fa
Feedback
Abdu Book Center

Abdu Book Center

رفتن به کانال در Telegram

በመጻሕፍት መደብራችን ፡ የታሪክ መጻሕፍት የትምህርት አጋዥ እና መማሪያ መጻሕፍት የተለያዩ ልበ-ወለድ እና መንፈሳዊ መጻሕፍት ቆየት ያሉና አዳዲስ መጻሕፍት ሌሎችም.. አድራሻችን=አዲስ አበባ ፒያሳ ጊዮርጊስ እሳት አደጋዉ ሻገር ብሎ አባቢያ ራሕመት ታቦር ሕንፃ ፊትለፊት ለበለጠ መረጃ በ0929574133 ደዉልሉን @Abduseller

نمایش بیشتر
1 998
مشترکین
+124 ساعت
+207 روز
+830 روز
آرشیو پست ها
"ሀገር ያጣ ሞት" ራሱ እንደሚለው "ከቅኝት ትዝታ፣ ከስሜትም ኀዘን" የሚገንንበት፤ ኀዘኑ አንባቢን የሚወርስ፤ እንደዐፈር ግድግዳ የሚንድ የሚያፈራርስ፤ መራር ሂዩመሩ ለሣቅ የተገለጠን ጥርስ በመሸማቀ
"ሀገር ያጣ ሞት" ራሱ እንደሚለው "ከቅኝት ትዝታ፣ ከስሜትም ኀዘን" የሚገንንበት፤ ኀዘኑ አንባቢን የሚወርስ፤ እንደዐፈር ግድግዳ የሚንድ የሚያፈራርስ፤ መራር ሂዩመሩ ለሣቅ የተገለጠን ጥርስ በመሸማቀቅ አግጥጦ የሚያስቀር፤ ለፈገግታ የተዛና ጉንጭ ቆዳን በኀፍረት የሚሸበሽብ፤ የገዛ ስጋ ወደሙን ከአንባቢ የሚያዋሕድ ኃይለ ድርሰት ነው። ​በጽሕፈት ባልተቀነፉ ትእምርተ ጥቅሶቹ ውስጥ የስብሃት አጋፋሪያዊ ፈሪሃ ሞት፤ የፎስትም የነፍስ ቁማር (Faustian bargain)፤ የአዳም የሕይወትን ኪስ አራግፎ ቅራቅንቦዉን የማጋለጥ ተጋድሎ፤ የእንዳለጌታ የመከራ "ምጣድ"፤ የበዕውቀቱ ዕረፍት የሚያሥሡ ታካች ነፍሶች፤ በጊዜ ስም "የአጥቢያ ዳኛ" ኾኖ የመጣ እግዜር፤ ከጸሐፌ ትእዛዝነት ወደ ጽሕፈ ዘመንነት የተሻገረ ሊቁ ዘነብ፤ ከቅዱሳት መጻሕፍት ከባህል ትርክትም በተውሶ የመጡ (ደራጎን ገዳይ፤ ሠላሳ ዘላይ ተጋዳሊ የሌላቸዉ) "ገድሎች"፤ ሕይወትን የሚፈክሩ ሐዲስ ሚቶሎጂዎች እና እኛ ኹላችን ከነዘመናችን ተከትበናል፡፡ በወሬ ስም የተጠራ ሀገር "አባት የለሽ ትዉልድ" ኾነን፤ በወሬ ምንነት ተስለናል፡፡ ​ሔኖክን "በነሀስ ሰሌዳ ደጋግመኽ ንቀሰን" በሚያሰኝ፤ ከተገነባባቸው የወለፈንዲ ሕልውናዎች ፍርስራሾች የተነሣ በሚያፍን፤ ነገር ግን ሊሸሹት በማይሹት ሥልት፤ ከግሩም ድርሰት በተዳሩ ቃላት፤ በነጠሩ ዐዳዲስ ገለጻዎች የተደረሰበት፤ እንደ ራሳችንን በዐሥራ ዐሥር አዉታር (multi-dimension) የምናይበት ስሙ ር ሥራ ነው። ​–ቴዎድሮስ ካሣሁን ​|ደራሲና ሐያሲ|

አርቅይሁን በላይነህ የሸዋን ታሪክ በኢትዮጵያውያን ልማዳዊ ታሪክ ትረካና ትንታኔ ስልት፤ ነገር ግን ለዘመናዊው የአካዳሚክ የታሪክ ጥናት ስልት በቀረበ መልኩ፣ ጥልቅ ትንታኔ አቅርቧል፡፡ የሸዋ ነገሥታ
አርቅይሁን በላይነህ የሸዋን ታሪክ በኢትዮጵያውያን ልማዳዊ ታሪክ ትረካና ትንታኔ ስልት፤ ነገር ግን ለዘመናዊው የአካዳሚክ የታሪክ ጥናት ስልት በቀረበ መልኩ፣ ጥልቅ ትንታኔ አቅርቧል፡፡ የሸዋ ነገሥታትንና መኳንንትን የትውልድ ሐረግና ትንቢት እንዲሁም የፖለቲካ፣ ወታደራዊና አስተዳደራዊ በሳል የአመራር ጥበብን በጥልቀት ተመልክቶታል፡፡ በተጨማሪም በመሳፍንቱ መካከል የነበረውን የሥልጣን ትግል፣ አመጽና መፈንቅለ መንግሥት እስከ ቅጣትና ምሕረቱ እንዲሁም ሹም ሽሩ በድራማዊ አገላለጽ ተርኳል፡፡ ይህ መጽሐፍ በታሪክ ተመራማሪዎች ብዙም ትኩረት ያልተሰጠውን፣ ነገር ግን ምናልባትም ወሳኝ የሆነውን የኢትዮጵያን ታሪክ በአማርኛ ቋንቋ ስለሚዳስስ፣ ለአብዛኛው ኢትዮጵያዊ አንባቢ ተመራጭ እንዲሁም ወደፊት ለሚደረጉ የታሪክ ምርምሮች በመነሻነት የሚኖረው ድርሻ ከፍተኛ ነው፡፡ ​ዶ/ር ተፈሪ መኰንን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም የታሪክ ተመራማሪ 2006 ዓመተ ልደት

“ምሁራዊ፣ ግልፅ ትችት የቀረበበት እና ቆሰቋሽ የሆነው ይህ መፅሐፍ፤ በውብ መንገድ ተፅፎ ተነባቢነትን ከሃሳብ ሰጪነት ጋር አጣምሯል። በሕይወት ዘመን የተለየ ምርምር ታግዞ፣ የዚህን የአፍሪካ ክፍል
“ምሁራዊ፣ ግልፅ ትችት የቀረበበት እና ቆሰቋሽ የሆነው ይህ መፅሐፍ፤ በውብ መንገድ ተፅፎ ተነባቢነትን ከሃሳብ ሰጪነት ጋር አጣምሯል። በሕይወት ዘመን የተለየ ምርምር ታግዞ፣ የዚህን የአፍሪካ ክፍል ተለዋዋጭነት ፊትለፊት የገጠመ አስፈላጊ እና ቅርት ያለ አስተምህሮን አሰናስሏል። እናም ለዚህ አካባቢ ዜጎች፣ ተሟጋቾች፣ ተመራማሪዎች እና ተማሪዎች አስተሳሰብ አነቃቂ ተግባቦት ነው።” ​ሳሪ ካቫናግ፣ ኤዲንበርግ ዩኒቨርሲቲ ​“ክርስቶፈር ክላፋም ምንም ጥርጥር በሌለው መንገድ በዓለም ላይ ዋነኛው የአፍሪካ ቀንድ ሊቅ ነው፤ እናም ይህ፣ በአካባቢው ላይ ለሚሰራ ሁሉ በግድ መነበብ ያለበት መፅሐፍ ነው። በተለመደው ወግ አዋቂነቱ እና ለቀንዱ ሕዝብ ባለው ጥልቅ ርህራሄ፣ በእጅጉ የተለየ ውስብስብ እና ብዙውን ጊዜም አሳዛኝ ፖለቲካዊ ጅምላውዥክ ስላበበበት አካባቢ የአዳሜ ዘመንን መረዳቶች አጋርቶናል።” ​ኬን ሜንክሃውስ፣ በዴቪድሰን ኮሌጅ የፖለቲካ ሳይንስ ፕሮፌሰር «የአፍሪካ ቀንድ።» 📚📚📖📖 ደራሲ፦ክርስቶፈር ክላፋም ትርጉም፦ኃይለመስቀል በሸዋምየለህ

ነገ ወደ ጋምቤላ እና አሶሳ ከተሞች ማስላክ የምትፈልጓቸዉ መጽሐፍት ካሉ አነጋግሩን። Abdu Book Delivery 0929574133 መጽሐፍትን እስከ ደጃፍዎ ክፍላተ ሃገር ከሃገር ዉጭ ላላችሁም ዴሊ
ነገ ወደ ጋምቤላ እና አሶሳ ከተሞች ማስላክ የምትፈልጓቸዉ መጽሐፍት ካሉ አነጋግሩን። Abdu Book Delivery 0929574133 መጽሐፍትን እስከ ደጃፍዎ ክፍላተ ሃገር ከሃገር ዉጭ ላላችሁም ዴሊቨር እናደርግላችኋለን። በሚገርም ግራፊክስ፣መጽሐፍትን በሚገልጽ ከፅሁፉ ጋር በሚሄድ ስራልኝ።

ያው ነው! ​ንፅህና ጠፋ፡ በዳይ በዳይን በደለው አቤል ምድር ላይ ጠፍቶ፡ ቃየንን ቃየን ገደለው፡፡ የገዳይ ደግ ስም፡ በደም ተነከረ ሟች በመቀደሙ፡ ገዳይ ሳይሆን ቀረ። ​በወንድሙ ካራ፡ ሆዱ እየተወ
ያው ነው! ​ንፅህና ጠፋ፡ በዳይ በዳይን በደለው አቤል ምድር ላይ ጠፍቶ፡ ቃየንን ቃየን ገደለው፡፡ የገዳይ ደግ ስም፡ በደም ተነከረ ሟች በመቀደሙ፡ ገዳይ ሳይሆን ቀረ። ​በወንድሙ ካራ፡ ሆዱ እየተወጋ፡ እልፍ ሰው ሲጋደም፤ ደፍሮ የት ነህ ብሎ፡ መጠየቅ ተሰኖት፡ ዝም አለ የሟች ደም፡፡ 📚 ያልተፈቀረች ሴት 📚 ✍️ደስአለኝ ቢተዉ ዓይናለም

“የአንድ አገር የኢኮኖሚ ዕጣ ፈንታ፤ በአገሩ ጂኦግራፊ ወይም ባህል ይወሰናል ብለው ለሚያስቡ ወገኖች፤ ዳሮን አቼሞሉና ጀምስ ኤ. ሮቢንሰን ጥሩ ዜና የላቸውም፡፡ ለአንድ አገር የበለፀገ ወይም የደኸየ
“የአንድ አገር የኢኮኖሚ ዕጣ ፈንታ፤ በአገሩ ጂኦግራፊ ወይም ባህል ይወሰናል ብለው ለሚያስቡ ወገኖች፤ ዳሮን አቼሞሉና ጀምስ ኤ. ሮቢንሰን ጥሩ ዜና የላቸውም፡፡ ለአንድ አገር የበለፀገ ወይም የደኸየ መሆን ወሳኙ፤ ሰው ሰራሽ ተቋማት እንጂ፤ የመልክአ ምድሩ አቀማመጥ ወይም የቀደሙ አባቶች እምነት አይደለም፡፡ ከአዳም ስሚዝ እስከ ዳግላስ ኖርዝ ያሉትን የተለያዩ የንድፈ ሐሳብ ምሁራን ሥራዎችን፤ አሁን በዘመናችን እስካሉት የኢኮኖሚያዊ ታሪክ ፀሐፊዎች ያሉትን የምርምር ሥራዎች ወደ አንድ የነጠረ ሀሳብ በማቀናበር አቼሞሉ እና ሮቢንሰን፤ ስሜትን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር የሚችልና በከፍተኛ ደረጃ የሚነበብ መጽሐፍ አዘጋጅተዋል” ​ኒአል ፈርጉሰን፤ የዚአሴንት ኦቭ መኒ ደራሲ ​“ልማትንና እድገትን በተመለከተ፤ የዓለም ዕውቅ ኤክስፐርቶች የሆኑት አቼሞሉ እና ሮቢንሰን፤ አንዳንድ አገሮች ለምን ሀብታሞች ሌሎች ደግሞ ለምን ድሆች እንደሆኑ፤ ሰበቡ የጂኦግራፊ ወይም የበሽታ እንዳልሆነ፤ ነገር ግን የተቋማትና የፖለቲካ ጉዳይ መሆኑን ይገልፃሉ፡፡ ይህ በከፍተኛ ሁኔታ ማንም ሰው ሊያገኘውና ሊጠቀመው የሚችል መጽሐፍ ለባለሙያዎችና ለአጠቃላይ ዕውቀት አንባቢዎች ጥልቅ ግንዛቤን የሚያስጨብጥ ነው” ​ፍራንሲስ ፋኩያማ፤ የዚኤንድ ኦቭ ሂስትሪ ኤንድ ዚላስት ማን ኤንድ ዚ ኦርጂንስ ኦቭ ፖለቲካል ኦርደር፤ ደራሲ 📚መንግስታት ለምን ይወድቃሉ 📚 የሥልጣን፣የብልፅግናና የድህነት ምንጮች ✍️ተርጓሚ፦አያሌዉ ምትኩ ብሩ

#ሁሉም_ኢትዮጵያዊ_ዓሊም_የተስማማበት_የቅዱስ_ቁርአን_የአማርኛ_ትርጉም_የነ__ሐጅ_ሙሀመድ_ሳኒ_ሃቢብና_ሸይኽ_ሰይድ_ሙሐመድ_ሳዲቅ_ትርጉም_ቅጅ_ብቻ_ነዉ‼(ራሕመቱሏሂ ዓለይሂ) ሁለቱ እንቁ የሃገራችን
+3
#ሁሉም_ኢትዮጵያዊ_ዓሊም_የተስማማበት_የቅዱስ_ቁርአን_የአማርኛ_ትርጉም_የነ__ሐጅ_ሙሀመድ_ሳኒ_ሃቢብና_ሸይኽ_ሰይድ_ሙሐመድ_ሳዲቅ_ትርጉም_ቅጅ_ብቻ_ነዉ‼(ራሕመቱሏሂ ዓለይሂ) ሁለቱ እንቁ የሃገራችን ዓሊሞች (ከ1958-1961 ለሦስት አመታት በፈጀዉ የቁርአን የአማርኛ ትርጉም) ቁርአንን ወደ አማርኛ ሲተረጉሙ ከነኚህ ኹለት የሃገራችን እዉቅ ዓሊሞች ጋር በመተባበር ነዉ፦ ሐጂ ፡ በሺር ፡ ዳውድ ፡ ቢ. ኤ. ኤም. ኤ. ከአዝሀር ፡ ዩኒቨርሲቲ ፡ ሼህ ፡ ዑብዳልከሪም ፡ ኑር ፡ ሑሴን ፡ ቢ. ኤ. አዝሀር ፡ ኤም. ኤ. እስክንድሪያ ፡ ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። የአማርኛ ትርጉሙ ተርጉመዉ ሲጨርሱ በጊዜዉ በተለያዩ የሃገራችን ክፍላተ ሃገር ይገኙ የነበሩ ዓሊሞች እንዲያርሙት ያስፈልጋል ስለተባለ፦ #ሸይኽ ፡ ቡሽረልከሪም ፡ ሙስጠፋ፦#ከወሎ ፡ #ሐጂ ፡ ዩሱፍ ፡ ዐብዱረሕማን ፡#ከሐረር #ቃዲ ፡ ሙሐመድ ፡ ዐብዱረሕማን ፡ #ከትግሬ #ሐጂ ፡ አሕመድ ፡ ዳላቲ ፡#ከሸዋ #ሐጂ ፡ መንዛረሁ ፡ ከቢር ፡ ሑሴን ፡#ከዐሩሲ ተመርጠዉ ፡ አብረዉ ፡ አርመዉታል ። በመጨረሻም ፡ ኹሉም ፡ ደጋግመዉ ፡ አርመዉት ፡ በአራሚዎቹ፣በተርጓሚዎቹ በጥቅሉ በዓሊሞች ፡ ተጠባባቂነትና ፡ አራሚነት ፡ በአርቲስቲክ ፡ ማተሚያ ፡ ቤት ፡ በ1961 ዓመተ ልደት ታትሟል። ቁርአኑን ሲተረጉሙ እነኚህን እዉቅ ፡ የቁርዓን ፡ ተፈሲር ኪታቦች ተጠቅመዋል። ​1ኛ ፡ ጀላለይን ፡ ሳዊ ፡ 2ኛ ፡ ተንዊር ፡ አልሚቅባስ ፡ 3ኛ ፡ አቡ ፡ አልሱዑድ ፡ 4ኛ ፡ ኢብን ፡ ጁዘይ ፡ 5ኛ ፡ ነሰፊ ፡ 6ኛ ፡ መራሕ ፡ ለቢድ ፡ 7ኛ ፡ ኻዚን ፡ 8ኛ ፡ ኢብን ፡ ከሢር ፡ 9ኛ ፡ በይዳዊ ፡ #ምስሉ_ላይ_የምትመለከቷቸዉ_ብቻ_ናቸዉ_ትክክለኛ_የነሐጅ_ሙሀመድ_ሳኒ_ሃቢቢ_የቁርአን_ትርጉም በመደብራችን ያገኟቸዋል። #ሁሉም_ኢትዮጵያዊ_ዓሊም_የተስማማበት_የቅዱስ_ቁርአን_የአማርኛ_ትርጉም_የነ__ሐጅ_ሙሀመድ_ሳኒ_ሃቢብና_ሸይኽ_ሰይድ_ሙሐመድ_ሳዲቅ_ትርጉም_ቅጅ_ብቻ_ነዉ‼(ራሕመቱሏሂ ዓለይሂ)

«የቡና ቤት ስዕሎችና ሌሎችም ወጎች»ን በ1976፣ «አዜብና ሌሎች አጫጭር ልቦለዶች»ን በ1982 ያቀረበልን መስፍን ሀብተማርያም፣ «አውደ ዓመት» የተሰኘውን ይህችን የወጎች መድበል ይዞ ብቅ ብሏል፡፡
«የቡና ቤት ስዕሎችና ሌሎችም ወጎች»ን በ1976፣ «አዜብና ሌሎች አጫጭር ልቦለዶች»ን በ1982 ያቀረበልን መስፍን ሀብተማርያም፣ «አውደ ዓመት» የተሰኘውን ይህችን የወጎች መድበል ይዞ ብቅ ብሏል፡፡ ​በእሁድ የመዝናኛ የሬዲዮ ፕሮግራሞች በርከት ያሉ ጽሑፎችን ሲያነብልን የቆየው መስፍን፣ ዛሬ ስምንት የተለያዩ ርዕሶችን አቅርቦልናል፡፡ ጽሑፎቹ የሚያዝናኑ ቁም ነገሮች ናቸው፡፡ እኔ ወድጃቸዋለሁ፡፡ እስቲ እናንተም አስተውሏቸው፡፡ « ዓዉድ ዓመት እና ሌሎችም ወጎቾ»2005, ዓመተ ኢትዮጵያ ✍️ከመስፍን ሀብተማርያም

"...ዝምታ ጸጥ ማለት ብቻ አይደለም።" "...ትልቁ ፍልሚያ ከራስ ጋር ነው።" "...ራስን ለማግኘት፣ ለጥሞና ግዜ፣ ቀጠሮ መስጠት አያሻም።" "...አርምሞ ይኖራል እንጂ አይሰበክም።" "...ብቸኝ
"...ዝምታ ጸጥ ማለት ብቻ አይደለም።" "...ትልቁ ፍልሚያ ከራስ ጋር ነው።" "...ራስን ለማግኘት፣ ለጥሞና ግዜ፣ ቀጠሮ መስጠት አያሻም።" "...አርምሞ ይኖራል እንጂ አይሰበክም።" "...ብቸኝነት ከባድ ጥንካሬ የሚጠይቅ የብልሆች ትምህርት ቤት ነው።" "...እንዳንዴ መንጋገር ካላግባባን ዝምታ ያግባባናል።" "...ተመስጦ የእኔኮ ትዕቢታዊ ትናጋን አክስሞ ወደ ሰፊው ዕርከን ያሻግራል!" "...ያማረው ውስጣዊ የዝምታ ዥረት ዜማ አለው። ይኼ በውጫዊ ጩኸት የማይደፈርስ ዜማ...ነው።" "...ውስጣቸው የተረበሹ ሰዎች ህዝብና ሀገርን ይረብሻሉ።" 📚 አርምሞ 📚 ዶ/ር ኤልያስ ገብሩ አዕምሮ ፪፻፲፬

አዲስ መጽሐፍ እቁብ ምዝገባ ጀምረናል ፍላጎቱ ያላችሁ inbox ኑ ሁለት ምርጫዎች ናቸዉ ያሉት በወር=500 እና በወር 1000 የእቁቡ ቆይታ ጊዜ 6 ወራት ሲሆን በወር 500 ምርጫዉን ያደረገ ሰዉ 5
አዲስ መጽሐፍ እቁብ ምዝገባ ጀምረናል ፍላጎቱ ያላችሁ inbox ኑ ሁለት ምርጫዎች ናቸዉ ያሉት በወር=500 እና በወር 1000 የእቁቡ ቆይታ ጊዜ 6 ወራት ሲሆን በወር 500 ምርጫዉን ያደረገ ሰዉ 500×6=3000 ETB እንዲሁም 1000 ምርጫዉን ያደረገ(የሚጥል) ሰዉ ደግሞ 1000×6=6000 ETB በየወሩ እጣ ይወጣል ባለእድለኛዉ የፈለገዉና የመረጠዉ መጽሐፍ ብሩ በቻለለት መጠን ይወስዳል ማለነዉ፤እቁብተኛዉ ከጣለዉ ብር ላይ ሚቆረጥ ብር የለም። ዉጭም ሃገርም ሆናችሁ እንዲሁም ክፍላተ ሃገር ሆናችሁ መመዝገብ ትችላላችሁ ለመመዝገብ ፍላጎቱ ያላችሁ 👉

ለውጪ ዜጎች ምቾት የሚነሣቸው የእቴጌ ጣይቱ ሰብዕና ብቻ ሳይሆን ሴት የእዚህን ያህል ሥልጣን ሲኖራት ማየታቸውም ጭምር ነው። የአውሮጳውያኑ ነገሥታት ሚስቶች ዋናኛ ሥራ ፓርቲ መደገስ፣ ሪቫን መቁረጥ
ለውጪ ዜጎች ምቾት የሚነሣቸው የእቴጌ ጣይቱ ሰብዕና ብቻ ሳይሆን ሴት የእዚህን ያህል ሥልጣን ሲኖራት ማየታቸውም ጭምር ነው። የአውሮጳውያኑ ነገሥታት ሚስቶች ዋናኛ ሥራ ፓርቲ መደገስ፣ ሪቫን መቁረጥ ነው። የህንዶች ንግሥተ ነገሥታት፣ የእንግሊዝ ንግሥት የሆነችው ቪክቶሪያ እንኳን አስተያየት ከማቅረብ ባለፈ በመንግሥታዊ አሠራሮች ያላግባብ ጣልቃ አትገባም። ​የብዙዎቹ ዲፕሎማቶች፣ ነጋዴዎች እና ተጓዦች አጭበርባሪነት እና አታላይነትን ከግምት ውስጥ እናስገባ። እቴጌ ጣይቱ እነሱን በጥርጣሬ ማየታቸው የሚያስገርም ነውን? አሳቸው በመልእክተኛው መልካም ባሕሪ ወይም ደግነት በቀላሉ ተሸንሽፈው ስምምነቶችን የመፈጸም አዝማማያ ያላቸው ሚኒሊክ ላይ አስፈላጊውን ቁጥጥር አድርገዋል። በመጨረሻም በአሳቸው ስምምነት፣ ምኒልክ የኢትዮጵያን ድንበሮች፣ የንግድ እና ዲፕሎማሲ ግንኙነቶች የወሰኑትን ስምምነቶች በሙሉ ተፈራርመዋል። «የምኒልክ ጊዜ» በበርካታ አስደናቂ ኩነቶች የተሞላ ሲሆን፣ ከእነዚህም አንዱ የጣይቱ ወሳኝ የታሪክ ተዋናይ ሆነው መውጣት ነው። ይህ ምኒልክ ከነገሠበት 1889 እስከሞተበት 1913 ያለው ጊዜ «የምኒልክ እና የጣይቱ ዘመን» ተብሎ እንደገና መሰየም ያለበት ሲሆን፣ አቆጣጠሩ ተሻሽሎም ከተጋቡበት 1883 የምኒልክ አእምሯዊ ብቃት እስከደከመበት እና ጣይቱ እስከ ወረዱበት 1910 መሆን ይገባዋል። ​ከመጽሐፉ የተወሰደ

“ጠዋት ከእንቅልፍህ ስትነቃ ለራስህ እንዲህ ብለህ ንገረው፦ ዛሬ የማገኛቸው ሰዎች ጣልቃ ገቦች፣ ምስጋና ቢሶች፣ ትዕቢተኞች፣ ከሓዲዎች፣ ምቀኞችና ርህራሄ የሌላቸው ሊሆኑ ይችላሉ። እንዲህ የሆኑት መል
“ጠዋት ከእንቅልፍህ ስትነቃ ለራስህ እንዲህ ብለህ ንገረው፦ ዛሬ የማገኛቸው ሰዎች ጣልቃ ገቦች፣ ምስጋና ቢሶች፣ ትዕቢተኞች፣ ከሓዲዎች፣ ምቀኞችና ርህራሄ የሌላቸው ሊሆኑ ይችላሉ። እንዲህ የሆኑት መልካሙን ከክፉው መለየት ስለማይችሉ ነው። እኔ ግን የመልካምን ነገር ውበትና የክፉንም ነገር አስቀያሚነት አይቻለሁ፤ ስለዚህ አንዳቸውም ሊጎዱኝ አይችሉም።” ​“ሰዎች ለመረጋጋት ሲሉ ከከተማ ወጥተው ወደ ገጠር፣ ወደ ባህር ዳርቻ ወይም ወደ ተራራ መሸሽ ይፈልጋሉ። አንተም ይህንኑ ትመኛለህ። ነገር ግን ይህ ሞኝነት ነው፤ በፈለግከው ሰዓት ወደ ራስህ ውስጥ ተመልሰህ ከሁሉም ነገር መራቅ ትችላለህና። ከገዛ ነፍስህ የበለጠ ሰላማዊና ከረብሻ የጸዳ ማረፊያ የለም።” ​“ይህ ነገር ሁሌም ይገርመኛል፦ ራሳችንን ከሌሎች ሰዎች ይልቅ አብልጠን እንደምንወድ የታወቀ ነው። ሆኖም ስለ ራሳችን ከምናስበው ይልቅ ሌሎች ስለ እኛ ስለሚያስቡት እንጨነቃለን። መልአክ ወይም ጠቢብ ሰው ተገልጦልን ‘በልብህ የምታስበውን አትደብቅ፤ ወዲያውኑ ውጣና ተናገረው’ ቢለን፣ አንዲት ቀን እንኳ አንዘልቅም ነበር። ለራሳችን ካለን እውነተኛነት ይልቅ የሌሎች አስተያየት ያንን ያህል ይገዛናል።” ​ከመጽሐፉ የተወሰደ

የሰው ልጆች ከእንስሳት ከሚለዩባቸው ባሕርያት መካከል ከፍ ያለ አስተሳሰባቸው፣ የመምራትና የማስተዳደር አቅማቸው፣ የመኖሪያ አካባቢያቸውን የማልማት፣ የማጽዳትና ምቹ የማድረግ ችሎታቸው፣ ማህበራዊ ግን
የሰው ልጆች ከእንስሳት ከሚለዩባቸው ባሕርያት መካከል ከፍ ያለ አስተሳሰባቸው፣ የመምራትና የማስተዳደር አቅማቸው፣ የመኖሪያ አካባቢያቸውን የማልማት፣ የማጽዳትና ምቹ የማድረግ ችሎታቸው፣ ማህበራዊ ግንኙነታቸውን ምቹ ለማድረግ ሕግና ደንብ አውጥተው መተዳደራቸውና የመሳሰሉት ናቸው። በመሆኑም ሰዎች ማህበራዊ ግንኙነታቸውን፣ ፖለቲካቸውንና ኢኮኖሚያቸውን ችግር የሌለበትና ፍትሐዊ ለማድረግ ሣሳብ ይለዋወጣሉ፣ ይከራከራሉ፣ ይበጃል በተባለ ሣሳብ ላይ ይስማማሉ። ይህም የሚሆነው ኑሯቸውን ከስጋት የጸዳ፣ መተማመንና ፍቅር ያለበት፣ ፍትህ የሰፈነበት፣ በጥቅሉ ምቹ ለማድረግ ነው። እነዚህን መሰረታዊ ፍላጎቶች ለማሟላት በሁለት ግለሰቦችም ሆነ በማህበረሰብ መካከል ተግባቦት ዋና ነገር ነው። ​የተግባቦት ቁልፍ ደግሞ መነጋገር ነው። አለመነጋገር ስለሌላው ግለሰብ፣ ስለቡድን፣ ስለማህበረሰብና ስለአገር ትክክለኛ ግንዛቤ ማዳበር አለመቻልን ብቻ ሳይሆን በግምት ላይ የተመሰረተ አሉታዊ ስሜትንና አለመግባባትን፣ መለያየትን፣ ጦርነትን፣ ጥፋትን ሊያስከትል ይችላል። ይህንን እውነት የሚያረጋግጡልን በዓለም ላይ ብዙ ታሪካዊ ክስተቶች አልፈዋል፤ በዚህ ዘመንም በአገራችንና በዓለም ዙሪያ እየሆኑ ያሉ አጥፊ ተግባሮች ነባራዊ ምስክሮች ናቸው። በዚህ ርዕስ ዙሪያ እኛ ኢትዮጵያውያን ግንዛቤያችንን እንድናዳብርና እንድንጠቀምበት የተግባቦትና የስነልቦና ባለሙያ የሆነው ዶ/ር ሳሙኤል ወልዴ በዘመኑ የተግባቦትና የስነልቦና ሳይንሳዊ ቲዎሪዎች አስደግፎ ስለመነጋገር ጥቅምና አስፈላጊነት ያተተባትን ይህችን መጽሐፍ አበርክቶልናል። ማንበብ የሚችሉ የአገራችን ሰዎች ሁሉ አንብበው ግንዛቤያቸውን እንዲያዳብሩ ምክሬን አስተላልፋለሁ። ​ፕሮፌሰር አታላይ ዓለም አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኢትዮጵያ

ደራሲ አጋዝ ገብረየሱስ ኃይለማርያም በአገራችን የፕሬስ ነጻነት ባልነበረበት፣ ቴክኖሎጂ ባልተስፋፋበትና በጉራግኛ ቋንቋ ለመጻፍ የሚያስችል የጉራግኛ የፊደል ገበታ ባልተቀረጸበት ወቅት ረዥም ልብወለድ
ደራሲ አጋዝ ገብረየሱስ ኃይለማርያም በአገራችን የፕሬስ ነጻነት ባልነበረበት፣ ቴክኖሎጂ ባልተስፋፋበትና በጉራግኛ ቋንቋ ለመጻፍ የሚያስችል የጉራግኛ የፊደል ገበታ ባልተቀረጸበት ወቅት ረዥም ልብወለድ መጽሐፎችን ለንባብ ያበቁ እንቁ ኢትዮጵያዊ ናቸው። በተለይ የጉራግኛ ቋንቋና ባህል እንዲሁም የጉራጌ ብሔር የአኗኗር ዘዴና የሥነ ልቦና ውቅር በጉራግኛ፣ በአማርኛና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎች በመጻፍ ለኢትዮጵያና ለዓለም ያስተዋወቁ ባለውለታም ናቸው። "ለምስጋና ወይም ለእውቅና ሳይሆን ሁሉም ኅሊናን የሚያስደስት ሥራ መሥራትን፣ አዳዲስ ሥራ መፍጠርን እንጂ የተለመደና የተቀዳ ሥራ አያስደስተኝም" የሚሉት እኚህ ደራሲ የአእምሯቸው ጭማቂ የሆኑ በርካታ የድርሰት ሥራዎቻቸው ለተደራሲያን ያቀረቡ ታላቅ ሰው ናቸውና ላመሰግናቸው እወዳለሁ። የጫሙት ሽካ 📚 የአገኪ 📚 የተሰኙ ረዥም በጉራጊኛ ቋንቋ የተፃፉ መጽሐፍት ፀሀፊ ​መሠረት አመርጋ፣ የጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ

መጀመሪያ የሰው ልጅ እሳትን አላመደ። ምድጃውን ዘረጋ። በእሳቱ ፍላጻ ነጻ እና ቁጡ መዋነብ በወጋገኑ ትርዒት ሕብር ነፍሱ ማለለች። በምድጃው ዙሪያ - ብርሃን - ጨልጦ - ሰከረ - ። እዚያ ተረቱን፤
መጀመሪያ የሰው ልጅ እሳትን አላመደ። ምድጃውን ዘረጋ። በእሳቱ ፍላጻ ነጻ እና ቁጡ መዋነብ በወጋገኑ ትርዒት ሕብር ነፍሱ ማለለች። በምድጃው ዙሪያ - ብርሃን - ጨልጦ - ሰከረ - ። እዚያ ተረቱን፤ ታሪኩን፤ ገድሉን፤ ምኞቱን፤ መሻቱን አደራ። ደመነፍሱን አነቃ። ጥንታዊና መሠረታዊ የሆኑ የሰው ልጅን የደመነፍስ ስሪት አንጓዎች በተረቶቹ ቀመረ። ሸመነ። የታሪክ ነጋሪውን አሀዱ የጀመረው እንዲህ ሆነ። «ብርሃንን ጨልጦ መስከር» 📚📚📚 👉✍️ያዕቆብ ብርሃኑ

ጣይ እና አንሺ ​ደሞዙን ቢጥል አንስተው ጠጡበት ባርኔጣውን ቢጥል ወስደው ደመቁበት ከዘራውን ቢጥል ተመረኮዙበት በሄደበት ሁሉ እየተከተሉ በጣለው ሲያጌጡ በጣለው ሲያተርፉ ራሱን ሲጥል ግን አይተውት
ጣይ እና አንሺ ​ደሞዙን ቢጥል አንስተው ጠጡበት ባርኔጣውን ቢጥል ወስደው ደመቁበት ከዘራውን ቢጥል ተመረኮዙበት በሄደበት ሁሉ እየተከተሉ በጣለው ሲያጌጡ በጣለው ሲያተርፉ ራሱን ሲጥል ግን አይተውት አለፉ:: ✍️በእዉቀቱ ስዩም

photo content

መስፍን ማሞ «እነሆ 'የእንስሳት አብዮት' …» ብሎናል። ከዝነኛዉ እንግሊዛዊ ደራሲ ከጆርጅ ኦርዌል "Animal Farm" ወደአማርኛ ቋንቋ የመለሰው አዲስ መታያዉ ነው። ይህ ሥራ በብዙ የዓለማችን ቋ
መስፍን ማሞ «እነሆ 'የእንስሳት አብዮት' …» ብሎናል። ከዝነኛዉ እንግሊዛዊ ደራሲ ከጆርጅ ኦርዌል "Animal Farm" ወደአማርኛ ቋንቋ የመለሰው አዲስ መታያዉ ነው። ይህ ሥራ በብዙ የዓለማችን ቋንቋዎች እየተተረጎመ፤ ትርክቱና የፈጠራው ይትብሃል ሁሉም ተደራሲን እያስደመመ የሚኖር ምጸት ሰንቄ ሥራ ነው። ተርጓሚ መስፍን ማሞ እንደወትሮው ሁሉ ዓይነ ግቡ ብዕርተኛ መሆኑን በዚህ የትርጉም ሥራውም ላይ አሳይቷል፤፤ ይህንን ዘመን ጠገብ ሥራ ውብ በሆነ አማርኛ ታድጎናል፤፤ ፈረንጅኛ ስም የያዙት ገጸ ባሕርያት ብቅ እያሉ ሲያነቡን ኑረው ልክ አዲስ የአማርኛ ወጥ ሥራ እየተደረስን ያለን ያህል ይሰማናል፤፤ ይህ ደግሞ ከመነሻ ቋንቋው የጠበቀበት አማርኛው የሸገነ መሆኑን የምናስተውለው፤ ያለ እረፍት ከገጽ ገጽ ስንፈተለክ ራሳችንን ማግኘታችን ነው፤፤ ተርጓሚው፤ «የእንስሳት እድር»

A lonely government clerk - shy, awkward, blundering - finds himself pursued by a mysterious stranger. Somehow he looks familiar. In fact, he realizes, he looks exactly like him. He even has the same name. But, unlike him, he is charming and confident. Soon the stranger starts insinuating himself into his life. He works at his office, stays at his apartment, ingratiates himself with his colleagues. No one seems surprised. Who is he? What does he want? Is he a double, or something darker altogether? ​Moscow-born Fyodor Dostoyevsky (1821-1881) served time in a convict prison in Siberia for his political alliances, and in his later years his passion for gambling led him deeply into debt. His many brilliant novels include Crime and Punishment, The Idiot and The Brothers Karamazov. ​Ronald Wilks has translated numerous Russian volumes for Penguin Classics, including works by Chekhov, Sologub, Tolstoy and Gogol. If you enjoy this novel, you may want to read more by Dostoyevsky - his major novels and stories are all available in Penguin Classics, including Notes from Underground, Crime and Punishment, The Gambler and Other Stories, The Idiot, Demons, Netochka Nezvanova, The Brothers Karamazov, Poor Folk and Other Stories, The House of the Dead and The Village of Stepanchikovo.