ከቃሉ ማዕድ
رفتن به کانال در Telegram
☀️ ክርስቶስን መስለን በመኖር ፣ ላልተደረሱት የሕዝብ ክፍሎች በመፀለይ ፣ ሰዎች ሁሉ እንዲድኑ የሚፈልገውን እግዚአብሔርን የሙጥኝ የምንልበት ቻነል ነው። 1ጢሞ 2:1-4 ☀️ ደግሞም አብ የሰጠንን ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ በልተን ደግሞም ጠትተን ዕለት ዕለት ደግሞ 💥በሁለንተናችን የሚያሳድገንን የቃሉን🎯 ማዕድ የምንቆርስበት ትምህርታዊ እና መንፈሳዊ ቤት ነው። ዮሐ6:35
نمایش بیشترکشور مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
323
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+67 روز
+6630 روز
آرشیو پست ها
323
🔆የእግዚአብሔር ፈቃድ ቢሆን ከዚህ ቀጥሎ የምንቆየው አካል የሆነው የሊቀካህናችን የኢየሱስን ክርስቶስ ጥላ ከሆኑት አንዱ እና ወሳኙ ትምህርት መሀከል፦📌 "የመማፀኛ ከተሞች" በሚል አርዕስት ይሆናል።
#Announcement
¶Follow | Join | Share #ከቃሉ_ማዕድ
323
2 ጴጥሮስ 3:9 9 ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደሚመስላቸው ጌታ ስለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንዲደርሱ እንጂ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ስለ እናንተ ይታገሣል።💥አስፈሪው ሃይማኖታዊ የዓለም ክልል💥 🔆 በብዙ የዓለም ክፍሎች ያልተደረሱ ሕዝቦች ከኢየሱስ ተከታዮች ጋር የሚገናኙበት ያልተቋረጠ ዕድል አላቸው። ሆኖም እነዚህ ያልተደረሱ ሕዝቦች በብዙ የተከማቹትና ከክርስቶስ ተከታዮች ጋር ለመገናኘት ያላቸው ዕድል አናሳ የሆነበት የዓለም ክፍል አለ። ይህም የዓለም ክፍል 10/40 መስኮት በመባል ይታወቃል። ይህ ጂኦግራፊያዊ የአሰላለፍ መስመር ከምዕራብ አፍሪካ ተነስቶ መካከለኛው ምስራቅ አቋርጦ እስከ እስያ ደረስ የሚዘልቅ ነው። ይህ መስመር በአብዛኛው የአለማችንን ታላቅ የሃይማኖት ክፍል ተከታዮችን ማለትም ሙስሊሞችን፣ ሂንዱዎችንና ቡድሂስቶችን የሚጨምርና የሚያጠቃልል ነው። በአጠቃላይ ሲታይ እነዚህን ሕዝቦች በወንጌል ለመድረስ አመቺ የሚባሉት በብዛት ባለው የዓለም ክፍል የሚገኙ ባህል አቀፍ የወንጌል ሠራተኞች ናቸው። እነዚህ የወንጌል ሠራተኞች ከመልክዓ ምድር፣ ከኢኮኖሚ፣ ከቋንቋም ሆነ ከባህል አንጻር ሲታይ ቅርበት ያላቸው ናቸው። 📌 እነዚህ በጥቂቱ በተደረሱ ሕዝቦች መካከል የሚገኙ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች ከአንድም አማኝ ጋር ሳይገናኙና ስለድነት ሳይሰሙ ዕድል ሳያገኙ ኖረው ያልፋሉ። እነዚህ ሰዎች ወንጌል እንዲሰሙ ለማድረግ የወንጌል ሠራተኞች እንቅፋቶቻቸውን አልፈው ለመድረስ በሚያስችል መልኩ ዝግጁ መሆን አለባቸው። በተለይም ከእነዚህ ሃይማኖቶች ወደ ኢየሱስ የሚመጡ ሰዎች ለባህላቸው በሚስማማና በሚመጥን መልኩ እንዲመለኩ ፍላጎታቸውን ማስተላለፍ ፈቃደኝነት ሊኖራቸው ይገባል። 📌እነዚህን እና መሰሎች በሚገባ ያልተደረሱ ሕዝቦች በአብዛኛው ፦ 👉 ድሆችና ጉዳተኞች 👉 የማህበረሰብ ልማት የሌላቸው 👉 ማህበራዊ ፍትህ የተጓደለባቸው 👉 የተሰደዱና የታሰሩ ሰዎች የሚበዙበት 👉ህገወጥ የሰዎች ዝውውር የሚበዛበት 👉የሴቶች እየያዝ ኢ-ፍትሐዊ የሆነበት እና ለችግር የተጋለጡ ልጆች የሚበዙበት፤ ስፍራ በመሆኑ አለማቀፋዊ አስፈሪ ስፍራ እንዲሆን አድርጎታል። 💥 ምን ያህሎቻችን ለእነዚህ ሕዝቦች እንፀልያለን❓ በዚህ አከባቢ የሚገኙ ፦ THUMB(Tribal belief,Hinduism, Un-religious, Muslims, Buddhism) በመባል የሚታወቁት የሀይማኖት ክፍሎች ኢየሱስን ሳያውቁ እንዳይሞቱ ልንፀልይ #ስምህ_ይቀደስ ልንል ይገባናል።🙏🙏🙏
ራእይ 7:9 9 ከዚህ በኋላ አየሁ፥ እነሆም፥ አንድ እንኳ ሊቆጥራቸው የማይችል ከሕዝብና ከነገድ ከወገንም ከቋንቋም ሁሉ እጅግ ብዙ ሰዎች ነበሩ፤ ነጭ ልብስም ለብሰው የዘንባባንም ዝንጣፊዎች በእጆቻቸው ይዘው በዙፋኑና በበጉ ፊት ቆሙ፤💥የኢየሱስ ስም ይቀደስ። አሜን! #አስር_አርባ_መስኮት #ኢየሱስ_ስምህ_ይቀደስ ¶Follow | Join | Share #ከቃሉ_ማዕድ
323
"በጌታ ኢየሱስ የመጀመሪያ መምጣት የተፈጸሙ በርካታ ነገሮች አሉ። መንፈሳዊ በረከቶችን ሁሉ አግኝተናል (ኤፌ1፥3) እነዚህን ሁሉ በረከቶች በሙላት የምናጣጥመው ግን ጌታ ዳግም ሲመጣ ነው። "
የተሰቀለው ገፅ 384 አንቀጽ 2
ራእይ 22:20 20 ይህን የሚመሰክር፦ “አዎን፥ በቶሎ እመጣለሁ፡” ይላል። አሜን፥ ጌታ ኢየሱስ ሆይ፥ ና።#ማራናታ #ከቃሉ_ማዕድ
323
"ስለዚህ ለኢየሱስ ብሉይ ኪዳን ስለእርሱ የሚያወራውን ያህል ስለ ተልዕኮም ይናገር ነበር ማለት ነው። በሌላ አገላለጽ ሁለቱም የአንድ ወሳኝ እውነት፤ ይህም የእግዚአብሔር የድነት ተልዕኮ የማይነጣጠሉ ክፍሎች ናቸው። ኢየሱስ መሲሑ እንደሆነ መናገር ማለት እርሱ በሕዝቦች መካከል ላለው ተልዕኮ ራስን መስጠት ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስን ካመናችሁ እና ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ እንዳስተማራቸው አድርጋችሁ ካነበባችሁ አንደኛውን ጥላችሁ ሌላውን ልትወስዱ አትችሉም።"⚠️
Christopher J H Wright
#Great_Commission
#ከቃሉ_ማዕድ
323
“በመንፈሱ ሰማያት ውበትን አገኙ፥”
— ኢዮብ 26፥13
✔ እልፍ አመታትን ከሰው ልጆች እና ከምድር ፍጥረታት በላይ የሚታየው ሰማይ አንድም ቀን ከለሩን ቀይሮ አያውቅም፤ አቀማመጡም በዘፍጥረት ዘመን "ይሁን" ተብሎ እንደታዘዘው ነው ታዲያ ለብዙ አመታት የኖረው ሰማይ በመኖር ብዛት ውበቱ ያልደበዘዘው ለምንድነው? ትላንት ያየነውን አይነት ሰማይ ነገም እናየዋለን፣ቀጣይ ሳምንትም፣ቀጣይ አመትም፣የዛሬ 10 ዓመትም ...... ሁሌም። "ታዲያ ለስልቹነት ቅርብ የሆነው የሰው ልጆች አእምሮ ለምን አልተሰላቸም?" ብለን ብንጠይቅ የሰማዩ ውበት የተቀዳበት ምንጭ የሚደርቅ ስላልሆነ ነው።
✔ ስለሰማይ ውበት ለማውራት አይደለም የፈለኩት፤ስለ እኛ ማንነት ነው።
ሰማያት እንኳን ውበትን የተቀበሉት በመንፈሱ ከሆነ የእኛ ዘላቂነትማ ምን ያህል ከመንፈሱ ጋር የተሰፋ ይሆን?
መጀመር ለብዙሃን የሚቻል ሊሆን ይችላል በጀመሩበት ሀይል እና ውበት መቀጠል ግን ህያው ምንጭ መጠጋትን ይጠይቃል።
ማንም ቢሆን የሚደበዝዝ እና የደከመ ፍፃሜ አይፈልግም፤
በጅማሬያችን ውበት ለመቀጠል እንድንችል ለዘመናት ለቆየው ሰማይ ውበት ሰጪ ወደሆነው መንፈስ እንጠጋ!!
👉 መንፈስ ቅዱስን በመጠጋት መባረክ ይሁንልን! አሜን
✍
Gift
#Abiding_with_Holy_spirit
#ከቃሉ_ማዕድ323
📌 "ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ያለን ልምምድ ባነሰ ቁጥር፣ ቤተክርስቲያንን ለማስቀጠል ብዙ የኬክና የቡና ፕሮግራም እናበዛለን።"
ወንጌላዊ ራያንሃርድ ቦንኬ
323
1 ቆሮንቶስ 9:16
16 ወንጌልን ብሰብክ እንኳ የምመካበት የለኝም፤ ግድ ደርሶብኝ ነውና፤ ወንጌልንም ባልሰብክ ወዮልኝ።
"ዓለም የምትጠፋው በእኩይ ድርጊት ሳይሆን በመልካሞች ዝምታ ነው።"
• አልበርት አንስታይን
"በክፋት ፊት ዝም ማለት ራሱ ክፋት ነው። ከእግዚአብሔር ፍርድ አናመልጥም፡፡ አለመናገር ራሱ መናገር ነው፤ አለማድረግ እንደሆነ ማድረግ ነው።"
• ዲትሪች ቦንሄፈር
አየሱስ ከሰማያት ስለ እኛ እንደወረደ፣ እንደሞተ፣ እንደተቀበረ፣ በሶስተኛውም ቀን ከሙታን እንደተነሳ ምስክሮቹ መሆንን ያብዛልን#ምስክር_ነኝ #ከቃሉ_ማዕድ @Kekalu_Maid
323
"መጽሐፍ ቅዱስ የፍቅር ታሪክ እንደሆነ ለመስማት አዲስ አይደለንም። ነገር ግን የፍቅርን አንድ ገጽታ ብቻ ይዞ ይህ እግዚአብሔር ሕዝቡን እንደሚወድ ማየት ይቅለለናል። ነገር ግን የመጽሐፍ ቅዱስ ዋና ዓላማ እግዚአብሔር በልብ፣ በነፍስ፣ በአእምሮ እና በኃይል እንደሚወድ ከሆነ ግን መላውን ታሪክ ከእግዚአብሔር ዕይታ አንጻር ማንበብ የበለጠ ሳይጠቅም አይቀርም። እግዚአብሔር ሕዝቡን መውደድ ብቻ ሳይሆን፣ እርሱን በሙሉ የሚወዱ ሕዝቦች እንዲሆኑ እየለወጣቸው ነው።"
ስቲቨን ሲ ሐውቶርን
(Perspective on the world Christian movement book's developer)
#ስምህ_ይቀደስ
#ከቃሉ_ማዕድ
323
══════════════✝✝✝═════════════
💢ኢየሱስም 'እኔ' ፧፦
> እኔ ከላይ ነኝ ዮሐንስ 8፥23
> የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ዮሐንስ 10፥36
> የዓለም ብርሃን ነኝ። ዮሐንስ 9፥5
> እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም። ዮሐንስ 14፥6
> የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ፤ ወደ እኔ የሚመጣ ከቶ አይራብም በእኔ የሚያምን ሁል ጊዜ ከቶ አይጠማም። ዮሐንስ 6፥35
> በሩ እኔ ነኝ በእኔ የሚገባ ቢኖር ይድናል... ዮሐንስ 10፥9
ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ፤ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል። ዮሐንስ 11፥25
> መምህርና ጌታ ትሉኛላችሁ፤ እንዲሁ ነኝና መልካም ትላላችሁ። ዮሐንስ 13፥13
> እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ፤ ዮሐንስ 15፥1
> አልፋና ኦሜጋ እኔ ነኝ.... ራእይ 1፥8
> ፊተኛውና መጨረሻው ሕያውም እኔ ነኝ.... ራእይ 1፥17💥 ሕይወት ለማግኘት ከፈለጉ ኢየሱስ በመስቀል ላይ እንደሞተና እንደተነሳ በልብዎ ያምኑ ጌታም እንደሆነ በአንደበትዎ ይመስክሩ። 📌 <<ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም መስክሮ ይድናልና።>> ሮሜ 10፥10 #የኢየሱስ_እኔዎች #ከቃሉ_ማዕድ ══════════════☦☦☦═════════════
323
🔆 እርሱ (ኢየሱስ ክርስቶስ)፦
📌 መላእክት 👉 መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና
ሉቃስ 2፥11
📌 ጠቢባን 👉 ልንሰግድለት መጥተናል
ማቴዎስ 2፥2
📌 እግዚአብሔር 👉 በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት
ማቴዎስ 17፥5
📌 ማርያም 👉 የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ ዮሐንስ 2፥2
📌 ነቢያት 👉 በእርሱ የሚያምን ሁሉ በስሙ የኃጢአቱን ስርየት ይቀበላል። የሐዋርያት ሥራ 10፥43
📌 ሰይጣን 👉 አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ
ማርቆስ 3፥11
📌 መጽሐፍ ቅዱስ 👉 ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ ነው።
1ኛ ጢሞቴዎስ 1፥15
📌ሐዋርያት👉 በእርሱ የሚያምን ሁሉ አያፍርም
ሮሜ 10፥11
እርስዎስ ለሕይወትዎ ዋስትና ወዴት ይጠጋሉ? ማንንስ ይመርጣሉ?
ምርጫዎትን ያስተካክሉ ከትናንት ስህተት ተምረው ነገ የማይፀፀቱበትን ውሳኔ ዛሬ ይወስኑ!!!💥 ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ እስከ ዘላለምም ያው ነው። ዕብራውያን 13፥8 #የክርስቶስ_ማንነት #ከቃሉ_ማዕድ
