Diinii kee Anaakara (Md Ali)
رفتن به کانال در Telegram
دروس وفتاوي ومحاضرات باللغة العفرية ★Diini barittooy, fatwaa kee Daqwa Qafar afat Tû mabul=> @Anaakar or @acmadxalol
نمایش بیشتر1 614
مشترکین
+224 ساعت
+87 روز
+2030 روز
آرشیو پست ها
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የወረቀት ብር ኖት ዘካ
~
በጥንት ዘመን ሰዎች ግብይት የሚፈፅሙት እቃን በእቃ በመለዋወጥ ነበር። የልውውጥ ገበያ ለአጠቃቀም አስቸጋሪ በመሆኑ የተነሳ ቀስ በቀስ እየቀዘቀዘ ሄዶ አንዳንድ እቃዎችን (ለምሳሌ በሃገራችን አሞሌ ጨው) እንደመገበያያ ገንዘብ በመጠቃቀም ተተካ። ይሁን እንጂ እነዚህ እቃዎች ለአያያዝ አስቸጋሪ በመሆናቸው የተነሳ ሰዎች ወደ ሌሎች አማራጮች ማማተር ይጀምራሉ። በዚህም የተነሳ ነበር ወርቅና ብር ለመገበያያነት መዋል የጀመሩት። ወርቅና ብር ታዲያ በጊዜ ሂደት በአንጣሪዎች አማካኝነት ተመሳሳይ መጠንና ክብደት እንዲይዙ ተደርገው ለአስተማማኝነታቸው ማህተም ዲዛይን ተደርጎባቸው መዘጋጀት ያዙ። እነዚህን ገንዘቦች ለደህንነታቸው በመስጋት ገንዘብ መንዛሪዎችና አንጥረኞች ዘንድ በማስቀመጥ መተማመኛ ደረሰኞችን በምትካቸው ይቀበሉ ነበር። ሰዎች በነዚህ ድርጅቶች ላይ ያላቸው እምነት በጨመረ ቁጥር ደርሰኞቹ በግብይት ላይ ለክፍያ መዋል ያዙ።
የወረቀት ብር ኖት ታሪካዊ አነሳሱ በዚህ መልኩ ነበር። በጊዜው እነዚህ ከገንዘብ መንዛሪ ድርጅቶች የሚመጡ ወረቀቶች ሰውየው በነዚህ የግል ድርጅቶች ዘንድ ወርቅ/ ብር እንዳስቀመጠ በመግለፅ ወረቀቱን የተቀበለ ሰው ሄዶ ወርቁን/ ብሩን መውሰድ እንደሚችል ከመጠቆም ባለፈ ኦፊሴላዊ ይዘትም ሆነ የህግ ከለላ አልነበራቸውም። አገልግሎታቸው በሰፋ ቁጥር ግን በጊዜ ሂደት መንግስታት የህግ ሽፋን ሊሰጡ ግድ ብሏቸዋል። በዚህን ጊዜ የታወቀ ተመን በመስጠት ላምጪው እንዲከፈል አስገዳጅ ህግ ወጣ። የማተሙ/ የማሳተሙ ኃላፊነትም የመንግስታት ሆነ። ይህ ነገር የተጀመረው በ1833 እንደሆነ ድርሳናት ይጠቁማሉ። (ዘመኑ በሙሉ እንደ ጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር ነው።)
መንግስታት ካላቸው ተቀማጭ የወርቅ መጠን በላይ እነዚህን የወረቀት መገበያያዎች ገበያ ላይ ሲያቀርቡ ጊዜ ግን በነባሩ የወርቅ መገበያያ ላይ ፈተና ተደቀነ። በዚህን ጊዜ የወረቀት መገበያያዎችን ወደ ወርቅ ከመቀየር የሚከለክል ህግ መውጣት ያዘ። በዚህ ረገድ ቀዳሚዋ ብሪታኒያ ስትሆን ይህ የሆነውም በ1931 ነበር። አሜሪካ በ1934 ተከተለቻት። የክልከላው ተግባራዊነት ግን ድንበር ተሻጋሪ ሳይሆን በሃገራቱ ውስጥ የተገደበ ነበር። ሃገራት ከሃገራት ጋር ሲገበያዩ ግን የወረቀት ብሩን ወደ ወርቅ የመቀየር ውላቸውን ይጠብቁ ነበር። ከ1971 ጀምሮ ግን የወርቅ መጠን እያነሰ ስለመጣ አሜሪካ ይህንኛውን አሰራር ጭምር አቆመች። የመጨረሻው ወርቅን ለግብይት ተመን የመጠቀም አሰራር በዚህ መልኩ ተዘጋ።
የወረቀት ብር ኖት እነዚህን ታሪካዊ ለውጦች በማሳለፉ የተነሳ ምንነቱን በመግለፅ ላይ የኢስላም ምሁራን እይታቸው ሊለያይ ችሏል። የብዙሃን ዑለማዎችን አቋም ብቻ ሳሰፍር የወረቀት ብር ማለት እራሱን የቻለ የተለየ መገበያያ ገንዘብ ሲሆን ወርቅና ብርን (ሲልቨር) የሚመለከቱ ህጎች ይመለከቱታል። የየሃገራቱ የወረቀት ኖት እራሱን የቻለ አንዱ ከሌላው የሚለይ ገንዘብ ነው። ለማሳጠር ስል ለዚህ ትርጓሜ የሚውሉ አጋዥ መረጃዎችን አልጠቅስም።
እነዚህ የወረቀት ብር ኖት ሲጀመሩ አካባቢ ዘካ ይወጅብባቸዋል ወይስ አይወጅብባቸውም በሚለው ላይ በኢስላም ምሁራን መካከል ውዝግብ ተከስቶ ነበር። የልዩነቱ መነሻ ለዚህ ገንዘብ ምንነት የተሰጡ ትርጓሜዎች መለያየት ነበር። ነገር ግን ይሄ መገበያያ በከፍተኛ መጠን በመስፋፋቱና የወርቅና የብርን ቦታ በመተካቱ የተነሳ ውዝግቡ ሙሉ ለሙሉ በሚባል መልኩ ከስሟል። ስለዚህ ትኩረታችን ይህ የወረቀት ብር ኖት ለዘካ መጠን በሚደርስበት መነሻ ተመን (ኒሷብ) ላይ ይገደባል ማለት ነው።
የወረቀት ብር ኖት ዘካ የሚወጅብበት መነሻው ተመን (ኒሷብ) ስንት ነው? በዚህ ላይ ሶስት የተለያዩ ሃሳቦች ተሰንዝረዋል።
አንደኛ:– የወረቀት መገበያያ ኖት መነሻ የዘካ ተመን የብር (ሲልቨር፣ ፊዷ) ኒሷብ ነው ያሉ አሉ። ይህም 200 ዲርሃም ማለትም 595 ግራም ነው።
ሁለተኛ:– ኒሷቡ የወርቅ ኒሷብ ማለትም 20 ዲናር ውይም 85 ግራም ነው ያሉም አሉ።
ሶስተኛ:– መነሻው መጠን ከወርቅና ከብር መነሻ ተመኖች ዝቅ ያለው ነው ያሉም አሉ።
ከሶስቱ ሃሳቦች ውስጥ ሶስተኛው ሚዛን የሚደፋ እንደሆነ በርካታ ዑለማዎች ደምድመዋል። መነሻቸውም:–
1ኛ፦ ድሃዎቹን የተሻለ ተጠቃሚ ያደርጋል።
2ኛ፦ ለዘካ አውጪውም ከውዝግብ ቀጠና ለመውጣት፣ ከተጠያቂነት ስጋት ለመትረፍ ይበልጥ ሰላማዊ ነው።
3ኛ፦ የመጀምሪያዎቹን ሁለት አቋሞች ያንፀባረቁ ምሁራን የሚያቀርቧቸውን መርጃዎችና ትንታኔዎች አንፃራዊ በሆነ መልኩ የተሻለ የሚያቀራርብ ነው።
4ኛ፦ ለዚህ የወረቀት መገበያያ ኖት የዘካ ተመን ከወርቅና ከብር (ሲልቨር) አንዱን መጠቀም ግድ ከሆነ ከሁለት አንዱ ቀድሞ የደረሰውን ኒሷብ በምን አሳማኝ መነሻ ልንዘለው እንችላለን? እንደሚታወቀው የብር (ሲልቨር) ኒሷብ ዛሬም በነብዩ ﷺ ዘመን ከነበረው አይቀየርም። ዛሬም እንደ ጥንቱ 200 ዲርሃም ማለትም 595 ግራም ብር ያለው ሰው ዘካ ማውጣት ግድ ይለዋል።
ይህ አቋም የሰዑዲያ የታላላቅ ዑለማእ ምክር ቤት፣ የእውቀታዊ ምርምር ቋሚ ኮሚቴ (ለጅነተ ዳኢማህ)፣ በራቢጦተል ዓለሚል ኢስላሚ ስር ያለው ቀራረል መጅመዒል ፊቅሂይ እና የሌሎችም ምርጫ ነው።
የዘንድሮ የወረቀት ብር ዘካ መነሻ (ሂሳብ) ስንት ነው?
`
በሰው በሰው የሰማኋቸው ዋጋዎች ስለተራራቁብኝ መረጃ ለመስጠት አልደፈርኩም። ስለዚህ ጉዳዩ የሚያሳስበው አካል ወቅታዊን የወርቅና የብር ዋጋ አጣርቶ ዝቅ ያለውን መነሻ በማድረግ በራሱ ማስላት ይችላል። የዘካ መጠኑም ለዘካ መጠን ከደረሰው ገንዘብ ላይ 2.5% ነው። በምሳሌ ግልፅ ለማድረግ ያክል፦
1– አመት የዞረ 300,000 ብር ያለው ሰው የ 300,000ን 2.5% ያወጣል፡፡ 300,000 x 0.025=7,500 ብር
2– አመት የዞረ 450,000 ብር ያለው ሰው የ 450,000ን 2.5% ያወጣል፡፡ 450,000 x 0.025=11,250 ብር
3– አመት የዞረ 5 ሚሊዮን ብር ያለው ሰው የ 5,000,000ን 2.5% ያወጣል፡፡ 5,000,000 x 0.025=125,000 ብር ይሆናል ማለት ነው። ወይም ደግሞ አጠቃላይ ገንዘቡን ለ40 ቢያካፍለው ማውጣት ያለበትን የዘካ መጠን ይሰጠዋል። የቀረቡትን ምሳሌዎች ለ40 ቢያካፈል ተመሳሳይ መጠን ያገኛል።
.
(ረመዳን 15/1442፣ ሚያዚያ 20/ 2013)
ትንሽ ተነካክቶ በድጋሜ የተለጠፈ
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ዘካ የሚሰጠው ለምን አይነት ሰው ነው?
~~~
የዘካ ባለሐቆች 8 ናቸው። በቁርኣን እንዲህ ተዘርዝረዋል:–
(إِنَّمَا الصَّدَقَاتُ لِلْفُقَرَاءِ وَالْمَسَاكِينِ وَالْعَامِلِينَ عَلَيْهَا وَالْمُؤَلَّفَةِ قُلُوبُهُمْ وَفِي الرِّقَابِ وَالْغَارِمِينَ وَفِي سَبِيلِ اللَّهِ وَابْنِ السَّبِيلِ ۖ فَرِيضَةً مِنَ اللَّهِ ۗ وَاللَّهُ عَلِيمٌ حَكِيمٌ)
"ግዴታ ምጽዋቶች (የሚከፈሉት) ለድሆች፣ ለምስኪኖችም፣ በርሷም ላይ ለሚሰሩ ሰራተኞች፣ ልቦቻቸውም (በእስልምና) ለሚለማመዱ፣ ጫንቃዎችንም (በባርነት ተገዢዎችን) ነፃ በማውጣት፣ በባለ እዳዎችም፣ በአላህ መንገድም በሚሰሩ፣ በመንገደኛም ብቻ ነው፡፡ ከአላህ የተደነገገች ግዴታ ናት፡፡ አላህም አዋቂ ጥበበኛ ነው፡፡" [አተውባ: 60]
መጠነኛ ማብራሪያ
① ድሃ ማለት:– ለመኖር (ልብሱ፣ ጉርሱ፣ ትዳር ለመመስረት፣ ለመማር፣) ምንም ነገር የሌለው ወይም ትንሽ ነገር ያለው ማለት ነው። እነዚህን ፍላጎቶች ለማሟላት ዘካ ሊሰጠው ይችላል።
② ምስኪን ማለት: – ለመኖር የሚሆን ነገር በተወሰነ መጠን ያለው ሲሆን የሚበቃው ግን አይደለም።
③ ዘካ ላይ የሚሰሩ ሰራተኞች:– ዘካ እንዲሰበስቡ በመሪ የሚላኩ ሰዎች ናቸው። ዘካ ሶስት ነገሮችን ይፈልጋል። መሰብሰብ፣ መጠበቅና ማከፋፈል። በሶስቱም ዘርፍ ላይ የሚሰማሩ ሰራተኞች ሃብታም ቢሆኑ እንኳ ዘካ ይሰጣቸዋል።
ልብ በሉ! ለዚሁ ስራ በመንግስት የሚሾሙትን እንጂ የግለሰቦች ወኪሎችን አይመለከትም። ደሞዝተኛ ሰራተኛም እዚህ ውስጥ አይገባም።
④ ልቦቻቸው (በእስልምና) የሚለማመዱ ማለት ሁለት አይነት ናቸው።
አንደኛ፡- ሙስሊም ያልሆነ ሰው ነው። ሙስሊም ባይሆንም ለተሻጋሪ ፋይዳ ሲባል ነው ሊሰጠው የተፈቀደው።
– ቢሰጠው ይሰልማል ወይም ሌላ ፋይዳ ይገኝበታል ተብሎ ተስፋ የሚጣልበት ከሆነ፣
– የሚያደርሰው ጉዳት ኖሮ በዚህ ማስቆም የሚቻል ከሆነ
ሁለተኛ፡- ሰለምቴ ነው።
– በዲኑ እንዲጠነክር ወይም ለሌላ ሰው መስለም/ መጠንከር ሰበብ ይሆናል ተብሎ ከተገመተ
– በሙስሊሞች ላይ ጉዳት የሚያደርስ ሆኖ በዚህ ማስቆም የሚቻል ከሆነ። [መጅሙዑል ፈታዋ፣ ኢብኑ ተይሚያ: 28/290]
⑤ እራሳቸውን ከአሳዳሪዎቻቸው በመግዛት ነፃ ለማውጣት የሚጣጣሩ ባሪያዎች ዘካ ከሚገባቸው ናቸው።
የተጠለፉ/ የተማረኩ ሙስሊሞችን ማስለቀቅም ከዚሁ ውስጥ ይካተታል።
⑥ ባለ እዳ:– የተጣሉ ሰዎችን ለማስታረቅ አስቦ እዳ የገባ ሰው ሃብታም እንኳን ቢሆን ዘካ ሊሰጠው ይችላል።
በራሱ ጉዳይ እዳ የተጫነው ከሆነ በኑሮው ባይቸገር እንኳ እዳውን ለመክፈል ሊሰጠው ይችላል።
⑦ በአላህ መንገድ የሚሰራ ማለት:– ለጂሃድ ዘማች ማለት ነው። ለትጥቅ፣ ለስንቅና አጠቃላይ ዝግጅት ዘካ ይሰጣል።
⑧ መንገደኛ:– አገሩ መግቢያ ከዘካ ገንዘብ ይሰጠዋል።
(ኢብኑ ሙነወር፣ መጋቢት 26/2013)
የቴሌግራም ቻናል :-
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የዘካ ፋይዳዎችና ዘካን ያለመስጠት አደጋዎች!
~~~~~~~~
ዘካ ለሰጪው የሚያስገኛቸው ፋይዳዎች፡-
① ዘካ ከአምስቱ የኢስላም ምሰሶዎች አንዱ እንደመሆኑ በትክክል የሚሰጥ ሰው ይህን የኢስላሙን ምሰሶ ነው ያፀናው። ባይሰጥ ደግሞ ይህን ምሰሶውን ነው ያናጋው።
② ዘካ በኢኽላስ እስከተወጣ ድረስ ኢማንን ይጨምራል፤ የአላህን ውዴታ ያጎናፅፋል።
③ ዘካ ወንጀልን ያብሳል። ነብዩ ﷺ "ውሃ እሳትን እንደሚያጠፋው ሶደቃ ሃጢአትን ያጠፋል" ብለዋል።
④ ዘካ ፈተናን መከራን ይመክታል።
⑤ ዘካ ማውጣት የአዛኝነት፣ የርህሩህነት፣ የተቆርቋሪነት ባህሪን ያላብሳል። ዛሬ ራስ ወዳድነት በነገሰበት ዘመን ለሙስሊም ወገን ከምላስ ባለፈ ከልብ መቆርቆርና ማዘን የእውነት ትልቅ መታደል ነው።
⑥ ዘካ የቀልብ መለዘብና በሞራል መገራትን ያጎናፅፋል። ከክፋት፣ ከስስት፣ ከድንበር ዘለል የዱንያ ፍቅር እንዲወጡ ሰዎችን ያግዛል።
⑦ ዘካ የህሊና እርካታን ፣ መንፈሳዊ ሰላምን፣ ስነ ልቦናዊ መረጋጋትን ያጎናፅፋል።
⑧ ዘካ ገንዘብን ያፋፋል፣ በረካ ይጨምርበታል።
⑨ ዘካ ለችግር ጊዜ ደራሽ ወገን እንዲኖረንም ይጠቅማል። መቼም ሁሌ ድሎት፣ ሁሌ ምቾት የለም። ዱንያ ተገለባባጭ ናት።
ለተቀባዩ ያሉት ፋይዳዎች:–
~~~~~
① በዘካ ድሃዎች ይደጎማሉ ወይም ይቋቋማሉ።
② ሃብታሙን በቅናትና በክፋት ከማየት እንዲታቀቡ ያግዛቸዋል።
③ ይህን የሚደጎሙበትን ህግ ለዘረጋው ጌታ ውዴታ ለሃይማኖታቸውም ቀናኢነትን እንዲያሳድሩ ይጠቅማቸዋል። ይህ ሳይሆን ሲቀር ግን ከፊሉ ጌታውን ሊያማርር፣ ኢማኑ ሊሸረሸር ይችላል።
④ ለገንዘብ ሲሉ እምነታቸውን ከመሸጥ፣ በጥፋት ላይ ከመሰማራት ያቅባቸዋል።
የዘካ ማህበራዊ ፋይዳዎች
~~~
① በሰጭና በተቀባይ መካከል ትስስር እንዲጠነክር ያደርጋል። ዝምድናን ይቀጥላል። የሰመረ ጉርብትና እንዲኖር ያግዛል። ምክንያቱም ነፍስ በጎ ለዋለላት አካል ተዘንባይ ነችና።
② ዘካ በአግባቡ ከተወጣ በሀብታሙና በደሃው መካከል ያለውን የሃብት ርቀት ስለሚያጠብ ለጤናማ ኢኮኖሚ የማይናቅ አስተዋጽኦ ያበረክታል።
③ ዘካ ከድህነት ወለል በታች ያሉ ወገኖች ተስፋ በመቁረጥ ወደ ስርቆትና ዝርፊያ በማምራት ማህበራዊ ቀውስ እንዳይፈጥሩ ይታደጋል።
④ ዘካ ሀብታሙን ሃላፊነት እንዲሰማው ስለሚያደርግ ከስግብግብ የካፒታሊዝም አስተሳሰብ በማቀብ የሃገር ሐብት በጥቂቶች እጅ ብቻ እንዳይሆን ያግዛል።
ዘካ አለመስጠት ያለው አደጋ
~~~~~
ባጭሩ እስካሁን የተዘረዘሩትን ፋይዳዎች ያሳጣል። የዱንያም የአኺራም ኪሳራን ያስከትላል። ሰጪንም፣ ተቀባይንም፣ ማህበረሰብንም አገርንም ይጎዳል።
ወገኔ ሆይ! ዘካ ወጅቦብሀል? እንግዲያውስ ውለታ ቢስ አትሁን። ላንተ የሰጠህ ጌታ ነው "ስጥ" ብሎ ያዘዘህ። በሰፊው ከሰጠህ ነው ጢኒጥየ ቆንጥረህ ስጥ ያለህ። ልብህ ፈታ ብሎ፣ ደስ ብሎህ ስጥ። ደስ እያለህ ጀነትን ትወርሳለህ።
ደግሞ አትሸወድ! ዘካ ገንዘብህን ያፋፋዋል እንጂ አይቀንሰውም። ነብዩ ﷺ "የአንድን ባሪያ ገንዘብ ሶደቃ አይቀንሰውም" ብለዋል።
በነገርህ ላይ የዘካው መጠን ያንተ ድርሻ፣ ያንተ ገንዘብ አይደለም። ዘካውን ባስቀረህ ጊዜ የሰው ሐቅ እየበላህ እንደሆነ ይታወቅህ። አይሰቀጥጥም? "ላቤን ጠፍ አድርጌ ያመጣሁት ነው" እያልክ የምትጎረር ከሆንክ ግን የነ ቃሩን ባቡር ላይ ተሳፍረሀል። ወዴት እንደሚወስድህ አልነግርህም።
ወንድሜ! ያገኘኸሁ ባንተ ብልጠትም ብቃትም አይደለም። ስንት የበቁ የነቁ በድህነት እየማቀቁ መሰለህ?! ስንት መንቻካ ዶክተሮች ፕሮፌሰሮች እንዳሉ ሁሉ ስንት ቁልቁል መደመር የማይችሉ ቱጃሮች አሉ?!
ይልቅ ልንገርህ! ሌሎችን በድህነት የሚፈትነው ጌታ አንተን በሃብት እየፈተነህ ነው። እራስህ በምታዝበት ገንዘብ ፈተናውን ከወደቅክ አሳዛኝ ክሽፈት ነው። ገንዘብህ ተከትሎህ ቀብር አይገባም። ወራሽ ወገኖችህ የቀብር ጥያቄን፣ የአላህን ምርመራ አይታደጉህም። ዛሬ ነገ አትበል! ሞት አለቅጥ የበዛበት ዘመን ላይ ነን። እንደ ወጣ የሚቀረውን ብዛት እያየን ነው። ነብዩ ﷺ ዘካ የማያወጣ ሰው ነገ በቂያማ ቀን የገዛ ገንዘቡ እባብ ሆኖ እንደሚያሰቃየው የተናገሩትን አስብ።
ደግሞም ዙሪያ ገባህን አስተውል። እድለኛ ማለት ሌላው ላይ ከደረሰው የተመከረ ነው። አላህ ሃብት ከሰጣቸው በኋላ ዘካ ሳያወጡ፣ ሐጅ ሳይፈፅሙ አልፈው በቁጭት ወላፈን እየተለበለቡ ያሉ ስንት አግኝተው ያጡ ወገኖች አሉ?!
ባጭሩ ገንዘብህ ወይ ጀነትህ ወይ እሳትህ ነው። ያሻህን መምረጥ ያንተ ድርሻ ነው።
( Ibnu Munewor ፣ ሚያዚያ 26/2013)
የቴሌግራም ቻናል:-
https://t.me/IbnuMunewor
🎤D/r Mucammad Cuseen Weeqisa.
#Arac_Qafar_Rakaakayak_Logyah_Magaala
Masjid: Niqmatul Mannaan.
#Caagid: #ummaan_num_Abinnaanihim_Geele.
Uddur:#Hijrâ_loowok1444,_Raamadaanak__15haytô_Bara (kameesi)
➡️#Ossitinâ kassis kee Daqwâ barnaamij Geytoonuh Ahaak Gubal Yan Linki Xaga
👇
https://t.me/AfarMahaNetwork
D/r Mucammad Cuseen Weeqisa.
#Arac_Qafar_Rakaakayak_Logyah_Magaala
Masjid: Niqmatul Mannaan.
#Caagid: khutba
Uddur:#Hijrâ_loowok1444,_Raamadaanak_9haytô_Bara (Jumqata)
➡️#Ossitinâ kassis kee Daqwâ barnaamij Geytoonuh Ahaak Gubal Yan Linki Xaga
👇
https://t.me/AfarMahaNetwork
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
