fa
Feedback
EMK Channel

EMK Channel

رفتن به کانال در Telegram

News, Politics, Jobs, Religion and Education

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
3 954
مشترکین
-224 ساعت
-147 روز
-8930 روز
آرشیو پست ها
#OLF የሀገር ሰላምና የዜጎች ደህንነት ሊረጋገጥ የሚችለዉ ሁሉም ወገኖች ለሁለንተናዊ መፍትሄ ተግተዉ ስሰሩ ብቻ ነው! (የኦነግ መግለጫ - የካቲት 14, 2012) የክስተቱን መንስዔና አጠቃላይ ምን
#OLF የሀገር ሰላምና የዜጎች ደህንነት ሊረጋገጥ የሚችለዉ ሁሉም ወገኖች ለሁለንተናዊ መፍትሄ ተግተዉ ስሰሩ ብቻ ነው! (የኦነግ መግለጫ - የካቲት 14, 2012) የክስተቱን መንስዔና አጠቃላይ ምንነቱን አስመልክቶ እስካሁን በቂ ግንዛቤና መረጃ ባይኖረንም እንኳ በትናንትናዉ ዕለት (የካቲት 13, 2012) በቡራዩ ከተማ የተፈጸመዉንና የኮሚሽኔር ሰለሞን ታደሰ ሕይወት የጠፋበትን ግድያና የአካል ጉዳት ያደረሰዉን ጥቃት በጽኑ እናወግዛለን። በጠፋዉ ሕይወትና በደረሰዉ አካላዊ ጉዳት ለተጎዱትም የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለጽን ለተጎጂ ቤተሰቦችና ጓደኞች ሁሉ መጽናናቱን እንመኛለን። በእንዲህ መሰሉ ጥቃትም ይሁን በሌላ በምንም መልኩ የተወሰኑ ግለሰቦችንና ቡድኖችን ዒላማ አድርጎ የሚፈጸሙ ጥቃቶችና አላስፈላጊ ጫናዎች የሀገሪቱን ችግሮች ይበልጥ ያባብሱና ያወሳስቡ እንደሆነ እንጂ ዘላቂ መፍትሄ ያመጣሉ ብለንም አናምንም። በመላ ሀገሪቱ በተለያዩ መንገዶች እየታዩ ላሉት የፖለቲካና የደህንነት ችግሮች ሁሉ ሰላማዊና ዘላቂ መፍትሄ ለማፈላለግ መንግሥት ከፍተኛዉን ድርሻና ኃላፍነት እንዳለዉ ይታወቃል። የዚህች ሀገር የፖለቲካ ኃይሎች ሁሉም ይህንን አስመልክቶ የድርሻቸዉን ለመወጣት ግዴታ አለባቸዉ። ሰፊዉ ሕዝብም እንደ ሀገርም ሆነ እንደ ሕዝብ የተጋረጡብንን ችግሮች በተመለከተ የችግሮቹን መንስዔና መፍትሄያቸዉን ለይቶ ያሉብን ችግሮች ለዘለቄታዉ መፍትሄ በሚያገኙበት አቅጣጫ ላይ የበኩሉን እገዛ ለማድረግ በንቃት መንቀሳቀስ አስፈላጊ ነዉ ብለን እናምናለን። More https://telegra.ph/OLF-02-22

ጀዋር መሀመድ በAhadu TV ከተናገራቸው በጥቂቱ! ❤💚❤ ❤💚❤ ❤💚❤ 👉እዚህ ሀገር ምርጫው ላይ ችግር ከተፈጠረ ችግሩ ከህዝብ በኩል ከተቃዋሚ በኩልም አይሆንም። ችግር ከተፈጠረም እራሱ ገዢው
ጀዋር መሀመድ በAhadu TV ከተናገራቸው በጥቂቱ! ❤💚❤ ❤💚❤ ❤💚❤ 👉እዚህ ሀገር ምርጫው ላይ ችግር ከተፈጠረ ችግሩ ከህዝብ በኩል ከተቃዋሚ በኩልም አይሆንም። ችግር ከተፈጠረም እራሱ ገዢው ፖርቲ ብቻ ነው የሚሆነው። 👉ብሄርተኝነት ጠነከረ ብለን ደንብረን ወደ ማፈን የምንሄድ ከሆነ አደጋ ውስጥ ነው የምንገባው። 👉የአብይ ትልቁ ውድቀት እና ድክመት የፖለቲካ መህዳሩን ከፍቶ ፤ ምህዳሩን ሊዳኝ የሚችል ህግና ህግጋት ማስረፅ እና የሊዕቃን ስምምነት መፍጠር አልቻለም። 👉ኦነግ እና ኦፌኮ ምንም የአላማ ልዩነት የላቸውም። ድሮም ቢሆን ልዩነታቸው የትግል መስመራቸው ነው የነበረው። ኦነግ በጠመንጃ ይፋለማል።ኦፊኮ ሀገር ውስጥ ተቃዋሚ ሆኖ ይፋለማል። 👉ምንም አይነት የተከፋፋለ ቄሮ የለም። ምናልባት መረዳት ያልቻሉ ሊመስላቸው ይችላል። አሁን ላይ ባለው የኦሮሞ ብሄርተኝነት ኦሮሞን መጥቶ ለመከፋፈል የሚሞክር ማንኛውንም አካል እራሱን እዛው ነው ያሚያጠፋው። የኦሮሞ ብሔርተኝነት ከ50 አመት በላይ በነ ማሞ መዘመር በነ ኃይሌፊዳ ተቀጥቅጦ የበሰለ ብሔርተኝነት ነው።ማንም ሊከፋፍለው፣ ሊያጠፋው ፣ ሊያፍነገው ቀርቶ ከቦታው ሊነቀንቀው አይችልም። 👉ብሔርተኝነት almost and always የጭቆና ውጤት ነው። ብሔርተኝነን ማፈን አይቻልም። ማኔጅ ማድረግ ግን ይቻላል።ላፍነው ካልክ ግን ይፈነዳል።

photo content

ቻይና ውሃን የሚገኙ የቲክቫህ ቤተሰቦች፦ እኛ ጥያቄያችን ገንዘብ ሳይሆን ወደሀገራችን መመለስ ነው፤ እኛ ገንዘብ አንፈልግም መንግስት ዜጎቻችን ናችሁ የሚለን ከሆነ በአስቸኳይ ወደሀገራችን ይመልሰን ሲ
ቻይና ውሃን የሚገኙ የቲክቫህ ቤተሰቦች፦ እኛ ጥያቄያችን ገንዘብ ሳይሆን ወደሀገራችን መመለስ ነው፤ እኛ ገንዘብ አንፈልግም መንግስት ዜጎቻችን ናችሁ የሚለን ከሆነ በአስቸኳይ ወደሀገራችን ይመልሰን ሲሉ እየጠየቁ ነው። ባለፉት ሳምንታት በተደጋጋሚ ጥያቄያችንን እያቀረብን ቢሆንም መፍትሄ አልተገኘልንም ብለዋል።

#BURAYUU ዛሬ ማምሻውን በቡራዩ በነበረ የሆቴል ምርቃ ላይ የተገኙ ሰዎች በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ድብደባ ተፈፅሞባቸዋል ተብሏል። በፀጥታ ኃይሎች ድብደባ ከተፈፀመባቸው ሰዎች መካከል እውቋ አር
+2
#BURAYUU ዛሬ ማምሻውን በቡራዩ በነበረ የሆቴል ምርቃ ላይ የተገኙ ሰዎች በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ድብደባ ተፈፅሞባቸዋል ተብሏል። በፀጥታ ኃይሎች ድብደባ ከተፈፀመባቸው ሰዎች መካከል እውቋ አርቲስት ሀዊ ቀነኒ እና ሌሎች ይገኙበታል። አርቲስት ሀዊ በተፈፀመባት ድብደባ ሆስፒታል ገብታ የህክምና እርዳታ እየተደረገላት ነው። የፀጥታ ኃይሎች ድምፃዊ ደሳለኝ ቤከማ እና አርቲስት ልጅ ያሬድን በቁጥጥር አውለው ነበር የተባለ ሲሆን ከሰዓታት በፊት ልጅ ያሬድ መለቀቁን ሰምተናል። ልጅ ያሬድ በፌስቡክ ገፁ "ኦነግ ሸኔ ደጋፊ ነህ ተብዬ መሬት ላይ አከባለውኛል ጭስ ቦንብም ወርውረዋል!' ብሏል። በቡራዩ ከተማ ስለተፈጠረው ክስተት OMN [ኦ ኤም ኤን] ከከተማው ከንቲባ ምላሽ ለማግኘት ጥረት ቢያደርግም ሊሳካለት እንዳልቻለ አሳውቋል። በቡራዩ ከተማ የተፈጠረው ምንድነው? ለምን ሰዎች ተደበደቡ? ስለጉዳዩ የፖሊስ ምላሽ ምንድነው? ዘርዘር ያለና የመንግስት ምላሽ የተካተተበት መረጃ ስንመለከት እንድታነቡት እናደርጋለን።

#UPDATE - የሟቾች ቁጥር 1,491 ደርሷል - በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር 62,247 በኮሮና ቫይረስ [2019-nCoV] የሞቱ ሰዎች ቁጥር 1,491 የደረሰ ሲሆን 62,247 ሰዎች ደግሞ በቫይረሱ ተጠቅተዋል። ከበሽታው አገግመው ከሆስፒታል የወጡ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 7,099 መድረሳቸውን ተመልክተናል።

📖#የእለቱ_መልዕክት📖 ምሳሌ 3 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁵ በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ፤ ⁶ በመንገድህ ሁሉ እርሱን እወቅ፥ እርሱም ጎዳናህን ያቀናልሃል። Fak. 3 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁵ Garaa kee guutuu Waaqayyoon amanadhu, hubannaa ofii keetiitti hin hirkatin! ⁶ Karaa kee hundumaatti isa yaadi, innis daandii kee siif in qajeelcha. መጽሓፍ ምሳሌ 3 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁵ ብምሉእ ልብኻ ብእግዚኣብሄር ተኣመን፡ ኣብ ልቦናኻ ኣይትጸጋዕ። ⁶ ኣብ ኵሉ መገድኻ ንእኡ ሕሰብ፡ ንሱ ኸኣ ኣኻይዳኻ ኬቕንዕ እዩ።

"ቦታ ማስለቀቅ ተፈልጎ ከሆነስ ለምን በለሊት ይደረጋል? አስለቃሽ ጭስ እና ጥይት በብዛት ተወርውሯል፣ ሰዎችም ተጎድተዋል"--- የ22 አካባቢ ነዋሪዎች ካደረሱኝ መረጃ "ለአረንጓዴ ስፍራ ተብሎ የተተወ ስፍራ ላይ ፅላት ሳይገባበት ቤተ ክርስቲያን እንሰራን ነው ያሉት። ህግ ለማስከበር ሙከራ ሲደረግ የፖሊስ መኪና አቃጥለዋል"--- የቦሌ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ከነገሩኝ ሙሉ መረጃ ወደ ሁዋላ ላይ ይቀርባል! @eliasmeseret ⬆️ አቶ ጥላሁን ጨምረው እንዳሉት "ጉዳዩን ወረዳውም፣ ፖሊስም ከካህናት ጋር ሲወያይ ነበር። ነገር ግን እናነሳለን ብለው እድሜ ከማራዘም ውጪ ምንም አላደረጉም። ከሌላ ቦታ የመጡ ወጣቶች ነገሩን እንዲያባብሱት ተደርጓል። ከዛም የከተማው ፖሊስ እና የፌደራል ፖሊስ ህግ እንዲያስከብሩ ተደርጓል። በዚህ ወቅት የፖሊስ መኪና አቃጥለዋል።" "ለምን ቦታው ላይ የእምነት ተቋም መሰራት አይችልም?" ለሚለው ጥያቄዬ አቶ ጥላሁን ሲመልሱ "እዛው ጋር ቤተ ክርስቲያን አለ። ህጉም አይፈቅድም፣ ተገቢው ቦታም አይደለም" ብለዋል። "ለምን እርምጃው ለሊት ላይ ተደረገ?" ብዬ ለጠየቅኩት ሲመልሱ ደግሞ "እንደዚህ አይነት ስራዎች ብዙ ግዜ የሚሰሩት ማታ ላይ ነው። ቀን ላይ ከሆነ ቀውሱ ይበዛል። ከዚህ በፊት ሁለት ግዜ ቀን ላይ ተሞክሯል፣ አልሆነም። ሌላ ተአምር የለውም" ብለዋል። @eliasmeseret

"ከሱቅ ሱቅ እየዞሩ ለብልፅግና ፓርቲ መደገፊያ ብር አምጡ እያሉን ነው"--- የአዳማ ከተማ የንግድ ማህበረሰብ አባላት በስልክ ከነገሩኝ ከትናንት ጀምሮ በርካታ ተመሳሳይ መልእክቶች በስልክ እና በሶሻ
"ከሱቅ ሱቅ እየዞሩ ለብልፅግና ፓርቲ መደገፊያ ብር አምጡ እያሉን ነው"--- የአዳማ ከተማ የንግድ ማህበረሰብ አባላት በስልክ ከነገሩኝ ከትናንት ጀምሮ በርካታ ተመሳሳይ መልእክቶች በስልክ እና በሶሻል ሚድያ ገፆቼ እየደረሱኝ ነበር። እንዲህ ላቅርባቸው: - "እኔ እዚህ አዳማ ከተማ በተለምዶ አራዳ የሚባለው የገበያ ስፍራ ሱቅ አለኝ። ወደ ሰባት የሚጠጉ ሰዎች ከሱቅ ሱቅ እየዞሩ ለብልፅግና ፓርቲ መደገፊያ ብር አምጡ እያሉን ነው። ሰዎቹ ውስጥ የቀበሌ እና የፀጥታ አካላትም አሉበት። ግራ ገብቶናል።" - "እየተጠየቅን ያለነው ከ5,000- 30,000 ብር ነው። በዛ ላይ ብሩን የማትሰጡ ከሆነ ሱቃችሁን እናሽገዋለን ይላሉ። ጉዳዩ ህጋዊ ይሁን አይሁን የምናውቀው ነገር የለም። በዚህ ብሩን አስገቡ ብለው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቁጥር ሰጥተውን ሄደዋል።" - "ትላንትናና ዛሬን ጨምሮ እኛ ከተማ ላይ በቁጥር ወደ 7 የሚሆኑ ሰዎች በየሱቁ እየዞሩ በተለይ አራዳ ተብሎ በሚጠራዉ ስፍራ ላይ ለብልፅግና ፓርቲ 10,000 ብር ማስገባት አለባቹ፣ ያለበለዚያ አሁኑኑ ነው ሱቃችሁን የምናሽገዉ እንዲሁም ቀበሌ ስትመጡ ምንም አይነት መስተንግዶ አታገኙም እናዉቃችኋለን እያሉ ሰዎችን እያስለቀሱ ነው የሚገኙት። አሁንም መጥተዉ ነበር ሲያስጨንቁን ነበር። - "የሚገርመው የሰዉ ሱቅ ጋር ከመጡ በሁዋላ ውስጥ ድረስ ገብተዉ እቃህን አይተዉ 30,000 ድረስ እንድታስገባ ይነግሩሀል። ከፈለክ የሰዎቹን አካዉንት ልልክልህ እችላለሁ። እንደ ፓርቲ ግን ይህ ስራ አግባብ ነዉ ብለህ ታምናለህ?" - "እኔ እንኳን 10,000 ብር ላይጎዳኝ ይችላል። ችግሩ ግን መስጠትም ችግር ነው፣ እምቢ ማለቱም ችግር ነው። አሁን ብሩን ሰጥቼ ብር እንዳዋጣሁ መረጃው ሌላኛው ቡድን ጋር ቢደርስ እና ነገ ሱቄ ቢቃጠል ማን መልሶ ይሰራልኛል?"

📖#የእለቱ_መልዕክት📖 ምሳሌ 3 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁵ በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ፤ ⁶ በመንገድህ ሁሉ እርሱን እወቅ፥ እርሱም ጎዳናህን ያቀናልሃል። Fak. 3 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁵ Garaa kee guutuu Waaqayyoon amanadhu, hubannaa ofii keetiitti hin hirkatin! ⁶ Karaa kee hundumaatti isa yaadi, innis daandii kee siif in qajeelcha. መጽሓፍ ምሳሌ 3 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁵ ብምሉእ ልብኻ ብእግዚኣብሄር ተኣመን፡ ኣብ ልቦናኻ ኣይትጸጋዕ። ⁶ ኣብ ኵሉ መገድኻ ንእኡ ሕሰብ፡ ንሱ ኸኣ ኣኻይዳኻ ኬቕንዕ እዩ።

📖#የእለቱ_መልዕክት📖 “ክርስቶስም ደግሞ እንደ ወደዳችሁ ለእግዚአብሔርም የመዓዛ ሽታ የሚሆንን መባንና መሥዋዕትን አድርጎ ስለ እናንተ ራሱን አሳልፎ እንደ ሰጠ በፍቅር ተመላለሱ።” — ኤፌሶን 5፥2 “Kristos akkuma nu jaallate, isinis immoo jaalalatti jiraadhaa! Inni aarsaa fooliin isaa tolu, qalma Waaqayyoof dhi'aatus godhee nuuf jedhee of kenneera.” — Efe. 5:2 “ከምቲ ክርስቶስ ዘፍቀረኩም፡ ነፍሱውን መባእን መስዋእትን ገይሩ ንኣምላኽ ንምዑዝ ጨና በጃና ዘሕለፈ፡ ከምኡ ብፍቕሪ ተመላለሱ።” — ኤፌሶን 5፥2

የኦነግ መግለጫ፦ በኢትዮጵያ መንግስት እየተፈጸመ ያለዉ የሰብዓዊ መብት ረገጣ በነፃ እና ገለልተኛ አካል ምርመራ ልደረግበት ይገባል! ከምዕራብ ኦሮሚያ (የወለጋ ዞኖች) ቴሌፎንና ኢንተርኔትን የመሳሰሉ
የኦነግ መግለጫ፦ በኢትዮጵያ መንግስት እየተፈጸመ ያለዉ የሰብዓዊ መብት ረገጣ በነፃ እና ገለልተኛ አካል ምርመራ ልደረግበት ይገባል! ከምዕራብ ኦሮሚያ (የወለጋ ዞኖች) ቴሌፎንና ኢንተርኔትን የመሳሰሉት የመገናኛ አገልግሎቶች በመንግስት ከተቋረጡ 1 ወር ኣለፈ። ከዚህም የተነሳ የዕለት ተዕለት ክስተቶችን በጊዜዉ ከነበቂ መረጃ ጋር ማግኘት አዳጋች ብሆንም እንኳ የመንግስት ወታደሮችና ታጣቂዎች በሰላማዊ (ትጥቅ-ኣልባ) ዜጎች ላይ እያካሄዱ ባሉት ግድያ የሰዎች ህይወት እንደቅጠል እየረገፈ መሆኑ መተለያየ መንገድ እየተሰማ ነዉ። በተለይም በሁለት ዞኖች (ምዕራብ ወለጋ እና ቄሌም ወለጋ) ዉስጥ የኢትዮጵያ መንግስት ወታደሮች በሕዝቡ ላይ እየፈጸሙ ያሉትን ግድያና ጭፍጨፋ በቃላት መግለጽ እንኳን ይከብዳል። የሰብዓዊ መብት ጥሰትና የጦር ወንጀል የሚሉት ቃላቶችም በትክክልና በበቂ ሁኔታ ልገልጹት ኣይችሉም። በደቡብ ኦሮሚያ (በጉጂ ዞኖች) ያለዉ ሁኔታም እምብዛም ከዚህ የተለየ አይደለም። በዚህ መልኩ ከአንድ ዓመት በላይ በወታደራዊ አስተዳደር (ኮማንድ ፖስት) ሥር በሕዝቡ ላይ እየደረሰ ያለዉን እሮሮና ስቃይ በተለያዩ ጊዜያት ገልጸን መፍትሄ እንድፈለግለት ብንወተዉትም እስካሁን የሕዝባችን ኡኡታና ችግሩ ተገቢዉን ተሰሚነት ሊያገኝ አልቻለም። More https://telegra.ph/OLF-02-02

#UPDATE የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ ተወልደ ገብረማሪያም እና የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ሊያ ታደሰ ቫይረሱ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገባ የሚከናወነውን የመከላከል ስራን አስመልክተው በጋራ መግለጫ ሰጥተዋል። ትናንት ምሽት በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ የዓለም አቀፍ መንገደኞች መግቢያ እየተካሄደ ያለውን ክትትልና ቁጥጥርም ለጋዜጠኞች አሳይተዋል። አቶ ተወልደ ገብረማርያም በርካታ አየር መንገዶች ወደ ቻይና መብረር አቁመዋል እየተባለ ስለሚነሳው መረጃ ምንነት እንዲህ ሲሉ አብራርተዋል፦ "የዓለም የጤና ድርጅት ስጋቱ ዓለም አቀፍ መሆኑን ማረጋገጡን፣ በረራም ሆነ ጉዞ አለመከልከሉንና ይልቁንም መወሰድ ስላለባቸው ጥንቃቄዎች ዝርዝር ጉዳዮችን ማውጣቱን ገልጸው እነዚህን ጥንቃቄዎች ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመሆን እየሰራን ነው። አብዛኞቹ ታዋቂ አየር መንገዶች በረራቸውን ቀጥለዋል። የሲንጋፖር፣ የካትሄይ ፓስፊክ፣ የአውስትራሊያ፣ የታይላንድ፣ የኒውዚላንድ፣ የኢንዶኔዥያ፣ የኤምሬትና ኳታር አየር መንገዶች በረራ አላቋረጡም። አንዳንድ አየር መንገዶች ወደ ቻይና በረራ አቋርጠናል ሲሉ የጊዜ ገደብ አስቀምጠዋል ይህም የቻይና አዲስ ዓመት እየተከበረ በመሆኑ ነው።" [ENA]

#UPDATE በቻይና የኮሮና ቫይረስ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር 12,024 መድረሱን ለማወቅ ተችሏል። የሟቾች ቁጥር ዛሬ ጥዋት ከገለፅነው 259 ሰዎች ከፍ እንዳላለም ተመልክተናል።

Fuulii Facebook yeroof na rakkisa waan jiruf karaa yaadota haaraa jiran kara kana argatu

Bety ~ እርስዎ የሀይማኖት መምህር ሆነው ለምን ከፖለቲካ ሰዎች ጋር ያዝወትራሉ ይባላል መምህር ሀ/ሚካኤል ~"ፓርላማ ውስጥ ስንት እና ስንት ሻሽ ጠምጥሞ የተቀመጠ ቄስ በሞላበት ሀገር ውስጥ እንዴ
Bety ~ እርስዎ የሀይማኖት መምህር ሆነው ለምን ከፖለቲካ ሰዎች ጋር ያዝወትራሉ ይባላል መምህር ሀ/ሚካኤል ~"ፓርላማ ውስጥ ስንት እና ስንት ሻሽ ጠምጥሞ የተቀመጠ ቄስ በሞላበት ሀገር ውስጥ እንዴት እኔን ከፖለቲካ ሰዎች ጋር ተገኘህ ይሉኛል?... እኔ ኢዜማ አብንም ቢጋብዘኝ ተገኝቼ ስለእምነት ከመናገር ወደኃላ አልልም... ይሄንን ምረጡ ያንን ምረጡ እስካላልኩ ድረስ ችግር የለውም። መምህር ሀይለሚካኤል በLTV

በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ሻምቡ ከተማ ቁጥራቸው በወል ያልተገለፀ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር/ኦነግ/አባላት ታሰሩ ሲሉ ከቤተሰብ መካከል አስታውቀዋል። የሻምቡ ከተማ ፖሊስ በጫካ የሚገኙ ሸማቂዎች ጋር ግንኙነት አላቸው ብለን የጠረጠርነውን ነው ያሰርነው ሲል ገልጿል። በምዕራብ ሸዋ ጊንደበረት ወረዳም የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ /ኦፌኮ/ 24 አባላት ታሰሩ ሲሉ የፓርቲው ወጣቶች ሊግ ኃላፊ ገልፀዋል። [VOA]

ለኢትዮጵያ መንግስት ለሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ለኦሮሞ የፖለቲካ ድርጅቶች ለተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች ለሚዲያ ተቋማት ለታዋቂ አክቲቪስቶች --- ጉዳዩ: በወለጋ እየተፈጸመ ስላለው የንጹሐን ግድያ በዝርዝር ስለማሳወቅ ----- በርእሱ እንደተመለከተው የመከላከያ ሰራዊቱ "የኦነግ ሸኔ ሽፍቶችን አጠፋለሁ" በሚል ምክንያት በምዕራብ ኦሮሚያ ባሉት አራት የወለጋ ዞኖች (ምስራቅ ወለጋ፣ ምዕራብ ወለጋ፣ ቄለም ወለጋ እና ሆሮ ጉድሩ ወለጋ) በርካታ ንጹሐን የኦሮሞ ተወላጆችን ገድሏል። የተገደሉት ንጹሐን ብዛት በየወረዳው ተዘርዝሮ ሲታይ የሚከተለውን ይመስላል። አንፊሎ: 64 መንዲ: 10 ጉሊሶ: 8 ገንጂ: 13 ቢላ: 6 ላሎ አሳቢ: 4 ቤጊ: 8 ሀሩ: 1 ጊዳሚ: 13 ጂማ ሆሮ: 4 ቆንዳላ: 5 ባቦ: 1 ነጆ: 3 አይራ: 2 ቦጂ ጨቆርሳ: 3 ደምቢ ዶሎ: 4 በድምሩ= 148 --- ይህ ቁጥር እስከ አሁን ድረስ በተጨባጭ መረጃ የተደረሰበትን ብቻ ነው የሚያመለክተው። የግንኙነትና የትራንስፖርት መስመሮች ሙሉ በሙሉ ከተቆራረጠባቸው አካባቢዎች መረጃዎች ሲገኙ ቁጥሩ ሊጨምር እንደሚችል ይጠበቃል። እንዲህ ዓይነት ጭፍጨፋ የሚካሄደው የዓመቱ የኖቤል የሰላም ሽልማት አሸናፊ የሆኑት ሰው በሚመሯት ሀገር ነው። እንዲህ ዓይነት ጉድ የሚሰማው በለውጥና በብልጽግና ጉዞ ወደ ኢትዮጵያ ህዳሴ እንደርሳለን በሚባልባት ሀገር ነው። አራቱ የወለጋ ዞኖች እና በደቡብ ኦሮሚያ የሚገኙት ሁለቱ የጉጂ ዞኖች ከፓርላማው እና ከኦሮሚያ ክልል ምክር ቤት እውቅና ውጪ ከአመት በላይ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ስር ናቸው። በዚህ ጊዜ ውስጥ በስድስት ዞኖች የሚኖረው ህዝባችን በራሱ መሬት ላይ እንደ ባእድ እየተቆጠረ ብዙ ግድያና ጥፋት ተፈጽሞበታል። በዚህ አንድ ወር ውስጥ ግን በተለይም በወለጋ ዞኖች የሞባይል ስልክና የኢንተርኔት መስመር ሙሉ በሙሉ ተቆርጦ ህዝቡ እየተጨፈጨፈ ነው። ሰፊው የኦሮሞ ህዝብ ለሀገሪቱ ሰላምና መረጋጋት ሲል ነው ችግሩን በሆደ ሰፊነት የያዘው። አሁን ግን ጭካኔው እጅግ በጣም በዝቷል። ስለሆነም ህዝቡ እንደ ወያኔ ዘመን በቁጭት ተነሳስቶ የራሱን እርምጃ ከመውሰዱ በፊት የሚመለከታቸው አካላት ለችግሩ አፋጣኝ መፍትሔ እንዲሰጡት አጥብቀን እንጠይቃለን። --- # የሟቾቹን ዝርዝር ያገኘሁት ለሚ ቤኛ በኦሮምኛ ከለጠፈው ፖስት ነው። # ሼር አድርጋችሁ አስተላልፉት። # "share" godhaati waliif dabarsaa. # Please share it.. ----

Mootummaan diraamaa siyaasaan hojjedha jedhee waan #qoshaashaa keessa galeera. Diraamichi mootummuma nyaachuuf deema. Ummanni keenya qeyee isaarratti dhumaa jira. Sababa mootummaan kun hojii qoshaashaa keessa galteen barattoonni Oromoo naannoo amaaraa jiran gatii hin malle akka hin kaffalle yaaddoo qabna. Mootummaan sababanyaan kun balaa hamaa nutti fiduuf deemti. Ummanni keenya dammaqinaan waan hunda hordofuu qaba.

Guyyoota 23 asitti 👇👇👇👇 Dhiha Wallaggaa fi Qellem Wallaggaatti namootni rasaasa RIB'n dhuman Anfilloo: 64 Mandii: 10 Gullisoo: 8 Ganjii: 13 Biilaa: 6 Laaloo Assaabii: 4 Begii: 8 Haaruu: 1 Gidaamii: 13 Jimmaa Horroo: 4 Qondaala: 5 Baabboo: 1 Najjoo: 3 Aayira: 2 Boojjii Coqorsaa: 3 Dambidoolloo: 4 Walumaa galatti lubbuu #148 Hubachiisa 👉 odeessa argame qofaan malee, baay'inni uummata nagaa dhumee akka heddummatu odeeffanneerra. Dula Mulugeta Gute irraa