fa
Feedback
Construction Proxy

Construction Proxy

رفتن به کانال در Telegram

#1 construction portal to get: ✅ construction news ✅ construction market ✅construction materials price ✅engineering estimates ✅ Sub contract https://constructionproxy.com Address any comment to admin👨‍💼 @ConproxyBot

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Construction Proxy

کانال Construction Proxy (@constructionproxy) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 19 519 مشترک است و جایگاه 3 480 را در دسته تجارت و رتبه 1 728 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 19 519 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 18 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -7 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -3 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 66.59% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 9.21% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 13 000 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 797 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 27 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
#1 construction portal to get: ✅ construction news ✅ construction market ✅construction materials price ✅engineering estimates ✅ Sub contract https://constructionproxy.com Address any comment to admin👨‍💼 @ConproxyBot

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 19 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته تجارت تبدیل کرده‌اند.

19 519
مشترکین
-324 ساعت
+17 روز
-730 روز
آرشیو پست ها
የ2017 4ኛ ሩብ ዓመት የኮንስትራክሽን ስራዎች ቀጥተኛ ዋጋ ጥናት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ You can compare with https://t.me/ConstructionResources/227

የህንፃ ግንባታ ደህንነትን ባለማስጠበቅ የ142 ሰዎች ህይወት አልፏል ተባለ #Ethiopia | የአዲስ አበባ ከተማ የግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር የህንፃ ደህንነትን ባለመጠበቅ የአካል ጉዳት እና የህይወት
+1
የህንፃ ግንባታ ደህንነትን ባለማስጠበቅ የ142 ሰዎች ህይወት አልፏል ተባለ #Ethiopia | የአዲስ አበባ ከተማ የግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር የህንፃ ደህንነትን ባለመጠበቅ የአካል ጉዳት እና የህይወት ማጣት እንዲከሰት ምክንያት የሆኑ የግንባታ አማካሪ፣ ተቋራጮችና የህንፃ ባለቤቶች ላይ ከእስራት እስከ ገንዘብ ቅጣት እርምጃ መወሰዱን ገልጿል። ለአራዳ ገለፃ ያደረጉት የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር አበበ እሸቱ 2 ሺህ 667 ህንፃዎችን ላይ ባደረግነው ምልከታ 1 ሺህ 557ቱ የሰራተኛን እና የአጎራባችን ደህንነት እንዳልጠበቁ ተረድተናል ብለዋል። የችግሩን ምንጭ ስንመለከትም ለህንፃ ደህንነት ሥራዎች ትኩረት አለመስጠትና በጀት አለመመደብ መሆናቸውንም ተገንዝበናል ነው ያሉት። ስለ ህንፃ ግንባታ ደህንነት ስራ ተቋራጩ፣ አማካሪውና አጠቃላይ በስራው የሚሳተፉ አካላት ይህንን ከግንዛቤ አስገብተው እንዲሰሩ የግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን አጽንዖት ሰጥቷል። #aradaFm

የህንፃ ግንባታ ስራ አጠቃላይ ድህነትን(Safety) በተመለከተ!🏗
+2
የህንፃ ግንባታ ስራ አጠቃላይ ድህነትን(Safety) በተመለከተ!🏗

+5
Granite Direct from Factory! All Products at Wholesale Prices 🔥🔥🔥 Starting from just 4800 Birr! ⚡⚡⚡ Contact Us: Phone: +251-9444-888-88 Telegram: @granite_ethiopia Delivery Available Across Ethiopia 🚛🚛🚛 Cut SIze Window Sill Tread & Riser 60x60 CM 40x40 CM Tiles Manufacturing Location: Teja Granite, near ECF School, Aleltu Woreda (15 KM from Sendafa) Call : +251-9444-88-888

Repost from Tender ጨረታ
የ6ኛው ዙር የ40/60  ንግድ ቤቶች የጨረታ አሸናፊዎች ዝርዝር https://t.me/constructiontenders

" የነዳጅ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል " - ሚኒስቴሩ የሐምሌ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት እንደሚቀጥል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገለጸ። የሐምሌ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከዛሬ ሰኔ 21 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በሰኔ ወር ሲሸጥ በነበረበት የመሽጫ ዋጋ እንዲቀጥል በመንግሥት መወሰኑን አሳውቋል።

Due to the overnight fire incident at Millennium Hall, the final day of Big 5 Construct Ethiopia and East Africa Infrastructu
Due to the overnight fire incident at Millennium Hall, the final day of Big 5 Construct Ethiopia and East Africa Infrastructure & Water Expo has been cancelled. Source: Big 5 social pages

ደሞዝ አልከፈልከኝም በሚል ምክንያት አሰሪውን የገደለ ወንጀለኛ በ21አመት ፅኑ እስራት ተቀጣ፡፡ ተከሳሹ ጌቱ መስፍን ይባላል፤ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀመው ነሀሴ 27 ቀን 2014 ዓ/ም ከረፋዱ 4 ሰ
+1
ደሞዝ አልከፈልከኝም በሚል ምክንያት አሰሪውን የገደለ ወንጀለኛ በ21አመት ፅኑ እስራት ተቀጣ፡፡ ተከሳሹ ጌቱ መስፍን ይባላል፤ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀመው ነሀሴ 27 ቀን 2014 ዓ/ም ከረፋዱ 4 ሰዓት ከ30 ሲሆን በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ለገሃር ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ኖህ ሪል ስቴት ከሚያሰራው ህንፃ 16ኛ ጅምር ፎቅ ላይ ነው። ሟች ሀጂብ ያሲን የተባለው ግለሰብ ከኖህ ሪል እስቴት ኮንትራት በመውሰድ ከስሩ በርካታ ሰራተኞችን ቀጥሮ የሚያሰራ ግለሰብ ነው። ነሀሴ 27 ቀን 2014 ዓ/ም የዘወትር ስራውን ለማሰራት ሰራተኞችን ወደ የስራቸው ያሰማራል። ተከሳሽም ሟች የነበረበት ቦታ ጭር ማለቱን እና ማንም አለመኖሩን እንደ ጥሩ አጋጣሚ በመውሰድ ደሞዜን ከለከልከኝ በሚል ምክንያት በተፈጠረ አለመግባባት ሟች ሀጂብ ያሲንን ስራ እየሰራ ባለበት 16ኛ ፎቅ ላይ በፌሮ ብረት ግንባሩን በመምታት እና አንገቱን በሽቦ ገመድ በማነቅና በማሰር ህይወቱ እንዲያልፍ በማድረግ ሟችን ከህንፃው ተሸክሞ በማውረድ የህንፃው መሰረት ስር የሚገኝ የተጠራቀመ ውሃ ውስጥ አስከሬኑን በመጣል ከአካባቢው ይሰወራል። የወንጀሉ መፈፀም ሪፖርት የደረሰው ፖሊስ ወንጀል ፈፃሚውን ለመያዝ በተደረገ ጥረት ተከሳሽ ጌቱ መስፍን ወንጀሉን ከፈፀመ በኋላ ምንም እንዳልተፈፀመ በኔጌሌ ቦረና ከተማ በአንድ ተቋም ውስጥ ተቀጥሮ በመስራት ላይ እንዳለ በቁጥጥር ስር ሊውል መቻሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ገልጿል። በተከሳሽ ጌቱ መስፍን ላይ ለሚመለከተው የፍትህ አካል በመላክ ክስ እንደተመሰረተበት የገለፀው የአዲስ አበባ ፖሊስ ተከሳሽ ጌቱ ጥፋተኛ ሆኖ በማግኘቱ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት በ21 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ እንደተወሰነበት ገልጿል። አዲስ አበባ ፖሊስ

የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን የጎርፍ አደጋ ቅድመ-መከላከል ሥራ አሁንም ተጠናክሮ እንደቀጠለ ገለፀ የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን ይህን ችግር ለመቅረፍ ባለፉት 11 ወራት ከ400 ኪሎ ሜትር
+1
የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን የጎርፍ አደጋ ቅድመ-መከላከል ሥራ አሁንም ተጠናክሮ እንደቀጠለ ገለፀ የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን ይህን ችግር ለመቅረፍ ባለፉት 11 ወራት ከ400 ኪሎ ሜትር በላይ ርቀት የሚሸፍን የድሬኔጅ መስመር ጽዳት እና ጥገና ሥራ ተከናውኗል። በበጋው ወራት ሲከናወን የቆየው የጎርፍ አደጋ ቅድመ-መከላከል ሥራ አሁንም ተጠናክሮ እንደቀጠለ ሲሆን፤ ባሳለፍነው ሳምንት የድሬኔጅ መስመር ጥገና ከተከናወነባቸው አካባቢዎች መካከል ገዳመ እየሱስ የሚጠቀስ ነው። የክረምቱን ወቅት የጎርፍ አደጋ ስጋት ለመቀነስ ህብረተሰቡ በየአካባቢው የሚገኙት ክፍት የመንገድ ዳር የውሃ መውረጃ መስመሮችን በጋራ በማፅዳት የበኩሉን አውንታዊ ሚና እንዲወጣ የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን ጥሪውን ያቀርባል። ምንጭ: የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን

የብረት ዋጋ ስንት ገባ, ቆርቆሮ ስንት ገባ: ብለው አሁንም ይደውላሉ, በዚህ በቴክኖሎጅ ዘመን በ ነፃ ሁሉንም online ገብተው ይመልከቱ Construction Proxyን የማያውቅ መሃንዲስስ አለ?
የብረት ዋጋ ስንት ገባ, ቆርቆሮ ስንት ገባ: ብለው አሁንም ይደውላሉ, በዚህ በቴክኖሎጅ ዘመን በ ነፃ ሁሉንም online ገብተው ይመልከቱ Construction Proxyን የማያውቅ መሃንዲስስ አለ? 11 አመት የሞላው ብቸኛው የኮንስትራክሽን ዌብ ሳይት ነው:: visit the website constructionproxy.com

በአያት ሪል እስቴት በግንባታ ሥራ ላይ የነበሩ ሁለት ሠራተኞች ከአራተኛ ፎቅ ወድቀው ሕይወታቸው አለፈ ሰኔ 14/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በዛሬው ዕለት ከረፋዱ 4 ሰዓት አካባቢ ሲ.ኤም.ሲ ሚካኤል አካ
+1
በአያት ሪል እስቴት በግንባታ ሥራ ላይ የነበሩ ሁለት ሠራተኞች ከአራተኛ ፎቅ ወድቀው ሕይወታቸው አለፈ ሰኔ 14/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በዛሬው ዕለት ከረፋዱ 4 ሰዓት አካባቢ ሲ.ኤም.ሲ ሚካኤል አካባቢ እየተገነባ በሚገኘው አያት ሪል እስቴት ላይ በግንባታ ሥራ ላይ የነበሩ ሁለት ሠራተኞች፤ ከአራተኛ ፎቅ ወድቀው ሕይወት ማለፋን አሐዱ ከቦታው ተገኝቶ ማረጋገጥ ችሏል። አደጋው የደረሰው በልስን ሥራ ላይ ተሠማርተው በነበሩ ሠራተኞች ላይ ሲሆን፤ ሁለት ሠራተኞች ከሕንጻው 4ተኛ ፎቅ ላይ ሆነው የልስን ሥራ በማከናወን ላይ ሳሉ የቆሙበት ሊፍት (ዊንች) ካቦው በመበጠሱ አደጋው ደርሷል። በወቅቱም ከሕንጻው ስር በመጎዝ ላይ የነበረ አንድ ሠራተኛ ዊንቹ ወድቆበት ወዲያውኑ ሕይወቱ ያለፈ ሲሆን፤ ከወደቁት ሁለት ሠራተኞች ውስጥ አንዱ ሠራተኛም በተመሳሳይ ወዲያው ሕይወቱ አልፏል። የልስን ሥራ ሲሰራ የነበረው አንዱ ሠራተኛ ደግሞ፤ ከባድ ጉዳት ደርሶበት ለሕክምና እርዳታ ወደ ሆስፒታል ተወስዷል። በትናትናው ዕለትም 4 የቀን ሥራ ሠራተኞች በተመሳሳይ ሁኔታ ከሪል እስቴቱ ሕንጻ ላይ ወድቀው ሁለት ሠራተኞች ሕይወታቸው ያለፈ ሲሆን፤ በሁለቱ ሠራተኞች ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት መድረሱን አሐዱ ያነጋገራቸው የሪል እስቴቱ የግንባታ ሠራተኞች ገልጸዋል። እንዲሁም ከትናንት በስተያ ሐሙስ ሰኔ 12 ቀን 2017 ዓ.ም አምስት የግንባታ ሠራተኞች ከሕንጻው ላይ መውደቃቸው የተገለጸ ሲሆን፤ የሁለቱ ሠራተኞች ሕይወት ሲያልፍ በሦስቱ ሠራተኞች ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷል ተብሏል። በሕንጻው ግንባታ ላይ የተሰማሩ ሠራተኞች በተደጋጋሚ ተመሳሳይ አደጋ እየደረሰባቸው እንደሚገኝ አሐዱ የገለጹ ሲሆን፤ በሳምንት አንድ ወይ ሁለት ሠራተኞች አደጋ እንደሚደርስባቸው ተናግረዋል። ምንጭ: አሐዱ ራድዬ

ዜና እረፍት። አልቤርቶ ቫርኔሮ። ከ1950ዎቹ ጀምሮ በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ዘርፍ ፈር ቀዳጅ በነበሩት አልቤርቶ ቫርኔሮ ህልፈት የተሰማኝን ሀዘን ለመግለጽ እፈልጋለሁ። ስራቸው የሀገራችንን የግንባ
ዜና እረፍት። አልቤርቶ ቫርኔሮ። ከ1950ዎቹ ጀምሮ በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ዘርፍ ፈር ቀዳጅ በነበሩት አልቤርቶ ቫርኔሮ ህልፈት የተሰማኝን ሀዘን ለመግለጽ እፈልጋለሁ። ስራቸው የሀገራችንን የግንባታ ከባቢ እና ታሪካዊነት ያላቸው ምልክቶችን ላቅ ባለ ደረጃ የቀረፀ ነው። ከታሪካዊ ስራዎቻቸው መካከል የአፍሪካ አዳራሽ (የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ የኢኮኖሚ ኮሚሽን)፣ የአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት፣ ሂልተን ሆቴል፣ ሚሊኒየም አዳራሽ፣ የጅማ አባጅፋር አውሮፕላን ማረፊያ ማሻሻያ፣ የአብርሆት ቤተመጻሕፍት፣ የአንድነት ፓርክ እና የብሔራዊ ቤተመንግሥት እድሳት ሥራ ይገኙበታል። የሥራ ውርሳቸው በነዚህ ብሔራዊ ምልክቶች እና በሚወክሉት የእድገት ትእምርት ሲታወስ ይኖራል። ለነፍሳቸው ረፍትን፣ በረፍታቸው ላዘኑ ሁሉ መጽናናትን እንመኛለን። ምንጭ። ጠቅላይ ሚኒስትር ገጽ

የብረት ዋጋ ስንት ገባ, ቆርቆሮ ስንት ገባ: ብለው አሁንም ይደውላሉ, በዚህ በቴክኖሎጅ ዘመን በ ነፃ ሁሉንም ገብተው ይመልከቱ Construction Proxyን የማያውቅ መሃንዲስስ አለ? 11 አመት የሞላው ብቸኛው የኮንስትራክሽን ዌብ ሳይት ነው:: constructionproxy.com

Ethiopian Building Code Standards Private Sector Engagement in Code Revision: Week 2 Sessions
Ethiopian Building Code Standards Private Sector Engagement in Code Revision: Week 2 Sessions

ከአንድ ትርሊዮን በላይ የሚገመት ሀብት የሚፈልጉት የተጀመሩ መንገዶች #Ethiopia | በኢትዮጵያ የተጀመሩ የመንገድ ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ እስከ አንድ ነጥብ አምስት ትርሊዮን የሚገመት ሀብት እን
ከአንድ ትርሊዮን በላይ የሚገመት ሀብት የሚፈልጉት የተጀመሩ መንገዶች #Ethiopia | በኢትዮጵያ የተጀመሩ የመንገድ ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ እስከ አንድ ነጥብ አምስት ትርሊዮን የሚገመት ሀብት እንደሚያስፈልግ የገንዝብ ሚኒስትር ዴኤታ እዮብ ተካልኝ ተናግረዋል ። የገንዝብ ሚኒስትር ደኤታው እዮብ ይህን ያሉት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተካሄደው 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 33ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ነው። ሚኒስትር ዴኤታው ከምክር ቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፤ ከተለያዩ የብድር አቅራቢ ተቋማት በተገኘ ብድርና ከልማት አጋሮች በተገኘ ድጋፍ በርካታ መንገዶች እየተሰሩ ነው ። እንደሀገር የተጀመሩትን የመንገድ ፕሮጀክቶች ለማጠናቀቅ ከአንድ ነጥብ ሶስት ትሪሊዮን እስከ አንድ ነጥብ አምስት ትሪሊዮን የሚገመት ሀብት እንደሚያስፈልግ አስታውቀዋል ዘገባው የጋዜጣ ፕላስ ነው ።

photo content

የጨረታ ማስከበሪያ ከፍተኛው መጠን ከ500ሺ ወደ 2 ሚሊየን ከፍ ተደረገ:: የመንግስት መ/ቤቱ የጠቅላላ ግዥውን ግምታዊ ዋጋ መሰረት በማድረግ ከ0.5% ያላነሰ እና2% ያለልበለጠ የጨረታ ማስከበሪያ
የጨረታ ማስከበሪያ ከፍተኛው መጠን ከ500ሺ ወደ 2 ሚሊየን ከፍ ተደረገ:: የመንግስት መ/ቤቱ የጠቅላላ ግዥውን ግምታዊ ዋጋ መሰረት በማድረግ ከ0.5% ያላነሰ እና2% ያለልበለጠ የጨረታ ማስከበሪያ የገንዘብ መጠን ወስኖ በጨረታው ጥሪው እና በጨረታ ሰነዱ ውስጥ መግለፅ ይኖርበታል፡፡ በዚህ መሠረት የሚወሰነው የጨረታ ማስከበሪያ መጠን ከብር 2,000,000 (ሁለትሚሊዮን ብር) የበለጠ መሆን የለበትም፡፡  አዲሱ የፌደራል የግዥ መመሪያ 1073/2017 ወደ ስራ ገብቷል። ዝርዝሩንና መመሪያውን 👇ያገኙታል:: @procinsightet/60

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ ኢድ-ሙባረክ! እንኳን ለ1,446 ኛው የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ConstructionProxy.com
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ ኢድ-ሙባረክ! እንኳን ለ1,446 ኛው የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ConstructionProxy.com

የአዲስ አበባ ከተማ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ማስተካከያ የቤንዚን እና የአውሮፕላን ነዳጅ መሸጫ ዋጋ በግንቦት ወር ሲሸጥበት በነበረው ዋጋ በስኔ ወር የሚቀጥል ሲሆን የነጭ ናፍጣ፣ የኬሮሲ
የአዲስ አበባ ከተማ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ማስተካከያ የቤንዚን እና የአውሮፕላን ነዳጅ መሸጫ ዋጋ በግንቦት ወር ሲሸጥበት በነበረው ዋጋ በስኔ ወር የሚቀጥል ሲሆን የነጭ ናፍጣ፣ የኬሮሲን፣ የቀላል ጥቁር ናፍጣ አና የከባድ ጥቁር ናፍጣ በቀጣይ በሥራ ላይ የሚቆይ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በሚከተለዉ መሠረት ስራ ላይ እንዲዉል በመንግስት የተወሰነ መሆኑን እየገለፅኩ የህዝብ ማስታወቅያና የሁሉም ከተሞች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከዚህ ደብዳቤ ጋር አባሪ መደረጉን አሳዉቃለሁ፡፡