DDU SU ACADEMIC HEAD OFFICE
前往频道在 Telegram
Excellence is not being the best Rather it is trying your best!!!
显示更多未指定国家未指定类别
1 115
订阅者
-124 小时
+27 天
+530 天
帖子数量
数据加载中...
反应
评论
Telegram 星星
按以下排序的热门帖子
数据加载中...
发布分析
帖子 | 浏览量动态 | |||||
የ12ኛ ክፍል ሀገራዊ የመልቀቂያ ፈተና በሰላም ተጠናቀቀ
በድሬደዋ ዩኒቨርሲቲ ከሰኔ 23 ቀን ጀምሮ ሲሰጥ የቀየው የ12ኛ ክፍል ሀገራዊ የመልቀቂያ ፈተና በሰላም ተጠናቀቀ። ዩኒቨርሲቲው በዘንድሮው የትምህርት ዘመን 2615 ተማሪዎችን ያስፈተነ ሲሆን ከተፈታኞቹ ውስጥ 1156 በተፈጥሮ ሳይንስ እንዲሁም 1459 የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች መሆናቸውን ማረጋገጥ ተችሏል፡፡ ከተፈታኞቹ ውስጥ 1332ቱ ሴቶች እንዲሁም 1283 ወንድ ተፈታኞች ሆነዋል፡፡
የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የመልቀቂያ ፈተና በተሳካ ሁኔታ ተጀምሮ እንዲጠናቀቅ የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ሰፊ የቅድመ ፈተና ስራዎችን ሲሰራ የቆየ ሲሆን በተለይ በኦንላይን ለሚፈተኑ ተማሪዎች ምቹ የመፈተኛ ኮምፒተር እና መሰል ግብዓቶችን የማሟላት ስራ መሰራቱ ተጠቁሟል፡፡ ዩኒቨርሲቲው ከዚህ ባሻገር ራቅ ካሉ ከተሞች እና አካባቢዎች ለመጡ ተማሪዎች የማረፊያ ቦታ፣ የምግብ እና መዝናኛ አገልግሎት በመስጠት ተፈታኞች ያለምንም ችግር እና መጉላላት ፈተናቸውን እንዲወስዱ ማድረግ ችሏል፡፡
ላለፉት ሶስት ሳምንታት የተሰጠው ሀገራዊው የ12ኛ ክፍል የመወጫ ፈተና ያለምንም ችግር እና የፈተና ስነ-ምግባርን እና ፀጥታ በተጠበቀ መልኩ የተሰጠ ሲሆን ለዚህ ስኬት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ላደረጉ የማኔጅመንት አባላት፣ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ለመጡ ፈታኝ እና የፈተና አስተባባሪ መምህራን፣ በየደረጃው ላሉ የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ አመራሮች፣ መምህራን እና የአስተዳደር ሰራተኞች ዩኒቨርሲቲው ልባዊ ምስጋናውን ያቀርባል፡፡ | 313 | 2 | 0 | 1 | Loading... |

