fa
Feedback
Orthodox mezemur ኦርቶዶክስ መዝሙር

Orthodox mezemur ኦርቶዶክስ መዝሙር

رفتن به کانال در Telegram

እኔ ግን በቸርነትህ ታመንሁ ልቤም በመድኃኒትህ ደስ ይለዋል የረዳኝን እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ ለልዑል እግዚአብሔር ስምም እዘምራለሁ ። መዝሙረ ዳዊት 13 : 5 - 6 o⁠:⁠-⁠)- ለማንኛውም ጥያቄ በስር ባስቀመጥነው ሊንክ ሊጠይቁን ይችላሉ 👇👇 - @tan_flf -

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
283
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-17 روز
+2530 روز
آرشیو پست ها
◈◈አባ አንተን ያለ◈◈ ዘማሪ ፍስሀ ዘለሸ

ከሊባኖስ ድንግል ነይ ሐና እና ኢያቄም ወለዱ ሰማይ አዲሷም ሰማይ አስገኘች ፀሐይ ምስራቀ ምስራቃት የአምላክ መገኛ ከሊባኖስ ድንግል ነይ ወደ እኛ(2) ተጨነቀ አዳም በመከራ በእርግማን ቀን ለቅሶን እየዘራ በልጅሽ ሞት አለም ተቀደሰ የፍጥረቱ እንባ በመስቀል ታበሰ(2) አዝ••• የህያዋን እናታቸው ሆነሽ ለቀደመች ሄዋን ጠበቃ ሆንሽ ደስተኛዋ ደስ ይበልሽ ማርያም ካንቺ ወጣ የአለሙ ሰላም(2) አዝ••• ፅኑ ገመድ ባንቺ ተቆረጠ የፍዳ አመት ይኸው ተለወጠ በሐና ልጅ በኢያቄም ፍሬ ደስታ ሆነ ቅኔና ዝማሬ(2) አዝ••• በወለዱሽ በሐና በኢያቄም ተማፅነናል ድንግል ማርያም ከአዳኝ ወጥመድ ከክፋ ጠላት ልጆችሽን ጠብቂ ከጥፋት ከአዳኝ ወጥመድ ከክፋ ጠላት ኢትዮጵያን ጠብቂያት ከጥፋት መዝሙር 🎙ዘማሪ አቤል መክብብ

+1
ምስጋናው_ይቀጥል ምስጋናው ይቀጥል ዝማሬው ይቀጥል እግዚአብሔር ስላለ ከያዘ የማይጥል በምናየው ነገር በምንሰማው ወሬ እንዳይቆም ምስጋና እንዳይቆም ዝማሬ ❴አዝ❵ የሰማእታቱ ደም የፈሰሰው በምድር አይተናል ሲያስቀጥል የክርስትናን ዘር እንድናምን ብቻ መች ተጠራን እና በእሳቱም መካከል ቅኔ አለን ምስጋና ❴አዝ❵ መች ማጥፋት ይቻላል እሳትን በእሳት አይቆምም ማህሌት ቅዳሴ ሰዓታት ከሰማዩም በላይ ከሰማዩም በታች ቤተ ክርስቲያን ዛሬም ነገም አለች ❴አዝ❵ የዓለም ጨው ሆነን በዓለም የበዛነው እየተደበደብን እየተገፋን ነው በገደሉን ጊዜ ቁጥራችን ይበዛል ከሞትም በኃላ ሂወት ይቀጥላል ❴አዝ❵ የተስፋይቱን ምድር ተነሱ እንወርሳለን በመዝሙር በእልልታ ቅጥሩን እያፈረስን  የሰላዮቹን ቃል ሰምታችሁ አትፍሩ በሃይማኖት ጽኑ በእምነታችሁ ኑሩ

♡ ኑ ተመልከቱልኝ ♡
ኑ ተመልከቱልኝ የአምላክን ቸርነት አንደበት የለኝም ስራውን ለማውራት ሰላምና ፍቅር በልቤ ተሞልቷል በምን ቋንቋ ላውራው ቃላቶች ያጥሩኛል/2/
ሰማይ ጉም ቢመስል ቀለያት ቢናጉ የጥፋት አጋንንት እጅጉን ቢተጉ እኔን የሚጠብቅ ኃይሉን አይሰውርም እረኛዬ ከእኔ ዘወትርአይርቅም/2/ ፍርሃት ከኔ ራቅ ጨለማም ተወገድ በጌታዬ ትምክህት እንደልቤ ልሂድ የሞት አበጋዞች ተስፋችሁ ጨልሟል እግዚአብሔር ሊያድነኝ ከአጠገቤ ቆሟል ቅዱሳን በሙሉ ለእኔ ዘብ ቆመዋል ወደ እነርሱ ኅብረት ሊስቡኝ ጓጉተዋል ዘወትር በመአልት ድንግል ትመጣለች በብርሃን እጆቿ ትባርከኛለች

ተወራርጃለሁ ተወራርጃለሁ ባርያሽ ከዓለም ጋራ እንዳልረታብሽ እመቤቴ አደራ[፪]                         አዛኝቱ አደራአዝ
ሁሌ እጠራሻለሁ[፪]በቃልኪዳንሽ የምህረት አማለጅ ማርያም አንቺ ነሽ ድንግል አንቺ ነሽ ማርያም አንቺ ነሽ የአለም ፈርጥ አንቺ ነሽ[፪]ማርያም እመቤቴ እመካብሻለሁ እሰከለተ ሞቴ                    እስከ ጊዜ ሞቴ የአለም ሁሉ መቅረዝ[፪]መንበረ ሥላሴ መድሃኒቴ እሷ ናት[፪] ለስጋ ለነብሴ እስኪ ላመስግናት ተፈታ ምላሴ [፪] የፃድቃን እመቤት[፪] የሃጥአን ተስፋ ወዳንቺ እጮሃለው ሳዝንና ስከፋ [፪] አደራሽሽነ ማርያም[፪] ኪዳነምህረት ፀጋሽን አልብሽ ልጅሽ ስራቆት[፪] ፅድቄንም አያለሁ[፪] በአንቺ በእመቤቴ ምልጃሽ እየረዳኝ አለሁኝ በቤቴ[፪] ❴አዝ❵ ሁሌ እጠራሻለሁ[፪] በቃልኪዳንሽ የምህረት አማላጅ ማርያም አንቺ ነሽ                           ድንግል አንቺ ነሽ                           ማርያም አንቺ ነሽ.
              [[፪]]              ሐኖስ በገና                  የበገና ዝማሬ ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች   

አባታችን ሆይ አባታችን ሆይ የምትኖር በሰማይ መንግሥትህ ትምጣልን ክብርህን እንድናይ/2/ ፈቃድህ በሰማይ ህይወት እንደሆነ እንዲሁም በምድር ሰላምን ስጠን/2/ ስጠን ለዛሬ የዕለት ምግባችንን በደላችንንም ይቅር እንድትለን/2/ ጌታ ሆይ አታግባን ከክፉ ፈተና አንተ ካረዳኸን ኃይል የለንም እና/2/ ኃይል እና ምስጋና መንግሥትም ያንተ ናት አሜን ለዘለዓለም ይሁንልን እረፍት ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ ወ/ቂርቆስ ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች    •➢ ሼር // SHARE 👇👇👇 @yemezmur_getimoche @yemezmur_getimoche @yemezmur_getimoche

በመከራ ፅና በመከራ ፅና በመከራ ፅና በፈተና ፅና ለጊዜው ነው እንጂ ሁሉም ያልፋልና /2/ ኢዮብ ተጨነቀ በጣም ተማረረ በመከራው ብዛት ትዕግስትን ተማረ ልጅ የሌለው ሆነ እጣንብረቱን በመከራ ፀና አልካደም አምላኩን መፈተን መልካም ነው ያነጣል እንደወርቅ በመጨረሻው ቀን በክብር እንደትደምቅ አንዱን ሳትሻገር ሌላው ቢገጥም በሕይወት ዘመንህ መከራው ያንተው ነው ከአምላክህ ተስማማ እራስህን አዋርድ በቃሉ ተመራ እንደፈቃዱ ሂድ ዋጋህ ከአምላክ ዘንድ በሠማይ አለና በርታ ክርስቲያን ሆይ በመከራ ፅና ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች    •➢ ሼር // SHARE 👇👇👇 @yemezmur_getimoche @yemezmur_getimoche @yemezmur_getimoche

☦️ወር በገባ በ15 የእናታችን ቅድስት ኢየሉጣ ልጃ ቅዱስ ቂርቆስ መታሰቢያቸው ነው በረከት እረድኤታቸው ይደርብን🙏 ☦️ቅድስት ኢየሉጣ ሆይ ሰላም ለአንቺ ይሁን🛐 የደከመች ማርታ ያልደከመችም ማርያ
☦️ወር በገባ በ15 የእናታችን ቅድስት ኢየሉጣ ልጃ ቅዱስ ቂርቆስ መታሰቢያቸው ነው በረከት እረድኤታቸው ይደርብን🙏 ☦️ቅድስት ኢየሉጣ ሆይ ሰላም ለአንቺ  ይሁን🛐 የደከመች ማርታ  ያልደከመችም ማርያም ልጆቿንም ሰማዕትነት የሰጠች ሶፍያ ከአንቺ  ጋር  አይተካከሉም። ☦️ቂርቆስ ሆይ! ሰላም ለአንተ ይሁን🛐 በምቆምበት ጊዜ በየሰዓቱ በወልድና በእናቱ ፊት የዚህ ምልጃዬ መልእክተኛ ነኝ በለኝ፡፡ሰላም ለአንተ፡፡ ☦️ተከዜን የምትተካከል የሰላማችን ወንዝ ቂርቆስ ሆይ! ከሕዝባችን ልብ ማጣት ታስወግድ ዘንድ በየጊዜው ለመባረክና ለማረጋጋት ና ና፡፡ ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች    •➢ ሼር // SHARE 👇👇👇 @yemezmur_getimoche @yemezmur_getimoche @yemezmur_getimoche

እንዴት መጣሁ ብዬ እንዴት  ወጣሁ  ብዬ   ከቶ አልደነቅም አምንሀለሁ እና  ትተህኝ አታውቅም   ያሁሉም  አለፈ  ቀረ ወደኃላ ማልቀስ ማንባት ይብቃኝ  ከንግዲህ ቦሀላ  /2 / ከንግዲህ አይመጣም ያቀን ተመልሱ ላያዳግም ሄዶል   እንባዬን  አፍስሱ በመስቀል ላይ ሆነህ  ችንካርህ ታይቶኛል ያሁሉ  መከራ   በአንተ አልፎልኛል         አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸► እንደምን ተነሳ  አላዛር አትበሉ ይችላል   እግዚአብሔር  ይችላል ሀያሉ   ታሪክ ሆኖ አልፎል  ያኔ ያስጨነቀኝ ስንቱን ተሻግረናል  ጌታ እየጠበቀን         አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸► ካሳን  ቤሪው ሜዳፍ ከጥልቁ ወጥቼ እዘምርለታለሁ  ዳግም ተሰርቼ የሽቶዬን ብልቃት ሰበርኩት በፊቶ በጽድቅ እንዳስበኝ ጌታ በምህረቱ           አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸► ቁስሌን  ቆሰልክልኝ  ጥሜንም ተጠማህ መቼ  ገባኝ እና የመስቀሉ አላማ ለካስ ስለፍቅር የማይሆኑት የለም አሳየህኝ ጌታ ታላቅ ነህ ዘላለም

ምስጉን ነው የተመሰገነ ምስጉን ነው የተመሰገነ ባሪያውንእኔን ይቅር ያለ ይመስገን ይመስገንልኝ ጎጆዬን አምላክ ሞላልኝ             
እጅህ ሰፊ እንደሆነ አውቃለሁ ጌታዬ የጎደለው ሞልቷል ይድረስ ምስጋናዬ ያጣሁትን ከአንተ አግኝቻለሁ ሁሉን ነገር ለበጎ ብያለሁ (2) አዝ ማቄን የቀደደ ደስታ አስታጠቀኝ ባዶ የነበርኩት ሁሉ ተሰጥቶኛል ሰጭም ነሽም እግዚአብሔር ብቻ ነው የሰው ድርሻ በር ማንኳኳት ነው (2) አዝ እገፋለው እንጂ እኔ አልጨነቅም መሰረቴ አንተ ነህ ከቶ አልናወጥም ስትሰጠኝ የሚታየውን(2) እንዳትረሳኝ የዘለዓለሙን አዝ ቢሰጥ አያልቅበት ለካስ ክቡር ጌታ ሁሉን ከወነልኝ በልዩ ችሎታ ድሆች ስንሆን ሁሉ አለንና (2) አምላካችን ይድረሰው ምስጋና
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች    •➢ ሼር // SHARE 👇👇👇 @yemezmur_getimoche @yemezmur_getimoche @yemezmur_getimoche

የካስከው አንተ የካስከው አንተ የበደልኩ እኔ የቆሰልከው አንተ የዳንኩት እኔ ወሰን የለውም መጠን መመርመር ከሕሊና ይልቃል ጌታ ያንተስ ፍቅር
አዝ
እስከ መስቀል ሞት የደረስክልኝ ስለ እኔ ብለህ የደማህልኝ በደምህ ዋጋ ተገዝቻለው ከእንግዲህ ወዲህ የራሴ አይደለሁ/2/
አዝ
አንተ ተደፋህ እኔ እንድል ቀና የእዳዬን ሸክም ተሸከምክና ጌተ ሴማኔ ጌታ  ጸለየ አስተምረኸኛል አረአያ ሆነህ/2/
አዝ
ጌታ ደወዬን በእውነት ተቀበልክ ሁሉን ቻይ ጌታ ስለኔ ደከምክ ልብ ኩላሊትን የምትመረምረው ማን መታህ አሉ አይንህን አስረው/2/
አዝ
በአይሁድ ሸንጎ ለፍርድ የቆምከው ንፁሁ በሐሰት የተከሰስከው አበሳ በደል አይደል ኖሮብህ እኔን ወደህ ነው ለዚህ መድረስህ/2/ ዘማሪ ገብረዮሐንስ ገብረፃድቅ ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች    •➢ ሼር // SHARE 👇👇👇 @yemezmur_getimoche @yemezmur_getimoche @yemezmur_getimoche

ርእስ : ከንቱ ነኝ ከንቱ ነኝ የከንቱ ከንቱ ነኝ ዋስትና መከታ እግዚአብሔር ካልሆነኝ ተስፋዬ የሚሆነኝ ሕይወት የሚሰጠኝ እግዚአብሔ ብቻ ነው የሚያስተማምነኝ አምላኬ ብቻ ነው የሚያስተማምነኝ እኔ ንጉሥ ነበርኩ በክብር ያጌጥኩኝ ሁሉን በምድር ላይ በጥበብ ፈፀምኩኝ የዚህ አለም ደስታ ምንም አላዋጣኝ በመጨረሻው ቀን በሞት ተወሰድኩኝ/2/ ከፀሐይቱ በታች አዲስ ነገር የለም ሰዎች ይደክማሉ እስከ ዘለዓለም ጥበቡን ፍለጋ ደክሜ ነበረ ሁሉም ከንቱ ሆኖ በመቃብር ቀረ/2/ ከእኔ አስቀድመዉ የከበሩ ሁሉ አፈር ተጭኗቸዉ የከበሩ ሁሉ እብደትና እዉቀት ሁሉን አወቅኳችሁ ምንም ቋሚ የለም ሁሉም ከንቱ ናቸዉ/2/ ልቤን የሰተሁት ተስፋ የጣልኩበት አልጨበጥ ብሎኝ አለሁኝ በጭንቀት የጥበቡም ብዛት ለትካዜ ሰተኝ እኔ በዚህ ምድር እጅግ ጐስቋላ ነኝ/2/ ልቤንም ፈተንኩት በደስታ በዛት የዚህን አለም ለውጥ ጣውት አቀመስኩት ሳቅም በልቤ ዉስጥ ይፍለቀለቅ ነበር ሁሉም ከንቱ ሆነ ገብቶ ከመቃበር/2/ ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች    •➢ ሼር // SHARE 👇👇👇 @yemezmur_getimoche @yemezmur_getimoche @yemezmur_getimoche

ገብር ኄር እግዚአብሔር የሰጠህ መክሊትህ የታለ ድንገት ቢመጣብህ ምን ታሳየዋለህ አንድ ከተሰጠው ያንን ከቀበረው አንተ ከገብረ ሐካይ ብልጫህ ምንድን ነው አደራ ጠባቂው የጸና በእምነቱ ታማኙ ገብር ኄር ባለ አምስት መክሊቱ ወጣ ወረደና ረርቶ አተረፈበት ጌታው በመጣ ቀን በእጥፍ መለሰለት ወደ ደስታው ገባ ክብርን ተሸለመ በጥቂቱ ታምኖ በብዙ ተሾመ        አዝ= = = = = ሊሠራ እንዳቅሙ ሁለት የተሰጠው ሌላ ሁለት አትርፎ ጌታውን ጠበቀው ሊቆጣጠራቸው ዳግመኛ ሲመጣ የመክሊቱን ዋጋ ከነትርፉ አመጣ ወደ ደስታው ገባ ክብርን ተሸለመ በጥቂቱ ታምኖ በብዙ ተሾመ        አዝ= = = = = አንድ መክሊት ብቻ የተሰጠው ሐካይ ምድር ሥር ደበቀው አኖረበት ድንጋይ  የአደራ መክሊቱን መቅበሩ ሳያንሰው ጨካኝ ክፉ ብሎ ጌታውን ሰደበው መክሊቱን ተቀማ አሥር ላለው ሰጡት ለቅሶ ወዳለበት ጨለማ ስር ጣሉት                ዘማሪት ሲስተር ሕይወት ተፈሪ ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች    •➢ ሼር // SHARE 👇👇👇 @yemezmur_getimoche @yemezmur_getimoche @yemezmur_getimoche