fa
Feedback
የቀጠናው ተመልካች

የቀጠናው ተመልካች

رفتن به کانال در Telegram

በአለማችን ቀጠናዎች የሚከሰቱ ክስተቶችን ይዘግባል፣ ሳይቀዘቅዝ በትኩሱ። ለጥያቄና ለአስተያየቶች በኢሜል asuleyma246@Gmail.com ብላችሁ ፃፉልኝ።

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
4 310
مشترکین
-524 ساعت
-227 روز
-8430 روز
آرشیو پست ها
🇮🇷🇺🇸 ትናንት ለኢራኖች የነገርናቸው፣ በለበጣ ስትሳደቡ፣ ሙድ ስትይዙ፣ ፕሬዝዳንቱ አይመልስልንም ብላችሁ እንዳትጠብቁ ነው። ግጥም አርጎ ይመልስላችኋል። ትናንት ትንሽ ማፋፈር፣ ትንሽ ማለቃቀስ ነበር፣ በስተመጨረሻ ግን ድርድሩን ቀጥለናል JD VANCE

🇬🇧 የእንግሊዙ ጠቅላይ ሚኒስት ኪር ስታርመር፣ ሥልጣኑን በገዛ ፈቃዱ ለቀቀ።

🇨🇴 የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን ጨምሮ የውጭ ጉዳዩ ማርኮ ሩብዮ እና የቬኔዝዌላ ግዚያዊ ፕሬዝዳንት ዶልሲ ሮድሪገዝ፣ ለአዲሱ የኮሎምቢያ ተመራጭ ፕሬዝዳንት የእንኳን ደስ ያለህ መልዕክት
+1
🇨🇴 የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን ጨምሮ የውጭ ጉዳዩ ማርኮ ሩብዮ እና የቬኔዝዌላ ግዚያዊ ፕሬዝዳንት ዶልሲ ሮድሪገዝ፣ ለአዲሱ የኮሎምቢያ ተመራጭ ፕሬዝዳንት የእንኳን ደስ ያለህ መልዕክት አስተላልፈዋል። የወቅቱ ኮሎምቢያ ፕሬዝዳንት ጉስጣቮ ፔትሮ በበኩሉ፣ የምርጫው ድምፅ መቀበያ ማሽኖች በእስራኤል ጣልቃ ገብነት ተጭበርብረዋል ብሎ የከሰሰ ሲሆን፣ ምርጫው እንደገና ሊቆጠር ይገባዋል ሲል ተናግሯል። ፕሬዝዳንቱ፣ በአህጉሩ ጠንካራ የወቅቱ የእስራኤል መንግሥት ተቃዋሚ ነው። በአሁኑ ሰዓት፣ የምርጫውን ውጤት በመቃወም በተለያዩ የኮሎምቢያ ከተሞች ግጭቶች ተነስተዋል።

🇨🇴 የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን ጨምሮ የውጭ ጉዳዩ ማርኮ ሩብዮ እና የቬኔዝዌላ ግዚያዊ ፕሬዝዳንት ዶልሲ ሮድሪገዝ፣ ለአዲሱ የኮሎምቢያ ተመራጭ ፕሬዝዳንት የእንኳን ደስ ያለህ መልዕክት
+1
🇨🇴 የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን ጨምሮ የውጭ ጉዳዩ ማርኮ ሩብዮ እና የቬኔዝዌላ ግዚያዊ ፕሬዝዳንት ዶልሲ ሮድሪገዝ፣ ለአዲሱ የኮሎምቢያ ተመራጭ ፕሬዝዳንት የእንኳን ደስ ያለህ መልዕክት አስተላልፈዋል። የኮሎምቢያ ፕሬዝዳንት ጉስጣቮ ፔትሮ፣ የምርጫው ድምፅ መቀበያ ማሽኖች በእስራኤል ጣልቃ ገብነት ተጭበርብረዋል ብሎ የከሰሰ ሲሆን፣ ምርጫው እንደገና ሊቆጠር ይገባዋል ሲል ተናግሯል። ፕሬዝዳንቱ፣ በአህጉሩ ጠንካራ የወቅቱ የእስራኤል መንግሥት ተቃዋሚ ነው። በአሁኑ ሰዓት፣ የምርጫውን ውጤት በመቃወም በተለያዩ የኮሎምቢያ ከተሞች ግጭቶች ተነስተዋል።

🇨🇴 የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን ጨምሮ የውጭ ጉዳዩ ማርኮ ሩብዮ እና የቬኔዝዌላ ግዚያዊ ፕሬዝዳንት ዶልሲ ሮድሪገዝ፣ ለአዲሱ የኮሎምቢያ ተመራጭ ፕሬዝዳንት የእንኳን ደስ ያለህ መልዕክት
+1
🇨🇴 የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን ጨምሮ የውጭ ጉዳዩ ማርኮ ሩብዮ እና የቬኔዝዌላ ግዚያዊ ፕሬዝዳንት ዶልሲ ሮድሪገዝ፣ ለአዲሱ የኮሎምቢያ ተመራጭ ፕሬዝዳንት የእንኳን ደስ ያለህ መልዕክት አስተላልፈዋል። የኮሎምቢያ ፕሬዝዳንት ጉስጣቮ ፔትሮ፣ የምርጫው ድምፅ መቀበያ ማሽኖች በእስራኤል ጣልቃ ገብነት ተጭበርብረዋል ብሎ የከሰሰ ሲሆን፣ ምርጫው እንደገና ሊቆጠር ይገባዋል ሲል ተናግሯል። በአሁኑ ሰዓት፣ የምርጫውን ውጤት በመቃወም በተለያዩ የኮሎምቢያ ከተሞች ግጭቶች ተነስተዋል። የወ

🇶🇦 ኳታር፣ ዛሬ በደረሰባት ፍንዳታ የቆሰለም፣ የሞተም የለም ካለች በኋላ፣ አሁን የሚመለከታቸው አካላት 54 የቆሰሉ እና 18 የጠፉ ሰዎች እንዳሉ ተናግረዋል።

🇷🇺🇺🇦 ሩሲያ የምትለወጠው ከሽንፈት በኋላ ብቻ ነው። ሩሲያ በጦር ሜዳ እስክትሸነፍ ድረስ፣ ምንም ነገር ሲቀየር አላየሁም። ምክንያቱም ከላይ በስልጣን ደስተኛ የሆኑ ወይም አሁን ባለው ሁኔታ ላይ ኢንቨስት ያደረጉ በጣም ብዙ ሰዎች አሉ። በሙስና ምክንያት በሚያስደንቅ ሁኔታ ሀብታም ናቸው። የአማካይ ሩሲያዊ ሕይወትን የተሻለ ለማድረግ ብዙ ኢንቨስት አያደርጉም። በእርግጠኝነት ስለ ወታደሮቻቸው ምንም ትኩረት አይሰጡም። ስለዚህ ሩሲያ እስክትሸነፍ ድረስ፣ ትለዋወጣለች ብዬ አላስብም። አሁን በብዙ ቦታ ክፍተቷን እየተጠቀምንበት ነው፣ አግዙን እንተጋገዝ። ዘለንስኪ *-*-*- 'የናቁት ወንድ ያስረግዛል' ሆነች እኮ ዘለንስኪ። በዚህ ጦርነት የፑቲን መልመጥመጥ እና እጅግ ዘገምተኝነት የሚያስደንቅ ነው፣ ዛሬ ድረስ፣ ጦርነቱን 'ጦርነት' ብሎ ለመጥራት ፈቃደኛ አይደለም። 'ጦርነት' ብሎ ሁኔታውን መግለፅ በሀገሩ ያሳስራል። በመቶ ዓመት ዓለም ዓይቶት የማያውቀው ጦርነት እየተደረገ። ይሄ ጤንነት ነው? SMO ይለዋል፣ Special Military Operation. ሠራዊቱ እያለቀ፣ ሩቅ ያደረገው ጦርነት፣ ሞስኮ ክሬምሊን ድረስ መጥቶለት፣ 'አይ ግጭት ነው' ግጭት ነው? ጦርነትን 'ጦርነት' ብሎ ላለመጥራት ልብ ከሌለው፣ ንቆታል ማለት ነው። ያ ደግሞ 'የናቁት ያስረግዛል' እየሆነበት ነው። በእርግጥ ከዚህ ሁሉ በኋላ፣ አይ በቃ 'ጦርነት' ነው ብሎ ቢል ይሳቅበታል! ስለዚህ 'ግጭት' ናት እያለ ይቀጥል። በኢትዮጵያም እንዲያ ነው፣ ራስን ማታለል ነው የተያዘው። 'ጦርነት አለ' ማለት ያሳስራል፣ 'ግጭት' ነው የሚባለው። በዚህም ቢሆን፣ እያስረገዙት ነው።

🇮🇷🇺🇸🇨🇭የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፡ በስዊዘርላንድ ሲደረግ የዋለው የዛሬው ድርድር እጅግ አመርቂ ውጤት የታየበት ነበር፣ ድርድሩ ሌሊቱን ይቀጥላል ብሏል።

⚡️🇨🇴 የኮሎምቢያው ፕሬዝዳንት ጉስታቮ ፔትሮ፣ እስራኤል የዛሬውን የሀገሩን የምርጫ ውጤት አጭበርብራለች ሲል ከሰሰ። ፕሬዝዳንቱ፣ እስራኤል በሀገሪቱ የድምጽ መስጫ ሶፍትዌር ላይ ጣልቃ ገብታለች ሲ
⚡️🇨🇴 የኮሎምቢያው ፕሬዝዳንት ጉስታቮ ፔትሮ፣ እስራኤል የዛሬውን የሀገሩን የምርጫ ውጤት አጭበርብራለች ሲል ከሰሰ። ፕሬዝዳንቱ፣ እስራኤል በሀገሪቱ የድምጽ መስጫ ሶፍትዌር ላይ ጣልቃ ገብታለች ሲል ከሰሰ፣ ሁሉም ድምጾች እንደገና እንዲቆጠሩ እና የሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች፣ ኦዲት እንዲደረጉ ጥሪ አቅርቧል። በዛሬው የፕሬዝዳንትነት እጩ የማጣሪያ ምርጫ፣ የእስራኤል ደጋፊ እና አቀንቃኝ የሆነው፣ Abelardo de la Espriella, ምርጫውን ያሸነፈ ሲሆን በአካባቢው ካሉ፣ እራሳቸውን LatAm ብለው ከሚጠሩትና ከቅርብ ጊዜ በኋላ ወደ ሥልጣን ከመጡት የእስራኤል ደጋፊ ሀገራት መሪዎች፣ ከአርጀንቲናው ሚሌ፣ ከቺሌው ካስት እና ከኢኳዶሩ ኖቦዋ፣ የእንኳን ደስ ያለህ መልዕክት ተቀብሏል። ፕሬዝዳንት ጉስታቮ ፔትሮ እና የኮሎምቢያ መንግሥት፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እስራኤል በሀገሩ ያሉ ተቀናቃኝ ፖለቲከኞችን፣ በጎረቤት ሀገሮች እንዳደረጉት ብለው እንደሚያምኑት፣ በመደገፍ ላይ የምታደርገውን ጣልቃ ገብነት እንድታቆም ሲያሳስቡ ቆይተዋል። ፕሬዝዳንቱ፣ በላቲን አሜሪካ ትልቁ የእስራኤል ፖሊሲዎች ነቃፊ መሪ ነው።

⚡️🇨🇴 የኮሎምቢያው ፕሬዝዳንት ጉስታቮ ፔትሮ፣ እስራኤል በሀገሪቱ የድምጽ መስጫ ሶፍትዌር ላይ ጣልቃ ገብታለች ሲል ከሰሰ፣ ሁሉም ድምጾች እንደገና እንዲቆጠሩ እና የሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች፣ ኦዲት እንዲደረጉ ጥሪ አቅርቧል። ጉስታቮ ፔትሮ እና የኮሎምቢያ መንግሥት፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እስራኤል በሀገሩ ያሉ ተቀናቃኝ ፖለቲከኞችን በመደገፍ ላይ የምታደርገውን ጣልቃ ገብነት እንድታቆም ሲያሳስቡ ቆይተዋል። ፕሬዝዳንቱ በላቲን አሜሪካ ትልቁ የእስራኤል ፖሊሲዎችን ነቃፊ መሪ ነው።

⚡️🇨🇴 የኮሎምቢያው ፕሬዝዳንት ጉስታቮ ፔትሮ፣ እስራኤል በሀገሪቱ የድምጽ መስጫ ሶፍትዌር ላይ ጣልቃ ገብታለች ሲል ከሰሰ፣ ሁሉም ድምጾች እንደገና እንዲቆጠሩ እና የሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ኦዲት እንዲደረጉ ጥሪ አቅርቧል። ጉስታቮ ፔትሮ እና የኮሎምቢያ መንግሥት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ፣ እስራኤል፣ በሀገሩ ያሉ ተቀናቃኝ ፖለቲከኞችን በመደገፍ ላይ የምታደርገውን ጣልቃ ገብነት እንድታቆም ሲያሳስቡ ቆይተዋል። ፕሬዝዳንት በላቲን አሜሪካ ትልቁ የእስራኤል ፖሊሲዎችን ነቃፊ መሪ ነው።

🇮🇷 የኢራን ቁልፍ ዋና ተደራዳሪ እና የፖርላማ አባል፣ ቃሊባፍ
🇮🇷 የኢራን ቁልፍ ዋና ተደራዳሪ እና የፖርላማ አባል፣ ቃሊባፍ

🇮🇷🇺🇸🇮🇱 የእስራኤልን ከሊባኖስ (በከፊል) ለመውጣት እና ጥቃት ለማቆም ውሳኔን ተከትሎ፣ ኢራን አቋርጣ የነበረውን የዛሬውን የስዊዘርላንዱን ድርድር እንደምትቀጥል አስታውቃለች።

🇮🇷🇺🇸🇮🇱 የኢራን ጫና ሠርቷል፡ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለእስራኤሉ ኔታንያሁ በነገረው መሠረት እስራኤል ወታደሮቿን ከሊባኖስ በከፊል ልታስወጣ ነው። የእስራኤል ሚዲያ እንደዘገበው IDF በሊባኖስ ያለውን ኃይሉን የመቀነስ ሂደት የሚጀምር ሲሆን፣ የሀገር ውስጥ ሚኒስትር ደግሞ ከነገ ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በሰሜናዊ ሰፈራዎች የሚገኙትን ሁሉንም ገደቦች ያስወግዳል ተብሎ ይጠበቃል። በተመሳሳይ፣ የእስራኤል ጦር ሬዲዮ እንደዘገበው፣ የኢራን ግፊት ስኬታማ ሆኗል። ዶናልድ ትራምፕ ቤንያሚን ኔታንያሁ እስራኤል ከደቡብ ሊባኖስ ጦሩን እንዲያስወጣ መመሪያ ሰጥቶታል ተብሏል። አንድ የኢራን ምንጭ በተጨማሪም ዩናይትድ ስቴትስ እስራኤል ከሊባኖስ በከፊል እንድትወጣ ተስማምታለች ሲል ተናግሯል። ይሁን እንጂ ኢራን፣ ማንኛውም የወደፊት መግባባት የሚደረሰው፣ እስራኤልን ከተያዙት የሊባኖስ ግዛቶች ሙሉ በሙሉ እንድትወጣ ማድረግ ሲቻል ነው በሚለው አጥብቃ እንደምታምን ተነግሯል። ከፊል እርምጃዎች ብቻ ችግሩን እንደማይፈቱት ተናግራለች።

🇶🇦 የኳታር ባለስልጣናት ፍንዳታው በቴክኒክ ችግር የተፈጠረ ነው፣ የሞተም ሆነ የቆሰለ የለም ብለዋል። ፍንዳታው ሀገር አንቀጥቅጥ ነበር ተብሏል።

🇶🇦⚡️ ሰበር ዜና፣ ሰበር ዜና - ምንነቱ ያልታወቀ እጅግ ከባድ ፍንዳታ፣ ከዶሃ ከተማ አቅራቢያ በሚገኘው በRas Laffan ጋዝ ኢንዱስትሪ መሠረተ ልማት ላይ ተከስቷል። እንደ ዓይን እማኞች ምስ
🇶🇦⚡️ ሰበር ዜና፣ ሰበር ዜና - ምንነቱ ያልታወቀ እጅግ ከባድ ፍንዳታ፣ ከዶሃ ከተማ አቅራቢያ በሚገኘው በRas Laffan ጋዝ ኢንዱስትሪ መሠረተ ልማት ላይ ተከስቷል። እንደ ዓይን እማኞች ምስክርነት "ሀገሩ በሙሉ የመሬት መንቀጥቀጥ እንደመታው ተንቀጥቅጧል።" 

🇮🇷🇺🇸| የኢራን ፓርላማ አፈጉባኤ ጋሊባፍ ለትራምፕ ዛቻ ምላሽ ሰጥቷል፡- አሜሪካኖች፣ 'ዛቻዎቻችን ምንም ነገር ቢያስገኙ ኖሮ፣ ዛሬ የተስፋ መቁረጥ ስሜት ውስጥ ባልገባን ነበር ብለው ለራሳቸው
🇮🇷🇺🇸| የኢራን ፓርላማ አፈጉባኤ ጋሊባፍ ለትራምፕ ዛቻ ምላሽ ሰጥቷል፡-
አሜሪካኖች፣ 'ዛቻዎቻችን ምንም ነገር ቢያስገኙ ኖሮ፣ ዛሬ የተስፋ መቁረጥ ስሜት ውስጥ ባልገባን ነበር ብለው ለራሳቸው አያስቡምን?' የአሜሪካንን ዛቻ በቁም ነገር አንመለከተውም። በንግግራቸው ላይ ጥንቃቄን ቢያደርጉ ይሻላቸዋል። የጦር ኃይላችን በተለየ መንገድ ምላሽ ለመስጠት ዝግጁ ነው። የቱንም ያህል ቢያወሩ፣ ወሬ ብቻ ናቸውና ምንም አያመጡም! በተግባር የምንገኘው እኛ ነን።

🇮🇷🇺🇸| የኢራን ፓርላማ አፈጉባኤ ጋሊባፍ ለትራምፕ ዛቻ ምላሽ ሰጥቷል፡- አሜሪካኖች፣ 'ዛቻዎቻችን ምንም ነገር ቢያስገኙ ኖሮ፣ ዛሬ የተስፋ መቁረጥ ስሜት ውስጥ ባልገባን ነበር ብለው ለራሳቸው
🇮🇷🇺🇸| የኢራን ፓርላማ አፈጉባኤ ጋሊባፍ ለትራምፕ ዛቻ ምላሽ ሰጥቷል፡- አሜሪካኖች፣ 'ዛቻዎቻችን ምንም ነገር ቢያስገኙ ኖሮ፣ ዛሬ የተስፋ መቁረጥ ስሜት ውስጥ ባልገባን ነበር ብለው ለራሳቸው አያስቡምን?' የአሜሪካንን ዛቻ በቁም ነገር አንመለከተውም። በንግግራቸው ላይ ጥንቃቄን ቢያደርጉ ይሻላቸዋል። የጦር ኃይላችን በተለየ መንገድ ምላሽ ለመስጠት ዝግጁ ነው። የቱንም ያህል ቢያወሩ፣ ወሬ ብቻ ናቸውና ምንም አያመጡም! በተግባር የምንገኘው እኛ ነን።

🇮🇷🇺🇸 ሰበር ዜና፡ የኢራን ልዑካን ቡድን ስብሰባውን ረግጠው ወጡ፣ የኢራን መገናኛ ብዙሀን TASNIM እንደዘገበው። ተደራዳሪዎቹ ረግጠው የወጡት የትራምፕን ማስፈራሪያ በመቃወም እንደሆነ ተነግሯል።

🇺🇸⚡️🇮🇷 ኢራኖች፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ "… በዚህ ጊዜ ውስጥ አንዱ ሌላውን ከማስፈራራት መቆጠብ አለበት!" የሚለውን የመግባቢያ ስምምነት አንቀጽ፣ በዛሬው ማስፈራሪያው ጥሶት ተገኝቷል፣ ብለዋል
🇺🇸⚡️🇮🇷 ኢራኖች፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ "…
በዚህ ጊዜ ውስጥ አንዱ ሌላውን ከማስፈራራት መቆጠብ አለበት!"
የሚለውን የመግባቢያ ስምምነት አንቀጽ፣ በዛሬው ማስፈራሪያው ጥሶት ተገኝቷል፣ ብለዋል።