ኬልቅያስ
رفتن به کانال در Telegram
ኬልቅያስ የቴሌ ግራም ቻናል ኦርቶዶክሳዊ የነፍስ ማዕዶችን የሕይወት ቃል ወንጌለ መንግሥት የምስል ( vidio ) ትምህርቶች ፣ ያሬዳዊ መዝሙራትን ፣ የቅዱሳን ዜና ሕይወት ፣ ወቅታዊ የቤተክርስቲያን መረጃዎች፣ የአብያተ ክርስቲያናት እና የገዳማት ታሪክ ፣ የአባቶች ምክር ፣ የጠቢባን የአባቶች አባባል ፣ መንፈሳዊ ጥቅሶች እና ኪነ - ጥበባዊ ልዩ ልዩ አውዶች የሚቀርብበት ነው።
نمایش بیشتر404
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
در حال بارگیری داده...
کانالهای مشابه
ابر برچسبها
هیچ دادهای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
اوت '24
اوت '24
+4
در 0 کانالها
ژوئیه '24
+7
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '24
+11
در 0 کانالها
Get PRO
مه '24
+14
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '24
+5
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '24
+11
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '24
+8
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '24
+13
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '23
+24
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '23
+32
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '23
+24
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '23
+35
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '23
+29
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '23
+31
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '23
+27
در 0 کانالها
Get PRO
مه '23
+16
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '23
+23
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '23
+19
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '23
+8
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '23
+11
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '22
+18
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '22
+19
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '22
+25
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '22
+20
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '22
+29
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '22
+11
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '22
+2
در 0 کانالها
Get PRO
مه '22
+2
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '22
+8
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '22
+1
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '22
+2
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '22
+9
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '21
+9
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '21
+11
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '21
+12
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '21
+3
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '21
+11
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '21
+11
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '21
+27
در 0 کانالها
Get PRO
مه '21
+222
در 0 کانالها
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 06 اوت | +2 | |||
| 05 اوت | 0 | |||
| 04 اوت | 0 | |||
| 03 اوت | +2 | |||
| 02 اوت | 0 | |||
| 01 اوت | 0 |
پستهای کانال
እለቱ እሁድ ነው ቅዳሴ እንዳይታጎል አገልጋዮቹ መጨነቅ ጀመሩ። በዚህ መካከል መሪጌታና አረጋዊው አባት ወደ ውስጥ ገቡ። ሌሎቹ እንግዶች ከደጅ አጸዱ ስር ከቁጥቋጦ መካከል ተሸሽገው ቆሙ። ለመሪጌታ ጉዳዩን አሳወቋቸውና መሪጌታ አቤልን አሟልተው እንዲገቡ ነገሯቸው። አንዱ ዲያቆን ሲያናግረው ስሙር ይሰማው ነበረ። አቤል ግን አንዳች ንፍታሌምን የሚበልጥበት ነገር በማግኘቱ እየተኩራራ አፍንጫው ውስጥ የሆነ ነገር ሲሰማው ቅዳሴውን ገብቶ ሊቀድስ ተስማምቶ ወደ ደጅ ወቶ ሲናፈጥ ደም ይንጠባጠብ ጀመረ። ጠርቶ ነግሯቸው ከአንድ አጸድ ስር ቀና ብሎ አንጋጦ ተቀመጠ። አረጋዊው አባት መሪጌታ ያሰቡት እንዳልሆነ ሲገባቸው ዲያቆን ቢጠፋ ንፍታሌምን እንዲገባ የግድ ብለውት ቅዳሴው ተጀመረ። ዝክረ ጻድቅ፣ስሙርም ከስርአተ ቁርባኑ ከመሪጌታና ከንፍታሌም እጅ ቆረቡና ቅዳሴ ሲያልቅ ሁላቸውም ወደየቤታቸው አቀኑ። ንፍታሌምና ባሪያውም ከመሪጌታ ቤት ዋሉ። ሌሊት ዘጠኝ ሰዓት ከመሆኑ በፊት አረጋዊው አባትና መሪጌታ ስሙርን ንፍታሌምናንፍታሌምና ባሪያውን ቀስቅሰዋቸው ወደ ተራራው አምስት ሆነው አቀኑ። ስሙር ግራ ገብቶታል ዝክረ ጻድቅ ደግሞ ፍርሀት እየናጠው ነው። ንፍታሌም ከሁሉም የበለጠ እርብሽብሽ ብሏል። መሪጌታና አረጋዊው ከፊት ቀድመው ሶስቱ ከኋላ ተከተሉ። ስሙር ድምጹ እየተንቀጠቀጠ " ንፍታሌም አንተ ልዩ ሰው ነህ በአንተ ላይ ክፉ ያሰብኩበትን ያለፈውን ቀን በድጋሚ ይቅር በለኝ። አንተ ትሁት ምሳሌም ነህ" አለው። ባሪያውም " ተደብቀህ ኖረህ ሰው በጠፋበት ሰው ሆነህ የተገኘህ ልዩ ሰው ነህ። ከአንተ ክርስትናን ተማርኩ" እያወሩ ወደ ሙሲቾ ተራራ ገሰገሱ። ከተራራው መሀል ሲደርሱ ሌሎች አራት ሰዎችን አገኙ። ከአራቱ አንዱ አቤል ነበረ። ሲያዩት ተደነቁ። አብረውት የነበሩትን ግን ከመሪጌታና አረጋዊው አባት ውጭ ማንም አላወቃቸውም። አቤል ስቅስቅ ብሎ ያለቅሳል። ዘጠኙም በአንድ ወደ አንድ ጉዞ። መሪጌታ አረጋዊውና ሌላው አረጋዊ ከፊት። የሚያማምሩት ልዩ ደም ግባት ያላቸው ወጣቶች ተከትለው ንፍታሌም ስሙር ባሪያውና አቤል ከኋላ ወደ ምሥጢራዊው መንደር ገሰገሱ።
❖ምዕራፍ 6 ተፈጸመ❖
| 2 | ሁሌ ባገኘኝ ቁጥር የሚያስቸግረኝ እንዴት የሚወደኝ ሰው አባትሽን በኔ ምክንያት ሊገድል ሆነ ከዚያ ነው በዚያ ምክንያት ተሰደን ከሀገር የወጣነው ፍቅር ከባድ ነው። እኔም ተመስገን ነው። የሚወደኝ ሕይወት አስተማሪ አጅ ጣለኝ። ምናኔንም በአባትሽ አየሁ በዓለም የሚኖር መናኝ ስውር ሰው። ከርሱ አንቺን ስሙርን አብሮኝ ባይኖርም ፀጋ ዘአብን ወለድኩ አሁን ደስተኛ ነኝ" አሏትና " ሰላሜ የምትይውን ልጅ ትወጂዋለሽ አይደል?" ጠየቋት ዛሬ መደበቅ አልቻለችም " አዎ በጣም እእወደዋለው። እማ እርሱ ምንም እንዳይሆንብኝ ያለርሱ መኖር ምችል አይመስለኝም" አለቻቸው። "ነይ እንተኛ ምንም አይሆንም ልጄ!" አሏትና ውስጣቸው እየተብሰለሰለ ወደ ውስጥ ተያይዘው ገቡ።
ከሙሲቾ ተራራ ከከፍታው ማማ ከስውራኑ ደጅ ከጠቢባኑ እልፍኝ ከቅኔው አዝመራ ውዳሴ ይፈሳል ዓለምን የናቋት ከርሷ የኮበለሉ የተውአት የተወቻቸው ደግሞ በዓለም እያሉ እርሷን የናቋት ብቻ በዚህ ልዩ ስፍራ ያሉት ከዚህ ከሥውሩም ዓለም በመስጋና ሰረገላ ተሳፍረው ደግሞ ወደ ሌላ ምሥጢር ምሥጢር ሊካፈሉ ሰማየ ሰማያት በተመስጦ ተሸጋግረው ያወድሳሉ። የዚያ መንደር ምስጋና አዎ ልዩ ነው። ከአፍ ብቻ የሆነ አይደለም ከጥልቁ የልብ ሸለቆ የሚፈስ በመንፈስ ቅዱስ በተቃኘ አንድ አይነት ልሳን የሚሰማ እንጂ። መቅደሱ ሙሉ ነው። ያ ሌሊት ይለያል ከስውሩ መቅደስ ውስጥ የተገኙት ሁላቸው በነጭ ካባቸው ደምቀው የወርቅ ዘንግ የሚያበራ የሚያንጸባርቅ መቋሚያ ጨብጠው እርሱን በሚመስል ጽናጽል ውዳሴን ያቀርባሉ። ዝማሬው ዝማሜው እየጫነ ወደ ፈጣሪያቸው ይወስዳቸዋል። ብዙዎቹ ለዚህ አገልግሎት ከያሉበት የሚሰባሰቡ ሲሆኑ በርካቶቹ እድሜ ጠገቦች ናቸው ጽሕማቸው ነጭ ጥጥ ይመስላል ከገጻቸው የሚታየው ፈገግታ ውስጥ ልዩ እርካታ አለ። እነዚህ የንጉሥ አገልጋዮች በርሱ የተወደዱ ናቸው። ንጉሣቸውም ድንቅ ስለሆነ ከነርሱ የሚሰማው የሚያስደንቅ ነው። ዜማቸው ድምጻቸው እንቅስቃሴአቸው ሁሉ አንድ ነው። ከበሮ የሚመቱት አባት ካሉት ሁሉ በድሜ ቀዳሚው ናቸው። ከበሮ አመታታቸው ለዛው አንዳች የተለየ ነው። ወረቡን የሚወርቡት ሊቅ እንደጨረሱ ደግሞ ባለ ምጡቅ አእምሮው ትህትናን የተላበሱት መሪጌታ አመሀ ጀመሩት ዝማሬው ምስጋናው የበለጠ ደመቀ ድምጻቸው ከነለዛው ጨመረ። ሁላቸውም ተያይዘው በምስጋና ወደ ሰማያት ወጡ። ድምጻቸው አልፎ አልፎ የሰባት ሰዓት መንገድ ታች አዋሽ ቆላቲ ላደላቸው ይሰማል። የሰማው ሰው እንኳ ነፍሱ ሀሴትን ታደርጋለች። አዎ ይህ ድምጽ ጽንጽሉ ከከበሮው ከበሮውም ጸጋ ከበዛላቸው ከጠቢባኑ ጥዑም ዜማ ጋር የተዋሀደ የተስማማ ልዩ ሰማያዊ ዜማ ነውና። በመቅደሱ ያለው ብርሃን ምሥጢር ነው። ምክንያቱም ከዚህ መንደር ሰው ሰራሹ መብራት የለም። ሰማያዊ ምሥጢር በምሥጢር ያሰናዳው እንጂ። ሊቃውንቱ ዝማሬአቸው ሲደምቅ ምስጋናው እንደቀጠለ ከውስጥ ከመቅደሱ ልዩ ልብስን የለበሱ የምሥጢራዊው መንደር አገልጋዮች ካህኑ ጽና ይዘው እያጠኑ ይወጣሉ። ተራዳኢው ካህንም በአገልግሎቱ ይራዳሉ። መስቀል የያዘው መልኩ ታይቶ የማይጠገብ በእድሜ በጣም ልጅ የሆነ ዲያቆን ተከትሎ ይወጣል። ሌላው ተከትሎ የወጣውም እንደርሱ ሁሉ በእድሜ ገና ልጅ ነው። ዲያቆናቱ ሶስቱም መንትያ ነው የሚመስሉት መልካቸው ውበታቸው ሁሉ አንድ ነው። ካህኑ ሲያጥኑ ልዩ መአዛ ያለው የእጣን ጢስ መቅደሱን ሞልቶ ያውዳል። ይህ ለታደሉቱ አንዳንዴ እሩቅ ተጉዞ ከተራራው ግርጌ ሄዶ የጣኑ ጢስ ያውዳቸዋል። መአዛው ይለያል ነፍስና ስጋን የሚለይ ነው እሚመስል ልብን ያሳርፋል። ከውስጥ ከካህኑ ተከትለው ዲያቆናቱ ሲወጡ ዝማሬው ውዳሴው የበለጠ ይደምቃል ምስጋናቸው ከእጣኑ ጢስ ጋር ካሉበት ሰማይ ወደ ሰማያዊው ሰማይ ያርጋል። በዚያ " ስበሀት ለአብ ስበሀት ለወልድ ስበሀት ለመንፈስ ቅዱስ" የካህኑ ድምጽ ነፍስን ሀሴት ይመላል። በቤተ መቅደሱ ከምሥጢራዊው መንደር ቤተክርስቲያን ውስጥ የተገኙት ሁሉ ተሰጥኦ በአንድ ልብ በአንድ ድምጽ አንድ ቃል ያወጣሉ " ይደሎሙ ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ" እንዲህ ያለ ልዩ ዜማ በዚህች ምሥጢራዊ መንደር እንጂ ፍጹም በዓለም ከቶ የለም። ብዙዎቹ ገጻቸው ላይ እንባ ይፈሳል። ድምጻቸው ግን ከውዳሴው አይቦዝንም። አገልግሎቱ ሲጠናቀቅ ትተዋት ከወጡት ዓለም ሰው ሁሉ በእንቅልፍ ዓለም ነው። በዚያ ውድቅት ከዚህ ከነርሱ ግን የምስጋናው አዝመራ የሚታጨድበት ነው። አገልግሎቱ ሲያልቅ በዚያ የተገኙት ሁሉ ከሁለት ጎራ ተከፍለው ከመቅደሱ ውጭ ተገናኝተው የአረጋውያኑ ስብስብ በአንድነት አንዳቸው ከአንዳቸው ትከሻ እየወደቁ ተቃቅፈው ሰላምታ ይለዋወጣሉ። ድምጽ አያሰሙም በዝምታ ውስጥ ልባቸው ይግባባል ዓይናቸው ይነጋገራል። እንዲሁ ደግሞ በእድሜ የሚያንሱት ወጣቶቹ ሕፃናቱ በአንድ ጎራ እንደ አረጋውያኑ እንደ አባቶቻቸው ሁሉ ይህን ይከውናሉ። በየ እድሜአቸው ሰላምታውን ሲፈጽሙ ሕፃናቱና ወጣቶቹ በደ ሊቃውንት አረጋውያኑ ወደ ታላላቆቻቸው ቀርበው ከእግራቸው አጎንብሰው ጉልበት እየሳሙ እንዳጎነበሱ አባቶቻቸው እጃቸውን ከራሳቸው ጭነውባቸው ከአንደበት ያልሆነ ልባው ምርቃትና ጸሎት ለነርሱ ያደርጋሉ። በፍቅር ያለ እንዲህ ያለ አብሮነት ከዚህችኛዋ መንደር ውጭ ከቶ በየት አለ። በፍቅር ተሰነባብተው ይለያያሉ። ያ ተራራ ይህን አገልግሎት ሲፈጽም ብርሃኑ ይሰወራል ምሥጢሩን ሁሉ በውስጡ እንደያዘ ይጨልማል። ከተራራው አናት የሚወርዱት አምስት ሰዎች እርምጃቸው የሚለያይ አይደለም በአንድ ከአንድ ወደ አንድ የሆነ ነበር ተከታትለው ከማይታየው ከጠቢባኑ መንደር ከሥውሩ ደጅ ወደ ሌላኛው መንፈሳዊ ግልጥ መቅደስ ይገሰግሳሉ። ከፊት የሚመሩት ከነሰላም ቤት በእንግድነት የሰነበቱት አባትና ሌላ አረጋዊ አባት ናቸው። መሪጌታ ደግሞ ከሁለት ወጣቶች ጋር ከኋላ ይከተላሉ። መንገዳቸው የዝምታ እንጂ ዋዛ ፈዛዛ የዚህ ዓለም ከንቱ ወሬ አልያ ቧልት የሚሰማበት አይደለም። አምስቱም ለአንድ አላማ በአንድ ከአገልግሎት ወደ አገልግሎት ይጓዛሉ። ማንም ሳይቀድም ማንምም ሳይዘገይ እኩል አዋሽ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን ደረሱ።
ስሙር ነጭ በነጭ ለብሶ ውስጡ አንዳች ተሰምቶት የማያውቅ ፍርሀት ይሁን ደስታ አንዳች ስሜት እየተሰማው ከቤተክርስቲያኑ ውስጥ ቆሞአል። ከጎኑ የቆመው አቤልም እንዲሁ ከፊቱ ምናልባትም ሲናፍቀው የኖረው ሲፈልገው የከረመው ዋጋ የከፈለለት ብዙ ጊዜ ሳያውቅ ያለፈው ነገር የተቃረበ ያክል እየተሰማው ብቻ ለአንዳች ክብር የታጨ መስሎ እየተሰማው ደግሞ እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ እድሉን ባለማስተዋል እንዳያጠፋ እየፈራ ከስሙር አጠገብ ቆሟል። ካህናቱ አገልግሎቱን እያገለገሉ ስሙርና አቤል ወደ ቤተ መቅደሱ ከገቡ ጥቂት ዘግይተው አቤልና ዝክረ ጻድቅ ባሪያ ደግሞ ገቡ። ሁለቱም በወንዶች መሳለሚያ በኩል ተከታትለው ተሳልመው ነው የገቡት። ስሙርና አቤል ሲገቡ አዩአቸው። ስሙር ንፍታሌም ውስጥ ገብቶ በትህትና ጎንበስ ቀና ብሎ ሲሳለም አየውና መንፈሳዊ ቅናትን ቀናበት። ባሪያውም እንዲሁ አድርጎ ከአንዱ ጥግ ንፍታሌም ከቆመበት አጠገቡ ደርሶ ቆመ። ስሙር ስለ ንፍታሌም የነበረውን ክፉ ነገር ሁሉ በጸጸት ከውስጡ አስወገደ። አቤል ግን ድጋሚ በንፍታሌም መፈተን ጀመረ። አንድ የጥላቻ ስሜት አስመሳይ ነው ሰላምን የነጠቀህ ነው የሚል ሀሳብ አብዝቶ ፈተነውና በልቡ ወንድሙን ከይቅርታ በኋላ መቅደስ ውስጥ ቆሞ ኮነነው።አገልግሎቱ ከኪዳን ሲደርስ ከንድ ነገር ተፈጠረ። አንዱ ዲያቆን የማይቻለው ሆኖ አልተገኘም። ሌላ ደግሞ ትርፍ ዲያቆን የለም። | 328 |
| 3 | 👤👤👤👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤👤👤👤
👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤
👤 ህቡዕ ገጽ 👤
💢💠 ከክፍል 179 የቀጠለ 💠💢
ስሙር ተሰናብተው ከመውጣታቸው በፊት ዝክረ ጻድቅን "ሁሌ ከዚህ ነው የምትገኘው?" ጠየቀው። ሀሳቡ ሌላ ጊዜ ሊያገኘው ነው። " እግዚአብሔር ካለበት" መለሰለት ስሙር ነገ አልችልም ሌላ ጊዜ እንገናኛለን" ብሎት ሲወጣ አቤል ተከተለው። ሰላም ግን ልቧ መለየት አቃተው እግሯም መራመድን እንቢ አላት ቆማ ቀረች። ከዋሻው መውጫ ሲደርሱ ስሙር " ሰላም በጣም መሽቷል ነይ እንጂ!" ሲላት ወደ ወንድሟ መራመድ ጀመረች። አቤልና ስሙር ወንዙን መሻገር ሲጀምሩ ወደ ኋላ ተመልሳ በማይታየው ጨለማ ውስጥ " ንፍታሌም!" ብላ ተጣራች። " አንዴ አናግረኝ" ስትለው ወደርሷ መቶ አጠገቧ ሲደርስ ስሙር " ሰላም ምን ሆነሻል ቆመናልኮ!" ሲል ተቻኩላ " ንፍታሌም አፈቅርሀለው!" አለችው። መብረቅ የወረደበት መሰለው።
💢💠🌿 ክፍል 180 🌿💠💢
ሰላም እንደቆመች ንፍታሌም ምላሽ ሳይሰጣት በዝምታ ብቻ ጥምጥም ሲልባት በእቅፉ ውስጥ ሆና ከንዳች ልዩ ደስታ ወደር የሌለው ፍሰሀ ሲሰማት ከእቅፉ መውጣት እንደ ሞት ሲያስፈራት ፍቅሯ በልቧ ውስጥ እንደ እሳት ሲቀጣጠል " አንተ ለኔ ልዩዬ ነህ ልዩ። በቃ አሸነፍከኝ ተረታው። ፍቅርህን በልቤ ይዤ ቀናት ወራትን ወልደው ብቻዬን አለፍኳቸው። ቢያቅተኝ ዛሬ የውስጤን አምጬ አወጣሁት። የኔ ንጉሥ በጣም ነው የምወድህ!" ስትለው አርሱም በእቅፉ ውስጥ እንዳለች ወደ ጆሮዋ የምስራች የሆነ ደስታን ያበሰራት ቃል ተሰማት " ሰላም እኔም በጣም እወድሻለው ላንቺ ያለኝ ፍቅር ወደር የለውም። እንዳንቺ የምወደው በዚህ ዓለም ላይ ማንም የለም። ከእንግዲህ እኔ ያንቺ አንቺም ደግሞ የኔ ብቻ!" ሲላት "ታውቃለህ ያኔ ከቤዛ ጋር ኩክየለሽ የነበርክ ጊዜ በቃ አቃተኝ ፍቅርህ ከአቅሜ በላይ ሆነብኝ። የማጣህ የማጣህ የሌላ የምትሆን መሰለኝና አንተንና ፍቅሬን የማድን የምታደግ መስሎኝ ነበረ አንተን ፍለጋ የመጣሁት። ንፍታሌም የኔ አሸናፊ ከእንግዲህ አንተን ከኔ ማንም አይወስድብኝም አይደል?" ስጠይቀው " በፍጹም እኔን ከአንቺ በልጣብኝ የምትወስደኝ ማን ትኖራለች? አይሆንም በቃ አንቺ ለኔ ከማንም በላይ ነሽ እኔምኮ አንቺን ማጣት አልፈልግም ሰላምዬ" ሲላት " እሺ አምንሀለው" አለች በእቅፉ እንዳለች ከዚያ ንፍታሌም ቀስ ብሎ ለቀቅ ሲያደርጋት ቀና ብላ ዓይኗን ከዓይኑ ጣል ስታደርግ ዓይኖቻቸው ያለ ቃል ሲናበቡ ሲግባቡ ልቧ ልዩ ስሜት እየተሰማው ንፍታሌም ሊስማት ወደርሷ ሲጠጋ ስሙር ከየት እንዳመጣ ባላወቀችው መሳሪያ እህቱን ቆሞ እያየ ንፍታሌም ሊስማት ወደርሷ ልክ ከንፈሮቹ ሲደርሱ ተኩሶ መታው። ንፍታሌም ትከሻውን የመታው መሳሪያ የኋሊት ሲደፋው ሰላም " ዋይ !" ብላ ጮኸች። " በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! አቡዬ አባቴ የዲማው ጊዮርጊስ እመቤቴ ድረሽ!" አሉ የሰላም እናት በልጃቸው ጩኸት ከተኙበት ዘለው ተነስተው። ሰላምም ተነስታ በረጅሙ ቁና ቁና ተነፈሰችና አማትባ አጭር ጸሎት አደረሰች። " ምነው ሰላሜ! ምንድነው? ምን አገኘሽ? እዚያ ጫካ ውስጥ ብቻሽን እየዞርሽ ኢኸው ትርፉ ኢሄ ነው!" አሉ እንደመቆጣትም እንደመቆጨትም ብላ። ሰላም ወዲያው በእንቅልፍ ልቧ ሆኖ ያየችው እውነት መስሏት ማመን አቅቷት ሰዓት ስታይ ሌሊት 9:40 ሆኗል። ፈጥና ተነስታ ወደ አባቷ ክፍል ገባች። አባቷም እንግዳውም መነኩሴ የሉም። ወጣችና ወደ ሌላኛው ክፍል አመራች። የያዘችውን የጅ ባትሪ አብርታ ስታይ የወንድሟ መኝታ ላይ አቤልም ስሙርም የሉም። ይህን ሆኖ ስታይ ጭራሽ ውስጧ እርብሽብሽ አለ። ለመጨረሻ ጊዜ ከንፍታሌም ጋር የተለያየችበትን ሁኔታ በቆመችበት እንዳለች በኅሊናዋ መልሳ አስታወሰችው። ከዋሻው በር ላይ ንፍታሌም ከጨለማው ውስጥ እርሷ ከዋሻው ከበሩ ደጅ ሆና ስሙርና አቤል ወንዙን ተሻግረው እየጠበቋት የረጅም ጊዜ ሸክሟን ንፍታሌምን ከፊቷ አቁማ " ንፍታሌም አፈቅርሀለው!" ብላ ያለችበትን ያን ቅጽበት አስታውሳ ፊቷ ፈገግታ ተሞላ። ያያት ያለ ይመስል እንደማፈር ብላ አንገቷን ደፋች። ቀጥላ ሰላም ውስጧን ስላወካት በእንቅልፍ ልቧ ስላየችው ህልም መሰል ነገር አሰበች። ወዲያው ፍርሀት ዋጣትና በፈገግታ ፈክቶ የነበረው ገጿ ጭጋግ የለበሰ ደመና የሸፈነው ሰማይ ሆነ። ሰላም ንፍታሌምን አይበለውና በመሳሪያ ተመቶ ወድቆ ከሆነ ያየችው እውን ሆኖ ከሞተ የምትሆነውን እየሰበች ከሀሳብ ወደ ሌላ የሀሳብ ዓለም ድንበር ተሻገረች። በቆመችበት ካየችው የቀጠለ ሌላ ጉስቁልና የበዛበት የመከራ ኩርንችት ያለበት ረጅም ጉዞ በቀቢጸ ተስፋ ስትጓዝ በውስጧ እንዲህ ሳለች። ንፍታሌም በመሳሪያ ተመቶ እንደወደቀ ሮጣ ላዩ ላይ ድፍት ብላ ብትለው ምን ብታደርገው እስትንፋስ ተለይቶታል። ወንድሟ ስሙርም በርሷ ምክንያት ተኩሶ የገደለውን ሰው በድንጋጤ ተጠግቶ ቢያረጋግጥ መሞቱን ሲያውቅ መሳሪያውን ለራሱም ተጎነጨውና ሳያጣጥመው ንፍታሌምን ተከተለው። በአንድ ጊዜ የልቧ ንጉሥ ፍቅሯና ተወዳጅ ወንድሟ ተያይዘው ጥለዋት ሲሄዱ ብቻዋን ስትቀር አቤል ፈዞ ቆሞ ሲያያት ሰላም በምናቧ ተመለከተች። ይህን ሁሉ ቆማ በውስጧ ስላ ስታመላልስ እናቷ ቆመው ልጃቸውን ያዩአታል። ከዚያ ሰላም ሕይወቷን ስትነጠቅ ፍቅሯን በገዛ ወንድሟ ስትቀማ ባዶ ስትሆን ያን የጨከነባትን ሰው እንኳ እንዳትከስ በራሱ ፈርዶ ወደ ማታገኘው ዓለም ሲያመልጣት የርሱንም የንፍታሌምንም አስክሬን ከዋሻው በር ላይ ትታ ለመራመድ አቅም እያነሳት ግና ሳትቆም ስትሰደድ እርቃ ስትሄድ ከብዙ ቀናት በኋላ ከአንድ በረሀ ደርሳ ከአንዱ ሸለቆ ውስጥ ገብታ ሕይወትን በምናኔ ስትቀጥል በተጋድሎ ስትኖር እናትና አባቷ ፍለጋ ሲደክሙ ውቧ ቆንጆዋ ሰላም አርጅታ በተጋድሎ ጸንታ ኋላ ከመሞቷ በፊት ሊቁን የምሥጢር ደጅ ባለቅኔ አወዳሽ መሪጌታ አመሀን ከአንድ ሥውር ስፍራ ተገናኝተው አብረው ኖረው ከአባቷ በፊት ስትሞት አባቷ ያለ ሀዘን ደስ እያለው ሲቀብራት እርሷም ንፍታሌምና ወንድሟ ስሙር ወደ ሄዱበት ወደ ወዲያኛው ዓለም ስትሄድ....... " ሰላሜ!" አሉ እናቷ እርቃ ከተጓዘችበት የሀሳብ ጉዞ ስበው አሁንና እዚ ላይ መልሰዋት። ድንግጥ ብላ " ወዬ እማዬ! ተነሳሽ እንዴ?" አለቻቸው። " የኔ ልጅ ምን ሆነሻል ንገሪኝ። ምንድነው እንዲህ የምትብሰለሰይበት?" ጠየቋት። " እኔንጃ ህልም ይሁን ቅዠት አላውቅም በፍርሀት ናጠኝኮ" አለቻቸው። " እስቲ ንገሪኝ ምን አይነት ነው። ሰላም ሁሉንም ነገረቻቸው። ሲሰሙ ደነገጡ " ቆይ እንግዳውን ለመጨረሻ ጊዜ መች ነው ያገኘሽው?" ጠየቋት። እርሷም ከነበረበት ዋሻ የተገናኙበትን ነገረቻቸው። " ትናንትኮ ነው የሆነው የምልሽ ሁሉ እማ" አለቻቸው። እናቷ ሰላም የቀን ውሎዋን አስባ የቃዠችም መሰላቸው ደግሞ ህልምም መስሎ ተሰማቸው። " ደግሞኮ የበለጠ ሌላ ፍርሀት ውስጥ የከተተኝ..." ስትላቸው " ሌላ ደግሞ ምን?" አሏት። ሰላም ሳሎን ቆማ በምናቧ ያየችውን አንድ በአንድ ነገረቻቸው። እናቷ የበለጠ ፈሩ ግራ ተጋቡና ልጃቸውን አቅፈው ሳሟትና "ኢሄ ሀሳብ ነው ዝም ብለሽ ተጨንቀሽ" አሏትና "ሰላሜ ባለፈው እንዳልኩሽ ቀድሞ እንዴት የምወደውን የልቤን ሰው ካጣው በኋላ መመነኑን ሰምቼ ልመንን እንደወሰንኩ የአባትሽ ቤተሰቦች ሽማግሌ ላኩ። ቤተሰቤ ሊድረኝ አሰበ። ልጠፋ አስቤ አልተሳካም። ኋላ አባትሽን እንዳገባው ሌላ ደግሞ | 739 |
| 4 | መሆኗን ዘነጋች። እንደሰማችው ሁሉ ስታይ ከጉድጓዱ የምትመለከተው አስደነቃት። ውኃው የጨሳል ሕብረ መልኩ ይለዋወጣል። ከማየትና ከማድነቅ በዘለለ ሰላም ምንም ለማድረግ አልደፈረችም። የምታየው ከኅሊና በላይ ሲሆንባት ስፍራውን በደንብ በማስተዋል ወደ ጀመረችው ፍለጋ ቀጠለች። ስሙርም በፊናው ለብቻው ከጫካው ውስጥ አሳዝኖት አስቀይሞት ለይቅርታ የሚፈልገውን ሰው አቶት አመሻሽ ላይ ቅዳሜ ልትጠናቀቅ ለእሁድ ዝግጅቱ ያለ ንፍታሌም መገኘት የማይሆን መሆኑን እያሰበ እየተጸጸተ ወደ ቤት ሲያመራ አቤልና ሰላምም ሳያገኙት ቀርተው ርቀው ከሄዱበት ደኑን አቆራርጠው እየተመለሱ መውጫው አካባቢ ላይ ሲደርሱ ዝክረ ጻዲቅን አገኙት። መጀመሪያ ሰላም ልብ አላለችውም እልፍ ካለች በኋላ ወደ ዋሻው ሲያቀና ነው የተከተለችው። አቤልም ሰላምን ተከትሏት ወደ ዋሻው አቅጣጫ እያመሩ ስሙር ከርቀት አያቸውና ሮጦ ደረሶባቸው ባሪያው ወደ ገባበት ዋሻ ተከታትለው ገቡ። ብዙ ጊዜ ሰላም ወደዚህ ዋሻ መታ ባሪያውንና ንፍታሌምን ማግኘት አልቻለችም ነበረ። ሶስቱም ወደ ውስጥ ጨለማውን ዘልቀው ገቡ። ባሪያው እንደተከተሉት አላወቀም ነበር። ገብተው መብራት ሲያበሩ ባሪያው ቁጭ ብሏል ብቻውን ነው። ስሙር ፍርሀት ዋጠው። ቀስ እያሉ ሲጠጉት ስሙር ባሪያው መሆኑን ሲያውቅ በደስታ ፊቱ በራ። ሰላም መቆየት አልሆነላትም " ንፍታሌምስ?" ጠየቀችው። ባሪያው ዝም አለ። ወደርሱ ደርሰው ስለ ንፍታሌም ጠየቁት መልስ አልሰጣቸውም። ከቆይታ በኋላ ውጪው ሲጨላልም ንፍታሌም ወራጁን ወንዝ ተሻግሮ መብራት እያበራ ሲመጣ ከውስ ደንግጠው ብርሃኑን አጠፉት። ንፍታሌም ወደ ዋሻው እያበራ ገባ። ከውስጥ እንዳለፉት ሶስት ቀናት ያገኘው አንድ ሰው አልነበረም አራት ሰው እንጂ። እርሱ መሆኑን አጠገባቸው ደርሶ ሲያውቁ ቀድሞ ስሙር ቀጥሎ አቤል ከእግሩ ወድቀው ይቅርታ ጠየቁት። እርሱም ይቅርታ ጠየቃቸው። ሰላም ኋላ ላይ ስላገኘችው በደስታ ተጠመጠመችበት። ወደ ቤት እንዲሄዱ ቢጠይቁት እንቢ አላቸው። ስሙር ተሰናብተው ከመውጣታቸው በፊት ዝክረ ጻድቅን "ሁሌ ከዚህ ነው የምትገኘው?" ጠየቀው። ሀሳቡ ሌላ ጊዜ ሊያገኘው ነው። " እግዚአብሔር ካለበት" መለሰለት ስሙር ነገ አልችልም ሌላ ጊዜ እንገናኛለን" ብሎት ሲወጣ አቤል ተከተለው። ሰላም ግን ልቧ መለየት አቃተው እግሯም መራመድን እንቢ አላት ቆማ ቀረች። ከዋሻው መውጫ ሲደርሱ ስሙር " ሰላም በጣም መሽቷል ነይ እንጂ!" ሲላት ወደ ወንድሟ መራመድ ጀመረች። አቤልና ስሙር ወንዙን መሻገር ሲጀምሩ ወደ ኋላ ተመልሳ በማይታየው ጨለማ ውስጥ " ንፍታሌም!" ብላ ተጣራች። " አንዴ አናግረኝ" ስትለው ወደርሷ መቶ አጠገቧ ሲደርስ ስሙር " ሰላም ምን ሆነሻል ቆመናልኮ!" ሲል ተቻኩላ " ንፍታሌም አፈቅርሀለው!" አለችው። መብረቅ የወረደበት መሰለው።
💠 ይቀጥላል 💠
💢💠 ታኅሳስ 29 2016 ዓ.ም ባሌ ሮቤ 💠💢 | 381 |
| 5 | " ከምሥጢራዊው ምሥጢር ከጠቢባን ጥበብ ከጻድቃኑ ጽድቅ ከቅዱሳኑ ቅድስና ያብቃህ። ጽናትን ያድልህ" ብለውት መንገዳቸውን አቀኑ። ንግግራቸው ሲቆም ንፍታሌም ካለበት ካቀረቀረበት ቀና ብሎ ሲያያቸው አረጋዊው አባት ከፊት ሕፃኑ ከኋላ ተከታትለው ፊትና ጀርባ ሆነው እየራቁ በሄዱ ቁጥር ፍጥነታቸው እየጨመረ ሄዶ ከእይታው ዛፎች ሰወሯቸው። ንፍታሌም ሲለዩት የበለጠ ባየው ነገር ተደናገጠ። እንዲህ ያለ ነገር ሲያይ የመጀመሪያው በመሆኑ ልቡናው ራደ። የሕፃኑ ነገር ከዓይኑ አልጠፋ አለ። " ተመለስ" የሚለውና ሌሎችም አረጋዊው የተናገሩት ነገር በአእምሮው ሲያቃጭል " ተወልጄ ያደኩባት የማውቃት የምትመስለኝ ባሌ ለካ አላውቃት ኖሯል። ከጠቢባን መንደር ወደርሷ ለጥበብ የሚላኩባት ለፈለገ ግዮን ነቅዐ ማይ የራቁ ሲመስሉ ቅርብ የሆኑ ከጥበብ የሚያስጎነጩ የመስቀሉ ትውልድ ስውር እልፍኝ ምዕራፈ ቅዱሳን የበረከት ሀገር የምስጋና መቅደስ ኖራለች ለካ!" አለና በተደሞ የመጣባት ሀገሩን እያወቃት የማያውቃትን ባሌን እስኪያያት ወደ ነቅዐጥበብ መግቢያ በር የሆነችውን ሀገሩን እያወቃት ሊተዋወቃት መዘግየቱን እያሰበ ከቆመበት ወደ ባሌ ልቡ እየናፈቀ የመጀመሪያውን እርምጃ ሀ ብሎ ተራመደ። አልቆመም። ያየውን የሰማውን ሁሉ እያደነቀ እየተደነቀ ደኑን አቆራርጦ ወደ ሰፊው ሜዳ በሚያደርሰው መንገድ ገሰገሰ እንጂ። ነቅዐማይን ሳይጎነጭ መመለሱን አረጋዊው አባት በቃላት ድንቅ ገለጻቸው በውስጡ ስለው ያሳዩት የጥበብ ሀገር ያልተዘመረላት የተሰወረችዋ ባሌ አስረሳችው። በውስጡ ፈለገ ግዮንን ቢያስብ እንኳ ከደጁ ያለውን ምሥጢር ሁሉ ሳያውቅ በአካል ቢቀር በታሪክ አለማወቁ እየጸጸተው ጭምር በጸጸት ሲራመድ የነበረው ሁሉ ትዝ አለው።ንፍታሌም ያኔ ያወሩት አሁን መሰለው። ንፍታሌም ያ ቀን ከብራናው ላይ በትዝታ በምስል ተስሎ ታየውና ከሀሳቡ እንደነቃ ብራናውን ገልጦ አየው ብራናው ላይ ምንም አይነት መልዕክት ምንም አይነት ጽሑፍ የለም። ፈዞ ቀረ።
ሙሉ ቤተሰቡ ለረጅም ሰዓታት አንድ ሰው ሳያይ ቆየ። ቀኑ አልፎ ፀሐይ ወደ ማደሪያዋ ልትገባ ከመግቢያዋ በር ደርሳ አዘቅዝቃለች። ከብቶች ከየቦታው ድምጽ እያሰሙ ወደ ማደሪያቸው ይጓዛሉ። የመሪጌታ ቤተሰብ በጊዜ ስብስብ ብሏል። ግና አንድ ሀሳብ በቤቱ ውስጥ ስጋት ፈጥሯል። " እንግዳውስ?" ጠየቁ መሪጌታ። ሁሉም ተፋጠጡ። ስሙር የቀኑን ክስተት አስታወሰ። እናቱም ቀና ብለው አይተውት መልሰው አቀረቀሩ። ሰላም ግን የንፍታሌም እስካሁን አለመምጣት እጅጉን ሰላም ነሳት። አቤል ግን ጥሩ አጋጣሚ የተፈጠረ ያክል ተሰማው። የስሙር እናት ወደ ስሙር ክፍል ገብተው የንፍታሌምን ቦርሳ ሲያዩ የለም። ደነገጡ። "ሰላም!" ብለው ተጣሩ። እንደመጣች ድምጻቸውን ቀንሰው ጠየቋት " ቦርሳውም የለምኮ የት ሄዶ ነው?" አሏት። ሰላም ልቧ ተሰበረ። በወንድሟ በብዙ አዘነችበት። ሰዓቱ እየገፋ እየገፋ ሲመጣ ሰላምና እናቷ ጭንቀታቸው ጨመረ። ሰዓቱ መሸ ሰማዩ ግን በጨረቃ ብርሃን በከዋክብት አጊጦ ልዩ ውበት ነበረው። ስሙርና አቤል ወደ ውጭ ተከታትለው ወተው ደጅ ተቀመጡና ማውጋት ጀመሩ። ስሙር " አቤል ስራህ ምን ነበረ? እስቲ ስለጠፋው ትተን ስለራሳችን እንጨዋወት" አለው። አቤል ስለራሱ ለስሙር መንገር ያለበትን ባጭሩ ስለሕይወቱ ተረከለት። ስሙር ከሰማውና በጥቂት ቀናት አቤልን በተረዳው መጠን ጨምሮ ስለርሱ ጠየቀው። አቤል ለጥያቄው መልስ ሲሰጥ እያወጋው እያወራው ሄዶ የደበቀውን ሁሉ አንድ በአንድ ይነግረው ጀመረ። ስራ መልቀቁን የሁል ጊዜ ናፍቆቱንና ከሚናፍቀው ለመድረስ በሚያደርገው ጉዞ ውስጥ ስንት ጊዜ መልካም አጋጣሚዎችን ባለማስተዋል እንዳመከነና ሌላውንም ሁሉ ለስሙር የሕይወት ገጽታውን አሳይቶት " በቃ እንዲህ ነው የኔ የማይረባ ከንቱ ሕይወት!" አለው ሳያውቅ እንባ ከዓይኑ እየወረደ። " ለዚህ ናፍቆት መነሻ ምክንያት የሆነህ ምንድነው?" ጠየቀው። አቤል ስለዚያች ምሥጢራዊ ስዕለ ማርያምና ከኋላዋ በቀይ ቀለም 💢 ህቡዕ ገጽ 💢 የሚል ጽሑፍና ሌላም ምሥጢር ስላለችባት ስዕል ነገረው። በዚያች ስዕል የሆነውን በማርታ ስለ ተፈጸመው ተአምር ሁሉ አንድ በአንድ በእንባ ነገረው። " እባክህ አታልቅስ አንተ የምታስደንቅ ሰው ነህ! ያውም ዲያቆን አገልጋይ! ካሰብክበት ትደርሳለህ።እና ወደዚህ የመጣኸው የምትናፍቀውን ፍለጋ ነው?" ጠየቀው። አቤል ይሰጠው ይመስል ጓጉቶ " አዎ ቢያድለኝ" አለው። ስሙር " ያ እባብስ ምን ፍለጋ ነው የመጣው?" አለው። " ስለርሱ አላውቅም ግራ ነው የሚገባኝ" አለው። ስሙርም አቤል ስለርሱ ለጠየቀው በተራው በነጮቹ ሀገር ያሳለፈውን ተረከለት። አሁን ግን ሁሉንም ትቶ ወደ እናት አባቱ ሀገር ወደ ምሥጢራዊቷ ኢትዮጵያ እንደመጣና ከእንግዲህ የዓለምን ጥበብና ፍልስፍና ሁሉ ትቶ በአባቱ መንገድ በመንፈሳዊ ሕይወት ቀሪ ዘመኑን ሊመራ እንዲወድና ከምሥጢራዊው መንደር ከሙሲቾ ተራራ ከሥውራኑ የምስጋና መቅደስ የውዳሴ እልፍኝ ከመንፈሳዊው ማዕድ መካፈል ህልም እንዳለውና ያ እስኪሆን በብርቱ እንዲደክም ነገረው። ስለሙሲቾና ምሥጢራዊው የጥበብ መንደር ብዙ ብዙ አወሩ። በሚያወሩት ውስጣቸው አንድ ሆነ። ተግባቡ ተስማሙ አንድ አሰቡ አንድ አለሙ። አብረው መንገዱን ሊጓዙ ልባቸው ሀሳባቸው አንድ ሆነ። " ያ ንፍታሌም ከምሥጢር ሊካፈል መቶ እንዳይሆን ብቻ! ኢሄ እባብ! እንኳን ሙሲቾን ሊያይ......" አለና ሊል ያሰበውን ሳይጨርስ መሪጌታ የሚያወሩትን ሁሉ ከኋላቸው ሆነው ሲሰሙ ቆይተው " ስሙር!" ሲሉት ደነገጠ። ሁለቱም ተነስተው ቆሙ። ሁለታችሁም ከቀናት በኋላ መንገድ እንሄዳለን መንፈሳዊ የሕይወት ጉዞ። አዎ ለዚያ ለመንገዳችሁ የነፍስ ስንቅ ያሻል ተዘጋጅታችሁ ከምሥጢር ሰንበተ ክርስቲያን ተካፈሉ" ብለዋቸው ወደ ቤት ተመለሱ። ስሙርና አቤል አንዳች ግራ መጋባት ውስጥ ገቡ። "የት ነው ምንሄደው? ምንድነው ምንዘጋጀው?" አለ ስሙር።አቤል " አንዳች ምሥጢራዊ ጉዞ ይሆናል። ንሰሐ ተቀበሉና ሥጋውና ደሙን ተቀበሉ ነው ያሉን። ማን ያውቃል ከምንናፍቀው የምንደርስበት ጉዞ ይሆናል" አለ። በዚያው ምሽት ሁለታቸውም ንሰሐ ሊቀበሉ ወሰኑ።
ንፍታሌም ወደ አዋሽ መቶ በነሰላም ቤት ሁለት ቀናትን አድሮ ማንም ሳያየው ቦርሳውን ይዞ ከወጣ ቀናት አልፈው ሶስተኛ ቀን ተቆጠረ። ንፍታሌምን ፍለጋ ሰላም የየዕለት ስራዋ እርሱን ፍለጋ መኳተን ሆኗል። ሰላም ስሙርና አቤል ንሰሐ ሲገቡ አጊኝተውት ይቅርታ እንዲጠይቁት ንሰሐ የተቀበሏቸው ካህን የገ/መንፈስ ቅዱስ አደልጋይ ቄስ ዲበኩሉ ስላዘዙ ከምሥጢር ሊካፈል የመጣው ንፍታሌም ከአካባቢው ርቆ እንደማይሄድ ስለተረዱ በተለይም መሪጌታን ስሙር አናግሯቸው ካገኘው ፍንጭ ስለተረዳ በፍለጋቸው የሰላም ስራዋም ያ ሆነ። አቤል በመጡ በስድስተኛው ቀን ከሰላም ጋር ወደ ደኑ አቅንተው ሲፈልጉት በተለያየ አቅጣጫ በቅርበት ላይ ሆነው የማያልቀውን ጫካ ሲያስሱ ሰላም በድንገት አባቷ በአንድ ወቅት ለአባ ትህትና ሲያወሩ የሰማችውን ያኔ ለማመን አዳጋች የሆነባትን ተአምራዊ ስውር ቦታ ላይ ደረሰች። ሰላም ፈዛ ቀረች። የምታየው እውነት አልመስላት አለ።ጥቅጥቅ ካለው ደን ወደ ውስጥ ርቀው አሁን ያለችበት በትልልቅ ቋጥኝ መሀል የምትገኝ ቲኒሽ ጉድጓድ ለደቂቃዎች በአንክሮ በፍርሀት ሆና ተመለከተች። ያኔ አባቷ ለአባ ትህትና ሲያወሩ የነበረው አሁን የምታየው መሆኑን ለማረጋገጥ እምብዛም አልቸገራትም ሲያወሩ የነበረውን በዚህ ስፍራ አየችና እፁብ አለች። ሰላም ንፍታሌምን ፍለጋ ላይ | 289 |
| 6 | 👤👤👤👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤👤👤👤
👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤
👤 ህቡዕ ገጽ 👤
💢💠🌿 ክፍል 179 🌿💠💢
ንፍታሌም በማያውቀው ሀገር ከነበረበት ወቶ ቦርሳውን እንደያዘ የሚላስ የሚቀመስ ወደ ሌለበት ዋሻ አቀና። መኝታ ከሌለበት ከቀዝቃዛው እልፍኝ ጨለማ ከዋጠው ዋሻ የሚሄድ አይመስልም። ፊቱ ላይ ገጽታው ወደ ደስታ ፍሰሀ የተጠራ እድምተኛ ነው የሚመስለው። ቦርሳውን እንዳነገተ ወደ ዝክረ ጻዲቅ የተፈጥሮ ችሮታ ወደ ሆነው ዋሻ ከወራጁ ወንዝ ሲደርስ ጫማውን አውልቆ እያንቦጫረቀ ተሻገረ። ከዋሻው በር ላይ ሲደርስ ንፍታሌም ባሪያውንና ጽናቱን ውሳኔውን በዓይነ ኅሊናው ተመልክቶ ፈገግ አለና ወደ ጨለማው ፍልፍል ዋሻ ገባ። ስልኩ ዘግቶ ስለነበረ። የጅ ባትሪውን አብርቶ ወደ ውስጥ ዘለቀ። ንፍታሌም ወደ ዋሻው ጥግ ላይ ያለ ስፍራ ደርሶ ቦርሳውን አስቀመጠ። ባሪያው ያለ መኖሩ እምብዛም አላስጨነቀውም። እዚያው ዋሻው ውስጥ ብቻውን መብራቱን አጥፍቶ ለረጅም ደቂቃዎች ተቀመጠና ድጋሚ መብራቱን አብርቶ ከቦርሳው ውስጥ የጸሎት መጽሐፍና ሌላ መጽሐፍ አወጣ። ከመጻሕፍቱ ውስጥ እያገላበጠ አንዳች ነገር ሲፈልግ ቆይቶ አነስ ያለች ብራና አገኘና አውጥቶ ከብራናዋ ላይ ዓይኑን ተከለ። ብራናውን እያየ ካለበት ዋሻ ወደ ሰከላ ግሽ አባይ የግዮን መነሻ ምሥጢራዊ ቦታ በሀሳብ ማዕበል ተሳፈረ። እዚያ ጥቅጥቅ ካለው ዋሻ ውስጥ ያሳለፋቸውን ቀናት በትዝታ የኋሊት ተመልሶ አስታወሰ። በተለይም በመጨረሻው እለት ከነቅዐ ጥበብ 63 ከነቃ ማይ በቶሎ ሊጎነጭ ነፍሱ በናፈቀች እለት በጨለማው ከደኑ ውስጥ ያገኛቸውን ወጣት መነኩሴ አስታወሰ። ያወሩት የነገሩት አንድ በአንድ በኅሊናው አቃጨለ። ኋላ ወደ ኋላው ዞሮ ወደርሳቸው ቢመለስ ከጸሎት መጽሐፉ ውስጥ ብራና አስቀምጠውለት የተሰወሩበት አስደናቂ አጋጣሚ ሁሉ አሁን እንደሆነ ያክል ሆኖ ታሰበው። ደግሞ ከመጽሐፉ ውስጥ ያገኘውን ብራና አውጥቶ ማየት ሲመኝ ግን ደግሞ ሲፈራ ከዚያው ካደረበት ቆሞ ጸሎት አድርሶ ሲጨርስ ከወጣቱመነኩሴጋ ሌሊት ቆሞ ሲያወራ መብራት እያበሩ በጫካው ውስጥ ያለፉት ሁለት ሰዎች አጠገቡ የደረሱበትን አጋጣሚ አስታወሰ።ንፍታሌም ዋሻው ውስጥ ተቀምጦ ያንን ዕለት በትዝታ ደገመው። ያ ቀን አዎ እንዲህ ነበር።ከፊት ቀድመው የሚሄዱት አባት እድሜያቸው ሲገመት ከ 110 የሚያንስ አይመስልም በጣም ደክመዋል። እርጅና ተጫጭኗቸዋል። ተክለ ሰውነታቸው ሲታይ መሄድ የሚችሉም አይመስሉም። ግና አሁንም መንገድ መሪ ናቸው። ከፊት ቀዳሚ ናቸው ከኋላ እንዲገባ የተከተላቸውን ደግሞ ከሚገባው የሚያደርሱ ብርቱ ናቸው። የዛሬው እንግዳቸው ከኋላ ተከታያቸው በእድሜው እጅግ ከርሳቸው ርቆ ያለ ከርሳቸው ተልዕኮ መንገድ ያደረሰው ያውም ምሥጢራዊ መንገድ ተከታይ አድርጎት በእርሳቸው እየተመራ ከናፍቆቱ ደርሶ የተመለሰ መሻቱ በርሳቸው መሪነት የተፈጸመለት ከ 10 ዓመት ያልበለጠ ሕፃን ነው። ንፍታሌም ዛፉን ተደግፎ እንደተቀመጠ ኮቴ ሲሰማ ዞረ። አስቀድሞ አረጋዊውን አባት አያቸው። ብቻቸውን ያሉ መስሎት ነበር። እርጅናቸውን አይቶ እንዴት ብቻቸውን ይሄዳሉ ብሎ አትኩሮ ሲመለከታቸው ከኋላቸው ጉንጩ ሞላ ያለ ሕፃን ልጅ አየ። እርሱ ባለበት አልፈው እንደሚሄዱ ወደርሱ በማቅናታቸው ገምቶ ፊቱን ከነርሱ መለሰ። አጠገቡ ደርሰው " እንዴት አለህ የኔ ልጅ ! ውድ ነገሮች ሁሉ በቀላል አይገኙም። ውድ መባላቸውም በሁሉ ቦታ በሁሉ ዘንድ በቀላል ስለማይገኙ ነው። የነዚህ ነገሮች ዋጋቸው ከፍ ይላል" አሉትና አለፍ እንዳሉት ዞረው " መንፈሳዊ ሰው ደግሞ ጽኑ ሊሆን ይገባዋል" ሲሉት ዘሎ ተነስቶ ቆመ። እርሳቸው ዞረው ይህን ሲሉት ሕፃኑ ግን ወደ ንፍታሌም አልዞረም። የሕፃኑን ማንነት ምንነት ለማየት ባይጓጓም ወደርሱ አንዴም ያለ መዞሩ ግን ጥያቄ ሆነበት ንፍታሌም። በአርምሞ ፈዞ እያያቸው። " ከሩቅ ሀገር ከዚህ ዓለም ርቃ ካለች ምሥጢራዊ ደጅ ደርሰን ልንመጣ ሌት ወጣን ጨለማውን ተጓዝን። አሁን በብርሃኑ እያበራን መጣን። በእርጅና ልጄን ወልጄው ተመለስኩ። እንዳልኩ የምነግርህ ሁሉ ግን በጣም ውድ ነው። ልጄም እያበሩ ከሚመለሱበት ለመድረስ ለመወለድ ጊዜ ፈጅቷል። ወጋ ተከፍሎበታል ደርሶ መመለሳችን። አንተም ሳይህ መንገደኛ ትመስላለህ። ከበረታህ ትደርሳለህ። አትቀመጥ። ተነስተህ ሂድ። ውጣ።" አሉት ከጎንብሰው ወደርሱ እንደዞሩ። ንፍታሌም ያኔ ነው ደንግጦ " ወዴት!" አለ። " ወደ ጀመርከው መንገድ ወደምትሻው። የሕይወት መንገድ ረጅም ነው ተጓዘው" ሲሉት የበለጠ ግራ ተጋባ። " መንገዴን እንዳልስት መሪ እየጠበኩ ልቆይ ብዬ ነው። ደካማ
ነኝ" ሲላቸው " እግዚአብሔር የዚህን ዓለም ኃያልነትነ ከንቱ ያደርግ ዘንዳ በደካማው ይሰራል። አትቁም ወደ ጠቢባኑ መንደር ተመለስ" አሉት። ንፍታሌም ተመለስ የሚለውን ሲሰማ ነቅዐ መይ የበለጠ ጠማው። ሕፃኑ ሁለቱ ሲነጋገሩ ባለበት ከንፍታሌም ዞሮ ጀርባ ሰጥቶት እንደቆመ ነው። ንፍታሌም ተመለስ ላሉት " ጥበብን እሻለው " የሚል ምላሽ ሲሰጣቸው " ከሀገርህ ታላቅ የጥበብ መንደር አለች። ያቺን መንደር ተሳለማት። ከጠቢባኑ ድረስ። እነርሱም ከምትሻት ጥበብ ከተጠማሀትም ትረካ ዘንድ ያደርሱሀል። የምትሻት የጥበብ ምንጭ ካለችበት እንዳለች የሚያስጎነጩህ መንገዷን የሚመሩህ ከርሷ የራቁ ሲመስሉ የቀረቧት ናቸውና ከርሷ ስትጎነጭ የምታገኘውን ሳትጎነጭ ከሩቅ ተሳለመው።፧ ለአዲሲቷ ኃያል ሀገር ግንባታ የመስቀሉ ትውልድን እንድትቀላቀል ወደ ሀገርህ ተመለስ የጥበብ መንደሮችንም አንኳኳ መርምራቸው አጥናቸው። አብዝተህ ናፍቃቸው አክብራቸው። ነገ ስታገኛቸው በሚገባ ጣዕማቸው ከምላስህ ፍቅራቸው ከልብህ አይለይም። መራራውን ያልቀመሰ ጣፋጩን ጣዕሙን አይረዳም። ጨለማን ያላየ ብርሃን ለርሱ ዋጋ ያጣል። ያላዘነ ደስታ ምንም ይሆንበታል። ያልደከመም እረፍቱ አያሳርፈውም። ነገን በጠቢባን መንደር ነፍስና ሥጋህ ሰላም እረፍት እንዲያገኙ ዛሬ የጣዕሙን መንገድ ተጓዝ" ንፍታሌም በዝምታ የሚሉትን ቃል በቃል ይሰማቸዋል። " ከዚያ ከአረጀው ምርኮኛ ባርነት ክብሩ ከሆነ ከፍታው የጠፋው ዝቅታው ክብር ከመሰለው ጨለማ ትውልድ ወጥተህ እንዲህ በጥበብ ከሚያበሩት ጋር ታበራለህ" ብለውት " የማነብርሃን" ሲሉት ሕፃኑ ዞረ። ያኔ ንፍታሌም ትዕይንቱን በአግርሞት እየተመለከተ ሕፃኑ ሲዞር ገጹ ላይ ያለውን ብርሃን ችሎ መመልከት አቃተውና አጎነበሰ። ሕፃኑ መልሶ ወደነበረበት ዞረ። ንፍታሌም ያየው የበለጠ በፍርሀት እንዲናጥ አደረገው። ቀድመው አረጋዊው ሲያወሩት ሲያዙት የነበረው ግልፅ ሳይሆንለት ቢቆይም። ሕፃኑን ጠርተው እንዲህ ነው የምታበራው ሲሉት ባየው ምስክር ተመለስ ሂድ የሚለውን ትዕዛዛቸውን ተረዳ ተቀበለ። " ከዚህ ምን ልጠብቅ ይገባኛል?" አለ ቃላቱን በጭንቀት አምጦ ወልዶ ድምጹ እየተቆራረጠ። " መንገድህ የቀና ይሁን። የላከህ ከዚህ መድረስህ ምልክት እንዲሆነው ከዚህ በፊት ከመጣህ ያገኘኸው ካለ እርሱን ለምልክት ስጠው። ከሌለም መንገድህን አሁን ጀምር በመንገድህ ምልክት ታገኛለህ" ሲሉት ወደ እርሳቸው ደርሶ ጉልበታቸውን ሊስም አስቦ የሕፃኑን የገጽ ብርሃን አስታውሶ መጠጋት ፈራና ባለበት ወድቆ ተንበርክኮ " የአባቶቼ ጸሎት የጸኑት እምነታቸው ትርዳኝ። ይባርኩኝ" አለ ከፊታቸው ከመሬት ላይ ተደፍቶ እንዳቀረቀረ። | 296 |
| 7 | بدون متن... | 515 |
| 8 | ገነትም ያሉት። ኅሊናችን መልካም ካላሰበ መልካም አናደርግም። ስለዚህ ሲዖል ውስጥ ነን። ነፍሳችሁን በክፉ አታስጨንቋት" አሉ። ባለቤታቸው ግን " ምን ይላሉ እኛ ተጨንቀን እርሶ ሆ! እኔ ደግሞ ደና ሰው መስሎኝ...አሁን ልጄን የት ይዟት ሄደ ይባላል?" አሉ። መሪጌታ " ከልጆቼ የምተማመንባት ባለ አእምሮ ሰላም ነች። አልጠብቃትም ሁሉን ታውቃለች" አሉ። ተፋጥነው ወደ ቤት አመሩ። ሰላም ስራ እየሰራራች ደረሱ መሪጌታ ግን ከዚያው ቆዩ። ባሪያውን አጊኝተውትም ብዙ አወሩት። እርሱም የሆነውን ሁሉ ሳይደብቅ ነገራቸው። ጨምሮም ስለ ንፍታሌም አስደናቂ ስብእና አወጋቸው። በመጨረሻም አንድ ነገር አሳሰቡት " በቅርቡ መንገድ እንሄዳለን! ስንቅህን አዘጋጅ ተዘጋጅም። እሁድ በሌሊት ወደ ቤተክርስቲያን ና ከነፍስ ማዕድም ተካፈል ቀጥለው ባሉ ቀናት ፈቃዱ ከሆነ...." ብለው ሳይጨርሱ ትተውት ሄዱ።
ስሙር አብዝቶ ሰላምን ተቆጣት እረሷም ቁጣውን በዝምታና ትዕግስት አቀዘቀዘችው። ስሙር ተናዶ ደጅ ወቶ ቁጭ እንዳለ ንፍታሌም መጣ። ገና ሲያየው ዘሎ ተነሳና " ምንድነው የምትፈልገው ከዚህ ቤተሰብ? ከእህቴ ትርቃለ አትርቅም?" አለው አንቆ ይዞት። ሰላም ከደጅ ሆና ያለውን ሰምታ የሆነውን አይታ ለእናቷ በፍጥነት ነግራ መጡ። " እንዳደርግልህ የምትፈልገው ምንድነው?" አለ ንፍታሌም። "ኧረ ባካችሁ ስሙር ምንድነው?" መሀል ገብተው አገላገሉ። " ከዚህ ቤት እንድትወጣ እረፍት እንድትሰጠን ፈልጋለው አልያ ግን....." ሲል ንፍታሌም ይቅርታ ጠይቆ ከቆይታ በኋላ ማንም ሳያየው ቦርሳውን ይዞ ከቤት ወጣ።
💠ይቀጥላል💠
💢💠 ታኅሳስ 26 2016 ዓ.ም ባሌ ሮቤ 💠💢 | 332 |
| 9 | የሚኖር አድርጎ ስሎት በሁኔታዎቹ ሁሉ ውስጥ ማስረጃ ልቡን ሊያሳምን ይፈልግበታል። ስሙር ግን ከሁሉ በተለየ ስለ እህቱ በማሰብ ደግሞም አባቱን መቅረቡ ስላሳሰበው በማስረጃ ከእህቱም ከአባቱም ከቤተሰቡም ሊያርቀው እግር በእግር ይከታተለዋል። መሪጌታና አረጋዊው እንግዳ አባት ደግሞ ስለትህትናው ስለፍቅሩ በመንፈሳዊ ዓይን ውስጡን መዝነውት እያዩት በስራው ሁሉ በልባቸው ይመርቁታል። በተለይም መሪጌታ ሌሊት ሲነሱ ተነስቶ ደኑ ድረስ ሸኝቷቸው መመለሱን ንግግሩንና መታዘዙን እያዩ ይደነቁበታል። ከአረጋዊው አባት ጋርም ብቻቸውን ሲሆኑ የአባ ኃይለ ጊዮርጊስ ደቀመዝሙር አይደል ምሥጢር ነው እንደርሳቸው" ይባባላሉ። ንፍታሌም ነጠላውን አጣጥፎ አስቀምጦ ብቻውን ወቶ ወደ ባሪያው መሄድ ፈለገና ከቤት ወጣ። ሰላም ደግሞ እናቷን ለማገዝ ስራ ጀመረች። ከቤት ወጣ እንዳለ የመሪጌታ ባለቤት ውኃ ሊቀዱ መቅጃ ቁንባዎች ይዘው ሲወጡ ተከተላቸው። አላዩትም ወደ ደኑ አቅጣጫ አመሩና ውኃ ከሚቀዳባት ምንጭ ደርሰው መቅዳት ሲጀምሩ ንፍታሌም " ውኃ ሁሌ ከዚህ ነው የምትቀዱት እናቴ?" አላቸው። ቀና ብለው አይተውት " አዎ ከዚህ ነው! ተከትለኸኝ መምጣትህን መች አየሁ!" አሉት። ዝቅ ብሎ መቅጃውን ተቀብሏቸው መቅዳት ሲጀምር ተደንቀውበት በውስጣቸው መረቁት። ተልዕኮ የተሰጠው ስሙር ደግሞ ንፍታሌምና ስራውን ተደብቆ ጥሻ ስር ተወሽቆ ይከታተለዋል። "እቺ ቲኒሽ ምንጭ እንዴት ለዚህ ሁሉ አካባቢ ሰው ትበቃለች?" አላቸው ንፍታሌም። አዋሽ የምሥጢር መንደር ነች ይበቃል የእግዜር ቸርነቱ በረከቱ ሁሉ በዚህ መንደር አለ" አሉት። " ቆይ ለምንድነው አዋሽ ቆላቲ የተባለው?" ጠየቀ። " ኤውልህ ከወዲያ ያለው ወራጅ ወንዝ አዋሽ ይባላል። በዚህ አካባቢ ደግሞ ቆላቲ የሚባል ዛፍ በብዛት ነበረ። ፍሬውን ልጆች እየለቀሙ ይበሉታል ጣፋጭ ነው። ኢኸው ይኼ ዛፍ! ብለው ምንጯጋ አጠገባቸው ያለውን ዛፍ አሳዩት። ንፍታሌም እየቀዳ የምንጩ ውኃ እጁ ላይ ጠብ ሲል ተደነቀ። ውኃው የሞቀ ነው። ለማረጋገጥ በመቅጃው ጨልፎ አጁ ላይ አፈሰሰ። " ምነው?" አሉት። " ውኃው ሙቅ ነው" አላቸው። " ይህቺ ምንጭ ብዙ አስደናቂ ነገሮች አሏት ልንገርህ ስማኝ" አሉት። ውኃ መቅዳቱን አቆመና ይሰማቸው ጀመረ። " እንዳልከው ነው ይች ምንጭ ውኃዋ ሌሊት ጠዋት በቅዝቃዜ ጊዜ ሙቅ ትሆናለች። ቀን በፀሐይ መተ ብትጎነጫት ደግሞ ሌላ ትሆናለች በጣም ነው የምትቀዘቅዘው። በጣም ብዙ ሰዎች ተከታትለው ቢቀዷት አታልቅም ለሁሉም ትለገሳለች። የሚያስደንቀው በበጋ ትልቁ አዋሽን ጨምሮ ሌሎችም የአካባቢያችን ወንዞች ጎድለው ሲታዩ ይቺ ምንጭ ትጨምራለች። ምንጯ በናፍቆት እንደ መድኃኒት በቲኒሹ የምትሆነው ክረምት ዝናብ ሲሆን ወንዞች ሲሞሉ እረሷ በተራዋ ትጎድላለች የምትጠፋም ነው የምትመስለው። በዓመት አንድ ጊዜ ጥምቀተ ባሕር አባቴ አቡዬ አዚህ ወተው ባርከውን ምንጯንም ባርከውልን ይመለሳሉ። ከዓመት ዓመት ከርሷ እንጠጣለን" አሉት ንፍታሌም በጣም ገረመው። እንደ ሁል ጊዜው በተደሞ " አይ ኢትዮጵያ አይ አንቺ ምሥጢር ሀገር!" አለና ወደ መቅዳቱ ተመለሰና በሁለት ቁነባዎች ሞልቶ ከድኖ ሁለቱንም ካልተሸከምኩ ቢላቸው የግድ ብለውት አንዱን አሸከማቸውና አንዱን ይዞ ወደ ቤት አቀኑ። የሰላም እናት ንፍታሌም ከአእምሮ በላይ ሆኖባቸዋል። ወዲያው ገብቶ ወዳቀደው ሲወጣ ሰላም ሰረቅ አድርጋ ወዴት እንደሚሄድ አየችው። ስሙርም ከርቀት በዓይነ ቁራኛ እየተከታተለው ሰላም እግሩን ተከትላ ለማንም ምንም ሳትል በቅርብ ርቀት ከኋላው ተከተለችው። ንፍታሌም ወዲያ ወዲህ ሳይል በአንድ ቀን መተዋወቅ ወዳጅ ወደሆነው ሰው መገኛ ሄደ። ስሙር ንፍታሌምን በቅርበት መከተል አልቻለም። ምክንያቱም ሰላምም በቅርበት ንፍታሌምን ትከተለው ስለነበር እርሷ እንዳታየው ከኋላዋ መሆን ስለነበረበት ከንፍታሌም ራቀና እህቱን ይከታተላት ጀመረ። ንፍታሌም ወደ ደኑ ከገባ በኋላ ሰላም እንጂ ስሙር ሊያየው አልቻለም። ወንዙ ጋር ሲደርስ ጫማውን አውልቆ በጁ ይዞ ሱሪውን ሰብስቦ ተሻገረ። ወደ ዋሻው ሲገባ ሰላም ደነገጠች። ንፍታሌም ወደ ውስጥ ዘልቆ ገባ። ከደቂቃዎች በኋላ ሰላምም ተሻግራ ወደ ዋሻው ተከትላው ገባች። ስሙር በንዴት ጦፈ። እዚያው መቆየታቸውን አረጋግጦ ወደ አባቱ ተመልሶ እቤት ያሉትን ሁሉ ይዞ መቶ ሊያጋልጠውም ፈልጎ እህቱን አንድ ነገር የሚያደርጋት ደግሞ መሰለውና ፈራ። ሲያመነታ ቆይቶ ወደ ቤት በሩጫ ወደ እናት አባቱ ተፋጠነ። በቃ ኢሄን መረጃ ካቀረበ በኋላ ዛሬ ነገ ሳይባል ንፍታሌም ወደ መጣበት እንደሚመለስ በልቡ ወስኗል። ዋሻው የሚያስፈራ ጨለማ በቅዝቃዜ የተሞላ ነው። ንፍታሌም ወደ ውስጥ ገብቶ አብርቶ ተመልክቶ ባሪያውን ሲያጣው ባለበት መብራቱን አጥፍቶ ቁጭ ብሎ ይጠብቀው ጀመር። ከደቂቃዎች ኋላ የሰው ኮቴ ሲሰማ መምጣቱን እንግጠኛ ሆኖ " ላብራሎት ሳጣዎትኮ እዚሁ ልጠብቆት ብዬ ቁጭ አልኩ" አለ። ሰላም ቀበል አድርጋ " ምን ጥያቄ አለው አብራልኝ እንጂ! ስንት ዘመን እዚ ስኖር ከማላውቀው ቦታ አነት እንዴት መጣህ ግን?" ስትለው ደንግጦ አበራና ተቆጥቶ " ምን ፍለጋ መጣሽ? ለምንድነው የምትከተይኝ?" አለ በቁጣ ሰላምን ሲያያት ባሪያው ቅር እንደሚለው በማሰብ። ስሙር ወዲያው አቤልን እናቱን መሪጌታን እያጣደፈ ይዟቸው መጣ። ተከታትለው ወደ ዋሻው ሲገቡ መሪጌታ ወንዙን ሳይሻገሩ ቆሙ።
" ቆይ ለምንድነው አቻኩላችሁ ወዲህ ያመጣችሁን?" አለች ሰላም አንድ አነስ ያለች ሜዳ ላይ ከጫካው መካከል ሲደርሱ። ንፍታሌም ቀበል አድርጎ " ሰላም ኤውልሽ መጀመሪያውኑ መምጣት አልነበረብሽም። አሁን በፍጥነት ወደ ቤት መመለስ አለብሽ!" አላት። ሰላም በጣም ከፋት። " ምን መሰላችሁ!" አለ ሰላም የማታውቀው ፊቱ የገረጣ ጎስቆል ያለ ወጣት። " አንቺ ተከትለሽው ወደዚያ ዋሻ ስትገቢ ወንድምሽ እየተከታተለሽ ነበረ። ንፍታሌም ቀድሞሽ ሲገባ ደግሞ አይቷል ወዲያው አንቺ መግባትሽን ሲያይ ነው ወደ ቤት እየሮጠ የተመለሰው። ምናልባትም ለንፍታሌም እንቅፋት እንዳይሆን ወደ ቤት መመለስሽ መልካም ነው" አላት። ምክንያቱ አሳምኗት ተስማማች። " እግዚአብሔር ከፈቀደ በሌላ ጊዜ እንገናኝ ይሆናል! ለሁሉም እኔ ዝክረ ጻድቅ እባላለው!" አላት ባሪያው ሰምታው ወደ ቤቷ ተመለሰች። እቤት ስትደርስ ከእንግዳው አባት በቀር ማንም የለም። ንፍታሌምና ባሪያው ስለ አዋሽ ብሎም ስለሙሲቾ ብዙ ተጨዋወቱ። ከሁሉ ይልቅ ንፍታሌምን ያስደነቀው " አንዳንድ ጊዜ ከሌሊቱ ግርማ ከጨለማው ፍርሀት የሚያወጣ አቅጣጫው የማይታወቅ የከበሮ የጽናጽል ድምጽ ይሰማል" ባሪያው ያለው ነበረ። ንፍታሌም " ግን አንተ ወደ ምሥጢራዊው ተራራ መቼ የምትሄድ ይመስልሀል?" ጠየቀው። ባሪያው " አሁንም ቢሆን እመኛለው! ግን አይቻለኝም እኔ ሌባ ነኝ። የሰው ነፍስ እጄ ላይ የጠፋ ኃጢአተኛ ከዚያ ቅዱስ ስፍራ መድረስ አይቻለኝም!" ብሎ አለቀሰ። ግን አንዳንዴ ከመናፈቅ ብዛት መሄድ እመኛለው። መሪጌታ በሌሊት ወደዚያ እንደሚሄዱ ስለማውቅ ከወሰንኩት አንዱ ሌሊት አንተ ተከትለሀቸው የወጣህበት ሌሊት አንዱ ነበረ። ስትማጸናቸው ሰማው። ምላሻቸውን አደመጥኩ። ያንተ አሜን ብሎ መልሳቸውን መቀበልና የእሺታ ቃል ግን እንዳልከተላቸው ውስጤን ከለከለው" አለ ባሪያው። እንዲህ እንዲህ እያሉ ብዙ ሲጨዋወቱ ቆይተው ተለያዩ። የመሪጌታ ቤተሰብም ዋሻውን ሲበረብር ቆይቶ ሰላምን አተው ወጡ። ሌሎቹ ሲቆጡ መሪጌታ "ሁሉ ነገር ከአእምሮ ይመነጫል። በጎም ክፉ ሀሳብም። ለዚህ ነው ሁሌ ከእጃችን ላይ ሲዖልም | 275 |
| 10 | 👤👤👤👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤👤👤👤
👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤
👤 ህቡዕ ገጽ 👤
💢💠 ከክፍል 176 የቀጠለ 💠💢
ስሙር ከብርድልብሱ ስር ገብቶ ሲያስብ ቆይቶ ትዝ ሲለው ዘሎ ድጋሚ ተነስቶ ወደ አባቱ መኝታ ሄደ። ግን ከመኝታቸው አላገኛቸውም። ሲመለስ እናቱ ተነስተው መተኛቱን አረጋግጠው ተመልሰው ተኙ። ዘጠኝ ሰዓት ሲሆን ከአንዱ ክፍል ከሶስቱ አንዱ ለጸሎት ሲነሳ ከሌላኛውም ክፍል ከሁለቱ አንድ ሰው እንዲሁ ለጸሎት ቆመ። ሰላምና ንፍታሌም። ሁለቱም የዘወትር ልማዳቸው ነው። ሰላም ቀድማ ጨርሳ ከወዲያኛው ክፍል ብርሃን ስታይ ወደ ክፍሉ መግቢያ በር ደርሳ ተደብቃ ስታይ ንፍታሌም እየሰገደ ነው። ቶሎ ቶሎ ይሰግዳል ጉልበቱ ግን መሬት የማይነካ ይመስል ድምጽ የለም። አጮልቃ በጨለማው ውስጥ እያየች እናቷ አጠገቧ ደርሰው " ሰላሜ!" አሏት።
💢💠🌿 ክፍል 178 🌿💠💢
ሰላም ድንግጥ ብላ ዘወር ስትል እናቷ ናቸው። " እማዬ!" አለች ድምጿን ዝቅ አድርጋ። " ምንድነው አጮልቀሽ የምታይው?" ጠየቋት የምታየውን ለማረጋገጥ ንፍታሌም ካለበት ክፍል እርሳቸውም አጮልቀው እያዩ። ንፍታሌም ባለበት ክፍል ውስጥ እየሆነ ያለውን ክንውን ካዩ በኋላ በእናትና ልጅ መካከል ቃለ ምልልሱ ቆመ። በዝምታ ሆነው መመልከት ብቻ ሆነ። የሰላም እናት ከቆይታ ብዛት ሰልችተው " አይደክመውም እንዴ? እኔንኳን ቆሜ ማየቱ ሰለቸኝ። የኔ ውሻ ገና በዚህ ልጅነቱ እንደው ምን ቢያመለክተው ነው?" አሉ ወደ ልጃቸው ጠጋ ብለው በጆሮዋ በለሆሳስ። ሰላም መልስ ሳትሰጥ በአግርሞት ታየዋለች። በንፍታሌም ላይ አዲስ ነገር ባየች ቁጥር ፍቅሯ መውደዷ ከእለት እለት እየጨመረ እያደገ ይመጣል። ዛሬም የበለጠ ወደደችው የበለጠ አክብሮቷ ጨመረ። ንፍታሌም ጨርሶ ወደ መኝታው ሲመለስ እናትና ልጅ ተያይዘው ተመልሰው ተኙ። እንደ ወትሮው ሁሉ ንፍታሌም ጎኅ ሳይቀድ ሳይነጋበት ተነስቶ 10:30 ሲሆን ወደ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን አቀና። ሲደርስ ኪዳን የሚያደርሱት ካህንና ዲያቆኑን ቀድሟቸዋል። ተሳልሞ ጥቂት ቆይተው ሰሞነኞች አገልጋዮች ቤተክርስቲያኑን ሲከፍቱ እርሱም ወደ ውስጥ ገብቶ ፈንጠር ብሎ ከቅኔ ማህሌቱ ትይዩ ለካህናት መግቢያ ቅርብ ሆኖ ቆመ። ጸሎተ ኪዳን ተጀመረ። አቤልና ስሙርም ወዲያው ከመኝታቸው ከእንቅልፋቸው ነቅተው ወደ ቤተክርስቲያን ሊሄዱ ተነጋግረው ተነሱ። እቤት ውስጥ ከስሙር እናት በቀር ማንንም አላገኙም። ይህ መሆኑ ስሙርን አበሳጨው። ሰላምና ንፍታሌም ተያይዘው የወጡ መስሎት ወደ እናቱ ቀርቦ " እማዬ ደናደርሽ! ሰላም ከእንግዳው ጋር ወታ ነው?" አያይዞ ጠየቃቸው። " አይ ስሙር እርሱ መች ይተኛና ሰላም ስትነሳ እርሱ የለምኮ። ኋላ ነው እርሷ አሁን ቅርብ የወጣችው" ሲሉት ትቷቸው ወጣ። አቤልና ስሙር አንድ ላይ ወደ ቤተክርስቲያን አቀኑ። " እኔ የምልህ ወንድሜ! ማን ነበረ ስምህ? አብርሃም!" አለ ስሙር። " አቤል!" አለ አቤል። " አዎ አቤል ኢሄ አብሯችሁ የመጣው ንፍታሌም ምንህ ነው? የልብህ ወዳጅህ ነው? ከሆነ አንዳንድ ነገር ብትመክረው ብዬ አሰብኩ" ሲለው አቤል ራሱን ነጻ ሊያወጣ " አጋጣሚ አብረን መጥተን እንጂ ያን ያክል ወዳጆች አይደለንም። የሚገርምህ እኔም እንዳንተ በአንዳንድ ጉዳይ ላይ ሀሳብ ነበረኝ። ግን እንደምታውቀው ነው በዚህ ዘመን ሰው ለርሱ ብለህ ስትነግረው ይቀየምሀል!" አለው። " ነፍሴ ምንም አልወደደችውም ያውም በእህቴ ድርድር አላውቅም እኔ! ደግሞ እንደ መልካም ሰው ቤተክርስቲያን ይሄዳል። እየታዘብኩ ነበረ አሁን ማታ ማታ አንተ ጸሎት አድርሰህ ከተኛህ በኋላ ነው ጸሎት አድርሼ የምተኛው እርሱ ግን በላ ተኛ በቃ" አለና ጨምሮ " የት ነው ግን የምታውቀው?" ጠየቀው። አቤል " እኔ ለመጀመሪያ ጊዜ ያገኘሁት ጎበ ተክለሃይማኖት ገዳም ነው። መቼም ሰው ደካማ ነው ገና ያየሁት እለት ነው ልቤ የታዘበው። ደግሞ አባቶች ለርሱ ያላቸውን ሳይ አታላይነቱ ያበሳጨኛል። የሚገርምህ ከቆይታ በኋላ በአጋጣሚ አዲስ አበባ ከአንዷ ኮረዳ ጋር ባልጠበኩት ሁኔታ ሳገኘው የበለጠ ነደድኩ። አበቶችንም አታሏቸዋል። አንተ እንዳልከውም ከእህትህ ሰላም ጋር ያለውንም ግንኙነት ሳስብ አታሏት ይመስለኛል። ልጁ በጣም አፈ ቂቤ ነው። ብዙ ሰዎች ስለርሱ የሚያወሩትና ሕይወቱ ፍጹም የሚገናኝ አይመስለኝም" አለ የስሙርን ሀሳብ ደግፎ። እያወሩ ከቤተክርስቲያኑ መግቢያ ደረሱና ተሳልመው ወደ ውስጥ ገቡ። ስሙር በወንዶች መሳለሚያ ሲሳለም አቤል አለፍ ብሎ በካህናት መሳለሚያ ተሳልሞ ወደ ውስጥ ገባ። እንደገባ ንፍታሌምን ብቻውን ጥግ ይዞ ቆሞ አለፈውና ከቅኔ ማኅሌቱ ከዲያቆናት መቆሚያ አንቀጽ ቆመ። አቤል በአገልግሎቱ ላይ ተሰጥኦ በመመለስ ከአገልግሎቱ በመካፈል አገልጋይ ዲያቆን መሆኑ ወዲያው ታወቀ። ጸሎተ ኪዳን አልቆ ካህኑ መስቀል አሳልመው በቁጥር በጣም ጥቂት በጣት የሚቆጠሩት ሰዎች ከውስጥ ሲወጡ አቤልም በምስራቅ በካህናት መውጫ ወቶ ከስሙር ጋር ከአንድ ጥግ ላይ ቆመው የሚነበበውን የእለቱን የቅዱሳን መታሰቢያ ስንክሳር ትተው የራሳቸውን ወሬ እያወሩ ቆዩ። ሰላም ግን ከሁሉ ቀድማ ወታ ከአንዱ ዛፍ ስር ቆማ ያን እንዲህ ነው ለማለት የሚከብደውን እንቆቅልሽ ሰው ትጠብቀው ጀመረ። ብትጠብቀው የሚወጣ የለም። ቀድሟት የወጣ መስሏት ወደ ቤት ተፋጠነች። የሚነበበው ስንክሳር ሲፈጸም አቤልና ስሙር እያወሩ ወተው ወደ ቤት አቀኑ። ካህኑ ወተው ሰሞነኛው ዲያቆን ብቻ እስኪቀር ንፍታሌም ብቻውን የቤተክርስቲያኑን ሁለንተና እየቃኘ " የቤትህ ቅናት በላችኝ!" የሚለውን ደጋግሞ በልቡ ይመላልሰዋል። አዎ መቅደሱ መጋረጃ የሚያጥረው ምንጣፍ የሌለው የካህናት መቀመጫ የሚጎድለው ሌላም ሌላም እያየ ከመቅደሱ ሰሞነኛው ዲያቆን ሲወጣ ከተቀመጠበት ሊወጣ ተነሳ። ዲያቆኑን ተከትለው አብሯቸው የመጣው አረጋዊ አባትና መሪጌታ ተከታትለው ወጡና ዘንበል ብለው ሰላምታ ሰተውት በምስራቅ ሲወጡ ንፍታሌም በወንዶች መሳለሚያ ወቶ አብረው ወደ ቤት አቀኑ። አብረው እየሄዱ መሪጌታ " አገልጋይ ነህ አይደል?" አሉት እርሱ ግን ዝም አለ። ሶስቱ በአንድነት እየመጡ ከርቀት ገና ሲያያቸው ስሙር " ኢሄ አታላይ የሆነ ሸፍጥማ እየሰራ ነው!" አለው አቤልን። ስሙር ሲደርሱ አባቱን ለብቻ ጠርቶ " አባዬ ኢሄ ልጅ ብዙም ባትቀርበው ውስጡ የተደበቀ ተንኮል አለ። አስመሳይ ነው" አላቸው። " ውስጡን እንዴት አወክ? ስሙር ሀሳብህን ተቀብያለው። አንተ ደግሞ አንድ ነገር አድርግልኝ። ያለከውን በቀላሉ እንድንደርስበት በደንብ ቅረበውና ወዳጁ ሆነህ አጥናው እርግጠኛ ስንሆን የምናደርገውን እናደርጋለን። ጥላቻህን አይወቅ በደንብ ቅረበው" አሉት መሪጌታ። እርሱም ደስ እያለው ተስማማ።
የስሙር እያንዳንዱ እንቅስቃሴ በቤተሰቡ ትኩረት ውስጥ ወደቀ። የሰላም እናት ከመሪጌታ ሕይወት ብዙ ስለተማሩ ንፍታሌም ምሥጢር የሆነ ሰው መሆኑን ለማወቅ ፍንጭ አጊኝተዋል እርግጠኛ ለመሆን በሁሉ ያጤኑታል። ሰላም ደግሞ ልቧ በፍቅር የወደቀለት ንጉሷ ስለሆነ በየደቂቃው ስለምትናፍቀው የበለጠ አውቃው የበለጠ ልትወደው የበለጠ ወዳው የበለጠ ልትቀርበው የበለጠ ቀርባው እርሷ የርሱ እርሱም የርሷ እንዲሆን እንደወደደችው በርሱ ለመወደድ ትኩረቷ ሁሉ በርሱ ላይ ሆነ። አቤል ግን የሚወዳትን ሰላምን ከጁ ነጥቆ የወሰደበት ያክል ራሱን ወዳጅ ሥነ ምግባር የጎደለው አስመስሎ | 279 |
| 11 | ቀዝቃዛ ውኃ ሲያፈሱበት ልብሱ ይጨሳል። ሁላቸውም ፈርተው እንዳሉ ነገሩት። ውኃ ከተጨመረበት በኋላም ልብሱን መንካት ፍጹም አልተቻለም። ሀኪሞቹ በዚያ ቅጽበት ከውጪ ያለውን ጫጫታ ጩኸት ለማስቆም ወደ ውጭ ከተሰበሰቡት ሰዎች ደርሰው የምትጮኸዋን ሰው ወስደው እንዲያርቁ አዘዙ። በገጠማቸው ልዩ ክስተትም ተደነጋግጠው እንዳሉ ወደ ታካሚው ክፍል ሲመለሱ ሌላ ያልጠበቁት ለማመን የሚከብዳቸው ነገር ሆነ።
ሀኪሞቹ ተፋጠው ቀሩ። ተፋጥነው ወደ ውስጠኛው ክፍል ተከታትለው ገቡ። እንዳሰቡት አይደለም። ያሰቡት አልሆነም። ወደ ሌላኛው ክፍል ማለፊያው በር ባሉበት በኩል ዝግ ነው። " በዚህ አይሆንም!" ብሎ ወደ ነበረበት ክፍል ተመለሰ። ሌሎችም ተከተሉት። ታካሚው ተኝቶበት ከነበረው አልጋ ግርጌ ላይ ያለው መስኮት ክፍት ነው። " በዚህ ነው ሁሉም ነገር የሆነው። ታካሚው ትልቅ መረጃ እጃቸው ሳይኖር አይቀርም። የግድያ ሙከራ ያደረሱባቸው ናቸው በዚህ ያሸሿቸው እንጂ ታማሚው በዚያ ሁኔታ የሚያመልጡበት ምክንያትና የማምለጥ አቅምም አይኖራቸውም። የወሰዱትም ገድለው ከዚሁ ጊቢ ሊጥሏቸው ካልሆነ በዚህ ሰዓት ውስጥ ተሸክመዋቸው የትም ሊወስዷቸው ድፍረት አይኖራቸውም" አለ አንዱ ወፈር ያለ ሀኪም። ወዲያው ለየቅል ወደ ተለያየ አቅጣጫ ተሯሯጡ። ጉዳዩ ከጥበቃዎች ደርሶ መሳሪያ እንደያዙ ጥበቃዎች በየአቅጣጫው ዘመቱ። የነበረው ህዝብ ሁሉ ሲሰማ ተረት እንጂ እውነት አልመስልህ እያለው የተወሰኑ ሰዎች ከታካሚው ክፍል ገብተው አረጋግጠው አምነው ጊቢው ውስጥ የነበረው ሰው ሁሉ አንድ በአንድ ጊቢው ውስጥ ተሰራጨ። ሁሉም መብራቱን አብርቶ ጊቢው በጨረቃ የተዋበ ሰማይ መሰለ። መርፌ እንጂ ሰው የሚፈልጉ አይመስሉም። አንድም ስፍራ ሳትቀር ጊቢዋን አካለሏት። የጠፋውን ሰው የበላው ጅብ ግን አልጮህ አለ። ከህዝብ አንዳንዶች ማጉረምረም ጀመሩ። "ደብቀውት ነው የሚያታልሉን! ኩላሊቱን አውጥተው ሊሸጡት ነው" የሚሉ ነበሩ። ደግሞ " ያን ያደረሱበት ሰዎች ናቸው ሀኪሞቹን አፍዘው የወሰዱት" የሚሉም ነበሩ። " ሰውዬው የሆነ ኃይል አለው። አላያቹም አዳሜ እርሱ ታሞ ተኝቶ ጤነኞቹ ሲንጫጩ። ድኖ አምልጦ እንዳይሆን" የሚልም አልጠፋም። ቢዚህ ሀሳብ ግን ሀሳቡን ካመጣው ሰው በቀር ማንም አልተስማማም። " እብድ ነው ምኑን ይህን ያልከውን ከርሱ እንጠብቃለን? ደግሞ ለምን ያመልጣል?" ሌላ ጥያቄ መጣ። " እብድ መሆኑ ታዲያ መኑ ላይ ነው" መላ ምቶች በዙ። ወዲያው ከሆስፒታሉ ለፖሊስ ተደወለ። ወዲያ ከተማዋ ትታሰስ ጀመር።በዚያ ሌሊት ነገሩን የሰማ ሁሉ ፍቺ የሌለው እንቆቅልሽ ሆነበት። ብዙው ሰው በነገር በነገር ሀኪሞቹ ልብሱን መንካት እንዳቃታቸውና የጮሁ ሰዎች ነገር መነጋገሪያ ሆኖባቸው መልሱን ሳያገኙ ወደየ በአታቸው አቀኑ። የኤርምያስ እናትም በሰሙት ነገር ከድንጋጤው ጋር ተጨምሮ ሰመመን ውስጥ ያሉ እየመሰላቸው እነራሄል ክብሮም ሌሎቹም ወደ ቤታቸው እያዘኑ እየተደነቁ ግራ እየተጋቡ ተመለሱ። የኤርምያስ እናት ከልጀቸው ቤት ሊያድሩ ግድ ብለዋቸው በአንድነት ከነራሄል ጋር ወደ ቤት አቀኑ። እቤት ሲደርሱ የውጭውን በር ክብሮም ከፍቶ ተከታትለው ገቡ። የነራሄልን ቤት በር ኤርምያስ ከፍቶ ገባ። ራሄል ተከተለች የኤርምያስ እናት ኋላ ገብተው ተቀመጡ። ሌላውም ሁሉ ወደየቤቱ ገባ። ራሄል ወደ መኝታ ክፍል ገብታ ደርቃ ቀረች። አንደበቷ ድዳ ሆነ። ልጇ ንፍታሌም ካስተኛችው ስፍራ የለም። ጊቢ ውስጥ የነበሩ ተከራዮች እርሷ ስትሄድ የቀሩት በሩ መለስ ብቻ ተደርጎ ስለነበር ወስደውት ከሆነ ተጠየቁ። የራሄል ልጅ የኤርምያስ ልጅ ንፍታሌም የለም። ዳግም ሌላ ጩኸት ሌላ ዋይታ ሆነ።
💠 ይቀጥላል 💠
💢💠ታኅሳስ 25 2016 ዓ.ም ባሌ ሮቤ 💠💢 | 372 |
| 12 | 👤👤👤👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤👤👤👤
👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤
👤 ህቡዕ ገጽ 👤
💢💠 ከክፍል 175 የቀጠለ 💠💢
አሁን ከደቂቃዎች በፊት አንድ ሰው መንገድ ላይ ደም ፈሶት ሰዎች ተሰባስበው በነፍሱ ለመድረስ ወደ ሆስፒታል ወስደውታል" ሲለው ሰሚው መልሶ ለእርምያስ ቤተሰብ ለመንገር የሰሚ ሰሚ መልሶ የሰማውን እንዳየ ሆኖ ለክብሮም እንዲህ አለው። " አይዟችሁ ተረጋጉ። በተለይ አንተ ትልቅ ሐላፊነት ነው ያለብህ። ቤተሰቡን አረጋጋና በፍጥነት በነፍስ ድረሱለት ጠፋ የምትሉት ሰው ከደቂቃዎች በፊት በመሳሪያ ይውጉት በጥይት ይምቱት ከመንገድ ወድቆ ደም ሲፈሰው ሰዎች ወስደው ወደ ሆስፒታል ወስደውታል። እባክህን በተለይም እናቱን አረጓጓቸው" ብሎ ኤርምያስን ተወግቶ እንዳየው ሰው እርግጠኛ ሆኖ ሲነግረው ክብሮም ለራሄል ነግሯት ወደ ሆስፒታል ከነፈ። እርሷም የሰማችውን ማመን አቅቷት እየጮኸች ተከተለችው። የኤርምያስ እናት ሲሰሙ እንኳ ሮጠው ሊከተሏቸው ራሳቸውን ችለው መራመድ አቅቷቸው በሰው ድጋፍ ወደ ሆስፒታል ተወሰዱ። ሆስፒታል ጊቢ ሲደርሱ እንደተባለውም ሰው ተሰባስቦ ሲያዩ ሁሉም ተደናገጡ። ራሄል ጩኸቷን አቀለጠችው።
💢💠🌿 ክፍል 177 🌿💠💢
የድንገተኛ ክፍል ያለበት አካባቢ በሰው የተጥለቀለቀ ነበረ። በዚያ ላይ ነው ራሄል ገና ከርቀት የሆስፒታሉ ግቢ ከመግባቷ ቀድመው እንደተባለው በሞት አፋፍ ላይ ወድቆ ከመንገድ አፋፍሰው ያመጡትን ሰው አጅበው የመጡ ሰዎችን ድንገተኛ ክፍል ጋር ስታይ ጩኸቷን የለቀቀችው። ጩኸቷ እንደተሰማ ወዲያው እርሷንም አብረዋት ያሉትንም ጠባቂዎች ወደ ድንገተኛ ክፍል ወደ ሚወስደው ብሎክ እንዳያልፉ አገዷቸው። የበለጠ ስጋት የበለጠ ፍርሀት ሆነ። ከወዲህ ያሉት ብዙዎቹ ራሄልንና የኤርምያስን እናት በማረጋጋት ተጠመዱ። ከወዲያ ከድንገተኛ ክፍል ደጃፍ ላይ ያሉት በርካታ ሰዎች ደግሞ የሚመጣውን የሀኪሞች ዜና በመጠባበቅ ውስጡ ይናጣል። አንዳንዱ ወዲያ ወዲህ ይራመዳል። ከነራሄል ጎራ ካሉት አንዱ ከወዲያ ካሉት አንድ የሚያውቀውን ሰው ጠርቶት አጠገቡ ሲደርስ ሰላም እንኳን ሳይለው " ቆይ ለመሆኑ እንዴት ነው የሚተርፍ ይመስላል?" ጠየቀው። ተጠያቂውም " መቼም ሰውና ውሻ እንደቀልድ አይሞትም እንጂ የሚተርፍ አይደለም። ውስጡኮ ምንም ደም የቀረ አይመስልም" አለው። እያወሩ ከድንገተኛ ክፍል የተወሰኑ ሀኪሞች ሲወጡ መጠነኛ ጫጫታ ሆነ። የሚያወራውን አቋርጦ ወደ ድንገተኛ ክፍሉ አመራ። የሚንጫጫው ሰው ተመሳሳይ ጥያቄ ከውስጥ ለወጡት ሀኪሞች ሲያቀርብ " የደረሰበት ጉዳት ከፍተኛ ነው። የምንችለውን ሁሉ እናደርጋለን። እባካችሁ እዚህ አካባቢ አትንጫጩ ለታካሚዎች ደህንነትም ጎጂ ነው" ብለው ጥለዋቸው ሄዱ። አንዱ ሀኪም ወዲያው አንዳንድ ለቀዶ ጥገና የሚያስፈልጉ መሳሪያዎችን ይዞ ወደ ክፍሉ ገባና አስቀምጦ መልሶ ወጣ። ሀኪሞቹ ሲወጡና ሲገቡ በሩን የምትዘጋ የምትከፍት አንዲት ረዳት ሀኪም ከውስጥ አለች። የኤርምያስ እናት ቁጭ ባለችበት ብዙዎች ከበው ያጽናኗታል። በተለይ አንድ የጎረቤታቸው በእድሜ ገፋ ያሉ እናት " አይዞሽ ጸልይ ምንም አይሆንም። እኔም ለእመቤቴ ተስያለው አታሳፍረንም" አሏቸው። የኤርምያስም እናት " ከዚህ ጉድ ከወጣው የርሱ አምላክ እውነትም ታላቅ ነው። እኔም ላምንበት ልጄን ልከተለው እወስናለው" አሉ። ሀኪሙ እቃውን አስቀምጦ እንደወጣ የመጀመሪያ ደረጃ እርዳታ የተደረገለት ራሱን ስቶ ያለውን ታካሚ ለቀዶ ጥገና የበኩሏን ስራ ለመወጣት ገና የታካሚውን የቆሸሸ የተበጫጨቀ ልብስ በመቀስ ልትቀድ በጇ ያረጀ አሮጌ ልብሱን ስትነካ " ዋይ ዋይ ኡ ዋይ ዉዉዉ ተቃጠልኩ ዋይ ዉ" ጩኸቷን ለቀቀችው። ወዲያው ሌሎች ሀኪሞች እየሮጡ ደረሱ። ረዳት ሀኪሟ ግን ጩኸቷን አላቆመችም። ደነገጡ ግራ ገባቸው። " ኢሄን ክፉ ኢሄን ሰው አውጡልኝ ከዚህ አውጡት" እያለች ስትጮህ ችግሯን ወዲያው ተረዷት። ግና ማንም ከመካከላቸው በምንና እንዴት እንደተነሳባት የተረዳ አልነበረም። እርሷን ይዘዋት በውስጠኛው ክፍል ወደ ሌላ ክፍል ወሰዷት። በርሷ የተተካው ወጣት ያቋረጠችውን ሊቀጥል ጀመረ። የታካሚውን የቆሸሸ ልብስ ግን ይዞ በመቀስ መቅደድና ለህክምና ማዘጋጀት ፍጹም አቃተው። የታካሚውን ልብስ ቲኒሽ ሲነካ ተቃጠለ። ሌላ ተጨማሪ ሰው አረጋገጠ ለማንም አልተቻለም። አቅቷቸው ግራ ተጋብተው ተፋጠው ከውስጥ ቆሙ።
ወደ ሆስፒታሉ የሚገባ የሚወጣ ቁጥሩ በርክቷል። የመጣው እቤቱን ልጆቹን እያለ ይሄዳል። ቆይቶ የሰማው በዝምድና በጉርብትና ተያይዞ ይመጣል። አንድ ሰው ግን ሰው ሳያስከትል ሰው ሳይከተል ብቻውን አስፓልቱን ይዞ ትንፉሹ ቀጥ እስክትል ድረስ እየሮጠ ከከተማ ወደ ሆስፒታል እየከነፈ መጣ። የዚህ ሰው የሩጫ መነሻው ከሮቤ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የከተማው ፖሊስ ጣቢያ ሲሆን ወንጀለኞችን ከሕግ ሰዎች ጋር በመሆን ጣቢያ አድርሶ ደሙ ፈሶ ሰዎች ወደ ህክምና ወደ ወሰዱት ሰው ደግሞ ይከንፋል። መምህራን ኮሌጅ ፊት ለፊት ሲደርስ ሳንባው በአፉ ሊወጣ ሆነ። ሩጫውን አቁሞ ከመንገድ ቁጭ አለ። ጥቂት አርፎ ሩጫውን በመጠኑ ቀጠለ። ሮቤ ሆስፒታል ጊቢ ሲገባ በሰው ተሞልቷል። የሞተም መሰለውና መራመድ እያቃተው ቀስ እያለ ወደ ፊት አመራ። ወደ ድንገተኛ ክፍል ጉልበቱ እየከዳው በዝግታ ሲራመድ ከጨለማ ወደ ብርሃን ደረሰ። ማንነቱ ከርቀት መታየት ሲችል ሌላ ጫጫታና ጩኸት በድንገት ሆነ። ደንግጦ ቆመና ወደ ግራው ዞሮ ሲመለከት " እራሱ እሱ ነው። እልልልል" ደግሞ ሌላ የደስታ ሁከት ሆነ። ከተሰበሰቡት እየከነፉ ወደርሱ የሚሮጡ ሰዎች አየ። የመጀመሪያዋ ራሄል ነች። ፈዞ ቀረ። ተጠመጠመችበት። ደግሞ ሌሎችም እንዲሁ። በሰው ድጋፍ ወደርሱ የምትመጣውን እናቱን ሲያይ ግን ቆሞ መጠበቅ አቅቶት ኤርምያስ ወደ እናቱ ሮጠ። ደርሶ ተጠምጥሞባቸው አቀፋቸውና " ምንድነው እማ ምን ሆናችሁ ነው?" አለ ኤርምያስ። እናቱ በዝምታ ከማንባት በቀር ምንም መልስ አልሰጡም። ሌሎች ሰዎች ግን ጥያቄ ሰነዘሩ። "በጩቤ ተወግቶ በጥይት ተመቶ ሲባል የነበረውስ ማነው ታዲያ?" ብዙዎች አጉረመረሙ። " እናቴ ከአንቺ ተለይቼ ወደ ቤት እየሄድኩ ከመንገድ የማውቀው ሰው ይዞኝ ስናወራ ቆየውና ተለይቼው ስሄድ ያላሰብኩት ሆኖ አገኘው። ከመንገድ አንድ ሰው ወድቆ ሁለት ሰዎች ጎድተውት ሲሮጡ ተመለከትኩ። እየጮኽኩ ተከተልኳቸው። ፈጣሪ ቀደማቸው ተያዙ። ያ ምስኪን ዝምተኛ እብድ ግን በሞትና በሕይወት መሀል ሆነ። ወንጀለኞቹን ወደ ሕግ ወሰድናቸው ሌሎች ደግሞ እርሱን ይዘውት ወደ ህክምና መጡ። እኔ አሁን ከፖሊስ ጣቢያ እየመጣው ነው" አለ ኤርምያስ። እናቱ ከርሱ የሰሙት ዜናም ለርሳቸው ቀላል አልሆነም። በዚያች ምሽት መልዕክት ያደረሳቸው ያ ሰው በገጠመው ልባቸው አምኖ መቀበል አቃተው። በድንገት ድጋሚ ከድንገተኛ ክፍል አቅራቢያ ከውጭ ከተሰባሰቡት ሰዎች መካከል ሌላ ድንገተኛ ጩኸት ሆነ። ኤርምያስ እየሮጠ ሄደ። ሌሎችም ተከተሉት። ወደጩኸቱ መድረስ ግን ተከለከለ። ኤርምያስ በስንት ልመና አልፎ ሲያይ መንፈስ ነው። " አቃጠለን ተቃጠልን ከዚህ ሆስፒታል አውጡት! ደሙን ያፈሰስነውን ያክል አቃጠለን ተቃጠልን አልቻልንም!" የሰው ትኩረት ወዲህ ሆነ። ኤርምያስ ግን ትቶ ወደ ድንገተኛ ክፍል ደርሶ አንኳኳ። አንዱ ሀኪም ከፈተና አናገረው። አውርተው የገጠማቸውን ነገር ሁሉ ሲነግሩት እርሱም ማመን አቃተው። ሀኪሞቹ ልብሱ ላይ | 310 |
| 13 | ናቸው?" ጠየቋት። እርሷም ሌላም ያላገኟቸው እንግዳ እንዳሉና የመጡበትን አጋጣሚ ሁሉ አንድ በአንድ ለእናቷ ነገረቻቸው። " ሰላሜ ደና ነሽ ግን አይደል? ምን አለ አዲስ ነገር? ሠርግሽን መችነው ወገቤን አስሬ ደግሼ ዘመድ ወገን ሚደሰተው? አሁንም ባል አልተገኘም? እንደው ነገር ማክረርሽን ትተሽ ለማግባት አልወሰንሽም?" አሏት። ልጃቸው ምንም ስለማትደብቃቸው በዚያው የንፍታሌምን ጉዳይ ለማጣራት። " እማ!" ብላቸው ጥቂት አስባ " እኛ ስለፈለግን ስለተመኘን ብቻኮ ሁሉም አይሆንም!" አለቻቸው። " ኤውልሽ እኔና አባትሽ ስለፈለግን ብቻ ምንም ማድረግ አይገባሽም አንቺም ፈልገሽ አምነሽ እንጂ" መለሱላት። " እኔም ብፈልግ ስለፈለኩ ብቻ የፈለኩት አይሆንም። እማዬ አሁን እንደምታውቂኝ አልምሰልሽ ፈሪ ሆኛለው። በቃ ብዙ ነገሬ እንደተቀየረ ይታወቀኛል። ብቻ አላውቅም። የምፈልገው ሆኖ ምኞታችሁ ቢሰካ እመኛለው። አንድ በጣም የምወደው ሰው አለ። ግን እርሱ ለኔ ያለውን ስሜት ገና አላወኩም። ስለርሱ ሳስብ ደስታና ፍርሀት የደበላለቅብኛል" አለቻቸው። እናቷ የልጃቸው ነግግር ውስጣቸውን ስለነካቸው አዝነውላት ነግረዋት የማያውቁትን የራሳቸውን ያለፈ ታሪክ ነገሯት። " እና አትዘግይ ቶሎ ንገሪው። ለመሆኑ ምንድነው የሚሰራው?" አሏት። " እማዬ ስራ የለውም" መለሰችላቸው። ወዲያው ስሜታቸውም ሀሳባቸውም ተለዋወጠ። " ስራማ ከሌለው አይሆንም። አንቺን የመሰለች ቆንጆማ ለዶክተር ለባለጋ ነው የምትገባው። እንዲያስ ከሆነ ይቅር" አሏት ቀለል አድርገው። ሰላም ቀበል አድርጋ " የማይሆነው እርሱ ሳይሆን እኔ ብል እንኳን እኔ እሆናለው ወይ ነው ጭንቀቴ። እርሱ ደግሞ ከኔ በላይ ብዙዎች ይመኙታል ይፈልጉታል። እኔ ፈልጌስ አገኘዋለው ወይ ነው ስጋቴ እማ። በጣም ነው የምወደው። ሁሌ በቃ ስለርሱ ብቻ ነው የማስበው" አለቻቸው። " ቆይ ምንም ሳይኖረው ነው የወደድሽው? ታዲያ ምኑን ወደድሽው ልጄ?" ጠየቋት። እርሷም መለሰች። " ኢሄስ ቅድም ሮጠሽ የተጠመጠምሽበት ምንድነው?" ጠየቋት። " ንፍታሌም ይባላል የቤተክርስቲያን መምህር ነው። እንዴት ያለ የሚገርም ሰው መስሎሻል! እናንተን ፍለጋ ወተንኮ እርሱን ደግሞ አተነው ጠፍቶ ተጨንቄ ቅድም ሲመጣ ሳየው ማመን አቅቶኝ ጭንቀቴ በደስታ ተተክቶ ነው ሮጬ የተጠመጠምኩበት። እርሱ ግን ደስተኛ አይደለም።አውቂያለው" መለሰችላቸው። በነገረቻቸው ነገር የጠረጠሩት ሁሉ እንዳልሆነ ተረድተው ጥርጣሬአቸውን ሻሩት። እያወጉ አረጋዊው አባትና መሪጌታ አምሽተው መጡ። እነርሱ ከመጡ በኋላ ሰላምና እናቷ ወዲያ ወዲህ ጉድጉድ ሲሉ አመሹና እራት ሰርተው ለእንግዳ የሚገባው ሁሉ ተዘጋጅቶ ሁሉም ከአንድ ተሰበሰቡ። ቡና የሚጠጣ ስላልነበረ እራት በጊዜ ቀርቦ በልተው ሻይ ጠጥተው ሲጨዋወቱ ቆይተው ሁሉም ወደየተዘጋጀላቸው የመኝታ ስፍራ አቀኑ። መሪጌታና እንግዳው አባት ከመኝታ ክፍል አልጋ ላይ። ሰላምና እናቷ ሰሎን ፍራሽ ላይ የተቀሩት ሶስቱ ወደ ማደሪያ ክፍላቸው አቀኑ። ስሙር እንደገባ መጽሐፍ ይዞ ቁጭ ሲል አቤል ይዞት የነበረውን ነጠላ አመሳቅሎ ለብሶ የጸሎት መጽሐፉን ይዞ ጸሎት ጀመረ። ንፍታሌም ደግሞ ልብሱን ቀይሮ ከመኝታው ስር ገብቶ ተኛ።
አቤል ጸሎቱን ሲያበቃ በግድግዳ በኩል ስሙር መሀል እንደተኙ ንፍታሌም ሌሊት ሁለቱም እንደማይሰሙ ሲያረጋግጥ ተነስቶ ጸሎት እያደረሰ መሪጌታ ወደ ክፍሉ መተው አይተውት ሲያበቃ መስቀል አሳልመውት ድምጽ ሳያሰሙ ወደ ቦታቸው ተመለሱ። ንፍታሌምም ተመልሶ ተኛ። እንቅልፍ ግን አልያዘውም። ስሙር አስቦ መልስ ያጣበትን ያባቱን የሌሊት ጉዞ ተከታትሎ ለማረጋገጥ አላርም ሞልቶ ስልኩ ሌሊት 7:10 ሲሆን ጮኸች። ተነስቶ ወደ አባቱ ክፍል አቅንቶ ሲያይ ከእንግዳው ጋር ተኝተዋል። ወደ መኝታው ተመልሶ ተኛ። ወዲያው ግን እንቅልፍ ጣለው። ንፍታሌም እርሱ ሲነሳ ተመልሶ ሲተኛም ተሸፍኖ ይሰማው ነበረ። ተኝቶ ከደቂቃዎች በኋላ ማንኮራፋት ሲጀምር ንፍታሌም የሰው ኮቴ ድምጽ ሲሰማ በፍጥነት ተነሳና። መሪጌታና አረጋዊው ነበሩ። በሩን መልሰው ዘግተውት ወደ ምሥጢራዊው የጠቢባን መንደር በዓለም ውስጥ ወዳለው ግና ከዓለም ርቆ ወደሚገኘው መንደር ጉዞ ሲጀምሩ ንፍታሌም በሩን በዝግታ ከፍቶ ወዲያው ተከተላቸው። ከጊቢ እንደወጡ ተከትሏቸው ወጣ። በቅርብ ርቀት ከኋላቸው ተከተለ። ወደ ደኑ መግቢያ ሲቃረቡ ሁለቱም ባሉበት ቆሙ ንፍታሌም አጠገባቸው ደረሰ። አረጋዊው አባት የክርስትና ስሙን ሲጠሩ " አዎ እኔ ነኝ አባ። ስትነሱ ከእንቅልፌ ነቃው። ወደምትሄዱት አብሬአችሁ ልሄድ ወደድኩ ለዚያ ተከተልኳችሁ" አላቸው። "ተባረክ ልጄ! መልካም አድርገኸል። የሚቀድሙትን የሚከተል ፍጻሜው ያምራል። እኛ እሩቅ እንሄድ ዘንድ አለን። አንተ ወደ ቤት ተመለስ!" ሲሉት " ይባርኩኝ!" አላቸውና መስቀል ተሳልሞ " እመለሳለው። ከሕይወቴ ድካም የተነሳ አባቶቼ ከሚሄዱበት ልሄድ ላልተቻለኝ ለኔ ግን በጸሎታችሁ ጊዜ አስቡኝ። ከፊት በትጋት ስትጓዙ ከኋላችሁ በጽናት እንድከተል ታናሹን እንዲያበረታኝ ለምኑልኝ!" ብሎ ወደ ኋላው ተመለሰ። መሪጌታና አረጋዊው አባት ቆመው እያዩት ቆይተው ወደ ጠቢባን መንደር አቀኑ። ያን እለት ባሪያውም የሚናፍቃትን መንደር ሊሳለማት ወስኖ የመሪጌታን መምጣት ከጫካው መግቢያ ላይ ሆኖ ሲጠባበቅ የንፍታሌምን መከተልና የተሰጠውን ትዕዛዝ የርሱንም ተማጽኖ ሲሰማ ያሰበውን ትቶ ወደ ዋሻው ተመለሰ። ሁለቱ ግን ግርማ ሌሊቱ ጸብሐ አጋንንቱ ቁረ ሌሊቱ ድምጸ አራዊቱ ሳያስፈራቸው በጨለማው መሀል ወደ ብርሃን መንደር ተጓዙ። ስሙር ሲገላበጥ ንፍታሌም እንደሌለ ሲታወቀው ቶሎ ተነሳ። ወዲያው ክፉ ክፉ ሀሳቦች ወደ አእምሮው ስለመጣ ፈጥኖ እህቱ ወዳለችበት ክፍል ሄደ። ንፍታሌም ግን የለም። ወዲያው ሊመለስ ሲዞር ንፍታሌም በሩን ከፍቶ ወደ መኝታው ሲመለስ ተከትሎት ሄዶ " ምነው ሰላም አይደለም?" አለው። ንፍታሌም " ኧረ ሰላም ነው ደጅ ወጥቼ እየተመለስኩ ነው" ብሎት ተሸፋፍኖ ተኛ። ስሙር ከብርድልብሱ ስር ገብቶ ሲያስብ ቆይቶ ትዝ ሲለው ዘሎ ድጋሚ ተነስቶ ወደ አባቱ መኝታ ሄደ። ግን ከመኝታቸው አላገኛቸውም። ሲመለስ እናቱ ተነስተው መተኛቱን አረጋግጠው ተመልሰው ተኙ። ዘጠኝ ሰዓት ሲሆን ከአንዱ ክፍል ከሶስቱ አንዱ ለጸሎት ሲነሳ ከሌላኛውም ክፍል ከሁለቱ አንድ ሰው እንዲሁ ለጸሎት ቆመ። ሰላምና ንፍታሌም። ሁለቱም የዘወትር ልማዳቸው ነው። ሰላም ቀድማ ጨርሳ ከወዲያኛው ክፍል ብርሃን ስታይ ወደ ክፍሉ መግቢያ በር ደርሳ ተደብቃ ስታይ ንፍታሌም እየሰገደ ነው። ቶሎ ቶሎ ይሰግዳል ጉልበቱ ግን መሬት የማይነካ ይመስል ድምጽ የለም። አጮልቃ በጨለማው ውስጥ እያየች እናቷ አጠገቧ ደርሰው " ሰላሜ!" አሏት።
💠 ይቀጥላል 💠
💢💠 ታኅሳስ 23 2016 ዓ.ም ባሌ ጎባ 💠💢 | 931 |
| 14 | 👤👤👤👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤👤👤👤
👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤
👤 ህቡዕ ገጽ 👤
💢💠 ከክፍል 174 የቀጠለ 💠💢
ሰላም ግን ደጋግማ ስለ ንፍታሌም በምታነሳው ሀሳብ ከእይታ ውስጥ ገባች። በተለይም እቤት እንደደረሱ ከቤት ንፍታሌምን አዲሱን እንግዳና አባቷን በማጣቷ በጣም ስትረበሽ ደጋግማ ስለ ንፍታሌም ስታነሳ መጠርጠሯ አልቀረም። ንፍታሌም ጨለማ ከወረሳት ዋሻ እንደወጣ በመጣበት አቅጣጫ ወደ መጣበት ለመመለስ ጉዞ ጀመረ። የሰላም እናት የልጃቸውን ያልለመዱት አዲስ ጠባይ ሲያዩባት " ሰላሜ ነይስቲ" ብለው ወደ ደጅ ሲወጡ ተከትላቸው ወጣች። ደጅ እንደወጡ " የምትይው ልጅ ምንሽ ነው?" ጠየቋት። ሰላም ሁለት ሀሳብ ሆነች። "ልናገር አልናገር?" ብላ አስባ ወሰነችና " እማዬ እኔ እርሱን......" ሳትጨርስ ንፍታሌም ከጊቢ ሲገባ አይታው ወደርሱ ስሜቷን መቆጣጠር አቅቷት ሮጠች። እናት ቆመው ማየት ጀመሩ።
💢💠🌿 ክፍል 176 🌿💠💢
የሰላም እናት ቆመው ከማየት በቀር ምንም ምን ሌላ አማራጭ አልነበራቸውም ያን አደረጉ። ሰላም እየከነፈች ሄዳ ተጠመጠመችበት። እናት ልጃቸው አንዳች ነገር ሆና እንጂ በጤናዋ ያቺ የሚያውቋት ሰላም እንዲ እንደማታደርግ እርግጠኛ ሆኑ። ንፍታሌም ሰላም አሻም እያለ ወላጆቹን እንደሚቀበል ሕጻን ተጠምጥማበት በድን ሆኖ ቀረ። የሚያዩትን ሰው በእቅፍ ውስጥ ሆኖ በድንጋጤ ተፋጦ እንዳለ ከቤት ውስጥ የወጣ ሌላ የማያውቀው ሰው ግንባሩን ከስክሶ በቁጣ ሳየው ንፍታሌም እርብሽብሽ አለ። ሰላም ዝምታውን ስታይ ለቃው ዓይን ዓይኑን እያየችው " የወንድሜና የእናቴን ወቶ መቆየት ምክንያት አድርገን ወተን የማታውቀው ጫካ ወስጥ የት እንደገባህ ፈልገን ስናጣህ በጣም ተጨነቅንኮ። የት ሄደህ ነው? እኔማ በጣም ነው የተጨነኩት። ምነው ይዤው ባልወጣው እያልኩ በጸጸት አለንጋ ልቤ ተገረፈ" አለችው እርሱ ግን ወደ ሚያዩት ሁለት ሰዎች ከማየት በቀር መልስ አልሰጣትም። ሰላም ዞራ ስታይ እናቷና ታላቅ ወንድሟ ቆመው እያዩአት ነው። " እናቴና ታላቅ ወንድሜ " አለችው ለማስተዋወቅ ያክል እርሷም ወደነርሱ ዞራ እያየች። " እማዬ ምንድነው የማየው ነገር? ቲኒሽ እንኳን እፍረት ሳይሰማት ስታደርግ ያየውት ምንድነው?" አለ ስሙር በቁጣ። እናት ግን የኋሊት በትዝታ ከረጅም ዓመታት በፊት የነበረ ሕይወታቸውን አስታውሰው በሀሳብ ተወስደው መልስ አልሰጡትም። የሰላም እናት መሪጌታ አመሀን ከማግባታቸው በፊት በጣም የሚወዱት አንድ የጎረቤት ልጅ ነበረ። ፍቅራቸውን ሳይገልጹለት እንደሚወዱት ሳይነግሩት ዛሬ ነገ እያሉ እያደር ፍቅራቸው እየጨመረ አንድ ቀን የሰሙት ዜና ህልማቸውን ትርጉም አልባ አደረገው። ያ የሚወዱት የልብ ወዳጃቸው ከቤት ተደብቆ ጠፍቶ ገዳም መግባቱን እና ያለበት እንደማይታወቅ ሰሙ። ያኔ ወሰኑ ዳግመኛ አፍቅሮ ያፈቀረውን ባጣ ንጹ ልባቸው ሌላ ወንድ ላያስቡበት። ያኔ ወሰኑ ወደ ፊት አልመው ትዳርን እንደማይናፍቁ። ያኔ ላያገቡ ያ ወዳጃቸው ያደረገውን ሊያደርጉ ገዳም ሊገቡ ወሰኑ። ይሁንና ግን እርሳቸው በዚያ የወጣትነት ጊዜያቸው ይህን ቢወስኑም የልባቸውን ግን ማንም ባለማወቁ ለአግርሞት የሆነ ውበታቸውን እያየ ለትዳር የማይመኛቸው አልነበረም። እየቀረበ ፍቅሩን የሚገልጽላቸውም አንድና ሁለት አልነበረም። አንድ ቀን ሲያደባ የኖረ የእሺታ መልስ ከርሳቸውም ከቤተሰባቸውም ያጣ ወጠምሻ ጎረምሳ ባልንጀሮቹን አደራጅቶ ውሃ ቀድተው ሲመለሱ ከወገባቸው ገንቦውን ሰብሮ ውሃው ሜዳ ፈሶ ጠለፏቸው። ይሁንና ግን ቤተዘመድ በፈረስ ደርሶ ያስጣላቸውን ቀን ዛሬ ላይ ቆመው የኋሊት ተጉዘው አስታወሱ። ከጠላፊዎች ያስጣሏቸው እለት ቀድመው በማመንታት የወሰኑትን እርግጠኛ ሆኑበት። እኔ ከእንግዲ የማንም አልሆንም ጠፍቼ ገዳም እገባለው ብለው ወሰኑ። ያኔ እድሜያቸው 16 ዓመት ነበረ። መሪጌታ ደግሞ የ 23 ዓመት ወጣት። መሪጌታ የአብነት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የሚወዳደራቸው የሌለ ጎበዝ ተማሪና በመምህራቸው የሚወደዱ ነበሩ። መምህራቸውም ከተማሪ ለይተው እንደወዳጅ ለብቻ አብረዋቸው እንዲያሳልፉ ያደርጉ ነበረ። አብረው በሚያሳልፉት ጊዜ ውስጥ ከመምህራቸው በተደጋጋሚ በሚያገኙት ነገር መሪጌታ ገዳማዊ ሕይወትን የሚናፍቁና ለመኖርም የወሰኑ ቢሆንም መምህሩጋ የሚከታተሉትን ትምህርት እስኪያጠናቅቁ በዚያ ቆዩ። እድሜያቸውም 23 ዓመት ሲሞላ በሀገሩ የታወቁ ሊቅ መሪጌታ አባታቸው ቆንጆ የተወደደች የትልቅ ሰው ልጅ አይተው አጩላቸው። መሪጌታ አላገባም ቢሉም አባታቸው ፈቃዴን ልትፈጽም ይጠባል ብለው ግድ ብለዋቸው ያዩላቸው ውብ ቆንጆ ልጅ ቤተሰብጋ ሽማግሌ ተላከ። ቤተሰቦችም የሊቅ የዘር ሀረግ ልጃቸውን ላይከለክሉ አሜን ብለው ተስማሙ። የሰርግ ቀን ተቆረጠ። የሰርጉ ቀን ሲቃረብ የታጨችላቸው ውብ ነገሩን ሰምታ አላገባም በሚል አቋሟ ጸንታ ከቤት ኮበለለች። ነገሩ በሀገር ሁሉ ተወራ። ከሁለት ቀኝ በኋላ ግን ኮብላዩአ ሙሽራ ከመንገድ ተይዛ ተመልሳ ድል ባለ ድግስ ለመሪጌታ ሚስት ሆና ተዳረች። ያቺ ኮብላይ ሙሽራ ዛሬ ውበቷ በቃል የማይገለጽ ቆንጆ ልጅ አድርሳ ቆንጆ ልጇ ከወንድ ተጠምጥማ ብታይ ትናንቷን ለማስታወስ ተገዳ በሀሳብ ነጎደች። " እማዬ!" አለ ስሙር አልሰማ ሲሉት። ከሀሳባቸው ብንን ብለው ነቁ። " ምን አልከኝ ስሙርዬ!" አሉት እርብትብት ብለው። " ማነው ኢሄ? ምንድነው ያየሁት? አንቺ ዝም ብትያትም ዝም ልላት አልችልም። እርሱም የማንም መንገደኛ ከእህቴ እንዲርቅ ማድረግ አቅም አያንሰኝም እነግረዋለው" ሲላቸው። የስሙር እናት " ሰላምን አንተ አይደለህም እኔ የመናገር አቅም የለኝም። እንዳትናገራት" አሉት ቆጣ ብለው። " ና ለሁሉም እንኳን በደና መጣህ ና" አለችው ሰላም ፈዞ በድን ሆኖ የቆመውን ንፍታሌምን። ከፊቱ ቀድማ ምንም ሳይናገር ተከተላት። ስሙርና እናቱ ግን ወደነርሱ የሚመጡትን ልጃቸውን እና ንፍታሌምን በአግርሞት ቆመው ያዩአቸዋል።
" ሰላም ለናንተ ይሁን ሰላም ዋላችሁ!" አለ ንፍታሌም አጠገባቸው ሲደርስ በፍርሀት። " እንዴት ዋልክ ልጄ! እግዚአብሔር ይመስገን። ግባ ግቡ ወደ ውስጥ" አሉ የስሙር እናት። ስሙር ግን ንፍታሌምን ክፉ አስተያየትን ሲያየው ንፍታሌም የበለጠ በተፈጠረው እርሱ ባላደረገው ግና ምክንያት በሆነው ነገር አጅግ እያዘነ ወደ ውስጥ ሰላምን ተከትሎ ገባ። ውስጥ ሲገቡ አቤል ከውስጥ ቁጭ ብሏል። ንፍታሌም በፈገግታ ሰላም ሲለው አቤል አገለማመጠውና ዝም አለው። ንፍታሌም " ትቼያችሁ ጠፋው አይደል? ይቅርታ አድርግልኝ በጣም" ሲል ሰላም " ኧረ አትጨነቅ ዋናው ደና ሆነ በሰላም መምጣትህ ነው ቁጭ በል!" አለችውና ተቀመጠ። ወዲያው እግራቸውን ተከትሎ ስሙር ገባና ቀድሞ ከነበረበት መቀመጫ ከንፍታሌም ፊትለፊት ተቀመጠ። ሰላም እየመሻሸ ስለ ነበረ የቤት ውስጥ ስራ እናቷን ለማገዝ ጥላቸው ወጣች። አቤልና ስሙር ንፍታሌም ቀና ብሎ ባያቸው ቁጥር ልብ የሚሰብር አስተያየት ሲያዩት እርሱ ግን ፈገግ እያለ ያቀረቅር ነበረ። በልቡ ግን ለወንድሞቹ ማዘን ምክንያት በመሆኑ እራሱን አብዝቶ ይወቅሳል። ሰላም ወደ ደጅ ስትወጣ እናቷ የሉም በቀጥታ ወደ ኩሽና አመራች። ስትደረስ እናቷ መደብ ላይ ተቀምጠው በሀሳብ ጭልጥ ብለው አገኘቻቸው። " እማዬ ምነው? ምን ሆነሽ ነው?" ጠየቀቻቸው። ከሀሳባቸው ወተው " አይ ምንም አልሆንኩም። እኔ የምልሽ እንግዶቹ እነማን | 852 |
| 15 | እንኳን እጅግ አሳዛኝ ነው። የሚያሳዝን ነው። የሚተርፍ እንኳን አይመስለኝም ብዙ ደም ፈሶታል። አጠገቡ ማንም የራሱ ሰው አልነበረም። የጎዱት ሰዎች በእርግጥ ተይዘዋል። ይገርምሀል ሰው ተጨካክኗል። ከአንዱ እጅ ላይ የተያዘውን ጩቤ ብታየው ውይ ኧረ! አንደኛው ደግሞ መሳሪያ ታጥቋል። በመሳሪያ ይምቱት በጩቤ ይውጉት እኔንጃ ብቻ ግን በቃ ያ ሁሉ ደም ፈሶት ፍጹም አይተርፍም። ጎድተውታል። የሕግ አካላትም መተው አፋፍሰው ወደ ሆስፒታል ወሰዱትና ደግሞ እዚህ ስደርስ ደግሞ ኢኸው! ኧረ ጌታ ሆይ ማረን!" ብሎ ሀሳቡን ተወቶ በጸሎት በተማጽኖ ንግግሩን ዘግቶ መንገዱን ቀጠለ። የሰማው ሰው ጊዜ ሳያጠፋ የሰማውን ይዞ ወደ ውስጥ ሰውን እየተጋፋ ደርሶ የተፈጠረውን ጠይቆ እንደተረዳ ያለ ጥርጥር አስቀድሞ ከሰማው ጋር ነገሩን አዛምዶ ለነገሩት መልሶ የሰማውን በቦታው እንደነበረ ለሶስተኛ ወገን እንዲህ ሲል ተናገረ። " ወይኔ እርሱ ይሆን እንዴ። አሁን ከደቂቃዎች በፊት አንድ ሰው መንገድ ላይ ደም ፈሶት ሰዎች ተሰባስበው በነፍሱ ለመድረስ ወደ ሆስፒታል ወስደውታል" ሲለው ሰሚው መልሶ ለእርምያስ ቤተሰብ ለመንገር የሰሚ ሰሚ መልሶ የሰማውን እንዳየ ሆኖ ለክብሮም እንዲህ አለው። " አይዟችሁ ተረጋጉ። በተለይ አንተ ትልቅ ሐላፊነት ነው ያለብህ። ቤተሰቡን አረጋጋና በፍጥነት በነፍስ ድረሱለት ጠፋ የምትሉት ሰው ከደቂቃዎች በፊት በመሳሪያ ይውጉት በጥይት ይምቱት ከመንገድ ወድቆ ደም ሲፈሰው ሰዎች ወስደው ወደ ሆስፒታል ወስደውታል። እባክህን በተለይም እናቱን አረጓጓቸው" ብሎ ኤርምያስን ተወግቶ እንዳየው ሰው እርግጠኛ ሆኖ ሲነግረው ክብሮም ለራሄል ነግሯት ወደ ሆስፒታል ከነፈ። እርሷም የሰማችውን ማመን አቅቷት እየጮኸች ተከተለችው። የኤርምያስ እናት ሲሰሙ እንኳ ሮጠው ሊከተሏቸው ራሳቸውን ችለው መራመድ አቅቷቸው በሰው ድጋፍ ወደ ሆስፒታል ተወሰዱ። ሆስፒታል ጊቢ ሲደርሱ እንደተባለውም ሰው ተሰባስቦ ሲያዩ ሁሉም ተደናገጡ። ራሄል ጩኸቷን አቀለጠችው።
💠 ይቀጥላል 💠
💢💠 ታኅሳስ 22 2016 ዓ.ም ባሌ ሮቤ 💠💢 | 941 |
| 16 | 👤👤👤👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤👤👤👤
👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤
👤 ህቡዕ ገጽ 👤
💢💠 ከክፍል 171 የቀጠለ 💠💢
ቦታውን ሲፈልግ ቆይቶ " እንዲህ ይላል" ሲላቸው ሀሳባቸውን ሰብስበው ዝም አሉ " ለአንድ ሰው በወይኑ አትክልት የተተከለች በለስ ነበረችው።ፍሬም ሊፈልግባት መቶ ምንም አላገኘባትም። የወይን አትክልት ሠራተኛውንም እነሆ ከዚህች በለስ ፍሬ ልፈልግ ሦስት ዓመት እየመጣሁ ምንም አላገኘሁም።ቁረጣት ስለምን ደግሞ መሬቱን ታጎሳቁላለች አለው። እርሱ ግን መልሶ ጌታ ሆይ ዙሪያዋን እስክኮተኩትላትና ፋንድያ እስካፈስላት ድረስ በዚህች ዓመት ደግሞ ተዋት። ወደ ፊትም ብታፈራ ደኅና ነው። ያለዚያ ግን ትቆርጣታለህ አለው። ይላል።" አላቸው። ብቻ በታሪኩ ውስጥ ያልገባቸው ብዙ ቢኖርም መልእክት እንዳለው በቀላሉ ተረዱ። እየተብሰለሰሉ እርምያስ ደወለ። ስልኩን አንስተው " ሄሎ " ሲሉ ምላሽ የለም። የሚሰሙት ከባድ ጩኸት ጫጫታ ነው። እናት ሰማይ ምድሩ ተገለባበጠባቸው።
💢💠🌿 ክፍል 175 🌿💠💢
የኤርምያስ እናት እየደጋገሙ " ሄሎ ሄሎ! ሄሎ ልጄ! ኤርምያስ! ኧረ ሄሎ!" ምንም ምላሽ የለም። በስልክ ውስጥ የሚሰሙት ጫጫታና ሁካታ ግን እየባሰ እየጨመረ እየበረከተ ሲመጣ ተሰማቸው። አቅም አነሳቸው የሚያደርጉት ጠፋቸው። " ስልኩ ለረጅም ደቂቃዎች ሳይዘጋ ምላሽም ሳይኖር ቆየ። " ሄሎ ኧረ ሄሎ!" አሁንም መልስ አጡ። ምናልባትም ከሚሰሙት ጩኸትና ጫጫታ ውስጥ አንዳች ጠቋሚ መልዕክት ካገኘው ብለው ጩኸቱን ሁካታውን ስልኩን ከጆሮአቸው ይዘው ሲያደምጡ ቆይተው በስተመጨረሻ " በሕግ አምላክ ያዙአቸው! ገድለውታል። ደሙን አፈሰሱት። አፈር ልብላ ገደሉት" እያለች አንዲት ሴት ስትጮኽ ሲሰሙ የኤርምያስ እናት አፋቸውን ደም ደም አላቸው ሁሉ ስሜታቸው ተለዋወጠ። አሞታቸው ፈሰሰ ልባቸው ዛለ ተስፋቸው ጨለመ። ደስታቸው ዳመነ። ሰማይ ምድሩ ተከደነባቸው። በቃ በተቀመጡበት በድን ሆነው ጆሮአቸው የሰማውን መቀበል አቅቶት ጭው አለባቸው። ያለ የሌለ አቅማቸውን አሰባስበው " ልጄን ቀሙኝ ልጄን አሳጡኝ። ብርሃን አልባ አደረጉኝ ጨለማ ወረሰኝ" ብለው አሰምተው የግዳቸውን ሲጮኹ ግቢ ውስጥ ያሉ ተከራዮች ከየክፍላቸው እየሯሯጡ እርሳቸው ካሉበት ተሰባሰቡ። በሁለት እጆቻቸው እራሳቸውን ይዘው አቀርቅረው እንደተቀመጡ አገኟቸውና " ምንድነው? ምን ተፈጠረ? ምን ሆነዋል ማዘር?" አለ አንደኛው። " ቆይ አሁን ቅርብ ጊዜ ደና አልነበሩም እንዴ?" አለች ሌላኛዋ ተከራይ ተማሪ። እያፈራረቁ የጥያቄ ናዳ ከበው አወረዱባቸው። የኤርምያስ እናት ከተቀመጡበት ሶፋ ደጠፍ ብለው በአንድ እጃቸው ያስቀመጡትን የጅ ስልካቸውን ዳብሰው ፈልገው አነሱና በጥያቄ ወደሚያፋጥጧቸው እያቀበሉ " ልጄ ላይ ደውሉልኝ እባካቹ ፍጠኑ" ሲሏቸው አብሯቸው የቆየው በተፈጠረው ነገር ግራ የተጋባው የግቢው የረጅም ጊዜ ተከራይ ነዋሪ ወጣት ከድንጋጤው በመጠኑ ተላቆ ስልኩን ተቀብሏቸው መደወል ጀመረ። ስልኩን ከፍቶ የኤርምያስ ስልክ ላይ ሲደውል በተደጋጋሚ " የደወሉላቸው ደንበኛ ስልክ አይመልስም" የሚል ድምጽ በተደጋጋሚ ሲሰማ የበለጠ ፍርሀቱ ጨመረ። ደነገጠ። የኤርምያስ እናት በመሀል ቀና ብለው "እ" ሲሉት የሚመልስላቸው ጠፋው። ስልኩን ተቀብለው ደወሉ። ስልኩ አይነሳም። " ልሂድ ቁርጤን ልወቀው" ብለው አቅም እያነሳቸው ተነስተው በሻርባቸው ወገባቸውን አስረው ከቤት ሲወጡ ከተወሰኑት በቀር ሌሎቹ ተከተሏቸው።
ምሽቱ ጨረቃ ከሰማይ የማይታይበት ጨለማ የወረሰው ነው። ሰዓቱ ገፍቷል። የአንዲት እናት አንጀት ግን ስለ ልጇ ይነዋወጻል። እርሷም መጽናናትን እንቢ ብላ እንደ ብሌኗ ስለምትሳሳለት ልጅ እንባዋን እያዘራች ወዳጆቿ የሰሙ ጎረቤቶቿ ሁሉ ተከትለዋት ከምትሄድበት መድረሻዋ የዓመታት መንገድ ያክል ርቋት ከደቂቃዎች በኋላ ስለልጇ የምትሰማውን ቀድሞ ኅሊናዋ ክፉ ክፉውን እያመለከታት ፍርሀት ውጧት ልቧ እየራደ እግሮቿ መራመድን እንቢ እያሉ እየታገሉ ልባቸው አብዝቶ መድረሳቸው እየናፈቀ የሚከተሏቸው ሁሉ ከቆይታ ኋላ የነገሩን ምንነት እስከሚያዩ በዝምታ መከተልን ብቻ ምርጫ አድርገው ተሰው መንጋ በኤርምያስ እናት መሪነት ወደነ ራሄል ቤት አቀና። መድረስ አይቀር እንደደረሱ የንፍታሌም እናት ከውጭ በር ደርሰው እጆቻቸው በሩን መጽፋት ማንኳኳት እንኳን አቅም አንሷቸው ሲያዞራቸው ባሉበት ቁጭ ሲሉ ከሚከተሏቸው አንደኛው የጎረቤት ሰው በሩን በኃይል ማንኳኳት ጀመረ። ወዲያው ክብሮም እየተጣደፈ መቶ " ማነው!" እያለ ባገኘው ምላሽ በሩን ወለል አድርጎ ሲከፍት የሚያየው የሰው ብዛት ችግር መኖሩን አሳበቀለት። " እንዴ ምንድነው ችግር አለንዴ? ምን ሆናችሁ ነው?" አለደንግጦ። " ኤርምያስ ምን ሆኗል?" አለ ያንኳኳው ሰው። ክብሮም ጭራሽ ጥያቄው የበለጠ አስደነገጠውና " ምን ሆነ ምንም አልሆነም። ምነው?" ጠየቀ መልሶ። " አሁን አቤት ነው?" ሰውየው ጠየቀ። ክብሮም " ቆዩኝ አንዴ መጣው" ብሎ በሩን መልሶ ዘግቶ ወደ ውስጥ ተፈተለከና የነ ራሄሌን ክፍል ማንኳኳት ያዘ። ራሄል ከልጇ ጋር እየተጨዋወተች ክብሮም ሲጠራት " ወዬ ክብሮም! ልክፈት ልትገባ ነው?" ጠየቀችው። " አይ አልገባም። ኤርምያስ አለንዴ?" አላት። " የለም እናቱ ጋር ሊጠይቃቸው ሄዶ አስከ አሁን አልመጣም" ስትለው ፍርሀቱ ባሰ። መልስ ሳይሰጣት ወደ በሩ ተመለሰ። በሩን እንደከፈተ ለብዙዎቹ መሪ ሆኖ ለቆመው ሰው " ኤርምያስ የለም እናቱን ጥየቃ ሄዷል። ቆይ ግን ምን ተፈጥሮ ነው?" ሲል ሰውዬው ደንግጦ " አሁን እቤት የለም?" ሲል የኤርምያስ እናት " እራሱኑ ነው የገደሉት። ልጄን ነጠቁኝ ወይኔ ብርሃኔን" እያሉ በሰለለ ድምጽ ሲያለቅሱ ክብሮም ሰማና በሩን መልሶ ዘግቶ ወደ ውጭ ወቶ ከሰው መሀል ወዳሉት ወደ ኤርምያስ እናት ደርሶ ሲያያቸው በቃ የሚናገረው የሚለው የሚያደርገው ግራ ገባው። " Mother!" አለ ዝቅ ብሎ ትከሻቸውን በጁ ይዞ። ወዲያው ራሄል እያወራት ክብሮም ድምጹ ሲጠፋባት ወደ ውጭ ስትወጣ ከውጭ የሰው ጫጫታ ስትሰማ እርሷም ወጣች። ያ እያረፈ የሚቆስል ልቧ ያ ድካም ያዛለው የልቧ ትከሻ ደግሞ ሌላ ሸክም ሊሸከም ጊዜው መጣ። በሩን ከፍታ ስትወጣ ሰው መንገዱን ሞልቶታል። ወዲያው እንደወጣች የኤርምያስን እናት ከበው ወዳሉት አቀናች። ክብሮምን አየችው አጠገቡ ደርሳ " ምንድነው?" ጠየቀችው። ከኋላው ስለነበረች አልታያትም። ክብሮም አንደበቱ ተሳስሮ " የ የ የኤርምያስ እናት" ብሎ አሳያት። አየቻቸው። ተንበረከከችና " ምንድነው የተፈጠረው? ኤርምያስስ?" አለቻቸው። ሁሉን አዲስ እንደሰማ ሰው የኤርምያስ እናት ለቅሶአቸውን ጩኸታቸውን ለቀቁት። ራሄል በአዲስ ኃይል ለቅሶን እንባን ማፍሰስ በለመደ ዓይኗ ተባበረቻቸው። "ኡኡኡኡኡኡ" ሌላ በርካታ ሰው ተሰባሰበ።
ከየአካባቢው ሰው እየተሯሯጠ በነበረው ሕዝብ ቁጥር ላይ የሚበልጥ ተጨመረ። የኤርምያስን እናትና ራሄልን ለማረጋጋት ብዙ ሰዎች በብዙ ደከሙ። በመሀል ነበረ አንድ ዜና ወደ ሰዎች ጆሮ ሲደርስ ነገሩ የበለጠ ድብልቅልቁ የወጣው። ሰው በተሰበሰበበት እያለፈ የነበረ መንገደኛ አንዱን " ምን ተፈጥሮ ነው እዚህ ደግሞ?" ብሎ ሲጠይቅ "በቅጡ አላወኩም አሁን መድረሴ ነው" አለ ተጠያቂው። ጠያቂውም " የሚገርም ቀን ነው። አሁን ቅርብ እኮ ነው እንዲሁ ያለ ሁኔታዎች የነበሩት። ያ | 891 |
| 17 | የማላስበው ነኝ። ኢሄኔ አቶን ወደ ቤትም ተመልሶ ሊሆን ይችላል። ለምን አትረጋጊም! እባክሽ ሰላም ተረጋጊ" ሲላት ውስጧ የሚላትን እውነቱን አውጥታ ተናገረች። " አልችልም! ንፍታሌም ለኔ ሕይወቴ ነው። እንደራሴ ነው የምወደው! በርሱ ላይ ምንም ክፉ ሆኖ ማየት መስማት አልችልም። የልቤን እኔ ነኝ የማውቀው። አቤል ኤውልህ እኔ እርሱን በጣም ነው የምወደው። ለርሱ ፍቅሬ ወደር የለውም። ስለዚህ አልችልም። ልቤ ነው የማይችለው!" አለችው። አቤል ደነገጠ። ሰላም ንፍታሌምን አወደዋለው ያለችውን ጆሮው እንዳልሰማ ራሱን ለማሳመን ለማመን ተመኘ። የሰማውን ማመን አቃተው።ግና ሁሉም አሁንና እውነት መሆኑን ሲረዳ ወደተወው የመውደድ ምዕራፍ ልቡ ተነዳ። ከፊቱ የቆመች በንግግሩ እንደ ነበልባል የምትነድ ውቧን ሰላም የሚወዳት ልቡ ተዳፍኖ የቆየ ፍቅሩን ገልጦ ትናንቱ ዛሬ ላይ ሊደገምበት ዓይኖቹ ልቡን ተከትለው ከፊቱ የቆመችውን የውበት መለኪያ ውብ መልከመልካም ጸባየ ሸጋ ልጅ በፍቅር አይን በመወደድ ስሜት ዳግም ሰላምን ያያት ጀመረ። ከሚያውቃት በላይ ቆንጆ ሆና ታየችው። " ሰላም አንቺ በጣም እድለኛ ሰው ነሽ። ያልሽው ሁሉ እውነት ቢሆንም ደግሞ ሌላውን እውነትም መቀበል ይገባል። አንቺ በጣም ቆንጆ እንከን የማይወጣልሽ ውብ ነሽ። አንቺን መውደድ የማይችል አይኖርም። ላንቺ መኖር ንፍታሌም የግድ ሕግ ይመስል መኖር የለበትም። ብዙ የሚወዱሽ አሉ። እድሉን ቢያገኙ ከንፍታሌም በላይ ላንቺ ክብር ሰተው ተንከባክበው በፍቅር የሚያኖሩሽ ሞኝ አትሁኚ። አንቺ እንደምታስቢውኮ ንፍታሌም ላያስብ ይችላል። ያ ደግሞ ነገ ይጎዳሻል። ስለዚህ..." " ስለዚህ ምን? ንገረኝ ምን? ተይው? ነው? እኔ ንፍታሌም ለኔ ያለው ስሜት ሁሉ አይመለከተኝም። የማውቀው ኢሄን ነው እኔ እርሱን ልቤ ያፈቅረዋል። እወደዋለው። እርሱን አላገኘው እንኳ ቢሆን በቃ ሳፈቅረው እኖራለው" ቁርጥ አድርጋ መለሰችለት። " ለሁሉም አንቁም እርሱንም እናትና ወንድምሽንም ለማግኘት እንንቀሳቀስ" አለ አቤል። "ፍጹም አይሆንም ንፍታሌም ወደ ቤት ተመልሶ ከሆነ ማረጋገጥ አለብን። ቀድመን እርሱን ማግኘት አለብን። ወደ ቤት እንመለስ" አለች ሰላም። አቤል ተበሳጨ። ግን ሀሳቧን ተቀበለና ወደ ቤት ጉዞ ሲጀምሩ ከደኑ ውስጥ ከጀርባቸው ጩኸት ሰሙ። የሴት ድምጽ ነው። " እማዬ ነች!" ብላ ተፈተለከች። አቤል ተከተላት።
ንፍታሌም ባሪያው ታሪኩን አንድም ሳይቀር ነግሮት እንደጨረሰ " አጠቃላይ አሁን ለነገርኩህ ያበቃኝ እናትና አባቴን ሳላውቅ እራሴን ከጎዳና ማግኘቴ እየተራብኩ እየተጠማው እንደኔው ከመንገድ ወድቀው ከሚመስሉኝ ጋር የሚረዳን ከሚበላው ከፍሎ የሚሰጠን በፍቅር የሚመለከተን በማጣት ሁለት ሶስት ቀን ሳንበላ የምንውልበት ጊዜ ነበረ። በምክንያቶች ወደዚህ ክፉ ልማድ ወደ ስርቆቱ ገባን መውጣቱ አበሳ ሆነ። በመጨረሻ ምክንያት አድርጎ ፈጣሪ እኚያን አስተማሪ አባት አገናኘኝ።" አለው። " የምትላቸው አባት ምን ሆነው ነው የታሰሩት?" አለ ንፍታሌም። " ሴት ደፈርክ በሚል ነበረ። እንዳላደረጉት እያወቁ ወንጀሉን ለፈጸመው ነጻነት ይህን እዳ ተቀበሉ። አባ ትህትና የርሳቸው ይለያል!" ሲል ደንግጦ " አባ ትህትና!" አለ። " አዎ አባ ትህትና!" አለው ባሲያው። ንፍታሌም ተደነቀ። " እና እዚህ ከመጣህ ቆየህ? ያልከኝ የነገርከኝ እዚህ ከመጣህ የደረሰብህ ነገር ከተፈጠረ ቆየ?" ጠየቀው። ባሪያው መለሰለት። ንፍታሌም " ግን እዚህ የምትቆየው እስከመቼ ነው?" አለው። ባሪያው በዝምታ ቆይቶ "ደግሞ ከዚህኛው መቆያዬ ሲያበቃ" አለው ፈገግ ብሎ።
ሰላምና አቤል እየሮጡ ድምጽ ወደሰሙበት አቀኑ። ባሰቡት ፍጥነት ከሚሰሙት ድምጽ መድረስ አልቻሉም ቢዘገዩም ግን ጩኸቱ ስላልቆመ ከጩኸቱ ለመድረስ አላዳገታቸውም። ሲደርሱ የስሙር እናት የልጃቸው እግር ላይ ተጠምጥመው ከእግሩ ወድቀው ነው የሚጮሁት። ሰላም ገና ከርቀት ስታይ ግራ ገባት። አቤል ግን እየሮጠ ደርሶ " ወንድሜ እባክህን ምን ሆነው ነው የሚጮሁት?" አለው። የመሪጌታ ባለቤት " እባክህን ያዝልኝ። እንዳያመልጠኝ ያዝልኝ" እያሉ ሲማጸኑት " እኔ እይዘዋለው ይልቀቁትና ይነሱ እርሶ" አላቸው። ሰላም ግራ እየተጋባች ወደ እናትና ወንድሟ ደርሳ "ምንድነው እማዬ?" አለች። " አብዷል ልጁ የማገኘው ሰው አለ ብሎ አብሬው ስኳትን ዋልኩ ሳላገኘው አልገባም ነው የሚለው" አሏት። ሰላም ወደ ስሙር ደርሳ "ስሙርዬ ማነው? ማንን ፈልገህ ነው? ተው እማዬን አታሳዝናት ከምንም በላይ ደግሞ አባዬ ነገሩን ሰምቶ እንዳያዝንብለህ! አሁን እንኳን ሌላ የማንወጣው ነገር ውስጥ ገብተናል" ስትለው ደነገጠ። " ምንድነው?" አላት። አንተንና እማዬን ፍለጋ ሶስት ሆነን ወተን ከንድ አብሮን የወጣ ሰው የት እንደገባ" ስትለው በርሱ ምክንያት ለተፈጠረው ነገር አዘነ። በዚህም በዚያም ብለው ስሙርን አሳምነው ወደ ቤት ይዘውት ሲመለሱ እቤት ሲደርሱ አዲሱ እንግዳ መነኩሴና መሪጌታ አመሀ የሉም።
ንፍታሌምና ባሪያውም በአንድ ቀን አጋጣሚ ብርቱ ዘመናትን የተሻገረ ወዳጅነት የሚመስል መቀራረብን ተቀራረቡ። ልብ ለልብ አወጉ። ንፍታሌም ብዙ ከባሪያው ተማረ። ንፍታሌም በእርግጥም እርሱ ከማንም አጋጣሚዎች ሁሉ ለርሱ አስተማሪው ናቸው። አውርተው በተለይም ስለ አካባቢውና በተለየ ስለ ሙሲቾ ተራራ ምሥጢራዊነት በሚገባ ባሪያው ነግሮት ንፍታሌምም ለቀናት በዚህ ጥቂት እንዲቆይ ነግሮት ተሰነባብተው ከዋሻው ወጣ። ሰላም ግን ደጋግማ ስለ ንፍታሌም በምታነሳው ሀሳብ ከእይታ ውስጥ ገባች። በተለይም እቤት እንደደረሱ ከቤት ንፍታሌምን አዲሱን እንግዳና አባቷን በማጣቷ በጣም ስትረበሽ ደጋግማ ስለ ንፍታሌም ስታነሳ መጠርጠሯ አልቀረም። ንፍታሌም ጨለማ ከወረሳት ዋሻ እንደወጣ በመጣበት አቅጣጫ ወደ መጣበት ለመመለስ ጉዞ ጀመረ። የሰላም እናት የልጃቸውን ያልለመዱት አዲስ ጠባይ ሲያዩባት " ሰላሜ ነይስቲ" ብለው ወደ ደጅ ሲወጡ ተከትላቸው ወጣች። ደጅ እንደወጡ " የምትይው ልጅ ምንሽ ነው?" ጠየቋት። ሰላም ሁለት ሀሳብ ሆነች። "ልናገር አልናገር?" ብላ አስባ ወሰነችና " እማዬ እኔ እርሱን......" ሳትጨርስ ንፍታሌም ከጊቢ ሲገባ ከይታው ወደርሱ ስሜቷን መቆጣጠር አቅቷት ሮጠች። እናት ቀመው ማየት ጀመሩ።
💠 ይቀጥላል 💠
💢💠 ታኅሳስ 18 2016 ዓ.ም ባሌ ሮቤ 💠💢 | 878 |
| 18 | 👤👤👤👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤👤👤👤
👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤
👤 ህቡዕ ገጽ 👤
💢💠 ከክፍል 173 የቀጠለ 💠💢
ሰላም ወዲያ እነርሱ እስኪጨዋወቱ ጉድጉድ ብላ ሻይ አፍልታ የጅ ውኋ አቀረበችና ሁሉም በአንድነት ለምሳ ቀረቡ። በልተው ተፈጽሞ ማዕዱ ተነስቶ አረጋዊው "ሊቁ ባለቤቶትስ?" አሉ። "አንድ ከውጭ የመጣ ልጄ ጠዋት በአንዳች ስሜት ተፈትልኮ ወደ ጫካው ሲሄድ እናቱም ተከትላው የወጣች ነው" አሉ ቀለል አድርገው። ሰላም ስትሰማ "በቃ ተጨዋወቱ አባዬ ወጥቼ ልያቸው" ብላ ስትወጣ " እኛም ከምንቀመጥ ወጣ እንላለን" አለ አቤል ወደ ንፍታሌም እያየ። እርሱም ላያሳፍረው ተነሳና ሶስቱም ተያይዘው ወደ ደኑ ወጡ። እያወሩ ከደኑ ገቡ። የሰላምን እናትና ወንድም ፍለጋ በአንድ እየሄዱ ንፍታሌም ከደኑ ውስጥ ወደ ኋላ ቀረና ጠፍተውበት በሌላ መንገድ ሲሄድ ከአንዲት ዋሻ ነገር ውስጥ የሳል ድምጽ ሰምቶ ወንዙን ተሻግሮ ወደ ዋሻው ገባ።
💢💠🌿 ክፍል 174 🌿💠💢
ንፍታሌም ጫማውን አውልቆ ኩልል ካለው ወንዝ ሱሪውን ሰብስቦ ጫማውን በጁ ይዞ ወደ ወራጁ ወንዝ ሲገባ ቅዝቃዜው እግሩን አደንዝዞት መቆም እያቃተው የግዱን እንደምንም ብሎ ወደ ዋሻው መግቢያ ሲያቀና ከመግቢያው እንደደረሰ በጁ የያዘውን ጫማ ከመግቢያው አስቀምጦ ፊቱ አካል ያለው ይመስል እራሱን ሰውሮ በውስጡ ምሥጢር አዝሎ ካለው ጨለማ ከወረሰው ዋሻ መግቢያ ወደ ውስጥ ዞሮ እንደቆመ አጭር ጸሎት አድርሶ አማትቦ ወደ ውስጥ ገባ። ባዶ እግሩን ስለነበረ እርምጃው ድምጽ አልነበረውም። ጥቂት እርምጃዎች በፍርሀት እንደተራመደ እጁን ወደ ኪሱ ከቶ የጅ ስልኩን አውጥቶ አበራ። ከዋሻው ጥገኛ ክፍል ላይ ባሪያው(ዝክረ ጻድቅ )ቆሞ እየጸለየ ነው። ያበራውን ስልኩን ወዲያ ወዲህ አዘዋውሮ ለማየት ሲጠቀም ብርሃኑ ቆሞ ከሚጸልየው ሰው ላይ አረፈ። ወዲያው ንፍታሌም እየጸለየ ያለ መሆኑን ሲረዳ በአፋጣኝ ብርሃኑን አጠፋና ያለ መጽሐፍ እጆቹን ዘርግቶ ሲጸልይ ያየው ሰው ጸሎቱን እስኪፈጽም ባለበት ተቀምጦ ሊጠብቀው አሰበና እግዚአብሔር በአንድም በሌላም በረከትን እንደሚያድል በማሰብ እርሳቸው ወደ ዞሩበት አቅጣጫ ፊቱን አዙሮ ከጸሎቱ ሊሳተፍ ተባበረ። ኅሊናውን መሰብሰብ ግን ፍጹም አልቻለም። ልዩ ልዩ ሀሳቦች ወደ አእምሮው እየመጡ ረበሹት። " ቆይ ይኼ ሰው እናቱ ጫካ ለጫካ እየተንከራተቱ ነው እርሱ ተደብቆ እዚህ ማንም ሳያየው የሚጸልየው? ቆይ ማንም ሳያውቅ እዚህ መቶ መጸለይ አይችልም ነበረ? ለምን እናቱን....?" እያለ ውስጡን ጥያቄ ሲንጠው ለዚያ ምላሽ ፍለጋ አድማስ በሀሳብ ይሻገራል። ንፍታሌም በሀሳብ ከሄደበት ዓለም " ድም ድም" የሚል የሚሰማው ድምጽ መለሰው። ንፍታሌም የሚሰማውን ድምጽ ምንነት ለመለየት ጊዜ አልወሰደበትም። ያ ለጸሎት የቆመው ሰው ስግደት መጀመሩን ተረዳ። እስኪጨርስ በትዕግስት ድምጹን አጥፍቶ ብዙ ቢጠብቅም እንዳሰበው በቶሎ አልፈጸመም። ኋላ ዝክረ ጻድቅ ጸሎቱን ልመናውን ስግደቱን አጠናቆ ባለበት ቁጭ ሲል ከዋሻው ውስጥ የሚሰማ ምንም አይነት ድምጽ ሲያጣ ንፍታሌም ፈራ ተባ እያለ " ከዚህች የጸሎት ዋሻ ከበአትዎ በድፍረት ስለመግባቴ ይቅርታ ያድርጉልኝ" ሲል ባሪያው ሰምቶ ድንግጥ አለ። " ማነህ! ማነህ አንተ? ምን ፈልገህ ወደዚህ መጣህ?" አለ። ንፍታሌም ከጥያቄዎቹ የሚያናግረው ሰው የሰላም ወንድም እንዳልሆነና በዚህች ዋሻ ተደብቆ የሚኖር ሰው መሆኑን ተረድቶ " ይቅርታ እኔ ለአካባቢው አዲስ ሰው ነኝ። አንድ ልጅ ከቤቱ ወቶ እናቱም ተከትለውት ከዚህ ጫካ እንደመጡ ሰምተን ፍለጋ ሶስት ሆነን ወጣን አጋጣሚ በዚህ በዋሻው ጋር ሳልፍ የሳል ድምጽ ሰምቼ ነው የገባሁት። ገብቼ መብራት ሳበራ ጸሎት ላይ እንዳሉ አወኩ እስኪፈጽሙ መብራቴን አጥፍቼ ጠበኮት። እንዲያውም የጠፋው ልጅ መስለውኝ ነበረ። እባኮት ይቅርታ የኔ አባት ይፍቱኝ!" አለ ንፍታሌም በትህትና። ባሪያው ትህትና የተሞላበትን የንፍታሌምን አነጋገር ሲሰማ በቤተክርስቲያን ያደገ በአገልግሎት ውስጥ ያደገ ሰው መሆኑን ከንግግሩ ተረድቶ " ማነህ? ምን ፈልገህ ነው?" ብሎ በመጠየቁ ተጸጽቶ ካለበት ተነስቶ ንፍታሌም ወዳለበት መራመድ ሲጀምር ንፍታሌም ዳግመኛ ስልኩን አበራና እያየ እየተያዩ ባሪያው ወደርሱ ሲመጣ ንፍታሌም ተነስቶ ቆመ። መቶ አጠገቡ ሲደርስ ከንፍታሌም እግር ላይ ወድቆ " እግዜር በጥበቡ የሰራትን መጠለያ እንደራሴ አንተንም እንደመጻተኛ ቆጥሬ የወንድሜን ልብ ሰበርኩ። ይቅር በለኝ!" ሲለው ንፍታሌም ከመቅጽበት ዝቅ ብሎ "ኧረ እባኮት እኔ እንዳሰቡት አልተሰማኝም ይነሱ። ኧረ በቅዱሳን!" ብሎ ትከሻውን ይዞት ሲነሳ ንፍታሌም ጎንበስ ብሎ " ይባርኩኝ" አለ መስቀል ለመሳለም። "እኔ ዓለም በስራዋ የተጠቀመችብኝ በኃጢአት አንቱ የተባልኩ መሰቀል እንጂ መስቀል መያዝ ያልተገባኝ ወንበዴ ነኝ" ሲለው ንፍታሌም ምንም የሚለው ጠፋው። ሁለቱ ዓይን ለዓይን ተያዩ። ባሪያው " የሾመችኝ ዓለም አንቃ አዋርዳ ሳትገለኝ እኔ ካለሁበት ወይኒቤት አንድ ያለ በደላቸው የታሰሩ ሰው እኔን አርነት አወጡኝ። በመታሰራቸው ከእድሜ የኃጢአት እስራት ፈቱኝ። መንገድ አሳዩኝ ሕይወት አስተማሩኝ። የተፈረደብኝ ጊዜዬ ሲያበቃ ከወይኒ ቤት ወደ ጎባ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ሄድኩ በዚያም ደገኛ አባት ተገናኘው የኖርኩባት የሾመችኝ ዓለም አስጠላችኝ። ከዚያ ወጥቼ ወደዚህ ወደ ማላውቀው መንደር መጣው። በዚህም መጠነኛ መከራ ገጠመኝ። በርሱ ግን የበለጠ ልፈልገው የወጣሁትን አገኘሁበት። ከዚህ የምሥጢር መንደር መድረሴም የሚመራኝ ፈጣሪዬ መሆኑን እርግጠኛ ሆንኩበት" አለው። ንፍታሌም ገራ ገባው። " የቀድሞ ስራዎ ምን ነበረ?" አለው። " አንቱታው ለኔ አይገባም አንተ በለኝ። ሌባ ነበርኩ። ሰርቃለው እታሰራለው። ስፈታ ተመልሼ እሰርቃለው"አለ ባሪያው ትናንቱን እያስታወሰ። "እዚህ ውስጥ ነው የሚኖሩት? እስቲ ድፍረት ካልሆነብኝ ስለራሶ ያውጉኝ" አለ ንፍታሌም። " ና አትቁም ታሪኩ ረጅም ነው። አረፍ በልና አወጋሀለው" አለ ባሪያው። ሁለቱም ከዋሻው ውስጥ ተቀምጠው እንደወዳጅ ያወጉ ጀመረ።
" ወይኔ ጉዴ ነው! እሺ የት ገባ ነው የሚባለው? ከኋላችን አልነበረንዴ? ምን ዋጠው የት ደረሰ?" እያለች ሰላም አጠገቧ ያለውን ሰው ንፍታሌምን የደበቀ ይመስል በጥያቄ ላይ ጥያቄ ታቀርብለታለች። አቤል የሰላም ያን ያክል ለንፍታሌም መጨነቅ አግባብ መስሎ ስላልታየው " ምንም አይሆንም አትጨነቂ። እርሱኮ ሕጻን አይደለም!" ሲላት " እርሱማ አዎ ግን በወንድሜና በእናቴ ምክንያት ነው ኢሄ የተፈጠረው። ምነው በቀረብኝ" እያለች ስትማረር " ሰላም ተረጋጊ እንጂ! ቢጠፋም ይጥፋአ! ምንድነው ራስሽን ማስጨነቅ! አንቺ እንዲጠፋ ይዘሽው አልወጣሽ" አላት አቤል ቀለል አድርጎ። ሰላም ግን ንግግሩ ንፍታሌምን የሚያፈቅረው ልቧን አነዋወጸውና "ምን ማለት ነው ይጥፋ ማለት? እርሱ ማለት ለኔ ምን እንደሆነ ታውቃለህ? ንፍታሌም አቅልለህ እንዳየኸው ለኔ ቀላል ጉዳዬ አይደለም! ለኔ ትርጉም አለው! እንዴት ይጥፋ ትለኛለህ እንደቀላል?" አለችው በስሜት በቁጣ ሆና። አቤል ሰላም በትክክል ለንፍታሌም ያላትን ከስሜቷ ተረዳ ከቃላቷ ሁሉን አወቀ። "ሰላም ይጥፋ ማለቴ እርሱ ትልቅ ሰው ነው ጠፍቶ አይቀርም። አሁን ነው ያጣነው እንጂ ይገኛል ለማለት ፈልጌ እንጂ እኔምኮ እንዳንቺው ወንድሜን በክፉ | 784 |
| 19 | አለ። " አይሰማም እንዴ? ምን ሆነሀል ነው የምልህ?" አለው ንፍታሌም። "ኧረ ሰላም ነው! ሰላም ሁን" ብሎ መልሶ ዘጋበት። " ሄሎ" ሲል ተዘግቷል። " ምን ሆኗል ኢሄ ልጅ!" ብሎ ስልኩን ለሰላም መለሰላት ተቀብላው መልሳ ደወለችበት አንስቶ " ኤውልህ ባንተም በርሷም ስልክ አትደውልብኝ። ቆንጆ የደስታ ጊዜ ይሁንላችሁ። በደንብ ተንከባከባት። ንፍታሌም የኔ እያልኩ ሳስብህ የኔ የሆነውን ልትወስድ ይሄን ያህል መደበቅና ከኔ መደበቅ መድከም አልነበረብህም። ለሁሉም ስላደረክልኝም ስላደረክብኝም በጣም አመሰግናለው" ብሎ መልሶ ስልኩን ሲዘጋ ሰላም የጨው ሀውልት ሆና ደንግጣ ፈዛ ቀረች።
ቀን 7:00 ሰዓት ሲሆን አራቱም ሁለት ሁለት ሆነው ሞተር ተሳፍረው ወደ አዋሽ ቆላቲ የሚያደርጉትን የሞተር ጉዞ አጠናቀው ከቤተክርስቲያኑ ወረድ ብሌ ካለው አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ጋር ወረዱ። መነኩሴው አረጋዊ አባትና ንፍታሌም በአንድ ሞተር አቤልና ሰላም በአንድ ሞተር የመጡ ሲሆን አቤል ደርሶ እስኪወርድ በጭንቀት ተከቦ ስለነበረ ከሞተሩ ላይ ሲወርድ በላብ ተነክሯል። ለሞተረኞቹ አቤል የርሱንና የሰላምን ንፍታሌም የርሱንና የመነኩሴውን ከፍለው ሞተረኞቹ ወዲያው ተፈተለኩ። ከአረጋዊው አባትና ከሰላም በቀር ንፍታሌምና አቤል ታይቶ የማይጠገበውን ድንቅ ተፈጥሮ ዓይናቸው ማየት እስከ ሚችልበት ድረስ አካባቢውን ዙሪያ ገባውን ተራራውን ደኑን ወንዙን የተዘራውን አረንጓዴ ሆኖ የሚታየውን ቡቃያ ፍራፍሬውን ሁሉን እየቃኙ ሰላምንና አረጋዊውን አባት ተከትለው በቅርብ ርቀት ተከትለው አብረው ይሄዳሉ። ድንገት ሲተያዩ ንፍታሌም በፍጹም ፈገግታ አቤልን ሲያየው አቤል ግን ተኮሳትሮ ግንባሩን ከስክሶበት ያየው ነበረ።ሰላምና መነኩሴው ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን ሲደርሱ ሰላም ከቦርሳዋ ነጠላ አውጥታ አመሳቅላ ስትለብስ መነኩሴው ተሳልመው ወደ ቅጥር ግቢው ገቡ። ሰላምም በሴቶች መሳለሚያ በኩል ለመሳለም ስታቀና ንፍታሌምና አቤልም ተሳልመው ወደ ውስጥ ገብተው አቤል በካህናት መሳለሚያ በኩል መነኩሴው ጸሎት እያደረሱ ባለበት አቅጣጫ ሄዶ ሲሳለም ንፍታሌም ደግሞ በወንዶች መሳለሚያ በኩል ተሳልሞ ጸሎት አድርሰው ሲጨርሱ ሰላም ቆማ ጠብቃቸው " ኑ በዚህ ጋር ወደ ቤት እንሄዳለን። ደርሳችሁ አንደኛችሁን ታርፋላችሁ" ስትል " አንደኛችንንማ ስንሞት ነው የምናርፈው" አሏት መነኩሴው እየተከተሏት። እነ መሪጌታ ቤት ጊቢ ሲገቡ "እዚህ ቤቶች!" እያሉ መነኩሴው እየተጣሩ መሪጌታ ወተው " ግቡ ማነው?" ሲሉ የልብ ወዳጃቸውን ሲያዩአቸው ዘለው ከቤት ወተው መሪጌታ ከመነኩሴው ጉልበት አጎንብሰው ከጃቸው መስቀል ተሳልመው በንፍቆት ሰላምታ ተለዋወጡ። አቤል መሪጌታን ሲያያቸው ደነገጠ። ከዚህ ቀደም ጎባ አቡነ ተክለሃይማኖት ያያቸው ሰው መሆናቸውን ባይጠራጠርም ገጽታቸው ግን ተለውጧል። የታደሱ መሰለው። ብዙ ሰዎች እንደ አቤል ሁሉ መሪጌታን በተለያየ ጊዜ ሲያዩአቸው በተለያየ የገጽታ ለውጥ ስለሚያዩአቸው እንዲህ ይላሉ።
ቀጥለው ንፍታሌምና አቤል በየተራ ከመሪጌታ እጅ መስቀል ተሳለሙና በስተመጨረሻ ሰላምን አሳልመዋት አቅፈው ሰላም ብለዋት ተከታትለው ወደ ውስጥ ገቡ። ሲገቡ አሌክሳንደር ከተቀመጠበት ተነሳና ተቀበላቸው። ወደ አረጋዊው መነኩሴ ተጠግቶ መስቀል ተሳለመና ሌሎቹን በየተራ ሲጨብጥ " ሊቁ ባለ ቅኔ ይኼን ነጭ ደግሞ ከየት ተገናኛቹ?" አሉ መነኩሴው። መሪጌታ " ከባልንጀሮቹ ጋር ለምርምር ከቀያችን መቶ እዚሁ የቀረ ደቀመዝሙር ነው" አሉ ፈገግ ብለው። ንፍታሌም ወዲያው አዲስ አበባ ከቤዛ ወንድም ጋር ከአንድ ሆቴል ውስጥ ያገኛቸውን ፈረንጆች አስታወሳቸው። ሲያወሩ በከፊል የሰማውን የኋሊት በሀሳብ ተመልሶ አስታወሰ። ከዚህም ፊቱ ካለ ሰው ብዙ ስለ አካባቢው እንደሚያገኝ አሰበ። ሰላም " ወዲያ እነርሱ እስኪጨዋወቱ ጉድጉድ ብላ ሻይ አፍልታ የጅ ውኋ አቀረበችና ሁሉም በአንድነት ለምሳ ቀረቡ። በልተው ተፈጽሞ ማዕዱ ተነስቶ አረጋዊው "ሊቁ ባለቤቶትስ?" አሉ። "አንድ ከውጭ የመጣ ልጄ ጠዋት በአንዳች ስሜት ተፈትልኮ ወደ ጫካው ሲሄድ እናቱም ተከትላው የወጣች ነው" አሉ ቀለል አድርገው። ሰላም ስትሰማ "በቃ ተጨዋወቱ አባዬ ወጥቼ ልያቸው" ብላ ስትወጣ " እኛም ከምንቀመጥ ወጣ እንላለን" አለ አቤል ወደ ንፍታሌም እያየ። እርሱም ላያሳፍረው ተነሳና ሶስቱም ተያይዘው ወደ ደኑ ወጡ። እያወሩ ከደኑ ገቡ። የሰላምን እናትና ወንድም ፍለጋ በአንድ እየሄዱ ንፍታሌም ከደኑ ውስጥ ወደ ኋላ ቀረና ጠፍተውበት በሌላ መንገድ ሲሄድ ከአንዲት ዋሻ ነገር ውስጥ የሳል ድምጽ ሰምቶ ወንዙን ተሻግሮ ወደ ዋሻው ገባ።
💠 ይቀጥላል 💠
💢💠 ታኅሳስ 16 2016 ዓ.ም ባሌ ሮቤ 💠💢 | 964 |
| 20 | 👤👤👤👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤👤👤👤
👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤
👤 ህቡዕ ገጽ 👤
💢💠 ከክፍል 169 የቀጠለ 💠💢
"እራሴን ፍለጋ እየሄድኩ ነው። እስከዛሬ ራሴን ሳላገኘው ብዙ ፈለኩ። አሁን ግን እራሴን ፍለጋ እየሄድኩ ነው። አባ ራሴን እንዳገኝ ይርዱኝ። ልከተልዎት?" አላቸው። ንፍታሌም ሄድ ብሎ ቆሞ ሲጠብቃቸው አቤል ጥቂት አውርተውት ተከተላቸው። ሶስቱም በአንድነት ወደ መነኻሪያ አቀኑ። ሰዓቱ ማለዳ 12 ሰዓት አቅራቢያ ነው። ቢኒያም ከእንቅልፉ እንደነቃ ስልኩን አንስቶ ለሰላም ደወለ። " ከቻልሽ ዛሬ ባገኝሽ!" አላት። " አልችልም መንገድ እየሄድኩ ነው" ብላው ስልኩን መልሶ ንፍታሌም ጋር ደወለ። " የት ነህ?" አለው። ንፍታሌም " መንገድ እየሄድኩ ነው ምን ያህል እንደምቆይ አላውቅም" አለው። ቢኒያም ንፍታሌምና ሰላም ግንኙነታቸው እንደጠረጠረው እንደሆነና ሁለቱም በምሥጢር ተያይዘው ወደ ሌላ ቦታ እየሄዱ መሆኑን ውስጡ ጠረጠረ። ሰላም ቤቷን ቆልፋ አባቷ ያሏትን ሰው ለማግኘት ወደ ተባለችበት አቀናች። ሮቤ መነኻሪያ ደርሳ ወደ ሀሮ ዱማል ከሚሄደው መኪና ጋር ቆማ እንዳለች አቤል ንፍታልምንና እኚያ ከእብዱ ጋር ያየቻቸውን አረጋዊ አባት ስታይ ክው ብላ ደርቃ ቀረች።
💢💠🌿 ክፍል 173 🌿💠💢
የምታየው ሁሉ እውነት አልመስል አላት። እኚያ አረጋዊ አባት እንዴት ከአባቴ ጋር ወዳጅ ሆኑ? ማናቸው? እሺ ንፍታሌምንስ የት ነው የሚያውቁት? የማርታ ወንድምስ ከየት ተገናኛቸው? የሚሉ ጥያቄዎች ውስጧን አነዋወጹት። ሰላም እንደምንግዜውም ረጅም ቀሚስ ለብሳ ከላይ ውኃማ መልክ ሻርብ አድርጋለች። ፈዛ ቆማ እያየቻቸው ሶስቱም አጠገቧ ደረሱ። አባቷ ያሏትን ሰው ከነንፍታሌም ጋር የምታየው መሆኑን ለማረጋገጥ አልቸገራትም አባቷ የነገሯትን ምልክት ሁሉ አገኘችባቸው። አረጋዊውን በግራና ቀኝ አጅበው የሚሄዱት ወጣቶች አንደኛው እንደራሱ የሚወዳት ሌላኛው ደግሞ እንደራሷ የምትወደው ናቸው። ሰላም ንፍታሌምን ገና ስታየው ነው የልቧ ምት የጨመረው። አጠገቧ እስኪደርሱም አረጋዊውን ሊሸኙ የመጡ የመሰሏት አቤልና ንፍታሌም አረጋዊውን ሳይለዩአቸው ምነው በአንድነት በሄድን ብላ ተመኘች። አቤል ወደ ሀሮ መኪና ሲቃረቡ ከአረጋዊው አባትና ከንፍታሌም ቀድሞ በቅርብ ርቀት ሰላምን አያትና ያ ሊቆጣጠረው የማይችለው ስሜት ተቀሰቀሰበት ውስጡ ተዳፍኖ የጠፋ የመሰለው እሳት ፍም ተቀጣጠለ። መኪናው አጠገብ ሲደርሱ " ይኼ ነው መኪናው" አለ አቤል በጠቋሚ ጣቱ ወደ ቆመው የሀሮ መኪና እያመለከተ። " አንድ አብራን የምትሄድ ልጅም አለች" አሉ አረጋዊው። ንፍታሌም ቀበል አድርጎ " እንዴት ነው የምናገኛት ታዲያ መታ ይሆን እንዴ?" ሲጠይቃቸው አቤልና ሰላም ዓይን ለዓይን ተገጣጠሙና ሰላም ቀድማ " ሰላም እንዴት አደራችሁ!" ብላ ወደነርሱ ስትቀርብ አቤል ፍርሀት ጉልበቱን አዛለው አንደበቱ ተሳሰረ። ንፍታሌም ዞሮ ሲያይ ሰላም ነች። " እግዚአብሔር ይመስገን ሰላም አደርሽ!"አለ ፈገግ ብሎ። የንፍታሌም ፈገግታ ቶሎ ምላሽ መስጠት ግን አቤልን ሰላም ነሳው ሳያውቅ ተረበሸ። አረጋዊው አባት ዘወር ብለው አዩአትና "ሰላም አደርሽ የኔ ልጅ! የመሪጌታ ልጅ ነሽ?" አሏት። " አዎ ነኝ አባ ይፍቱኝ!" ብላ መስቀል ከጃቸው ተሳልማ "መኪናው ይኼ ነው እንግባ!" ስትላቸው አረጋዊው አባት " ኑ ልጆች" ብለው አራቱም ተከታትለው ገቡ። ሲገቡ መኪናው ሞልቷል ከኋላ የሁለት ሰው ቦታ የቀረ ሲሆን ከንድ ተጓዥ ደግሞ ከፊትለፊት በመውረዱ አረጋዊው አባት እርሱ ከተነሳበት ሲቀመጡ ንፍታሌም ቀድሞ ወደ ኋላ አመራ። ሰላምም ተከተለችው። ኋላ ከመጨረሻው ወንበር ንፍታሌም ቀድሞ ተቀመጠ። " አቤል ና እዚጋ ተቀመጥ የአንድ ሰው ቦታ አለ" ስትለው አቤል አሻፈረኝ ብሎ ቆመ። ሰላም ንፍታሌም አጠገብ ተቀመጠች። በዚህም ከጋጣሚ ደስተኛ ነበረች። ምንም ይሁን ምን ከምትወደው ሰው ጋር ያን ረጅም ሰዓት አብራው መጓዝ በራሱ ወደር የሌለው ደስታ ይሰጣታል። "ተመቸህ?" አለችው ሰላም " አዎ ተመችቶኛል" ንፍታሌም መለሰላት። " ወዴት እየሄዳችሁ ነው? ከርሳቸው ጋር ልትሰነብቱ ነው ሁለታችሁም?" አለችው። ንፍታሌም " እርሳቸው ከሚሄዱበት እንደ አምላክ ፈቃድ እንግዲህ........አንቺስ ወዴት እየሄድሽ ነው?" መልሶ ጠየቃት። " እርሳቸውን ከወዳጃቸው አገናኝቼ ልመለስ ታዝዤ ነው ለዚያ የተገናኘነው" አለችው። እያወሩ የመኪናው ረዳት ትኬት መቁረጥ ሲጀምር አቤል ወደ ፊት ጠጋ ብሎ የአራት ሰው ከፍሎ ወደ ነበረበት ተመለሰ። ገንዘብ ሰብስቦ ረዳቱ ሲጨርስ መኪናው ከመነኻሪያ ወዲያው ወጣና ጉዞ ጀመረ።
ጠዋት 2:00 ሲሆን ዶ/ር ቢኒያም በቀጥታ ውስጡን የሚያውከውን ሀሳብ መፍትሄ ሊያበጅለት ወደነ ኤርምያስ መጣና እንደደረሰ የውጪውን በር ማንኳኳት ያዘ። ከጊቢው አዲስ ተከራይታ የገባች አንዲት ጠይም ወጣት በሩን ከፍታ " አቤት!" ስትለው " ደና አደርሽ የኔ እህት! ሰላምን አገኛታለው?" ሲላት " ጠዋት ቦርሳዋን ይዛ መንገድ ልሄድ ነው ብላኝ ወጣች። ቤተሰቦቿ ጋር ሄዳለች" ስትለው " እርግጠኛ ነሽ ቤተሰቦቿ ጋር ነው የሄደችው?" ጠየቃት። " አዎ እንደዚያ ነው ያለችኝ" አለችው። ቢኒያም አመስግኖ ወደ መጣበት ተመለሰ። ውስጡ ምንም ማመን አልቻለም ከኪሱ ስልክ አውጥቶ ሰላም ላይ ደወለባት። ስልኳ አይነሳም። ደጋግሞ ደወለ ግን አይነሳም። በጣም ተናደደ። ቀጥሎ ንፍታሌም ላይ ደወለበት። " ሄሎ ዶ/ር ቢኒያም ሰላም ለርሶ!" አለ ንፍታሌም። " ያክብርልኝ! አክብሮቱ ይቆየኝ። የት ነህ?" አለው። " መኪና ውስጥ ነኝ መንገድ እየሄድኩ። ምነው በሰላም?" ጠየቀው። " የምትሄድበት ሀገር ስም የለውም?" አለው ቆጣ ብሎ። " ምነው ተናደሀል እንዴ? ወደ ቆላ እየሄድኩ ነው በዚህ በሀሮ በኩል። ምነው በሰላም ነው ፈለከኝ እንዴ?" መልሶ ጠየቀው። እያወሩ ስልክ ተዘጋ። ንፍታሌም መልሶ ሲደውል ስልኩ በቂ መደወያ ገንዘብ እንደሌለው ሲረዳ " እባክሽን ስልክ ተባበሪኝ ስልኬ ሳንቲም ጨርሳ...." ሲላት ሰላም ስልኳን ከቦርሳዋ ስታወጣ ብዙ ሚስኮል አየችና መልሳ ደወለች። " ሄሎ! ሰላም ደና ነሽ! ስልክ የማታነሺው በሰላም ነው? ነው ወይስ መደወሌ..." ሳይጨርሰው " ኧረ በፍጹም ቦርሳዬ ውስጥ ሆና ድምጽ አልባ ( silent ) ነበረች። ይቅርታ ዶ/ር ቢኒያም" ስትል ንፍታሌም ደነገጠ። " ይሁን ለማንኛውም። እኔ የምልሽ ዛሬ አይመቸኝም አልሽኝ አይደል? መቼ ላግኝሽ የማወራሽ ነበረኝ። አሁን እየሄድሽ ነው?" አላት። " አዎ አሁን እየሄድኩ ነው መኪና ውስጥ ሆኜ ነው የማወራህ" አለችው። " ግን የት ነው የምትሄጂው?" ሲላት ሰላም " ሀሮ እየሄድኩ ነው" ስትለው ተናዶ መልስ ሳይሰጣት ስልኩን ዘጋ። ሰላም ስልኩ የተቋረጠ መስሏት ኋላ ልትደውልለት አስባ ንፍታሌም ስልክ ስለጠየቃት ስልኳን ሰጠችው። ተቀብሏት ለቢኒያም ደወለለት። ስልኩ አይነሳም። ደግሞ ደወለለት። " ሄሎ ሰላም በቃ ተይው ከእንግዲ ማስተካከል ያለብኝን እኔ እራሴ አስተካክላለው። አሁን ጥሩ ስሜት ላይ ስላልሆንኩ ማውራት አልፈልግም። ደና ሁኚ" ሲል ንፍታሌም ሳቅ ብሎ " እንዴ ምን ሆነህ ነው? ሰሜትህን የሚረብሽ ምን ችግር ተፈጠረ?" ሲጠይቀው ቢኒያም ስልኩን ከጆሮው አንስቶ በዓይኑ ሲያይ የሰላም ስልክ ቁጥር ነው። የሚያወራው ንፍታሌም መሆኑን ማመን አቃተውና ወደ ጆሮው መልሶ " ሄሎ" | 791 |
