4 933
مشترکین
+424 ساعت
+97 روز
+330 روز
آرشیو پست ها
4 932
Repost from Leoul Zewelde
ቆላድባ ፤ አንዲት ፍየል ላይ የአላህ ስም ተፅፎ ...
[ ልዑል ዘወልደ ]
ጅግጅጋ ይመስለኛል ፥ አንዲት ፍየል ወጠጤ የአላህ ስም ተፅፎባት ተወለደች ። በፅሁፉ ጥርጣሬ ስለገባኝ ፥ የፍየሏ ሆድ ላይ የታተመውን አረቢኛ በፎቶ ወስጄ በአስተርጓሚ አሳየሁት ። ሲረጋገጥ ፥ በሐፍረት ሟሸሽኩ ። አይ ፈጣሪ ፥ መገለጫው ብዙ ! ሱብሀን አላህ አልኹ።
አንድ ግዜ እንዲሁ ፥ የጠፈር ሣይንቲስትና ሊቁ መጋቢ ሐዲሥ ሮዳስ በትምህርታቸው ፤ እመቤታችን በራዕይ አስራ ሁለት ላይ ጨረቃን ተጫምታለች ! ሲሉ ሰማሁና እፈር ሲለኝ ወጥቼ ጨረቃን አየኋት ። ያው እፍረት ገንዘቤ ነው ፤ እውነትም ልጇን አቅፋ በጨረቃ ላይ ትታያለች ፥ ክብሩን የሰማዩ ባለቤት ፈጣሪ ይውሰድ ።
ልጅ እያለን የመክሰስ ቂጣ ከታደልን ወዲያ የምናደርገው ድርጊት ነበር ። በጥርሳችን ቅርፅ በማውጣት ሆዳችን ከመግባት በተረፈው መጫወት ። የኔ ደሞ ይብሳል ፥ ቂጣ ቆርምሜ የማልሰራው አገርና አህጉር ካርታ አልነበረኝም ። የሚገርመኝ ፤ የጥበብ ስራዬን ለማመሳከር ለሰዎች ሳሳይ መልሳየው የሚሳሳት ሆኖ አላገኘውም ። ከምስክሩ በኋላ ታዲያ በራሴ በመደመም ውድ ሥራዬን መብላት ያሳሳኛል ።
መክሊቴን እያሳደግኹት የመጣሁት ፥ በግድ አጥና እየተባልኩ የግቢ በር በላዬ ላይ ሲቆለፍብኝ ግዜ ነው ። ከአሰልቺው ጥናት የሚያናጥበኝ ቅዱስ ምግባር ፥ በግድግዳና ኮርኒስ ላይ ፓተርን መፈለግ ሆነ ።
ከፊቴ ያለ አሸዋ ግርፍ ግድግዳ ላይ ከዚህ በፊት ያላየኋቸውን ግጥምጥሞሽ ፍለጋ በሰመመን እጠፋለሁ ። ጥንቸል ፣ የሊስትሮ እቃ ፥ ቀጭኔ ፣ እትዬ ወርቄ ፥ የበሪኪና ዋንጫ ፥ ኢትዮጵያ ( አፍሪካ ተገልብጣ ) ፥ ምሳ'ቃ ፥ ጥርስ ብሩሽ ፥ ሣይንስ ቲቸርን .... የማላገኘው ቁስና ግኝት አልነበረም ። ለጉድ እናውዘዋለሁ ።
አይምሮዬ እረፍት አልነበረውም ፤ ሲብስብኝ መንገድ ላይ ሁሉ በደመና ቅርፅ ደርዝ መስራት ጀመርኩ ። በዚህ ነገር አብረውኝ ያሉ ጓደኞቼና ወላጆቼ ለጉድ ተማረሩ ። ትንሽ የምትረዳኝና አብራ የምትዳረቀኝ በህሪያ ብቻ ናት ። በህሪያ አሳዳጊዬ እና የቤት ሰራተኛችን ናት ።
እየበሰልኩ ስመጣ ግን ፣ ይሄን ነገሬን ማስተዋል ጀመርኩ ። ሰዎች በውስጣችን ላልተጠየቅነው ጥያቄ መልስ ተሸክመን እንደምንዞር ። በምሳሌ ላስረዳ መሰለኝ ...
የቤት ኪራይ ክፍያ ቸግሮት አማቱ ቤት የገባ አዲስ ጎጆ ወጪ ነበር ። አንድ ፊት ብቻ በየሄደበት ሁሉ እየተደጋገመ ቢታየው ግዜ ፥ አዋቂ ሳይካትሪስት ጋር ይሄዳል ።
- እሺ ፥ ምንድነው ?
- ይኸውልህ ፥ ሁሉም ቦታ ላይ የሚታየኝ አንድ ፊት አለ !
- እንዴት ?
- በቃ ... ምንጣፍ ላይ ፣ ዳቦ ላይ ፣ ሶስት አይን ያለው ሶኬት ላይ ... ያን ፊት የላማየው ቦታ የለም !
- ይሄ እኮ የተለመደ በሽታ ማለቴ ብዥታ ነው ነው ። ፐሬዶልያ ይባላል ። በአንተ እድሜ ላይ ካሉ ሶስት ሰዎች ሁለቱ ይገጥማቸዋል ።
- ዶክተርዬ
- ወይ
- እነዛ ሁለቱ ሰዎች አማቻቸውን ነው የሚያዩት ?
- ምን ?!
- አይ ምንም ሃሃሃ
አብዛኛውን ግዜ የምናየውን አይደለም የምናስተውለው ፤ ከሱ ይልቅ ሁነትን በውስጣችን ከያዝነው እውነት ጋር እያመሳከርን ፥ እንቀበላለን ። ይህን የምናደርገው ሰልፍ እቲማችንን ለመጠበቅ ሲሆን እያደር ግን ወደ ምርቃና (*በኦሮምኛ confirmation bias ማለት ነው) ይመራል ።
ከያ ወዲህ አይምሯችን ተቃራኒ ሀሳቦችን ለማስተናገድ ክፍት አይሆንም ። የተለየ ሀሳብ ያላቸውን ሰዎች መጋፈጥ እንፈራለን ። በሶሻል ሚዲያ የምንከተለው የውስጥ ሀሳባችንን ቫሊዴት የሚያደርጉልንን ሰዎች ብቻ ይሆናል ። አካታችነትና ምክንያታዊት ይጎለናል ። በዚህ መጠቃቱ የሚብሰው በግትርነት የተለያዪ ሀሳቦችን ማሰባጠር ተስኖን ውሳኔዎችን ስናሳልፍ ነው ።
አንድ ግዜ ፥ ፓተርን በመፈለግ ባህሪዬ እንደሌላው ከማታገለኝ አሳዳጊዬ ከበህሪያ ጋር እየተከራከርን ነው ። እሷም ከኔ ተጋብቶባት ከኔው ብሳ ቁጭ አለች ። በስኒ ላይየቀረ ዳካ ሁሉ እያነበበች ፤ ትተነትን ገባች ። ይሄኔ ፥ እኔ በተቃራኒው መቆም ጀመርኩ ። የተሻለኝ ራሱ በዛው ቀጥዬበት ይመስለኛል ።
በዘይት የተጨማለቀ ሂጃቧን እያሳየቺኝ ፥ እስኪ እንካ አንበው አለቺኝ ። አይኗ በለቅሶ ቀልቷል ። ሂጃቧ ላይ ለደቂቃዎች አተኩሬ ከ"ላ" በስተቀር ምንም ፓተርን አልሰራልህ አለኝ ።
- እሺ ምንድነው በህሪያ ?
- አላህ ! ነው የሚለው
- ምን ?
- ሁለት ቀን ባልሰግድ አትሰግጂም ብሎ እያናገረኝ ነው ። ያረቢ አል-ረሕማን ፥ ባክህ ተዉሂዴ ያማረላት አርገኝ ።
- እንዴ...! ቆይ አላህ የምር መታየት ከፈለገ ለምን 120 ላይ አይመጣም ?
- እህ ! እኔ መች 120 የማየውን ነው ? በዛ የሚመጣው ፤ ቆሻሻዋን በሂጃቤ ቆሻሻ ይንገረኝ እንጂ ...
በህሪያ አሳዘነቺኝ ። በልጅ ልቤ ማፅናናት ግራ ገብቶኛል ። ትንሽ ቆይቼ የምትወደው ፕሮግራም ትዝ አለኝ ።
- እሺ የምር መገለጥ ከፈለገ ፥ ለምን በህብረ-ትርዒት ላይ አይመጣም ?
- ቢስሚላሂር አንተ ! ዘፈን እኮ ሀራም ነ ...
- ምን ?!
- ...እ...እ...እ... ፥ ሃሃሃ
4 932
Repost from Sost Kilo
It's been a long long time !
[ ል ዑ ል ፡ ዘ ወ ል ደ ]
ፅድ አናት ላይ የኮኮብ ዕድ ሳይ - በዝንፍ ቅርንጫፍ የተጥመለመለ ሲባጎ ብልጭ ድርግም ሲል - የሥጦታ ሙዳዮች ዙሪያው ሲቆለል - ዜማ ባየሩ ሲናኝ ፥
በዓመቱ ኦሜጋ ሁሉም ወደልጅነቱ ሲሰበሰብ - በቀለም ያሸበረቁ ሞሳዎች ተሰብስበው ሲዘምሩ - ኩርሽም ከረሜላዎች ከአፋቸው ሟሙቶ ሲወርድ - ህፃንነት ፍፅምና መሆኑን አምነው አዛውንቶች አሜን ሲሉ ፥
የበረዶ ጥጥ ብናኞችን አሳበው መላዕክት ሰብ'ን ሲስሙ - የከተማው ካቴድራሎች ስለግርግሙ ንጉሥ ብስራት ሲደውሉ - የተነጠፉ መንገዶች ሁሉ ወደቤት ሲወስዱ - በብልቃጥ የነበረ መንፈስ ተኖ ቤትን ሲሞላ ፥
የዛፉ ላይ ድቡል ኳሶች እየተብረቀረቁ ሲወዛወዙ - ቀያይ ሻማዎች ግለው የቤቱን ድባብ ሲለኩሱ - በቁር ቆፈን ውስጥ የነበሩ ጉንጮች ሲፈግጉ - ልጆቻቸው የታከቡላቸው እናቶች አይን እንደታጠበ ብርጭቆ ሲብለጨልጭ - ሳቆች ተርፈው ወለል ላይ ሲወዳድቁ ፥
በክፍት ልቦች ውስጥ የገባ ንዝረት መልሶ ሲፈስ - ፍልቅልቅ ብላቴኖች ጌታውን እንዳየ ውሻ ከግድግዳ ግድግዳ ሲዘሉ ። ምኞታቸውን ጦምረው የሚመጣውን ሽማግሌ በተስፋ ሲጠብቁ ፥
ቃጭል ያነገቱ አጋዘኖችን በየብስ ሠረገላ እየተጋለቡ ፥ በራማ ጋሪ እየከነፉ ሲመጡ - ጆንያ ተሸካሚው ሽማግሌ ሪዙን እየፈተለ ሲደውል - ቦቲውን እያማታ በየአጥቢያው ሆ'ሆይ ሲል …
ከአንቺ መሆን እመኛለሁ ። አድማስ ተሻግሮ የተኛ ልቤ ፥ ቀኑ ሲደርስ ጠብቆ ይቆሰቆሳል ። Carla Thomas ፥ እየዘፈነች ነው ፥
It's been a long long time ,
Cant' explain why you crossed my mind
I guess it's just to wish you ...
a merry Christmas ❄️
4 932
Listen to the most recent episode of sost kilo podcast: It's Christmas - ሽልም የኮኮብ ዕድ ሳይ •••https://anchor.fm/sostkilo/episodes/Its-Christmas-e1bt9ih 🎙️❄️
