙጅሪም ከዚያ ቀን ስቃይ ነፍሱን በልጆቹ ሊበዥ ይመኛል፥ ቅሉ ግን ለእነርሱ ቤዛ የሌለበት ቀን ስለሆነ ከእሳት ቅጣት አይቤዥም፦ 70፥11 ዘመዶቻቸውን ያዩዋቸዋል፡፡ አመጸኛው ከዚያ ቀን ስቃይ ነፍሱን በልጆቹ ሊበዥ ይመኛል፡፡ يُبَصَّرُونَهُمْ ۚ يَوَدُّ الْمُجْرِمُ لَوْ يَفْتَدِي مِنْ عَذَابِ يَوْمِئِذٍ بِبَنِيهِ
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
#አማናን መጠበቅ! ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፡‐ “አንድ ሰው ግራ ቀኙን ተመልክቶ የሆነ ወሬ ከነገረህ አማና (ሚስጥር) ነው ማለት ነው።” 📚 ቲርሚዚ ሶሂህ ብለውታል: 1959
نمایش همه...
●▯ውይይት ▯● "ዕብራውያን 1፥10" ◍ ኡስታዝ ወሒድ 🆅🆂 ◍ ወገናችን ክብረት
نمایش همه...
“ወንድምህ በፈጸመው ወንጀል ላይ ነቀፋ እየሰነዘርክ መዘባበትህ፣ እርሱ ከፈጸመው ወንጀል የበለጠ ነው” ኢብኑል ቀይም አልጀውዚ መዳሪጅ አል'ሳሊኪን 1/178
نمایش همه...
👍 35 14
Photo unavailableShow in Telegram
#የምህረትና በንስሃ ወደ አላህ የመመለስ ትሩፋት! ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፡‐ “ነፍሴ በእጁ በሆነችው አላህ እምላለሁ!  እናንተ ሀጢያት የማትፈፅሙ ቢሆን ኖሮ አላህ ያጠፋችሁ ነበር። ከዛ ሀጢያት የሚፈፅሙ ህዝቦችን ያመጣና በሀጢያታቸው ምክንያት አላህን ምህረት ይጠይቁታል እሱም ይምራቸዋል።” 📚 ሙስሊም ዘግበውታል: 2749
نمایش همه...
ቲላዋ 💌 🍃ራሀቱል ቀልብ 🍃 •┈┈• ❀ 🍃🌸🍃 ❀ •┈┈• @slmatawahi
نمایش همه...
31:51
Video unavailableShow in Telegram
ዝምታን እንማር ! | ኡስታዝ አህመድ አደም | ሀዲስ በአማርኛ | Ustaz ahmed adem | Hadis Amharic @QesesTube @seifuonebs
نمایش همه...
●▯ውይይት ▯● "ግድያ በእስልምና በክርስትና" ◍ ወንድም ሳላህ ◍ ወንድም ራስታ 🅥🅢 ◍ ክርስቲያን ወገኖች
نمایش همه...
አምላካችን አሏህ በመልእክተኛው ወሕይ ከማውረዱ በፊት ልክ አንድ ሕጻን የእናት ሁለት ጡቶችን መርጦ እንዲጠባ በኢልሃም"innate knowledge" እንደሚያሳውቀው ሁሉ አንድ ነገር ኸይር ወይም ሸር መሆኑን ሁለቱንም ለአንድ ሰው በውሳጣዌ ግንዛቤ ያሳውቃል፦ 90፥10 *ሁለት ”መንገዶችም” አልመራነውምን?"* وَهَدَيْنَٰهُ ٱلنَّجْدَيْنِ 76፥3 *"እኛ አመስጋኝ ወይም ከሐዲ ሲሆን ”መንገዱን መራነዉ”*። إِنَّا هَدَيْنَٰهُ ٱلسَّبِيلَ إِمَّا شَاكِرًۭا وَإِمَّا كَفُورًا "ማመስገን" እና "አመስጋኝ" የሚለው ቃል "ማመን" እና "አማኝ" ለሚል ቃል ተለዋዋጭ ሆኖ የገባ ነው፥ ሰዎች በነቢይ በኩል መልእክቱ ደርሷቸው አመስግነው አመስጋኝ ቢሆኑ አሏህ ይወድላቸዋል ይጨምርላቸዋል። በተቃራኒው ክደው ከሓዲ ቢሆኑ አላህ ከእነርሱ የተብቃቃ ነው፥ ለባሪያዎቹም ከህደትን አይወድም። ይቀጣቸዋል፥ ቅጣቱ ብርቱ ነው፦ 39፥7 *"ብትክዱ አላህ ከእናንተ የተብቃቃ ነው፥ ለባሪያዎቹም ከህደትን አይወድም፡፡ ብታመሰግኑ እርሱን ይወድላችኋል"*፡፡ إِن تَكْفُرُوا فَإِنَّ اللَّهَ غَنِيٌّ عَنكُمْ ۖ وَلَا يَرْضَىٰ لِعِبَادِهِ الْكُفْرَ ۖ وَإِن تَشْكُرُوا يَرْضَهُ لَكُمْ 14፥7 *ጌታችሁም «ብታመሰግኑ በእርግጥ እጨምርላችኋለሁ ብትክዱም እቀጣችኋለሁ፥ ቅጣቴ በእርግጥ ብርቱ ነውና» በማለት ባስታወቀ ጊዜ አስታውሱ"*፡፡ وَإِذْ تَأَذَّنَ رَبُّكُمْ لَئِن شَكَرْتُمْ لَأَزِيدَنَّكُمْ ۖ وَلَئِن كَفَرْتُمْ إِنَّ عَذَابِي لَشَدِيدٌ "መሺኣህ" مَشِئَة የሚለው ቃል "ሻአ" شَاءَ ማለትም "ፈቀደ" ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ፈቃድ" ማለት ነው፥ ስለዚህ ሰው አምኖ ለሚሠራው መልካም ሥራ አሊያም ክዶ ለሚሠራው መጥፎ ሥራ ነጻ ፈቃድ አለው፦ 18፥29 *«እውነቱም ከጌታችሁ ነው፡፡ የሻም ሰው ይመን! የሻም ሰው ይካድ!»* በላቸው፡፡ وَقُلِ الْحَقُّ مِن رَّبِّكُمْ ۖ فَمَن شَاءَ فَلْيُؤْمِن وَمَن شَاءَ فَلْيَكْفُر 64፥2 *"እርሱ ያ የፈጠራችሁ ነው፡፡ ከእናንተም ከሓዲ አለ፥ ከእናንተም አማኝ አለ፡፡ አላህም በምትሠሩት ሁሉ ተመልካች ነው"*፡፡ هُوَ الَّذِي خَلَقَكُمْ فَمِنكُمْ كَافِرٌ وَمِنكُم مُّؤْمِنٌ ۚ وَاللَّهُ بِمَا تَعْمَلُونَ بَصِيرٌ "የሻም ሰው ይመን! የሻም ሰው ይካድ" የሚለው ሰው የማማረጥ ነጻ ፈቃድ እንዳለው አመላካች ነው፥ በተጨማሪም "የሻም" ለሚለው የገባው ቃል "ሻአ" شَاءَ ነው። በዓለማችን ላይ "ካፊር" እና "ሙእሚን" ያለው ሰው በፈቃዱ በመረጠው ምርጫው ነው፥ አሏህ የምንሠራውን ሁሉ ተመልክቶ በምንሠራው ሥራ ይጠይቀናል፦ 16፥93 *ትሠሩት ከነበራችሁትም ሁሉ በእርግጥ ትጠየቃላችሁ*፡፡ وَلَتُسْأَلُنَّ عَمَّا كُنتُمْ تَعْمَلُون 102፥8 ከዚያም *ከጸጋችሁ ሁሉ በዚያ ቀን ትጠየቃላችሁ*። ثُمَّ لَتُسْأَلُنَّ يَوْمَئِذٍ عَنِ النَّعِيمِ “ነዒም” نَّعِيمِ ማለት “ጸጋ” ማለት ሲሆን ይህ የተሰጠን ጸጋ አድርግ የተባለውን የመታዘዝዝና ያለመታዘዝ፥ አታድርግ የተባለውን የመከልከልና ያለመከልከል ነጻ ፈቃድ"free will" ነው። ሰው በሚሠራው ሰናይ ሆነ እኩይ ሥራ ግብረገባዊ ተጠያቂነት"moral accountability" ያለው ፍጡር መሆኑ እነዚህ ሁለት አናቅጽ ፍንትው እና ቁልጭ አድርገው ያሳያሉ። አሏህ በሠራው እና በሚሠራው ሥራ አይጠየቅም፥ ሁለት ምርጫ ያላቸው ፍጡራን ግን በሚሠሩት ሥራ ይጠየቃሉ፦ 21፥23 *ከሚሠራው ሁሉ አይጠየቅም፡፡ እነርሱ ግን ይጠየቃሉ*፡፡ لَا يُسْأَلُ عَمَّا يَفْعَلُ وَهُمْ يُسْأَلُونَ ሰዎች በተሰጣቸው ነጻ ፈቃድ ይሠሩት የነበሩትን መልካም ነገር ይመነዳሉ፥ በተቃራኒው ይሠሩት የነበሩትን መጥፎ ነገር ይቀጣሉ፦ 18፥180 *"ይሠሩት የነበሩትን ነገር በእርግጥ ይመነዳሉ"*፡፡ سَيُجْزَوْنَ مَا كَانُوا يَعْمَلُونَ 6፥120 *"እነዚያ ኃጢአትን የሚሠሩ ይሠሩት በነበሩት ነገር በእርግጥ ይቀጣሉ"*፡፡ نَّ الَّذِينَ يَكْسِبُونَ الْإِثْمَ سَيُجْزَوْنَ بِمَا كَانُوا يَقْتَرِفُونَ አሏህ በነጻ ፈቃዳቸው ካመኑት እና መልካም ከሠሩት ሙተቂን ያድርገን! አሚን። ✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
نمایش همه...
ሁለት አማራጭ በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 91፥8 *"አመጽዋን እና ፍርሃትዋንም ባሳወቃት"*፡፡ فَأَلْهَمَهَا فُجُورَهَا وَتَقْوَاهَا በቁርኣን "ነፍሥ" نَفْس ማለት “ራስነት”own self-hood” ማለት ሲሆን "ማንነት" ነው፥ አምላካችን አሏህ ለነፍሥ በኢህላም አመጽ ምን እንደሆነ እና አሏህ መፍራት ምን እንደሆነ አሳውቋታል፦ 91፥8 *"አመጽዋን እና ፍርሃትዋንም ባሳወቃት"*፡፡ فَأَلْهَمَهَا فُجُورَهَا وَتَقْوَاهَا እዚህ አንቀጽ ላይ "ባሳወቀ" ለሚለው የገባው ቃል "አልሀመ" أَلْهَمَ መሆኑን ልብ በል! "ኢልሃም" إِلْهَام የሚለው ቃል እራሱ "አልሀመ" أَلْهَمَ ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ውሳጣዊ ግንዛቤ"intuition" ማለት ነው፦ ተፍሢሩል ኢብኑ ከሲር 91፥8 *ኢብኑ ዐባሥ "አመጽዋን እና ፍርሃትዋንም ባሳወቃት" የሚለውን ሲናገር፦ "ለእርሷ መልካም እና ክፉን ገልጾላታል"*። ሙጃሂድ፣ ቀታዳህ፣ ሶሓክ እና ሰውሪይ ተመሳሳይ ነገር ብለዋል፥ ሠዒድ ኢብኑ ጁበይር፦ "መልካም እና ክፉን ባሳወቃት" ብሏል"*። قال ابن عباس : ( فألهمها فجورها وتقواها ) بين لها الخير والشر . وكذا قال مجاهد ، وقتادة ، والضحاك ، والثوري . وقال سعيد بن جبير : ألهمها الخير والشر . "ፉጁር" فُجُور ማለት "አመጽ" ማለት ሲሆን ይህም አመጽ አሏህ ያዘዘውን መልካም ነገር ባለማድረግ እና የከለከለውን መጥፎ ነገር በማድረግ ማመጽ ነው፥ "ተቅዋ" تَقْوَا ማለት ደግሞ "አሏህን መፍራት" ማለት ሲሆን ይህም ፍርሃት አሏህ ያዘዘውን መልካም ነገር በማድረግ እና የከለከለውን መጥፎ ነገር ባለማድረግ መታዘዝ ነው። ከዚያም ሰው ዐቅሉ ሲያመዛዝን አሏህ ነቢይ ልኮ በወሕይ "ይህ መልካም ነው" "ይህ መጥፎ ነው" በማለት ቅኑን መንገድ ከጠማማው መንገድ ይገልጥልናል፦ 2፥256 በሃይማኖት ማስገደድ የለም፡፡ *ቅኑ መንገድ ከጠማማው በእርግጥ ተገለጠ*፡፡ لَا إِكْرَاهَ فِي الدِّينِ ۖ قَد تَّبَيَّنَ الرُّشْدُ مِنَ الْغَيِّ ۚ አሏህ ያዘዘውን መልካም ነገር በማድረግ እና የከለከለውን መጥፎ ነገር ባለማድረግ አሏህ የሚፈራው "ሙተቂን" مُتَّقِين ሲባል በተቃራኒው አሏህ ያዘዘውን መልካም ነገር ባለማድረግ እና የከለከለውን መጥፎ ነገር በማድረግ ያመጸው አመጸኛ "ፉጃር" فُجَّار ይባላል፦ 38፥28 *"በእውነቱ እነዚያን ያመኑትን እና መልካሞችን የሠሩትን በምድር ውስጥ እንደሚያጠፉት እናደርጋለን? ወይስ "አላህን ፊረዎቹን እንደ ከሓዲዎቹ እናደርጋለን?"* أَمْ نَجْعَلُ الَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ كَالْمُفْسِدِينَ فِي الْأَرْضِ أَمْ نَجْعَلُ الْمُتَّقِينَ كَالْفُجَّارِ “ዘንብ” ذَنب ማለት “ኃጢአት” ማለት ነው፥ “ኃጢአት” ማለት በሥነ-ኃጢአት ጥናት”hamartiology” አሏህ ያዘዘውን መልካም ነገር አለማድረግ፥ የከለከለውን ክፉ ነገር ማድረግ ነው። አምላካችን አሏህ ለሰው የሰጠው መልካም እና ክፋ የማሰብ፣ የመናገር፣ የማድረግ ነጻ ምርጫ በችሎታችን ልክ ነው፥ ያለ ችሎታችን ልክ አያስገድደንም፦ 23፥62 *ማንኛይቱንም ነፍስ ችሎታዋን እንጂ አናስገድዳትም*፡፡ وَلَا نُكَلِّفُ نَفْسًا إِلَّا وُسْعَهَا 2፥286 *አላህ ነፍስን ከችሎታዋ በላይ አያስገድዳትም*፡፡ لَا يُكَلِّفُ اللَّهُ نَفْسًا إِلَّا وُسْعَهَا "ዉሥዕ" وُسْع ማለት "ዐቅም" "ችሎታ" ማለት ሲሆን አንድ ሰው አንድን ነገር የማድረግ እና ያለማድረግ ችሎታ ከአሏህ የተሰጠ ነጻ ፈቃድ ነው፥ ከተሰጠው በላይ ለማድረግ ላለማድረግ የተገደደ ሰው አይጠየቅም። “የተገደደ ሰውም በእርሱ ላይ ኃጢኣት የለበትም” فَمَنِ اضْطُرَّ غَيْرَ بَاغٍ وَلَا عَادٍ فَلَا إِثْمَ عَلَيْهِ ተብሏልና፦ ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 10, ሐዲስ 2123 ኢብኑ ዐባሥ እንደተረከው፦ “ነቢዩም”ﷺ” አሉ፦ *”አላህ በኡማዬ ላይ ስህተት፣ መርሳት እና የገተደዱበትን ነገር አንስቷል”*። عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ، عَنِ النَّبِيِّ ـ صلى الله عليه وسلم ـ قَالَ ‏ “‏ إِنَّ اللَّهَ وَضَعَ عَنْ أُمَّتِي الْخَطَأَ وَالنِّسْيَانَ وَمَا اسْتُكْرِهُوا عَلَيْهِ ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 40, ሐዲስ 48 ዓኢሻህ "ረ.ዐ." እንደተረከው፦ "የአላህ መልዕክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *"ብዕር ከሦስት ሰዎች ተነስቷል፥ እነርሱም፦ የተኛ ሰው እስኪነሳ ድረስ፣ ዕብደ ወደ ዐቅሉ እስኪመለስ ድረስ እና ልጅ እስኪጎሎብት ድረስ"*። عَنْ عَائِشَةَ، رضى الله عنها أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ "‏ رُفِعَ الْقَلَمُ عَنْ ثَلاَثَةٍ عَنِ النَّائِمِ حَتَّى يَسْتَيْقِظَ وَعَنِ الْمُبْتَلَى حَتَّى يَبْرَأَ وَعَنِ الصَّبِيِّ حَتَّى يَكْبَرَ ‏ አሏህ ፍትሓዊ አምላክ ነው፥ ባለማወቅ ስህተትን ለሚሠሩ እና መልእክቱ ያልደረሳቸውን ሰዎች አይቀጣቸውም፦ 2፥286 *"ጌታችን ሆይ! ”ብንረሳ ወይም ብንስት አትቅጣን” በሉ*፡፡ رَبَّنَا لَا تُؤَاخِذْنَا إِن نَّسِينَا أَوْ أَخْطَأْنَ 33፥5 *በእርሱ በተሳሳታችሁበትም ነገርም በእናንተ ላይ ኃጢአት የለባችሁም፥ ግን ልቦቻችሁ ዐዉቀው በሠሩት ኃጢአት አለባችሁ"*። አላህም መሃሪ አዛኝ ነው። وَلَيْسَ عَلَيْكُمْ جُنَاحٌۭ فِيمَآ أَخْطَأْتُم بِهِۦ وَلَٰكِن مَّا تَعَمَّدَتْ قُلُوبُكُمْ ۚ وَكَانَ ٱللَّهُ غَفُورًۭا رَّحِيمًا 17፥15 *መልእክተኛንም እስከምንልክ ድረስ የምንቀጣ አይደለንም*፡፡ وَمَا كُنَّا مُعَذِّبِينَ حَتَّىٰ نَبْعَثَ رَسُولًا
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
የካቲት 16 ወይንም February 24 በዕለተ ቅዳሜ ከምሽቱ 2:30 ጀምሮ በጋዜጠኛ አብዱረሒም አህመድ (Abdurahim Ahmed) የቲክቶክ አካውንት በኩል ለሒዳያ ኢስላማዊ ማዕከል ፕሮጀክቶች የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ይካሔዳል። ሒዳያ ኢስላማዊ ማዕከል በሚሽነሪ እንቅስቃሴዎች ዙሪያ ትኩረቱን አድርጎ የሚሰራ ተቋም ሲሆን ለቀጣይ ሁለት አመታት ያቀዳቸው 3 ፕሮጀክቶች እንዲሳኩ ለማድረግ የፈንድሬይዚንግ ፕሮግራም በአሏህ ﷻ ፍቃድ ይካሔዳል። በዚህ የድጋፍ መርኅ ግብር ተገኝተው የዳዕዋው አካል እንዲሆኑ ጥሪ ቀርቧል። 1000499318212 Hidaya Islamic Center አጭር የንግድ ባንክ ቁጥር - 8212 የአብዱረሂም ቲክቶክ አካውንት ፎሎው ያድርጉ https://www.tiktok.com/@abdurahimahmed99?_t=8k2WeDvrYQI&_r=1
نمایش همه...
👍 39
Photo unavailableShow in Telegram
የመጽሀፍ ቅዱስ ግጭቶች #27 https://vm.tiktok.com/ZMM1DKVhw/
نمایش همه...
👍 18
የመጽሀፍ ቅዱስ መበረዝ ማሳያዎች #4 https://vm.tiktok.com/ZM6oHsoAW/
نمایش همه...
👍 11
Photo unavailableShow in Telegram
የመጽሀፍ ቅዱስ ግጭቶች #26 https://vm.tiktok.com/ZM6K5Eu6C/
نمایش همه...
👍 19
Photo unavailableShow in Telegram
አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች ለጉዳይ ስንንቀሳቀስ ከሚያስቸግሩን ነገሮች ውስጥ አንዱ መስጅድ ያለበትን ቦታ በቀላሉ አለማወቃችን ነው። ይህንን ችግር የሚፈታና በቀላሉ የትም አካባቢ ያሉ መስጅዶችን በቴሌግራም በኩል በቀላሉ የምታገኙበትን ቻናል ልጠቁማችሁ ... ያላችሁበትን አካባቢ ስሙን ብቻ ሰርች ማድረጊያው ላይ በመጻፍ ለናንተ ቅርብ የሆነውን መስጅድ ከነጎግል ማፕ አድራሻው የምታገኙበት የቴሌግራም ቻናል ሲሆን በሀገራችን ያሉ መስጅዶችን በዝርዝር እየተጨመሩበት ይቀጥላል። ለአብነት ጀሞ አካባቢ ብትሆኑና አቅራቢያችሁ ያለ መስጅድ ብትፈልጉ በቀላሉ ሰርች ማድረጊያው ላይ "ጀሞ" ብላችሁ መጻፍ ብቻ ነው የሚጠበቅባችሁ። ከሚመጣላችሁ ዝርዝር ውስጥ ማፑን በመመልከት የሚቀርባችሁ ጋር መስገድ ትችላላችሁ። ክፍለ ሀገርም ቢሆን በተመሳሳይ ነው። ◾️ ከመስጅዶች በተጨማሪ የሙስሊም የቀብር ቦታዎችንም አካቷል። ሼር በማድረግ በናንተ ምክንያት ሶላታቸውን ሳይቸገሩ በሰገዱ ሰዎች ልክ የአጅሩ ተካፋይ ይሁኑ...! https://t.me/ethiopianmosques
نمایش همه...
👍 71 21👏 1