DDU SU ACADEMIC HEAD OFFICE
رفتن به کانال در Telegram
Excellence is not being the best Rather it is trying your best!!!
نمایش بیشترکشور مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
1 115
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+17 روز
+530 روز
تعداد پستها
در حال بارگیری داده...
واکنشها
نظرات
ستارههای تلگرام
بهترین پستها بر اساس
در حال بارگیری داده...
تجزیه و تحلیل انتشار
پست ها | ديناميک بازديد ها | |||||
የ12ኛ ክፍል ሀገራዊ የመልቀቂያ ፈተና በሰላም ተጠናቀቀ
በድሬደዋ ዩኒቨርሲቲ ከሰኔ 23 ቀን ጀምሮ ሲሰጥ የቀየው የ12ኛ ክፍል ሀገራዊ የመልቀቂያ ፈተና በሰላም ተጠናቀቀ። ዩኒቨርሲቲው በዘንድሮው የትምህርት ዘመን 2615 ተማሪዎችን ያስፈተነ ሲሆን ከተፈታኞቹ ውስጥ 1156 በተፈጥሮ ሳይንስ እንዲሁም 1459 የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች መሆናቸውን ማረጋገጥ ተችሏል፡፡ ከተፈታኞቹ ውስጥ 1332ቱ ሴቶች እንዲሁም 1283 ወንድ ተፈታኞች ሆነዋል፡፡
የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የመልቀቂያ ፈተና በተሳካ ሁኔታ ተጀምሮ እንዲጠናቀቅ የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ሰፊ የቅድመ ፈተና ስራዎችን ሲሰራ የቆየ ሲሆን በተለይ በኦንላይን ለሚፈተኑ ተማሪዎች ምቹ የመፈተኛ ኮምፒተር እና መሰል ግብዓቶችን የማሟላት ስራ መሰራቱ ተጠቁሟል፡፡ ዩኒቨርሲቲው ከዚህ ባሻገር ራቅ ካሉ ከተሞች እና አካባቢዎች ለመጡ ተማሪዎች የማረፊያ ቦታ፣ የምግብ እና መዝናኛ አገልግሎት በመስጠት ተፈታኞች ያለምንም ችግር እና መጉላላት ፈተናቸውን እንዲወስዱ ማድረግ ችሏል፡፡
ላለፉት ሶስት ሳምንታት የተሰጠው ሀገራዊው የ12ኛ ክፍል የመወጫ ፈተና ያለምንም ችግር እና የፈተና ስነ-ምግባርን እና ፀጥታ በተጠበቀ መልኩ የተሰጠ ሲሆን ለዚህ ስኬት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ላደረጉ የማኔጅመንት አባላት፣ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ለመጡ ፈታኝ እና የፈተና አስተባባሪ መምህራን፣ በየደረጃው ላሉ የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ አመራሮች፣ መምህራን እና የአስተዳደር ሰራተኞች ዩኒቨርሲቲው ልባዊ ምስጋናውን ያቀርባል፡፡ | 313 | 2 | 0 | 1 | Loading... |

