FastMereja.com
رفتن به کانال در Telegram
نمایش بیشتر
📈 تحلیل کانال تلگرام FastMereja.com
کانال FastMereja.com (@fastmereja) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 48 827 مشترک است و جایگاه 3 622 را در دسته آموزش و رتبه 660 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 48 827 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 22 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -453 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -5 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 11.22% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 7.21% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 5 477 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 3 522 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 20 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
توضیحی برای کانال ارائه نشده است.
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 23 ژوئیه, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته آموزش تبدیل کردهاند.
48 827
مشترکین
-524 ساعت
-1237 روز
-45330 روز
آرشیو پست ها
48 828
ባማኮን ሪል እስቴት በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ አካባቢ የገነባውን ዘመናዊ አፓርታማ አስመረቀ!
#Fastmereja I ባማኮን ሪል እስቴት በቦሌ አዉሮፕላን ማረፊያ አካባቢ የገነባውንና ግንባታው ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀውን ዘመናዊ የመኖሪያ አፓርታማ ህንፃ በዛሬዉ እለት በይፋ መርቆ ለደንበኞቹ አስረከበ።
ፕሮጀክቱ በሀገሪቱ የታየውን ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጫና እና የህንጻ መገንቢያ ቁሳቁሶች ዋጋ ንረት ተቋቁሞ፣ በደንበኞች ላይ ምንም ዓይነት ተጨማሪ ክፍያ ሳይጠይቅ መረከቡ ተገልጿል።
የባማኮን ሪል እስቴት የሽያጭና ማርኬቲንግ ዋና ኦፊሰር አቶ ፍሬው በየነ በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደገለጹት፤ ህንፃው በአጠቃላይ 22 ሰፋፊ መኖሪያ ቤቶችን እና ተጨማሪ አንድ የፔንት ሃውስ (Penthouse) መኖሪያን ያካተተ መሆኑ ተገልጿል።
ህንፃው በየወለሉ (per floor) ሁለት አፓርታማዎችን ብቻ የያዘ ሲሆን፣ ይህም ቤቶቹ ሰፋፊ፣ ዘመናዊና ምቹ እንዲሆኑ ታስቦ የተገነባ መሆኑን ጠቁመዋል።
እንዲሁም በየወለሉ ላይ የሚገኙት “A” እና “B” የተሰኙት ቤቶች 206 እና 208 ካሬ ሜትር ስፋት ያላቸው ሲሆን፣ ለነዋሪዎች አስተማማኝ ፀጥታና ግላዊነትን (Privacy) የሚያጎናጽፉ የቅንጦት (Super Luxury) መኖሪያዎች መሆናቸው ተብራርቷል።
በተጨማሪም ቤቶቹ ዘመናዊ (Modern) እና የሀገር ውስጥ ባህላዊ ምግቦችን ለማዘጋጀት የሚረዳ (Traditional) ባለሁለት ኩሽናን ያካተቱ ሲሆን፣ ይህም የምግብ ሽታና ጭስ ወደ ሳሎን እንዳይሰራጭ ታስቦ የተሰራ ነው።
በሀገሪቱ የነበረው የገንዘብ ምንዛሬ ለውጥ (Devaluation)፣ የጦርነት ተፅዕኖ እና የነዳጅ ዋጋ መጨመር በህንፃ መገንቢያ ግብአቶች ላይ ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ ቢያስከትልም፤ ኩባንያው ደንበኞቹን ከተጨማሪ ክፍያ በጠበቀ መልኩ ቤቶቹን ማስረከብ መቻሉን የሥራ ኃላፊው ገልጸዋል።
በተጨማሪም ባማኮን በአጠቃላይ ስምንት እህት ኩባንያዎች ያሉት ሲሆን፣ እነዚህ ኩባንያዎች እርስ በርስ የሚደጋገፉበት ጠንካራ አቅም መኖሩ ሥራው ሳይስተጓጎል እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ እገዛ ማድረጉን ገልጸዋል።
“ህንፃው ወደ ሽያጭ ከመውጣቱ በፊት ከ80% እስከ 85% የሚሆነው ግንባታው ተጠናቆ እንደነበር የተጠቀሰ ሲሆን ይህም በደንበኞች ላይ ምንም አይነት የዋጋ ጭማሪ ሳይደረግ ሙሉ በሙሉ አጠናቀዉ (Fully Finished) ለማስረከብ መቻላቸዉንም ገልፀዋል።
ባማኮን ሪል እስቴት ከተቋቋመ ሰባት ዓመታት የሆነው ሲሆን፣ አሁን ያስረከበው ህንፃ አራተኛ ፕሮጀክቱ ነው። ዋናው እናት ኩባንያ የሆነው ባማኮን ኢንጂነሪንግ በአዲስ አበባ የባንክ ዲስትሪክት አካባቢ በርካታ ግዙፍ ህንፃዎችን በመገንባት የሚታወቅና በዘርፉ ከ23 ዓመታት በላይ ልምድ ያለው ታላቅ ኩባንያ መሆኑ ይታወቃል።
#ቢዝነስ
48 828
ትግራይ ክልል የ”አምባሳደር አሸንዳ” መዓረግ ነጠቀ
#FastMereja I የትግራይ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ትናንት በሰጠው ይፋዊ መግለጫ፣ በ2017 ዓ.ም የ”አምባሳደር አሸንዳ” ውድድር አሸናፊ በመሆን ማዕረጉን ተቀብላ የነበረችው ወ/ት ዜማ እምብዛ ከተሰጣት የክብር ማዕርግ መነሳቷን አስታውቋል። ቢሮው ውሳኔውን ያስተላለፈው ግለሰቧ የተጣለባትን ባህላዊ ኃላፊነት ወደ ጎን በመተው ለሕዝቡ እሴትና ክብር የማይመጥኑ ተግባራትን ፈጽማለች በሚል ክስ ነው።
እንደ ቢሮው መግለጫ መነሻ ከሆነ፣ ወ/ት ዜማ እምብዛ ከዚህ ቀደም ለፈጸመቻቸው ተመሳሳይ ጥፋቶች በእድሜዋና በቤተሰባዊ ምክክር ታይቶ፣ ይፋዊ ይቅርታ እንድትጠይቅና እንድትታረም ዕድል ተሰጥቷት ነበር። ይሁን እንጂ የተሰጣትን ዕድል ከመጠቀም ይልቅ የአሸንዳ ባህልን የማስተዋወቅ ኃላፊነቷን ወደ ጎን በመተው፣ የአሸንዳ በዓልን “አሸንዳ ኢትዮጵያ” በሚል መጠሪያ የማስተዋወቅ ሥራ መጀመሯንና ይህ ተግባር ደግሞ የሕዝቡን ባህላዊ እሴቶች እንደማይወክል ቢሮው በክሱ ላይ አመልክቷል።
በዚህም ምክንያት የተጣለባትን ትልቅ አደራና ኃላፊነት ባለመወጣቷ እንዲሁም ከባህሉ መርሆዎች ውጪ በመንቀሳቀሷ፣ የተሰጣት የ”አምባሳደር አሸንዳ” ማዕርግ ከሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በይፋ መነጠቁን የትግራይ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ለሕዝብ ይፋ አድርጓል።
48 828
🎞 የፊልም ባለሙያ መሆን ለምትፈልጉ ምርጥ ዕድል!!!
🎥 በልቀት ኮሌጅ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ የፊልም ባለሙያዎች ልዩ የአጭር ጊዜ የፊልም ጥበብ ስልጠና ለመስጠት ተዘጋጅተዋል፤
✍ አሰልጣኞች
👉 ደራሲና አዘጋጅ መዓዛ ወርቁ
👉 የፊልም ዳይሬክተር እና ደራሲ ብሩክ ሞላ፤
👉 ዳይሬክተር አብርሀም ገዛኸኝ፤
👉 ሲኒማቶግራፈር ዳንኤል ግርማ፤
🎞 የስልጠና አይነቶች
👉 የፊልም አክቲንግ
👉 ዳይሬክቲንግ
👉 ሲኒማቶግራፊ
👉 በፊልም ጽሑፍ አጻጻፍ
🗓 የምዝገባ ቀን ሐምሌ10/2018 ያበቃል
ስልጠናው ከሀምሌ 11/2018 ጀምሮ ቅዳሜና እሁድ በቀን መርሐ -ግብር ይሰጣል።
💡ለምዝገባ
አራት ኪሎ ከትምህርት ሚኒስቴር ጀርባ ኢክላስ ህንፃ 3ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው የኮሌጁ ሬጅስትራር ጽ/ቤት በመምጣት መመዝገብ ይችላሉ።
📱 ለበለጠ መረጃ
2519 84 71 71 44/251940 08 99 99 /251930325090 መደወል ይችላሉ።
በተጨማሪም በቴሌግራም
@Liketcollege መመዝገብ ይችላል።
48 828
Atleet Ganzabee Dibaabaa Gara Seektara Riil Isteetii Makamte.
#FastMereja I Atleet Ganzabee Dibaabaa milkaa’ina damee ispoortiitiin goonfatte gargaaramuun, damee daldala riil isteetii Itoophiyaa keessatti saffisaan guddachaa jiru keessatti investimantii haaraa jalqabuu ishee Fast Merejan dhaga’eera.
48 828
" በደሞዝተኞች ላይ የሚጣለው ግብር ሊሻሻል ይገባል " - ፕራግማ ካፒታል
ደሞዝተኛው ማህበረሰብ ከከፍተኛ የኑሮ ውድነት ጋር ተያይዞ የሚደርስበትን የኢኮኖሚ ጫና ለመቀነስ፣ መንግስት በደሞዝ ላይ የሚጥለውን የግብር መጠን ሊያሻሽል እንደሚገባ ፕራግማ ካፒታል የተሰኘው ድርጅት ገለጸ።
ድርጅቱ፣ ኢትዮጵያ ከምስራቅ አፍሪካ ሀገራት መካከል በደሞዝተኞች ላይ ከፍተኛ ግብር የምትጥል ሀገር መሆኗን አመልክቷል።
ከፍተኛ የኑሮ ውድነትና የዋጋ ግሽበት ከግብር ጫናው ጋር ተዳምሮ በደሞዝተኞች ላይ ከባድ የኢኮኖሚ ጫና እየፈጠረ መሆኑን የገለጰው ድርጅቱ፣ መንግሥት የደሞዝ ግብር ስርዓቱን ሊያሻሽለው እንደሚገባ ጠቁሟል።
መረጃው የኢትዮኤፍኤም ነው
48 828
የ1 ሚሊዮን ብር ሽልማት የሚያስገኘው የቤላ ስፖርት የክረምት የፉትሳል ውድድር ቅዳሜ ይጀመራል
#FastMereja I የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ከቤላ ስፖርት ትጥቅ አምራች ድርጅት ጋር በመተባበር የሚያዘጋጁትና አሸናፊውን ቡድን የ1 ሚሊዮን ብር ባለቤት የሚያደርገው 2ኛው ዙር የቤላ ስፖርት የክረምት የፉትሳል ውድድር በሚመጣው ቅዳሜ በይፋ እንደሚጀመር በጋዜጣዊ መግለጫ ተገለጸ።
ከሐምሌ 11 እስከ ነሐሴ 11 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በጨፌ ሜዳ ለአንድ ወር በሚቆየው በዚህ ውድድር ላይ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ፣ በከፍተኛ ሊግ እና በሱፐር ሊግ የሚሳተፉ ተጨዋቾች ይሳተፋሉ።
ሁለቱ አካላት ውድድሩን በጋራ ለማዘጋጀት የሚያስችል የሁለትዮሽ ስምምነት የተፈራረሙ ሲሆን፣ ዝግጅቱ ክለቦች አዲሱ የውድድር ዘመን ከመጀመሩ በፊት አቋማቸውን ለመለካት ትልቅ ዕድል እንደሚፈጥርላቸው ታውቋል። ውድድሩን አሸናፊ ለሚሆን ቡድን ከተዘጋጀው 1 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ሽልማት በተጨማሪ፣ ለውድድሩ ኮከብ ተጫዋች፣ ኮከብ ግብ አግቢ እና ኮከብ በረኛ እያንዳንዳቸው የ20 ሺህ ብር የክብር ሽልማት እንደሚሰጣቸው ተገልጿል። #ኹነት
48 828
በአርቲስት መኮንን ላእከ የመኪና ስጦታ ዙሪያ ኮሚቴው ለዩቶፒያ ቴክኖሎጂ ጠንካራ ምላሽ ሰጠ
#FastMereja I ለአርቲስት መኮንን ላእከ በሕዝብ ፊት ቃል የተገባለትን መኪና በተመለከተ በዩቶፒያ ቴክኖሎጂ እና በአዘጋጅ ኮሚቴው መካከል ያለው አለመግባባት ወደ አዲስ ምዕራፍ ተሸጋግሯል። የአርቲስቱ የልደት አዘጋጅ ኮሚቴ ዛሬ ባወጣው ይፋዊ መግለጫ፣ አርቲስቱ እስካሁን መኪናውን እንዳልተረከበና ድርጅቱ ከተደረገው የመጀመሪያ መግባባት ውጪ አደገኛ የባንክ ብድርና የውክልና ግዴታዎችን በማምጣቱ ስጦታው ሳይሳካ መቅረቱን በዝርዝር አስታውቋል።
የኮሚቴው መግለጫ እንደሚያስረዳው፣ መጀመሪያ ላይ ዩቶፒያ ቴክኖሎጂ ለአርቲስቱ መኪና ለመስጠት ኮሚቴው የተወሰነ አስተዋጽኦ እንዲያደርግ በጠየቀው መሠረት ባለ 1 ሚሊዮን ብር ቅድመ ክፍያ በታዋቂው የማስታወቂያ ባለሙያ ዘላለም ኩራባቸው አማካኝነት ተዘጋጅቶ ነበር። ሆኖም ገንዘቡ ከተዘጋጀ በኋላ ድርጅቱን ለማግኘት ኮሚቴው ከአምስት ጊዜ በላይ በአካል ቢሮ ድረስ በመሄድ ጥረት ቢያደርግም ለረጅም ወራት ያገኘው ምላሽ እንዳልነበረ ገልጿል።
ከአምስት ወራት መዘግየት በኋላ ግን ድርጅቱ መኪናውን ለመስጠት አዲስ ሁኔታ ማቅረቡን ኮሚቴው ይፋ አድርጓል። የቀረበው አዲስ ሐሳብ መኪናው በአርቲስት መኮንን ስም በሚወሰድ የባንክ ብድር እንዲገዛ፣ አርቲስቱ ለድርጅቱ ሕጋዊ ውክልና እንዲሰጥ እና ድርጅቱ በተበደረው ገንዘብ እየሠራበት ዕዳውን እንዲከፍል የሚጠይቅ ነው። ይህ አዲስ አካሄድ አርቲስቱን በከፍተኛ ሕጋዊና ፋይናንሳዊ ኃላፊነት ውስጥ የሚጥል በመሆኑ በኮሚቴውና በአርቲስቱ በኩል ተቀባይነት ሳያገኝ ቀርቷል።
በልደት መድረኩ ላይ የተላለፈው መልዕክት “ዩቶፒያ ቴክኖሎጂ ለአርቲስት መኮንን ላእከ መኪና አበረከተ” የሚል እንጂ ስለ ባንክ ብድር ወይም ስለ ውክልና የተባለ ነገር እንዳልነበረ የጠቀሰው መግለጫው፣ ድርጅቱ የራሱን የማስታወቂያ ፍላጎት ካሳካ በኋላ ቃሉን ለመቀየር መሞከሩ ተገቢ እንዳልሆነ ገልጿል። አርቲስት መኮንን ላእከ በሰይፉ ሾው ላይ ቀርቦ መኪናውን እንዳልተረከበ መናገሩም እውነትን መግለጽ እንጂ ተቋሙን ለማጠላላት የተደረገ እንዳልሆነ ተብራርቷል። ኮሚቴው ከማብራሪያው ጋር በተያያዘ ድርጅቱ እንዲፈረም የጠየቀውን የውክልና ሰነድ ናሙና ለሕዝብ እይታ ያያዘ ሲሆን፣ በሕዝብ ፊት የተገባ ቃል በማስታወቂያ መሣሪያነት ብቻ ሳይሆን በታማኝነትና በተግባር ሊፈጸም እንደሚገባ አሳስቧል።
ፎቶ ፎከስ ስቱዲዮ
48 828
መንገደኞችን መልካም መንገድ በማለት ውሃ እና ቆሎ የሚሰጡት ሃላባዎች
#FastMereja | መነሻቸውን ወላይታ ሶዶ አድርገው መድረሻቸውን አዲስ አበባ ላደረጉ አሽከርካሪዎችና ተጓዦች በሃላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ የክብር አቀባበልና የውሃና ቆሎ ግብዣ እየተደረገላቸው ነው። ተጓዦቹ አዲሱን አማራጭ መንገድ መጠቀም መጀመራቸውን ተከትሎ የአካባቢው ማህበረሰብ የአቀባበል መርሃግብሩን አዘጋጅቷል።
አሽከርካሪዎችና ተጓዦች ከአዲስ አበባ ወደ ሃላባ፣ ወላይታና አካባቢው ለማቅናት የነበረውን ረጅም መንገድ በማሳጠር በሃላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ በኩል ያለውን የኮረኮንች (ፒስታ) መንገድ መጠቀም ጀምረዋል። ይህ አዲስ መንገድ ምንም እንኳን አስፓልት ባይኖረውም፣ በአሁኑ ወቅት እጅግ አጭር በመሆኑ ተመራጭ ሆኗል። ተጓዦቹ በዚሁ የፒስታ መንገድ አልፈው በስልጤ ዞን ሚቶ ወረዳ ከሚገኘው አስፓልት መንገድ ጋር በመቀላቀል ወደ አዲስ አበባ የሚያደርጉትን ጉዞ በስኬት እያካሄዱ ነው።
ይህንን አዲስ ጉዞ ምክንያት በማድረግ ሰላም ወዳዱ የሃላባ ማህበረሰብ ለአሽከርካሪዎችና ለተሳፋሪዎች “እንኳን በደህና መጣችሁ፣ ቀጣይ መንገዳችሁ የሰላም ይሁን” በማለት ሞቅ ያለ አቀባበል አድርጎላቸዋል። የአካባቢው ነዋሪዎች ይህ መንገድ ምንጊዜም ሰላማዊና ምቹ መሆኑን በመግለጽ የውሃና የቆሎ ግብዣ በማቅረብ ላይ ይገኛሉ።
ይህንን በስፍራው የተከናወነውን ህዝባዊ መስተንግዶና አዲስ የጉዞ መረጃ ለ”ፋስት መረጃ” ያደረሰን ናሙስ አባባ ነው።
48 828
ቪዚት ሩዋንዳ የአስቶን ቪላ ዋና ስፖንሰር ሆነ
#FastMereja I የአስቶን ቪላ የእግር ኳስ ክለብ ከ”ቪዚት ሩዋንዳ” (Visit Rwanda) ጋር በታሪኩ ትልቁ የተባለውን የይፋዊ ቱሪዝም፣ የቡና አቅራቢነት እና የፊት ለፊት ማሊያ ስፖንሰርሺፕ ስምምነት በዛሬው ዕለት በይፋ ተፈራርሟል።
ይህ አዲስ ስምምነት የቪዚት ሩዋንዳ አርማ በወንዶች፣ በሴቶች እና በታዳጊዎች (አካዳሚ) ቡድን ማሊያዎች ላይ እንዲሁም በተለያዩ የስታዲየም ስፍራዎች ላይ ጎልቶ እንዲታይ ያደርጋል። ሁለቱ ወገኖች ከቱሪዝም ማስተዋወቅ ባሻገር በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በስፖርታዊ ስልጠናዎች እና በበጎ አድራጎት ስራዎች ላይ በጋራ ለመስራት ተስማምተዋል።
የአስቶን ቪላ የቢዝነስ ኦፕሬሽን ፕሬዝዳንት ፍራንቼስኮ ካልቮ ስምምነቱን አስመልክተው ሲናገሩ፣ ይህ ጥምረት ክለቡ በአለም አቀፍ ገበያ ላይ እያደረገ ላለው መስፋፋት ማረጋገጫ መሆኑን ገልጸው፣ በቱሪዝም እና ስፖርታዊ ልማት ዙሪያ ትርጉም ያላቸው ስራዎችን ለመስራት መጓጓታቸውን አስታውቀዋል። በሌላ በኩል የሩዋንዳ ኮንቬንሽን ቢሮ ዋና ስራ አስፈጻሚ ጃኔት ካሬመራ፣ ስምምነቱ ሩዋንዳን የኢንቨስትመንት እና የቱሪዝም መዳረሻ አድርጎ ለማስተዋወቅ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ጠቁመው፣ በዩናይትድ ኪንግደም እና በአውሮፓ አዳዲስ ደንበኞችን ለመድረስ እንደሚያግዝ ገልጸዋል። ክለቡ አስቀድመው የ2026/27 የውድድር ዘመን ማሊያ የገዙ ደጋፊዎች የቪዚት ሩዋንዳን አርማ በነጻ ማሊያቸው ላይ ማስተከል እንደሚችሉ አስታውቋል።
48 828
በአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ የሴቶች የሰላም ፎረም ተካሄደ!
#Fastmereja:-በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም፣ እኩልነት እና ልማትን ለማምጣት የሴቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎ፣ አመራርእና የሰላም ትምህርት ወሳኝ መሆናቸው ተገለጸ።
ይህ የተባለው በአዲስ አበባ ኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል በተካሄደውና በርካታ ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈው “የኢትዮጵያ ሴት መሪዎች የሰላም ፎረም” (Ethiopian Women’s Leaders Peace Forum) ላይ ነዉ።
በሴቶች ዓለም አቀፍ የሰላም ቡድን (IWPG) እና በኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን ትብብር የተዘጋጀው ይህ ፎረም፣ “የሰላም ትምህርትን ማሳደግ፣ የሴቶች አመራር እና ዓለም አቀፍ አጋርነት” በሚል መሪ ቃል በይፋ ተከፍቷል።
የIWPG የልዑካን ቡድን በቅርቡ በቡሩንዲ፣ በታንዛኒያ እና አሁን ደግሞ በኢትዮጵያ ያደረገውን ጉዞ አስመልክቶ ማብራሪያ የሰጠ ሲሆን፣ በጉዟቸው ያገኟቸው ማህበረሰቦች ሁሉ ዋነኛ ፍላጎት “ዘላቂ ሰላም” መሆኑን ገልጸዋል።
በፎረሙ ላይ የተገኙት የHWPL የኢትዮጵያ ቀጠና ስራ አስኪያጅ ፖል በበኩላቸው፣ ድርጅታቸው ከIWPG እና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN ECOSOC) ጋር በመሆን በኢትዮጵያና በአፍሪካ ህብረት ውስጥ በሰላም ዙሪያ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።
የሴቶች ፌዴሬሽን አመራር፣ የሴቶች ማህበር ከፌደራል እስከ ቀበሌ ድረስ የተዘረጋ ጠንካራ መዋቅር ያለው፣ ከ54 በላይ አባል ማህበራትን ያቀፈና ከ8.6 ሚሊዮን በላይ ሴቶችን የሚወክል ግዙፍ ተቋም መሆኑን ገልጸዋል።
ይህንን መዋቅር በመጠቀምም ሴቶች በሀገሪቱ የሰላም ግንባታ እና ልማት ውስጥ ያላቸውን ቁልፍ ሚና ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
ሰላም በድንገት የሚመጣ ሳይሆን በእያንዳንዱ ሰው ጥቃቅን ጥረቶች የሚገነባ መሆኑን ተጠቅሶ፤ ሴቶች የሰላም ተጠቃሚዎች ብቻ ሳይሆኑ ሰላምን የሚፈጥሩ መሪዎች መሆናቸውን እና በአንድ ሴት ላይ የሚመጣ በጎ ለውጥ ቤተሰብን፣ ማህበረሰብን አልፎም ቀጣዩን ትውልድ እንደሚቀይር አስረድተዋል።
በፎረሙ ላይ የቀረበው ሌላው ቁልፍ መልዕክት ዘላቂ ሰላም በአንድ ተቋም ወይም ግለሰብ ጥረት ብቻ ሊረጋገጥ እንደማይችል ነው። ይልቁንም ከመንግስት፣ ከትምህርት ተቋማት (አካዳሚ)፣ ከሲቪል ማህበረሰብ፣ ከሴቶች፣ ከወጣቶች እና ከሚዲያ ጋር በጋራ በመተባበር እንዲሁም በ”ሰላም ትምህርት” አማካኝነት እንደሚገነባ አጽንኦት ተሰጥቶበታል።
የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን ተወካይ ለዓለም አቀፍ የሴቶች የሰላም ቡድን (IWPG) ስላደረገው ድጋፍና አጋርነት ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን፣ ከቡድኑ ጋር የተጀመረው ትብብር ልምድ ለመለዋወጥ እና በቀጣይ በጋራ ለመስራት (በመግባቢያ ሰነድ ወይም Moሀ ጭምር በመደገፍ) ትልቅ በር የሚከፍት መሆኑን ጠቁመዋል።
48 828
የአርቲስት መኮንን ላዕከ የመኪና ውዝግብ
#FastMereja | ተወዳጁ አርቲስት መኮንን ላዕከ “ቃል የተገባልኝ መኪና እስካሁን አልደረሰኝም” በማለት ያቀረበው ቅሬታ በዩቶፒያ ቴክኖሎጂ በኩል ምላሽ ተሰጥቶበታል። አርቲስቱ በቅርቡ በሰይፉ በኢቢኤስ ፕሮግራም ላይ የ57 ዓመት ልደቱን ካከበረበት ጊዜ አንስቶ ቃል የተገባለትን መኪና እንዳልተረከበ በይፋ መናገሩን ተከትሎ፣ ኩባንያው ስምምነቱ ለምን እንደተቋረጠ ዝርዝር ማብራሪያ ሰጥቷል።
የአሁኑ ውዝግብ መነሻ የሆነው ከአስራ አንድ ወራት በፊት በዝምታ ሬስቶራንትና ላውንጅ በተደረገው የልደት በዓል እና የዳግም ሙሽርነት ስነ-ስርዓት ላይ ነው። በወቅቱ የዩቶፒያ ቴክኖሎጂ ማኔጂንግ ዳይሬክተር አቶ አዶኒክ ወርቁ እና የድርጅቱ አምባሳደር አርቲስት እንግዳሰው ሀብቴ በቦታው ተገኝተው፣ መኪናውን ለአርቲስቱ እንደሚያመቻቹ ቃል ገብተው ነበር።
ይሁን እንጂ የዩቶፒያ ቴክኖሎጂ ማኔጅመንት ባወጣው ይፋዊ መግለጫ፣ ጉዳዩ “ስጦታ” ሳይሆን በቅድመ-ሁኔታዎች ላይ የተመሰረተ ስምምነት እንደነበር አስታውቋል። ኩባንያው እንደገለጸው፣ ስምምነቱ የአርቲስቱን የብድር ሂደት ለመጨረስ የሚያስችል ህጋዊ ውክልና ማግኘት፣ ለመኪናው የሚያስፈልገውን ቅድመ-ክፍያ መፈጸም እና አርቲስቱ ለኩባንያው የማስተዋወቂያ ስራዎችን መስራት የሚሉ ግዴታዎችን ያካተተ ነበር።
ኩባንያው አክሎም፣ መኪናው ለአራት ወራት ያህል በሾውሩማቸው ውስጥ ተይዞ ቢቆይም፣ አርቲስቱ እና አዘጋጅ ኮሚቴው በተባሉት ቅድመ-ሁኔታዎች መሰረት አስፈላጊውን ህጋዊ እና የገንዘብ ግዴታዎች ባለመወጣታቸው ስምምነቱን ለመሰረዝ መገደዳቸውን ገልጿል። በሌላ በኩል ዩቶፒያ ቴክኖሎጂ አሁንም ለጥበብ ማህበረሰብ ያለውን አክብሮት በመግለጽ፣ በቀጣይ ለሚገባቸው አካላት ድጋፍ የማድረጉን ስራ እንደማያቋርጥ አስታውቋል።
ፎቶ ሲሳይ ጉዛይ
48 828
አህመድ ተሾመ (ዲንቢ) «ጊዜ አይገድም» የተሰኘውን 3ኛ አልበሙን ሊለቅ ነው!
#Fastmereja I ታዋቂው ድምፃዊና የዜማ ደራሲ አህመድ ተሾመ (ዲንቢ) «ጊዜ አይገድም» የተሰኘውን 3ኛ ሙሉ የሙዚቃ አልበሙን የፊታችን ሐምሌ 10 ቀን ለሕዝብ ይፋ እንደሚያደርግ በዛሬዉ እለት በተሰጠ መግለጫ ተገልጿል።
በናሆም ሪከርድስ (Nahom Records) አማካኝነት በተለያዩ የሙዚቃ ማሰራጫዎችና በዩቲዩብ የሚለቀቀው ይህ አልበም፣ በአጠቃላይ 13 ትራኮችን የያዘ ሲሆን የሀገር ፍቅርን፣ ማህበራዊ ህይወትንና ፍቅርን የሚዳስሱ ይዘቶች እንዳሉት ተገልጿል። አልበሙ «ጊዜ አይገድም» እና «ይረፍዳል» የሚሉ ተቃራኒ እውነታዎችን ያጣመረ ልዩ ፍልስፍናዊ ጭብጥም እንዳለዉ ነዉ የተገለፀዉ።
ይህ አልበም «ጊዜ አይገድም» (ወይም «ጊዜ አይሄድም») ከሚለው ሀሳብ በተጨማሪ «ጊዜ ይረፍዳል» የሚል ተያያዥ እውነታን ይዟል።
ይህም ተስፋ ላለው ሰው ጊዜ እንደማይሄድና ሁሌም ብርሃን እንዳለ የሚያሳይ ሲሆን፣ በሌላ በኩል ደግሞ ጊዜ የማይጠብቅ መሆኑንና «ይረፍዳል» የሚለውን ተቃራኒ የህይወት እውነታ በአንድ ላይ አጣምሮ የያዘ ልዩ ፍልስፍናዊ ስራ ስለመሆኑም ነዉ የተገለፀዉ።
በአልበሙ ዝግጅት ላይ ከፍተኛ ተሳትፎ ያደረገው ድምፃዊና የግጥም ደራሲ ካድር አሊ «እሳሳታለሁ» እና «ከፍ በል» የተሰኙ ሁለት ስራዎችን በግጥምና በድምፅ ያበረከተ ሲሆን፣ ስራው ዘመን ተሻጋሪና በጥራት የተሰራ መሆኑን ገልጿል።
አህመድ ተሾመ (ዲንቢ) ከዚህ ቀደም «እዮሪካ» እና «ኦሜርታ» የተሰኙ እጅግ ተወዳጅና ስኬታማ አልበሞችን ለአድማጮች ያበረከተ ሲሆን፤ «ዲንቢ ለዲንቢ»፣ «ተጠየቂ ናዝሬት»፣ «አውራአምባ»፣ «በትዝታው ፈረስ» እና «አይ መሬት ያለ ሰው» የተሰኙ በርካታ የራሱ ተወዳጅ ሙዚቃዎች አሉት።
ከዚህ ቀደም «እዮሪካ» እና «ኦሜርታ» የተሰኙ ተወዳጅ አልበሞችን ለአድማጮች ያበረከተው አህመድ ተሾመ (ዲንቢ)፤ ለማዲንጎ አፈወርቅ፣ ለፀሀዬ ዮሀንስ፣ ለብዙአየሁ ደምሴ እና ለዘቢባ ግርማ በርካታ ተወዳጅ ዜማዎችን በመስራት የሚታወቅ ስኬታማ ባለሙያ ነው።
#ኪነ_ጥበብ
48 828
የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የ100ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በታላቅ ድምቀት ሊያከብር ነው
#FastMereja I የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (EPHI) የተመሰረተበትን 100ኛ ዓመት የምስረታ በዓል አስመልክቶ ከሐምሌ 7/2018 ዓ.ም በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ የተለያዩ ዝግጅቶችን እያከናወነ እንደሚገኝ ተነግሯል። ኢንስቲትዩቱ የክፍለ ዘመኑን ጉዞ ለመዘከርና በጤናው ዘርፍ የተመዘገቡ አዳዲስ ምርምሮችን ለማቅረብ መዘጋጀቱን አስታውቋል።
የኢንስቲትዩቱ ይፋዊ መርሃ-ግብር እንደሚያሳየው፣ ዋናው በዓልና ሳይንሳዊ ጉባኤው ከሐምሌ 9 እስከ ሐምሌ 11/2018 ዓ.ም ባሉት ሶስት ተከታታይ ቀናት በልዩ ሁኔታ ይካሄዳል። በዓሉ የኢንስቲትዩቱን የ100 ዓመታት ጉዞ የሚያሳዩ ፎቶግራፎችና ቪዲዮዎች፣ የምስጋናና የእውቅና አሰጣጥ ስነ-ስርዓቶች እንዲሁም በጤናው ዘርፍ ተስፋ ሰጪ በሆኑ አዳዲስ ግኝቶች ላይ ያተኮሩ የጥናትና ምርምር ስራዎች የሚቀርቡበት መድረክ እንደሚሆን ተነግሯል።
#ኹነት
48 828
የኢትዮጵያ የሕዝብ ጤና ኢንስቲትዩት የ100ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በታላቅ ድምቀት ሊያከብር ነው
#FastMereja I የኢትዮጵያ የሕዝብ ጤና ኢንስቲትዩት (EPHI) የተመሰረተበትን 100ኛ ዓመት የምስረታ በዓል አስመልክቶ ከሐምሌ 7/2018 ዓ.ም በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ የተለያዩ ዝግጅቶችን እያከናወነ እንደሚገኝ ተነግሯል። ኢንስቲትዩቱ የክፍለ ዘመኑን ጉዞ ለመዘከርና በጤናው ዘርፍ የተመዘገቡ አዳዲስ ምርምሮችን ለማቅረብ መዘጋጀቱን አስታውቋል።
የኢንስቲትዩቱ ይፋዊ መርሃ-ግብር እንደሚያሳየው፣ ዋናው በዓልና ሳይንሳዊ ጉባኤው ከሐምሌ 9 እስከ ሐምሌ 11/2018 ዓ.ም ባሉት ሶስት ተከታታይ ቀናት በልዩ ሁኔታ ይካሄዳል። በዓሉ የኢንስቲትዩቱን የ100 ዓመታት ጉዞ የሚያሳዩ ፎቶግራፎችና ቪዲዮዎች፣ የምስጋናና የእውቅና አሰጣጥ ስነ-ስርዓቶች እንዲሁም በጤናው ዘርፍ ተስፋ ሰጪ በሆኑ አዳዲስ ግኝቶች ላይ ያተኮሩ የጥናትና ምርምር ስራዎች የሚቀርቡበት መድረክ እንደሚሆን ተነግሯል።
#ኹነት
48 828
🎞 ተወዳጆቹ የፊልም ባለሙያዎች ስልጠና ሊሰጧችሁ ነው!!!
🎥 በልቀት ኮሌጅ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ የፊልም ባለሙያዎች ልዩ የአጭር ጊዜ የፊልም ጥበብ ስልጠና ለመስጠት ተዘጋጅተዋል፤
✍ አሰልጣኞች
👉 ደራሲና አዘጋጅ መዓዛ ወርቁ
👉 የፊልም ዳይሬክተር እና ደራሲ ብሩክ ሞላ፤
👉 ዳይሬክተር አብርሀም ገዛኸኝ፤
👉 ሲኒማቶግራፈር ዳንኤል ግርማ፤
🎞 የስልጠና አይነቶች
👉 የፊልም አክቲንግ
👉 ዳይሬክቲንግ
👉 ሲኒማቶግራፊ
👉 በፊልም ጽሑፍ አጻጻፍ
🗓 የምዝገባ ቀን ሐምሌ10/2018 ያበቃል
ስልጠናው ከሀምሌ 11/2018 ጀምሮ ቅዳሜና እሁድ በቀን መርሐ -ግብር ይሰጣል።
💡ለምዝገባ
አራት ኪሎ ከትምህርት ሚኒስቴር ጀርባ ኢክላስ ህንፃ 3ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው የኮሌጁ ሬጅስትራር ጽ/ቤት በመምጣት መመዝገብ ይችላሉ።
📱 ለበለጠ መረጃ
2519 84 71 71 44/251940 08 99 99 /251930325090 መደወል ይችላሉ።
በተጨማሪም በቴሌግራም
@Liketcollege መመዝገብ ይችላል።
48 828
አከራዮች ከተማ አስተዳደሩ የማያዳግም እርምጃ እወስዳለሁ አለ
#FastMereja | የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያን 11.5 በመቶ ማድረጉን ተከትሎ፣ ሕግን በመጣስ በህገ-ወጥ መንገድ የቤት ኪራይ ጭማሪ በሚጠይቁ አከራዮች ላይ ከባድ አስተዳደራዊና ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ።
የከተማ አስተዳደሩ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ እንደገለጸው፣ አንዳንድ አከራዮች በተቀመጠው የሕግ ማዕቀፍ ውስጥ ከመስራት ይልቅ፣ ሕገ-ወጥ አሰራሮችን እየተገበሩ ይገኛሉ። በተለይም ተከራዮችን “ቤቱን ለራሴ ወይም ለዘመዴ እፈልገዋለሁ” በሚል ሐሰተኛ ምክንያት በማስለቀቅ፣ በምትኩ ከፍተኛ የኪራይ ዋጋ በመጫን፣ የ11.5 በመቶውን ጭማሪም ሕጋዊ አስመስለው የመጫን ተግባራት በስፋት እየተስተዋሉ ነው።
በተጨማሪም፣ አከራዮች በውል ሰነድ ላይ የከተማ አስተዳደሩን የ11.5 በመቶ ጣሪያ በመጥቀስ በሕጋዊ መንገድ እየተስማሙ፣ በተግባር ግን በአፍ እጅግ ከፍተኛ ዋጋ በመደራደር ተከራዩን ለከፍተኛ የገንዘብ ጫና የሚዳርጉበት የ”ድርብ ውል” አሰራር የተለመደ እየሆነ መምጣቱን የተሰጡ ጥቆማዎች ያመለክታሉ። ይህ ድርጊት በግልጽ ሕግ ተጠያቂ የሚያደርግ ሕገ-ወጥ ተግባር መሆኑን ቢሮው አስገንዝቧል።
በዚህ ረገድ ተከራዮች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ቢሮው አሳስቧል። በተለይም በአፍ የተጠየቀው ከፍተኛ የክፍያ ዋጋ በውል ሰነድ ላይ ካልተቀመጠ፣ ተከራዮች ክፍያቸውን ሁልጊዜ በባንክ በኩል ብቻ እንዲፈጽሙ በማድረግ ሕገ-ወጥነቱን በማስረጃነት እንዲይዙ መክሯል።
ቢሮው አክሎም፣ አከራዮች መተሳሰብና ሰብአዊነትን እንዲያስቀድሙ ጥሪ በማቅረብ፣ ሕግ ተላልፈው በሚገኙት ላይ ከባድ አስተዳደራዊና ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ በጥብቅ አስጠንቅቋል። ማህበረሰቡም ይህንን ሕገ-ወጥ ተግባር በጋራ ለመከላከል ጥቆማ በመስጠት የበኩሉን ኃላፊነት እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።
48 828
🏢 የሰመር ሪል እስቴት ልዩ የቤት ባለቤት የመሆን እድል!
በከተማችን እምብርት ቡልጋሪያ አደባባይ አካባቢ የሚገኙትን እጅግ ዘመናዊ፣ ሰፊ እና ምቹ የመኖሪያ አፓርታማዎችን በፈለጉት የካሬ አማራጭ ለሽያጭ አቅርበናል።
📐 የምርጫዎትን የካሬ እና የመኝታ አማራጮች ይምረጡ፦
🛏️ ባለ 1 መኝታ – 81 ካሬ
🛏️ ባለ 2 መኝታ – 111 እና 134 ካሬ
🛏️ ባለ 3 መኝታ – ከ168 ካሬ ጀምሮ
💰 እጅግ አስገራሚ ዋጋ እና ልዩ የክፍያ አማራጭ፦
💵 ዋጋ፦ በካሬ 89,000 ብር ብቻ!
📉 ቅድመ ክፍያ፦ 10% ብቻ በመክፈል ውል ያሰሩ!
🏦 የባንክ ብድር፦ 50% የባንክ ብድር የተመቻቸለት።
⏳ ጊዜ አይውሰዱ!
ይህ ታላቅ የዋጋ ቅናሽ የሚቆየው ለውስን ጊዜ ብቻ ስለሆነ፣ ቀድመው በመምጣት የዕድሉ ተጠቃሚ ይሁኑ።
📍 ቦታ፦ ቡልጋሪያ አደባባይ አካባቢ
📞 ለበለጠ መረጃ አሁኑኑ ይደውሉልን፦0912355631
48 828
የኢትዮጵያ የእምነት እናቶች ሀገራዊ ፈውስና ሰላም ለማምጣት የ3 ቀናት ብሔራዊ የጾምና የንስሐ ጸሎት ጠየቁ
#FastMereja I በኢትዮጵያ የተለያዩ የእምነት እናቶች፣ ሀገሪቱ ከምትገኝበት ማህበራዊ፣ ሥነ-ምግባራዊና ሰብአዊ ቀውስ እንድትወጣ እንዲሁም ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን በማለም፣ ለሁሉም የሃይማኖት መሪዎች የ3 ቀናት ብሔራዊ የንስሐና የጾም ጸሎት እንዲታወጅ ጥሪ አቅርበዋል።
ዶክተር ኤርጊጎ ተስፋዬ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር በክብር እንግድነት በተገኙበት በዚህ መርሀ ግብር የሀይማኖት አባቶች በፀሎት ፕሮግራሙን እንደከፈቱት ለማወቅ ተችሏል።
እናቶቹ «ልዩ ቀን ለኢትዮጵያ» በሚል መሪ ቃል ባወጡት መግለጫ፣ በሀገሪቱ እየተስፋፉ ያሉ የጥላቻ ንግግሮች፣ ቂም፣ በቀልና የእርስ በርስ ግጭቶች የማህበረሰቡን አንድነት እየጎዱ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በተጨማሪም መፈናቀል፣ ሙስና እና ግጭቶች በእናቶችና በቤተሰቦች ላይ ከባድ ስቃይ እያደረሱ መሆኑን በመጠቆም፣ «የሟችም የገዳይም እናት እኔው ነኝ» በሚል መንፈስ የግጭቱ ሰለባዎች ሁሉ ሊደገፉና ሊፅናኑ እንደሚገባ ወይዘሮ ትዕግሥት ታምራት ከአስተባባሪዎቹ አንዷ አሳስበዋል።
በመግለጫቸው የሃይማኖት አባቶች በሀገር ሰላምና እርቅ ሂደት ታሪካዊ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።
እናቶቹ ሁሉም ኢትዮጵያውያን በተመሳሳይ ቀናት በጾም፣ በጸሎትና በንስሐ በመተባበር ለሀገራዊ ፈውስና ለዘላቂ ሰላም ወደ ፈጣሪ እንዲማፀኑ አሳስበዋል።
ወይዘሮ መአዛ በቀለ ከዕለቱ መርሀ ግብር አስተባባሪዎች አንዷ ባሰሙት ንግግር ሰላምን እና ፍቅርን ለማንገስ መፍትሔ በሐይማኖት አባቶች ዘንድ አለ ብለዋል። በእውነተኛ ንስሐ የኢትዮጵያ ትንሣኤ ይሆናል በመሆኑም መንፈሳዊ አባቶች ትልቅ አደራ ተጥሎባችኃል ሲሉ ወይዘሮ መኣዛ ንስሀ መግባት ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ የሰላም፣ የእርቅና የመተማመን መንገድን ለመገንባት የጀመረቻቸው የሀገራዊ ምክክርና የሽግግር ፍትህ ሂደቶች ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ ወሳኝ እርምጃዎች ተደርገው ይታያሉ። እነዚህ ሂደቶች የሚፈለገውን ውጤት እንዲያመጡ ግን የህዝቡ ተሳትፎ፣ መተማመን፣ ይቅርታና የሞራል መታደስ ወሳኝ መሠረቶች ናቸው።
በዚህ አውድ የእምነት እናቶች ያቀረቡት የ3 ቀናት ብሔራዊ የንስሐና የጾም ጸሎት ጥሪ፣ ልዩነቶችን በውይይት ለመፍታት፣ የቆዩ ቁስሎችን ለማከም እና የጋራ ሀገራዊ እሴቶችን ለማጠናከር ከሚደረጉ ጥረቶች ጋር የሚስማማ መንፈሳዊ አስተዋፅኦ ነው።
ዘላቂ ሰላም በሕግ ብቻ ወይም በፖለቲካ ስምምነት ብቻ አይገነባም፤ እውነትን በመቀበል፣ ፍትሕን በማክበር፣ ይቅርታን በማጎልበትና በጋራ የወደፊት ተስፋን በመገንባት እንጂ። ስለዚህ ሀገራዊ ምክክር፣ የሽግግር ፍትህ ሂደት እና የእምነት ተቋማት የሚያበረታቱት የንስሐና የጸሎት መንፈስ ተደጋግፈው ሲጓዙ፣ በመተማመን፣ በእርቅና በአንድነት የተመሠረተች ኢትዮጵያን ለመገንባት ጠንካራ መሠረት የሚፈጥር ነው።
በዕለቱ በተደረገው መርሀ ግብር መንፈሳዊ አባቶች ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ እና እንዲመካከሩ ዕድል የተሰጣቸው ሲሆን እነርሱም ተመካክረው መፍትሔ የሚሉትን ሀሣብ አቅርበዋል።
በዛሬው መርሀ ግብር ላይ የታደሙ እንግዶች ከሻይ ዕረፍት በኃላ የተሰማቸውን ሀሣብ ገልፀዋል። የኢትዮጵያ የእምነት እናቶች ለሰላም በሚል መሪ ሀሣብ የተካሄደው ይህ ፕሮግራሙ ላለፉት 20 አመታት ቅድመ ዝግጅት ሲደረግበት እንደነበር አስተያየት ሰጪዎች ተናግረዋል።
እናቶች ይህን መርሀ ግብር ዕውን ለማድረግ በትዕግሥት ተሞልተው ለዚህ ቀን በማድረሳቸው ምስጋና ሊቸራቸው ይገባል ሲሉ በመድረኩ ላይ አስተያየት የሰጡ ተናግረዋል።
#ማህበራዊ
48 828
📽 የፊልም ጥበብ ስልጠና ለምትፈልጉ ልዩ ዕድል!!!
🎥 ልዩ የአጭር ጊዜ ስልጠና በታዋቂ እና ተወዳጅ የፊልም ባለሙያዎች ከልቀት ኮሌጅ ተዘጋጅቶላችኋል፤
👉 የምዝገባ ቀን ሐምሌ10/2018 ያበቃል
ከግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በዲግሪ ደረጃ የፊልም ትምህርትን በማስተማር የመጀመሪያና ብቸኛ የሆነው ልቀት ኮሌጅ ለ2018 ሁለተኛውን ዙር የክረምት አጭርና እጅግ ውጤታማ የስልጠና መርሐ ግብር አዘጋጅቷል።
💡 አሰልጣኞች
👉 በፊልም አክቲንግ የስልጠና ዘርፍ ዳይሬክተር እና ደራሲ ብሩክ ሞላ፤
👉 በዳይሬክቲንግ ስልጠና ዳይሬክተር አብርሀም ገዛኸኝ፤
👉 በሲኒማቶግራፊ ዘርፍ ሲኒማቶግራፈር ዳንኤል ግርማ፤
👉 በፊልም ጽሑፍ አጻጻፍ ደራሲና አዘጋጅ መዓዛ ወርቁ ይሰጣሉ።
ስልጠናው ቅዳሜና እሁድ በቀን መርሐ -ግብር የሚሰጥ ሲሆን ከሀምሌ 11/2018 ጀምሮ መሰጠት ይጀምራል።
💡ለምዝገባ
አራት ኪሎ ከትምህርት ሚኒስቴር ጀርባ ኢክላስ ህንፃ 3ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው የኮሌጁ ሬጅስትራር ጽ/ቤት በመምጣት መመዝገብ ይችላሉ።
📱 ለበለጠ መረጃ
2519 84 71 71 44/251940 08 99 99 /251930325090 መደወል ይችላሉ።
በተጨማሪም በቴሌግራም
@Liketcollege መመዝገብ ይችላል።
