Abdu Book Center
رفتن به کانال در Telegram
በመጻሕፍት መደብራችን ፡ የታሪክ መጻሕፍት የትምህርት አጋዥ እና መማሪያ መጻሕፍት የተለያዩ ልበ-ወለድ እና መንፈሳዊ መጻሕፍት ቆየት ያሉና አዳዲስ መጻሕፍት ሌሎችም.. አድራሻችን=አዲስ አበባ ፒያሳ ጊዮርጊስ እሳት አደጋዉ ሻገር ብሎ አባቢያ ራሕመት ታቦር ሕንፃ ፊትለፊት ለበለጠ መረጃ በ0929574133 ደዉልሉን @Abduseller
نمایش بیشتر1 911
مشترکین
-124 ساعت
+147 روز
+2330 روز
آرشیو پست ها
1 911
መጽሐፉ በሁለተኛው የኢትዮጵያና የጣሊያን ጦርነት ወቅት አባቶቻችንና እናቶቻችን በማይነገር ጭካኔ*ው በብረት ከሚመካ ፈጣሪን ከማያውቅ ልበ ድፍን ሠራዊት ጋር የተጋፈጡባቸዉን ክፉዎቹን የጦርነቱን ወራት በዓይነ ሕሊናችን የሚያሳየን የገዛ ራሳችን ታሪክ ነው። ሮዶልፎ ግራዚያኒ ወደ ኢትዮጵያ ሲመጣ ሙሶሊኒ ዘንድ ቀርቦ ተናገረው የሚባለው አባባል ዘወትር በሕሊናችን ታትሞ የሚኖር ነው። "ኢትዮጵያን የምትፈልጋት ከኢትዮጵያውያን ጋር ነው ወይስ ያለ ኢትዮጵያውያን?"
«❖❖❖»
ይህ መጽሐፍ በመጽሐፉ ደራሲ በሄሊ ቮን ሮዛን በወጉ የተደራጀ መረጃና የአገላለጽ ውበት በኢትዮጵያውያን ብርቱ የጦር ሜዳና የዲፕሎማሲ ተጋድሎ ነጻነት ተመለሰ ከተባለ በኋላ ንጉሡ፡ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን በገቡበት አዲስ የፈተና ምዕራፍ ውስጥ ያሳልፈናል። በዚህኛው ምዕራፍ ንጉሡ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ከጦርነቱ መልስ በጦርነቱ የፈራረሰውን የመንግሥት ሥርዓት፡ የደቀቀውን ኢኮኖሚና፡ የተጎሳቆለውን ኢትዮጵያዊ ሞራል መልሰው ለማቀናጀት አቅማቸውና ዘመናቸው በፈቀደላቸው መጠን ያለፉበትን አድካሚ ጉዞ ገደባቸውን ሳያጋንኑ ፡ ጉድለታቸውን ሳይሸሽጉ በነጻ ታዛቢ ሚዛናዊነት በየረድፉ ያስቃኘናል።
ይህን መጽሐፍ ስናነብ ንጉሡ በረጅሙ የግዛት ዘመናቸው በመንግሥታቸው ውስጥ በነበሩት በመሳፍንቱና በዘመናዊያኑ ልሂቃን መካከል የግራ ቀኙን ሚዛን ጠብቀው አገሪቱን ወደፊት ለማራመድ የተጓዙበትን የሠርከስ ገመድ ላይ ጉዞ የሚመስለውን የፖለቲካ ሕይወታቸውን እያስተነተነ ለሕሊና ዳኝነት ያቀርብልናል።
«❖❖❖»
1 911
📚📚📖
መሠረታዊ የሆኑት መርሆዎች ለስኬት ቁልፍ ናቸው። ስቴፈን ኮቬይ ደግሞ እነዚህን መርሆዎች በአስገራሚ መልኩ በውስጡ ይዟቸዋል። እናም እባክዎን መጽሐፉን ይግዙት፤ ግን ከዚህ በላይ ዋንኛውና ትልቁ ነገር ያንብቡት!
አንቶኒ ሮቢንስ የ UNLIMITED POWER ደራሲ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ደህና ሁን ዴል ካርኔጌ። ስቴፈን ኮቬይ በህይወቴ ከፍተኛ ተጽዕኖ ከፈጠሩብኝ ሰዎች ዋንኛ ነው። መርሆዎቹ ከፍተኛ እና ኃይል የተሞሉ ናቸው፤ ይሠራሉ። ይህን መጽሐፍ ትገዙት ዘንድ አደራ እላለሁ፤ አንብቡት። በምትቃርሟቸው መርሆዎች ህይወታችሁና ተሞክሯችሁ እየተለወጠ ይሄዳል።
--- ሮበርት ጂ. አለን
የ CREATING WEALTH እና NOTHING DOWN ደራሲ
THE SEVEN HABITS OF HIGHLY EFFECTIVE PEOPLE የተባለው ይህ መጽሐፍ በእውነት ለየት ያለ ነው። አንድ ሰው መነሳሳት አድሮበት በሕይወት ለሚገጥሙት የተለያዩ ኃላፊነቶች ብቁ እንዲሆን ይረዳዋል። በግሉ ሕይወት ብቻ ሳይሆን በሥራ እና በማኅበራዊ ግንኙነት ብሎም በቤተሰብ ሕይወት ዙሪያ ከሌሎች እስከ አሁን ካነበብኳቸው መጻሕፍትም በላይ ጠቃሚ ሆኖ አግኝቼዋለሁ።
--- ሻል ኤች. ቶማስን
የ MARRIOTT SCHOOL የአስተዳደር ዲን
እንዲሁም የ NOVATIONS ደራሲ
1 911
......የሰዉን ልጅ ከእንስሳ የሚለየዉ ባለታሪክ መሆኑ ብቻ አይደለም።ታሪክን አስቦና መርጦ በየዘመኑ የሚፈጥር፣ይህን አድርጎም በተረከበዉ ላይ የሚያክል እንጂ የቀደምቶችን ቅርስና ዉርስ ነዉ በሚል ዝግ ተቀባይነትና ወራሽነት እራሱን አለማሰሩ ነዉ።ይህ ሳይሆን ሲቀር የነገ መሰረትን እዉን ማድረግ ባለመቻል አደራዉን፣ኃላፊነቱን እና ተረኛ አባትነቱኖ ያልተወጣ ይሆናል።የዚህ ሁሉ ምክንያት የትላንት ዉርሱን ከዛሬ ህይወቱ...ሊያየዉ ከሚችለዉ የነገ እጣ ፈንታዉ ጋር አቀናጅቶ ሊመዝንና ሊመርጥ በሚያስችል አስተሳሰባዊ ቅኝት የሚጠበቅበትን የሀሳብ ፍተሻ በማካሄድ ወደ ተግባር ለመግባት አለመቻሉ ነዉ።
...................................................................
.....የተለያዩ የሀገራችን ትዉልዶች ዜግነታዊ ኃላፊነታቸዉንና ፍቅራቸዉን ተመርኩዘዉ...የበኩላቸዉን መስዋዕትነት ከፍለዋል።በዚህም አማካኝነት እንደ ሀገርም እንደ ህዝብም ህልዉናችንና ማንነታችን ለዛሬ ሊበቃ ችሏል።በሂደቱ የተከሰቱ በጎም ሆኑ መጥፎ ገፅታዎች አሉ።....
የእኛዉ ናቸዉና በታሪክነት ይቀጥላሉ።መጥፎ የሚባሉትን ልንሸፋፍናቸዉ፣እየመረጥን ጎራርደን ልንጥላቸዉ አይገባም።...ሊታዩ አይገባምም ብለን ዕይታችንን መጨፈን፣አእምሯችንን መከርቸም አያሻንም።የሚበጀንም፣የሚያስፈልገንም አይደለምና።....ታሪክ እንደ ጅረት ተያይዞ የሚፈስ እንጂ እንደ ኩሬ በድንበር ተገድቦ የረጋ ወይም የተቀመጠ አይደለም።
📚📚📚ኩርኮራ
የኤርትራ ጉዳይ፣የልሂቁ ሚና፣የማንነት ፖለቲካ በዘመናዊት ኢትዮጵያ
ዘሪሁን ተሾመ
ሐምሌ 1999
1 911
“......እነኚህ የአበሻ ሕዝቦች ሰፊ ግዛት አላቸዉ።ከቀይ ባህር ዳርቻ ከምፅዋ፥ከሱአኪንና ከአርቂቆ ተነስቶ ግዛታቸዉ እስከ መቃ ዲሾና ሶፋላ ይደርሳል።በምዕራብም በኩል ግዛታቸዉ የሚዋሰነዉ ከኑባዉያንና ከሌሎችም ሕዝቦች ጋር ነዉ።...”
ኦልፎንሶ አልቡ ከርክ 1503
📚📚📚 አጤ ምኒልክ
ከጳዉሎስ ኞኞ ገፅ 37
የመጀመሪያ ሕትመት 1984
1 911
እጅግ በጣም ቆንጆ መጽሐፍ 📚 በዛሬዋ ቀን ዳግማዊ የሕትመት ብርኅን አየ።
✍️ Mohammedzein Abagero
"የዋህና ትሑት" መኾንን ያለብን በአእምሯችን ነው ወይስ በልባችን? አንዳንድ ጊዜ ኹለቱንም በኹለቱም መኾን ይቻላል ። በተለይ "ትዝታን" ሕይወት አድርገው ከሚያኖሩን የኪነት ውጤቶች ጋር ስንገናኝ፤ ... ለአፍታም ቢኾን የዋህና ትሑት የመኾንን ስሜትና ዕውቀት አሳድሮብኛል ... ይሄ ሶምነስ-- ይሄ የምራመደው ወዳለፈው ነው የተባለው ማኅፀን።
ማኅፀንና አእምሮ አንድ ዓይነት ምግባር እንዳላቸውም ነገረኝ ይሄ የያዝሽው፣ ይሄ የያዝከው መጽሐፍ።
... ሐሳብም ሽልም ባያኖሩ ከመጠሪያቸው፣ ከክብራቸው ዝንፍ እንደማይሉም አስታወሰኝ።
ትዝታን፣ አሁንንና ተስፋን፤ እንቁላልን፣ ፅንስን እና "ሰውን" አያቁሩም - አፍሳሽ ነውና ተፈጥሯቸው። ለፍትሕ ማደሪያነት አይኾኑም። ይልቅስ፣ ይልቅስ ... በአንብሩጥ ጥግ፣ በቄማሼ ሰርጥ ደናሚት የምትባል ሕያው ፍሬ ታይታ ነበር፤ በ"ልጅ ወንዶች" እና በሶምነን ልብ ውስጥ ትዝታም ሳትኾን፣ አሁንም ሳትኾን፣ ተስፋም ሳትኾን፤ ውልብታዋ እንደ መናኛ ነገር የተቆጠረ፣ ምዕተ ዓመትን ወደ ዓመተ ምሕረት ያልቀየረች፤ ነገር ግን ድሮም የነበረች አሁንም ያለች ወደፊትም ለዘላለሙ የምትኖር ...
ሙሐመድዘይን አባገሮ "የምራመደው ወዳለፈው ነው" ቢለንም፤ ፊቱን ወደሚመጣው መልሷልና ፤ አብዮታዊም፤ ዝግመተ ለውጣዊም፤ ቁሞ ቀረዊም ባልኾነ የድርሰቱ ጠባይ ምክንያት ነገን ማሰናደቅ ችሎበታል።
ደራሲ ገዛኸኝ ሀብቴ
1 911
በመሠረቱ ሕይወት እኛዉ እንዳደረግናት ነዉ የምትሆንልን።
ሰዎች የሥራ፤ማኅበራዊ እና ግላዊ ስኬቶቻቸዉን ሲያቀናጁ በዉጭም ሆነ በዉስጣዊ ሕይወታቸዉ እጅግ ላቅ ያለ እርካታን መቀዳጀት መቻላቸዉን ይኼ መጽሐፍ 📖 በሚጠባ ያስቀምጥልናል።
📚ስኬታማነት 📚
✍️ዴል ካርንጌ
ትርጉም፦።ኤፍሬም አለሙ 2008
1 911
“......እነኚህ የአበሻ ሕዝቦች ሰፊ ግዛት አላቸዉ።ከቀይ ባህር ዳርቻ ከምፅዋ፥ከሱአኪንና ከአርቂቆ ተነስቶ ግዛታቸዉ እስከ መቃ ዲሾና ሶፋላ ይደርሳል።በምዕራብም በኩል ግዛታቸዉ የሚዋሰነዉ ከኑባዉያንና ከሌሎችም ሕዝቦች ጋር ነዉ።...”
ኦልፎንሶ አልቡ ከርክ 1503
📚📚📚 አጤ ምኒልክ
ከጳዉሎስ ኞኞ ገፅ 37
የመጀመሪያ ሕትመት 1984
1 911
" ዮቶር ፪ " በአለማየሁ ደመቀ ! 📚
"የነብስህን ዐይን ክፈትና ተመልከት። መጀመሪያ በሁለመናህ ላይ ስልጣኑን ተቆናጠጥ። በውስጥህ ያለውን ጨለማ በብርሃን ካልሞላኸው በቀር የውጪውን ጨለማ አትገፈውም። ይኽ ጨለማ ከምታውቀው ጨለማ ይጠነክራል እንጂ አይለይም። አካል፣ አዕምሮህን እና መንፈስህን በአንድ አሰልፍ፤ በአንድ ግዛቸው። ያኔ የነፍስህ ዐይን ይከፈትና ማየትም መገንዘብም ትጀምራለህ። ያን እስክታደርግ ድረስ ግን ጨለማው ባደረሰብህ ጥልቅ ፍርሃት ሳቢያ ራስህን በመሳት ጀምረህ ራስህን ጨርሶውኑ ታጣዋለህ። መጨረሻህም ሞት ይሆናል ከንቱ ሞት!"
"አንተ ማን ነህ ግን?" አፌን መክፈት በተሳነው ሰላላ ድምፅ ጠየኩት
እኔ የምትሰማው ድምፅ ነኝ። ማየት ስትችል ደግሞ ብርሃን ነኝ "የድምፅና የብርሃን ውቅር"ልትለኝ ትችላለህ። አሁን ወደ ውስጥህ ተመለስ። ሁለመናህን ከራስህ ጋር አዋህድ። ያለኸው በአካላዊ ዐይንህ ብቻ የምታይበት ዓለም ውስጥ አይደለህም። የነብስህን ዐይን ክፈት። ቁልፉ ደግሞ ቀላል የው አካልን፣ አዕምሮንና መንፈስን ማዋሀድ ነው።
1 911
ዐብዱልቃዲር፤ገንዘብን በአግባቡ እንድንገነዘብ ያደረገበት ድንቅ መጽሐፍ ነዉ።ገንዘብን ከታሪካዊ አመጣጡ ጀምሮ፣አሁን እስከደረስንበት የዲጂታል ዘመን ያሉ ፅንሰ-ሃሳቦችን፣እንዲሁም በየደረጃዉ የነበሩ አስተሳሰቦችን እና ክስተቶችን በጥልቀት ዳሷል።ለሁሉም አንባቢ በሚገባ መልኩ በምሳሌ-ዎች እየተነተነ ያቀረበበት መጽሐፍ ነዉ።መጽሐፉ በሴራ ትንተና ላይ ብቻ የሚያተኩር አይደለም።መዉጫ መንገዶችን፣ሃገራዊ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን እና በግለሰብ ደረጃ የሚሆኑ መፍትሔዎችንም ጠቁሟል።
ይህን መጽሐፍ 📚ማንበብ "ገንዘብ ከየት ተነስቶ የት ደረስን?"የሚለዉን ለማወቅ ብቻ ሳይሆን፤መዉጫ መንገዱ ድቅድቅ በሆነዉ ወጥመድ ዉስጥም ቢሆን፣አሁን ባለዉ አዉድ ገንዘባችንን በምን መልክ እንጠቀምበት?እንደአቅማችን የኢንቨስትመንት ዉሳኔ ስናደርግ ምን ምን አይነት ሁኔታዎችን እንገምግም?እንዲሁም የሃብታምነት ፍላጎታችንን ተጠቅመዉ፣በኛ ላይ ሃብታም ለመሆን የሚፈልጉ ሰዎችን እና ድርጅቶችን ለመለየት ምን አይነት ጥንቃቄ እናድርግ?የሚለዉን ለማወቅ አብዝቶ ይጠቅማል።በሌላ አነጋገር፤ታሪክን ለማወቅ ብቻ ሳይሆን ለኢንቨስትመንትም ዉሳኔ እንደ ማጣቀሻ የምንጠቀምበት መጽሐፍ ነዉ።አንብቡት! ታተርፉበታላችሁ።
አሚኑ ኑሩ(የፋይናንስ ባለሙያ)
1 911
ከድር ሰተቴ ባለቅኔ ብቻ አይደለም፤ከዚያም ከፍ ይላል።እኛ ግጥሞችን ለመፃፍ ብዕርና ወረቀት እንፈልጋለን፤እሱ ግን ግጥሞቹን ንፋስ ላይ ይፅፋቸዋል፤የሰዉ ልብ ላይ ያትማቸዋል።እሱ በራሱ ግጥም ነዉ፤ቅኔ ነዉ።ግጥሞቹ ከልቡ የሚፈልቁና በቀጥታ ለሰዉ የሚደርሱ ናቸዉ።በነሸጠዉ ጊዜና ቦታ ብዕርና ወረቀት ሳያስፈልገዉ፣መዝገብ ሳያገላብጥ በየትኛዉም ርዕስ ጉዳይ ላይ የተሰማዉን በቅኔ ይተነፍሰዋል።ይዘራዋል።
ልበ ብርሃኑ ባለ ቅኔ ሙሉጌታ ተስፋዬ(አያ ሙሌ)የግጥም ዛር ሲሰፍርበት አጠገቡ ያለዉን ሰዉ ብዕርና ወረቀት ያዝ በማለት እንደሚያወርደዉ ሰምቻለሁ።የከድር ሰተቴ የሚደንቀኝ ቅኔዎቹ አንድም ወረቀትና ብዕር ሳይፈልጉ ንፋስ ላይ ተዘርተዉ በሰዉ ልብ ዉስጥ ቀርተዋል።ንግግሩ እንኳ ቅኔ የሆነ ደፋር የጥበብ ቀንዲል ነዉ ሰተቴ።ሀብታችሁን አጥኑት
ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን ( Teddy Afro )
1 911
ከገበያ ጠፍቶ የነበረዉ መጽሐፍ የሕትመት ብርሃን አየ
...."ምን ልንገርሽ? ሔር.."
“ቆንጆ ነሽ በለኝ !...እወድሻለሁ በለኝ!...ወንዶች ጋር ሳወራ እንደምትቀናብኝ ንገረኝ !
...እንደምትፈልገኝ ንገረኝ! የሆነ ነገር በል፣በቃ የፈለከዉን..."ጠንካራዋ ሔራን ከተዋወቅን ጀምሮ ለመጀመሪያ ጊዜ እያለቀሰች ነበር።.....
📚 ከዕለታት ግማሽ ቀን
Alex Abreham
1 911
ይህ መጽሐፍ የአእምሮ ትኩረት መንገዶችን ያስተዋዉቀናል።ከምንፈልገዉ ስኬት እንድንደርስ እንቅፋት የሆነብንን የዉስጠ ኅሊና ገደቦች የምናስወግድበትን ብልኃትም ይጠቁመናል።
1 911
ድምጽ አሰምቶ ማልቀስም ራስን ለከፋ አደጋ ማጋለጥ መሆኑን ቀድመው ከታሰሩት ጓደኞቼ በመረዳቴ ድምጽ አልባ ዕንባዬን ከአጋሮቼ ጋር ሆኜ ተወጣሁት በተመሳሳይ አደጋ የሞቱት በአንድ ምሽት ብቻ ሃያ አንድ መሆናቸውን እንደዚሁ በምስጢር ስንረዳ ሟቾች በግፍ ተገድለው እንደ ውሻ ሬሳ አንዱ በአንዱ ላይ ተመሳቅለው ከምርመራው ክፍል ውጪ ከደጅ እንዳደሩና ዝናብ ሲመታቸው ካደረም በኃላ በውል ሳይነጋ በአንድ ግልጽ የፖሊስ መኪና ሬሳቸው ተጭኖ ባሕር ዳር ከተማ በተለያየ ቦታ ተንጋለው አልፎ አልፎ በአንዳንዶቹ ላይ "ነጭ ሽብርተኞች በቀይ ሽብር እንደመስሳቸዋለን!" የሚል ወረቀት ተጽፎባቸው ቀኑን ሙሉ ውለው በእስረኛ በተቆፈረ ጉድጓድ በጅምላ "ቤዛዊት" ከተባለ ቤተ መንግስት ጀርባ እንደተቀበሩም ሰማን። በየቦታው የሚሞቱትን ጓዶቻችን ሁሉ ከለበሱት ልብስና ጫማ ጋር ይቀበሩ እንደነበር ከአንድ ራሱን ከለወጠ ፖሊስ እኔ ብቻ ሰምቻለሁ።
በዚህ ዓይነትና በተለያዩ አሰቃቂ አገዳደል ብዙዎቹ ሕይወታቸውን እንዲያጡ ሲደረግ ቀሪዎቹ በረቀቀ ዘዴ ቃል ስንሰጥና ስንደበደበ ጥርሳችንን ነክሰን ሳንወሸክት አጋጣሚውን አልፈነዋል። የሦስት ዓመት አስራቴንም እንደጨረስኩ ወደ ደጀን መጥቼ አሁን ድረስ በዚህ ስራ እኖራለሁ።
መጽሐፍ በመደብራችን ያገኙታል።
1 911
"Fully conveys the basic principles of (Graham's) enormously successful &popular approach to investing." -Money magazine
#mustread #books #booklovers #reading #newarrivals
1 911
'A singularly profound and moving work....It's not often that you read abook of this length and find yourself thinking "I wish it was longer"but Yanagihara takes you so deeply into the lives and minds of these characters that you struggle to leave them behind.'
THE TIMES
#mustread #booklovers #ReadingCulture #NewArrivals #books #reading
1 911
መዉደድ ጉዱ ፈላ፤አንገት አስደፋሽዉ፤
ከፍቅር የሚበልጥ፤ፍቅር ዐሳየሽዉ።
ሐሜት በነነ፤ጥላቻ ተለካ፤
ሌላ ወንጌል ጻፍኩኝ፤
"ሰዉም በዚህ ሚዛን፤ይፈቀራል ለካ?"
መዉደድሽ በለጠኝ፤ማፍቀርሽን አነስኩ፤
ከእቅፍሽ ሥር ሆኜ፤እንዴት ዓለም አሰስኩ።...
📚ርእስ የለዉም 📖
የግጥም ስብስብ
ኤሊያስ ሽታሁን
1 911
የነበረውን ድባብ እና ቋንቋውን ለመረዳት ያደረገውን ጥረት እያነሳ፣ የአውሮፓውያን አሳሾች ለከተማዋ የነበራቸውን ከፍተኛ ጉጉት ይተርካል። በተለይም ሀረር በምስራቅ አፍሪካ እንደ ‘ቲምቡክቱ’ የምትታይ የእውቀት ፋና እንደነበረች ያስረዳል። የሪቻርድ በርተንን የተሳሳቱ ድምዳሜዎች በምሁራዊ ትችት እያረመ፣ የቋንቋውን ትክክለኛ ምንነትና ውበት ለማሳየት ይጥራል። በመጽሐፉ ውስጥ የሚገኙት ወጎችና ትዝታዎች፣ ሀረር የቀድሞ ክብርዋን ብቻ የምትዘክር ከተማ ሳትሆን፣ ዛሬም ድረስ በነዋሪዎቿ ልብ ውስጥ ህያው ሆና የምትኖር 'የፍቅርና የሰላም መዲና' መሆኗን ያረጋግጣሉ። በመጨረሻም፣ ደራሲው ሀረር በዘመናዊነት እና በጥንታዊነት መካከል ያላትን ትግል ይቃኛል። የጁገል ግንብ ዛሬም ቢሆን የከተማዋን ነፍስ እንደያዘ ቢቆይም፣ ወጣቱ ትውልድ ቋንቋውን እና ባህሉን ከመጠበቅ አንጻር ያለበትን ኃላፊነት ያስታውሳል። መጽሐፉ የሀረርን ታሪክ ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያን ብዝሃ-ባህላዊ ውበት የሚያሳይ መስታወት ሆኖ ያገለግላል። ደራሲው በተራቀቀ ቋንቋ እና በጥልቅ ምርምር የታጀበው ትረካው፣ አንባቢው የሀረርን ‘ዐጃኢባት’ (ድንቆች) እንዲረዳ እና ከተማዋን በታላቅ አክብሮት እንዲመለከታት ያደርገዋል።
ጥቅሶች እና አባባሎች ከመጽሃፉ ውስጥ (Notable Quotes & Sayings)
"ሀረር የጥበብ ማዕድ ናት። [Harar is a table of wisdom.]"
•ደራሲው ሀረርን የበርካታ ምሁራንና የአውሮጳ አሳሾች ትኩረት መሆኗን በሚገልጽበት ክፍል የተጠቀሰ። [Mentioned where the author describes Harar as the focus of many scholars and European explorers.]
"ጌይ ኡሱእ ከሁሉም በፊት ከተማዋን የራሱና የማንነቱ ምንጭ አድርጎ የሚያይ ሰው መሆን አለበት። [A 'Gey Usu' must first and foremost be someone who sees the city as the source of his identity.]"
•የከተማዋን ነዋሪ (ጌይ ኡሱእ) ማንነትና ከከተማዋ ጋር ያለውን ቁርኝት በሚተነተንበት ክፍል የተወሰደ። [Taken from the section analyzing the identity of the city dweller (Gey Usu) and his bond with the city.]
"ጀሊል ያሳወቀኝን ልንገርህ ጥርት አድርጌ፣ ቶሎ ዒልም ሸምት ወርደህ ከሀረርጌ(ይ)። [Let me tell you clearly what the Creator revealed to me; go quickly to Harar and gather knowledge.]"
•በመግቢያው ላይ በትንቢታዊ ግጥም መልክ የቀረበ አገላለጽ። [An expression presented in the form of a prophetic poem in the introduction.]
"ለዕድለኛ ሰው የህይወት ጥሪ ይደርሰዋል (A call of life reaches a lucky person)"
•ደራሲው ወደ ሀረር ከተማ ለመጀመሪያ ጊዜ የገባበትን አጋጣሚና የከተማዋን መስህብ በሚገልጽበት ክፍል የተጠቀሰ
"ሀረር የዒልም (እውቀት) እና የስልጣኔ ምንጭ እንደሆነች... (Harar was a source of knowledge and civilization...)"
•አያቶቻቸው ስለ ከተማዋ ታላቅነትና ስለነበራት የታሪክ ክብር የሰጡትን ምስክርነት ሲጠቅስ
"ሀረርን ያለ ጁገል፣ ጁገልንም ያለ ሀረር ማሰብ ይከብዳል (It is difficult to imagine Harar without Jugol, or Jugol without Harar)"
•የጁገል ግንብ ለከተማዋ ያለውን አስፈላጊነትና የማይነጣጠሉ መሆናቸውን ሲያስረዳ
"ጌይ! ሀረር! ቢዮ አደሬ ! ነፍሴ ! እወድሻለሁ! (Gey! Harar! Biyo Adare! My soul! I love you!)"
•ደራሲው ለከተማዋ ያለውን ጥልቅ ፍቅር እና ቁርኝት የሚገልጽበት የመክፈቻ መወድስ።
"ከተሜው ሲለኩስ ኩራዙን ከራስጌ... (When the city-dweller lights his lamp at his head...)"
•የሀረርን ስልጣኔ እና የእውቀት ብርሃን ለመግለጽ በአያቶቹ አንደበት የተነገረ ትንቢታዊ ግጥም።
"‘ጌይ’ የሕዝቡ ማንነት ውስጣዊ ዐይን ናት። (Gey is the inner eye of the people's identity.)"
•የ‘ጌይ’ ስም ከጂኦግራፊያዊ ቦታነት ባለፈ ያለውን ስነ-ልቦናዊ ትርጉም ሲያብራራ።
ተዛማጅ መጻሕፍት
-First Footsteps in East Africa By Richard Burton
ደራሲው ለታሪክ ማጣቀሻነት በስፋት የተጠቀመበት እና በከተማዋ ላይ የመጀመሪያውን የምዕራባውያን እይታ ያቀረበ ስራ በመሆኑ።
-In the City of Saints: Religion, Politics and Gender in Harar By Camilla Gibb
ደራሲው በመጽሐፉ ውስጥ ለምሁራዊ ማጣቀሻነት በተደጋጋሚ ስለሚጠቀሙት።
ከእፁብ ድንቅ የfb ፔጅ የተወሰደ
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
