fa
Feedback
Amharic book store

Amharic book store

رفتن به کانال در Telegram

እዚህ Channel ላይ ያስተምራሉ ያዝናናሉ ብለን የምናስባቸውን መፅሀፎች ማግኘት ይችላሉ 🎯ተከታታይ ልቦለድ 🎯ግጥም 🎯ፍልስፍና 🎯ምክር የተለያዩ PDF መፅሐፍት ለማግኘት ይቀላቀሎ ቻናሉን ማጋራት አይዘንጋ 🙏 🙏 🙏

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
458
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+197 روز
+20330 روز
آرشیو پست ها
✅ብርቅርቅታ ✅ተርጓሚ አብይ ደምሴ ✔️ግዜው የሁለተኛው የአለም ጦርነት ነው። ቦታው በጦርነቱ ወላፈን በብርቱ እየተደቆሰች በነበረችው ፈረንሳይ ፓሪስ። መልከመልካሙ አሜሪካዊ ወታደር ዎከር እና ውቧ ፈረንሳዊት ሶላንጅ በፍቅር ይወድቃሉ። ጦርነቱ እንደተፈፀመ ወደ አሜሪካ ይዟት ተመልሶ ይጋባሉ። ✔️የዎከር እና የሶላንጅ ፍቅር ተረት ውስጥ እንደሚገኙ ተረኮች ፍፁም ነበር። ዎከር ሶላንጅን ያመልካታል። ሶስት ሴት ልጆች ወለዱ። ይሁን እንጂ የፍቅሩን ያህል ቀናተኛ ነበር። በዚሁ ቅናት ተገፋፍቶ ከጓደኛው ጋር ግንኙነት እንዳላት በመጠርጠር ሶላንጅን አንቆ ከገደላት በኋላ ራሱን ያጠፋል። በተረት የጀመረ ፍቅራቸው በትራጄዲ ይደመደማል። ✔️የመጽሐፉ ዋናው ታሪክ የሶስቱ ሴት ልጆችን ቀሪ እጣ ፈንታ ይመለከታል፦ ሒላሪ፣ አሌክሳንድራ፣ ሜጋን። ከሶስቱ ነፍስ የምታውቀው ትልቋ ሒላሪ ነበረች። አሌክሳንድራ እና ሜጋን በጉዲፈቻ ለሃብታም ቤተሰቦች ተሰጡ። ሒላሪ ግን እንደ እህቶቿ አልተመቻትም። ሕይወት ለሷ ጨካኝ ነበረች። በተደጋጋሚ የመደፈር አደጋ ደርሶባታል። ✔️ልጆቹ ከሃያ አመት በላይ ተለያይተው ካደጉ በኋላ ግን ሒላሪ እህቶቿን ማፈላለግ ጀመረች። ነገሮች ተለዋውጠዋል። እህቶቿ ስለ ወላጆቻቸው የሚያውቁት ነገር አልነበረም። በዚህ ሂደት ውስጥ አስደንጋጭ እውነታዎች መገለጥ ጀመሩ። ቀሪውን ከመጽሐፉ! https://t.me/Amharic_Books_storee

አንድ ሰሚናር ላይ እድል አግኝቼ ተካፍዬ ነበር።አስተማሪው እጅግ አንድበተ ርቱዕና ሲናገር ንግግሩ ልክ እንደ ውሃ በቀላሉ ወደ ውስጤ ይፈስ ጀመር።እጅግ ከሰማኋቸው ብዙ ውብ ነገሮች አንዱና ዋናው እን
አንድ ሰሚናር ላይ እድል አግኝቼ ተካፍዬ ነበር።አስተማሪው እጅግ አንድበተ ርቱዕና ሲናገር ንግግሩ ልክ እንደ ውሃ በቀላሉ ወደ ውስጤ ይፈስ ጀመር።እጅግ ከሰማኋቸው ብዙ ውብ ነገሮች አንዱና ዋናው እንዲህ የሚል ነበር። "ስኬት ማለት ከየት እንዳለን ማወቅ፣እንዴት እንደምንሄድ ማወቅና ወደ የት እንደምንሄድ ማወቅ ነው" ብሎ የተናገረውን ከሰሚናሩ በኋላ ቁጭ ብዬ ሳስብበት እውነትም ትልቅ አባባልና እጅግ ለህይወቴ አስፈላጊ መሆኑ ገባኝ። 📓ርዕስ፦የሀላፊነት ሽልማት ✍️ደራሲ፦ዳውድ ዑስማን ሮዕብ ዕለት ለህትመት የበቃ አሪፍ መጽሐፍ ነው #ደራሲው ገዝታችሁ እንድታነቡት ጋብዟችኋል። https://t.me/Amharic_Books_storee

1️⃣. ኢጎ ምንድን ነው? ኢጎ ከህጻንነትህ ጀምሮ ማህበረሰቡ የፈጠረብህ የውሸት ማንነት ነው፡፡ይህ እብድ የሆነ አለም እብድ አድርጎ አእምሮህን ቀርጾታል፡፡ 🤎መጥላት፣ መቅናት፣ መናቅ፣መፍረድ፣ መከፋፈል፣ ዘረኛ መሆን፣ በሀብት መመካት፣ እኔ እኔ ብቻ ማለት...ወዘተ ነገሮች በውስጥህ ተሰግስገዋል፡፡አንዳንዴ ጊዜ ፡ "እንዴት እንደዚህ አይነት መጥፎ ሰው ሆንኩኝ?" ትያለህ፡፡መጥፎ የሆንከው ግን አንተ ሳትሆን ኢጎህ ነው፡፡ 🔢. ምርጥ ከሆኑ ሰዎች ጋር ብቻ ጊዜህን አሳልፎ፡፡መጥፎ ሰው ብትሆንም እንኳን በምርጥነታቸው ትሸነፋለህ፡፡ጓደኞችህን በጥንቃቄ ምረጥ፡፡ 🔢. ሀሳብህን ከገንዘብህ በላይ ተቆጣጠረው፡፡አእምሮህ የአሉታዊ ሀሳቦች ጭፈራ ቤት ከሆነ ሙሉ ህይወትህ ገደል ይገባል፡፡በልብህ ማዕከል የሚነግሰው ሀሳብ ውሎ አድሮ የህይወትህ እውነታ ይሆናል፡፡እናም በጥንቃቄ ጠብቀው፡፡ሁልጊዜ አዎንታዊ ሀሳብን ብቻ አስብ፡፡ለመሆኑ አሁን ምን እያሰብክ  ነው? 🔢 ሰዎችን አፍቅር፡፡ከልብህ አክብር፡፡ምን ይሉኛል ብለህ ግን ምንም ነገር አታድርግ፡፡ሰዎች የሚሉትን ነገር አያጡም፡፡ በውሃ ላይ ብትራመድ ራሱ ዋና ስለማትችል ነው ማለታቸው አይቀርም፡፡ራስህ ላይ ብቻ አተኩር፡፡አጭር ለሆነችው ህይወት ሰው ምን ይለኛል ብሎ መጨነቅ መሸወድ ነው፡፡ + 🔢. ቁሳቁስ ደስታ አይሰጥህም፡፡አሁን ደስታ የራቀህ  ብራንድ ነገር ስሌለህ ከመሠለህ ይቅርታ፡፡አለም ውስጥ ያለው ቁሳቁስ ሁሉ የአንተ ቢሆንም እውነተኛ ደስታን አታገኝም፡፡አዎ ብራንድ ነገር ስትገዣው ሊያሳብድህ ይችላል፡፡ግን አንድ ቀን ባደረ ቁጥር የገዛህው ነገር  የሚሰጥህ ደስታ እየተሸረሸረ ይመጣል፡፡እስቲ ከዚህ ቀደም ቋምጥህ የገዛሀቸውን ነገሮች አስብ፡፡ ⭐️እነዛ ተንሰፍስፈህ የገዛሻቸው ነገሮች ዛሬ ያንን የቀደመ ደስታህን ይሰጡሀል? በፍጹም፡፡ዛሬም ለመግዛት የምትንሰፈሰፉቸው ነገሮች እንደዛው ናቸው፡፡ከገዛሀቸው በኋላ ይደብሩሀል፡፡ይህ መጥፎ ጨዋታ ነው፡፡ደስታህ ያለው በውስጥህ ነው፡፡ከፍያ የለውም፡፡ነጻ ነው፡፡ጥሩ ሰው መሆን ብቻ ደስታ ይሰጥሀል፡፡አንተ ሰው እንዲያደርግልህ የምትፈልገውን ነገር ለሰው ስታደርግ ደስታ ወደ አንተ ይመጣል፡፡ 🔢. ሁሉም ነገር ሱስ ነው፡፡ህይወትህን መጥፎ የሚያደርገው መጥፎ ሱስ ነው፡፡መጥፎ ሱስን ግደለው፡፡መቃም፣ ማጨስ፣ መስከር፣ መዋሸት፣ መቅናት፣ መስነፍ...ማንኛው ወደኋላ የሚጎቱትህን ነገሮች ከህይወትህ ነቀለህ ጣላቸው፡፡በምትካቸው በጎ ሱስ ፈጠር፡፡ያ መሄድ ወደ ምትፈልግበት አለም ይወስድሀል፡፡ https://t.me/Amharic_Books_storee

✍ፍስሀ ያዜ 💪 በእውነት አባቶቻችን እንዴት ብልህ እና ጀግኖች ነበሩ! አንዲት ስንዝር መሬት ለጠላት አሳልፈው የማይሰጡ ፤ ግብፅን፣ ሱዳንን እና ሱማሊያን ያስገበሩ ፤ ፋርስን ተዋግተው ያሸነፉ፤ የግሪኮቹ ሆሜር እና ሄሮዱተስ ያወደሷትን የተቀኙላትን ሀገር የገነቡ ወርቃማ የኢትዮጵያ ልጆች። 😭 አባቶቻችን አጥንታቸውን እና ደማቸውን የገበሩለትን የአገሩን መሬት እየሸነሸነ የሚሸጠው እና በሌኒንና ማርክስ የግራ ዘመመ ርዕዮተ አለም ተጠምቆ ሀገሩን የበታተነውን ትውልዱን እርስ በእርስ የሚያባላውን የ60ዎቹን ትውልድ ቢያዩ እንዴት ያፍሩብን ይሆን? 😭የራሳችንን ጥለን የምዕራባውያንን ባህል መከተል እንደ ስልጣኔ የምንቆጥረውን የዚህ ዘመን የዘቀጠ ትውልድ ቢያዩ እንዴት አንገታቸውን ይደፉብን! . . . 👉አገራችንን እንወቅ ታሪክን እናንብብ 👉ደራሲው "የሳጥናኤል ጎል ኢትዮጲያ" በሚል መፅሀፉ እናውቀዋለን። https://t.me/Amharic_Books_storee

ሜል ሮቢንስ በሕይወቷ ተስፋ የቆረጠችበት ወቅት ነበር። ስራ አጥታለች፣ ትዳሯ እየፈረሰ ነበር፣ ጠዋት ከአልጋዋ ለመነሳት እንኳን አቅም አጥታ ነበር። አንድ ቀን ምሽት ቴሌቪዥን ላይ ሮኬት ሲወነጨፍ አ
ሜል ሮቢንስ በሕይወቷ ተስፋ የቆረጠችበት ወቅት ነበር። ስራ አጥታለች፣ ትዳሯ እየፈረሰ ነበር፣ ጠዋት ከአልጋዋ ለመነሳት እንኳን አቅም አጥታ ነበር። አንድ ቀን ምሽት ቴሌቪዥን ላይ ሮኬት ሲወነጨፍ አየች። "5-4-3-2-1... እሳቱ ተለኮሰና ሮኬቱ ወደ ላይ ተወነጨፈ።" በማግስቱ ጠዋት አላርሟ ሲጮህ፣ እንደተለመደው ተኝታ መቅረት አልፈለገችም። በልቧ "5-4-3-2-1" ብላ እንደ ሮኬት ከአልጋዋ ተስፈንጥራ ተነሳች። ይህች ትንሽ እርምጃ ሕይወቷን ቀየረችው። አእምሯችን አዲስና ከባድ ነገር ስናስብ በ5 ሰከንድ ውስጥ "ሰበብ" መፍጠር ይጀምራል። "ዛሬ ይበርዳል፣ ቆይ ትንሽ ልተኛ፣ ነገ እጀምራለሁ..." ይላል። ያ አእምሮህ ሰበብ አምጥቶ ሳይገድልህ በፊት፣ በ5 ሰከንድ ውስጥ እርምጃ መውሰድ አለብህ። 5-4-3-2-1 ብለህ ስትቆጥር፣ አእምሮህ ሰበብ መደርደሩን ያቆምና ወደ ተግባር ይገባል ትላለች።የ5 ሰከንድ ህጎች የተሰኘው መጽሐፏ በዚህ ሃሳብ ላይ የሚያጠነጥን ነው መጽሐፍ፦የ5 ሰከንድ ህጎች በሜል ሮቢንስ https://t.me/Amharic_Books_storee

🌍የአፍሪካ ፍልስፍና፡ በምክንያታዊነት እና በማንነት መካከል ያለ ፍልሚያ የአፍሪካ ፍልስፍና መኖር አለመኖር ጉዳይ በዘመናዊው የአካዳሚክ ዓለም ውስጥ ለረጅም ጊዜ አነጋጋሪ ሆኖ የቆየ አጀንዳ ነው። ይህ ክርክር የሚመነጨው “ፍልስፍና ምንድን ነው?” ለሚለው ጥያቄ ከሚሰጠው ትርጓሜ እና አውሮፓውያን ለዘመናት በአፍሪካውያን ላይ ከነበራቸው የተዛባ አመለካከት ነው። በአንድ በኩል ፍልስፍና ግለሰባዊ እና በጽሑፍ የሰፈረ መሆን አለበት የሚሉ ወገኖች ሲኖሩ፣ በሌላ በኩል ደግሞ የአንድ ማኅበረሰብ የዓለም እይታ እና ጥበብ እንደ ፍልስፍና መቆጠር አለበት የሚሉ ሙግቶች ይነሳሉ። ለክርክሩ መነሻ የሆነው ዋነኛው ምክንያት የአውሮፓውያን “ፍልስፍና የኛ ብቻ ነው” ባይነት ነው። እንደ ዴቪድ ሂዩም እና ኢማኑኤል ካንት ያሉ የምዕራባውያን ፈላስፋዎች አፍሪካውያንን ምክንያታዊነት የጎደላቸው አድርገው ይስሏቸው ነበር። ካንት በአንድ ወቅት “ጥቁር መሆን ብቻውን የሚናገረው ነገር ትርጉም የሌለው ለመሆኑ በቂ ማስረጃ ነው” እስከማለት ደርሷል። ይህ የተሳሳተ ግምት አፍሪካውያን የራሳቸው የሆነ ረቂቅ አስተሳሰብና ፍልስፍና ሊኖራቸው አይችልም የሚል የተሳሳተ መደምደሚያ ላይ ጥሏቸዋል። በ20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ ፕላሲድ ቴምፕልስ የተባሉ ሚስዮናዊ "Bantu Philosophy" የተሰኘውን መጽሐፍ በማሳተም ክርክሩን አዲስ መልክ አስያዙት። እሳቸውም የአፍሪካውያን የባህል እሴቶች፣ እምነቶችና ወጎች በራሳቸው ፍልስፍናዊ መዋቅር እንዳላቸው ተከራከሩ። ይህ አካሄድ "ኢትኖ-ፍልስፍና" ተብሎ የሚጠራ ሲሆን፣ ፍልስፍናን እንደ ግለሰብ ሳይሆን እንደ ማኅበረሰብ የጋራ ዕውቀት ይመለከታል። እንደ ሌኦፖልድ ሴዳር ሴንግሆር ያሉ የኔግሪቲውድ (Negritude) ንቅናቄ መሪዎች የአፍሪካውያንን ስሜታዊነትና ከተፈጥሮ ጋር ያላቸውን ቁርኝት እንደ ልዩ የዕውቀት መንገድ (Epistemology) አቅርበውታል። ሴንግሆር “ክላሲካል አውሮፓዊ ምክንያታዊ ነው፤ አፍሪካዊ ግን ተሳታፊ (Participant) ነው” በማለት የአፍሪካውያን የማሰብ መንገድ ከምዕራባውያን የተለየ መሆኑን አስረድተዋል። ታዋቂው ኬንያዊ ምሁር ጆን እምቢቲ (John Mbiti) "African Religions and Philosophy" በሚለው መጽሐፋቸው የአፍሪካውያንን የጊዜ ጽንሰ-ሀሳብ ተንትነዋል። አፍሪካውያን ለጊዜ ያላቸው አመለካከት ወደ ፊት ሳይሆን ወደ ኋላ (ያለፈው ዘመን) ላይ ያተኮረ መሆኑን ገልጸው፣ ይህም ለአፍሪካዊ ፍልስፍና አንድ ማሳያ መሆኑን ተከራክረዋል። በሌላ በኩል ደግሞ እንደ ፓውሊን ሁንቶንጂ (Paulin Hountondji) ያሉ ምሁራን ኢትኖ-ፍልስፍናን አጥብቀው ይተቻሉ። ሁንቶንጂ ኢትኖ-ፍልስፍናን “ምናባዊ ፍልስፍና” (Myth) ነው በማለት ይገልጹታል። ለእሳቸው ፍልስፍና ማለት የግለሰቦች የነቀፌታና የምክንያታዊነት ውጤት እንጂ የባህል ትረካ አይደለም። እውነተኛ የአፍሪካ ፍልስፍና በአፍሪካውያን የተጻፈና በምክንያት ላይ የተመሰረተ መሆን አለበት ይላሉ። ሄንሪ ኦዴራ ኦሩካ (Henry Odera Oruka) በሁለቱ ጽንፎች መካከል ያለ መንገድ ለመፈለግ ሞክረዋል። እሳቸውም "Sage Philosophy" በሚለው ጥናታቸው፣ በየገጠሩ የሚገኙ ጥበበኛ አዛውንቶች ምንም እንኳ ዘመናዊ ትምህርት ባይኖራቸውም፣ የማኅበረሰባቸውን ወግ በምክንያት የመመርመርና የመተቸት ብቃት እንዳላቸው አረጋግጠዋል። ይህም ፍልስፍና በአፍሪካ ውስጥ በቃል ደረጃም ቢሆን በተግባር መኖሩን አስመስክሯል። ስለ አፍሪካ ፍልስፍና በሚነሳበት ጊዜ የዘርዓ ያዕቆብ ስም ሳይጠቀስ አይታለፍም። በ17ኛው ክፍለ ዘመን የኖረው ኢትዮጵያዊው ፈላስፋ ዘርዓ ያዕቆብ በ"ሐተታ" መጽሐፉ፣ ከዴካርት በፊት የሰው ልጅ አእምሮን (Reason) እንደ ብቸኛ የእውነት መለኪያ አድርጎ ተጠቅሟል። ይህ ድንቅ ሥራ የአፍሪካ ፍልስፍና በጽሑፍ የሰፈረ፣ ምክንያታዊና ግለሰባዊ መሆኑን ለዓለም ያረጋገጠ ታላቅ ማስረጃ ነው። ክርክሩ ከዕውቀት ፍለጋ ባለፈ የማንነት ጥያቄ ነው። አፍሪካውያን የራሳቸው ፍልስፍና የላቸውም ማለት የማሰብ ብቃት የላቸውም እንደማለት ይቆጠራል። ስለዚህ የአፍሪካ ፍልስፍናን ማረጋገጥ የቅኝ ግዛት አስተሳሰብን የመስበር እና የአፍሪካን ሰብአዊነት ዳግም የማወጅ ሂደት ነው። ሌላው በክርክሩ ውስጥ የሚነሳው ነጥብ ቋንቋ ነው። "አፍሪካዊ ፍልስፍና በአውሮፓ ቋንቋዎች መቅረቡ ማንነቱን አይቀንሰውም ወይ?" የሚለው ጥያቄ ይነሳል። ፈላስፋው ክዋሲ ዊሬዱ (Kwasi Wiredu) አፍሪካውያን የራሳቸውን ጽንሰ-ሀሳቦች ወደ አውሮፓ ቋንቋዎች ሲተረጉሙ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸውና "የአእምሮ ቅኝ ግዛትን" ማስወገድ እንደሚገባ ያሳስባሉ። በአሁኑ ወቅት የአፍሪካ ፍልስፍና ራሱን የቻለ የትምህርት ዘርፍ ሆኖ እያደገ ነው። የክርክሩ ትኩረትም "አለ ወይስ የለም?" ከሚለው ወጥቶ "ይዘቱ ምንድን ነው? ለአለምስ ምን አዲስ ነገር ያበረክታል?" ወደሚሉ ጥያቄዎች ተሸጋግሯል። እንደ ኡቡንቱ (Ubuntu) ያሉ ፍልስፍናዎች ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ የሰው ልጅ ትስስርን በተመለከተ ትልቅ ትምህርት እየሰጡ ይገኛሉ። https://t.me/Amharic_Books_storee

#ኢኪጋይ #አዲስ_መጽሐፍ_በገበያ_ላይ 100 ዓመትና ከዚያ በላይ በጤናና በደስታ መኖር ይፈልጋሉ? ኢኪጋይ መጽሐፍ ጃፓኖች እንዴት መቶ አመት እና ከዚያ በላይ በጤናና በደስታ እንደሚኖሩ ምስጢራቸውን ዘርዝረው ለአለም ያሳዩበት መጽሐፍ ነው፡፡ #ኢኪጋይ መጽሐፍ ሁላችንም ረጅም፣ ትርጉም ያለውና ደስተኛ ሕይወት ለመኖር የሚረዱንን ቀላል ምስጢሮች ይገልጽልናል፡፡ #ስለመጽሐፉ _የተሰጡ_አስተያየቶች፡- አሁን የቱንም ያህል ተስፋ የቆረጡ ቢሆኑ፣ ኢኪጋይ መጽሐፍ በርግጥም ነገዎን በጉጉት እንዲጠብቁት ያደርግዎታል... ህይወትዎም ካሰቡት በላይ አርኪ ይሆናል። #ቢቢሲ_BBC #ኢኪጋይዎን አግኝተው የሚጀምሩት ጉዞ በርግጥም ከህይወትዎ ታላላቅ ጉዞዎች መካከል ቀዳሚው ነው። #ፎርብስ #ኢኪጋይ ፣ሁላችንም ረጅም፣ ትርጉም ያለው እና ደስተኛ ህይወት ለመኖር የሚረዱንን ቀላል ምስጢሮች ቀስ በቀስ ይገልጽልናል። ይህ መጽሐፍ በሳይንስ ላይ የተመረኮዙ ጥናቶች፣ በቀጥታ ከተደረጉ ውይይቶች ጋር በሚያምር ሁኔታ የተገለጡበት ነው፡፡ ከኋላዎ ከመግፋት ይልቅ፣ ከፊት ሆኖ ሞቅ እያደረገ በትእግስት እና በእርጋታ ይመራዎታል። #ኔል ፓስሪቻ በዓለም አቀፍ ቁጥር አንድ የደስተኝነት ምስጢር መጽሐፍ ደራሲ ደስታን ከስራ ውጭ አገኘዋለሁ ብለው ተሞኝተው ይሆናል። እውነተኛው የደስታ ቁልፍ ግን ኢኪጋይ ነው፤ በስራ ውስጥ ሀሴትን መቀዳጀት። #ዘ ኢንዲፔንደንት የግድ መከተል ያለብዎት የአኗኗር ዘይቤ! ኢኪጋይ ከሌሎች ዘይቤዎች ልዩ ነገር አለው። እንቅፋት የሆነብዎን በር ለመግፋት አይታገሉ፤ ይኸው ቁልፉ። #ዘ ጋርዲያን https://t.me/Amharic_Books_storee

📖ሽሽት | Are you afraid of the dark ✍️ሲድኒ ሼልደን (Sidney Sheldon) ✅ትርጉም:- ኤፍሬም እንዳለ ምርጥ ልብ አንጠልጣይ ልብ ወለድ መፅሐፍ https://t.me/Amharic_Books_storee

✔️መፅሐፍ ሃያ ሶስት ፳፫ The prophet kahlil Gibran ✅ወደ በርከታ ቋንቋዎች በመተርጉም አለም ላይ ግንባር ቀደም ከሆነ መፅሐፍት አንዱ የሆነው the prophet። ከ108 ቋንቋዎች በ
✔️መፅሐፍ ሃያ ሶስት  ፳፫     The prophet  kahlil Gibran   ✅ወደ በርከታ ቋንቋዎች በመተርጉም አለም ላይ ግንባር ቀደም ከሆነ መፅሐፍት አንዱ የሆነው  the prophet።  ከ108 ቋንቋዎች በላይ በመተርጎም 16ኛ  ደረጃ ላይ ይገኛል ። ✅ፍቅርን እንጂ ሃሳቦቻችሁን አትስጧቸው! 📖📖📚📚 ⭐በደረትዋ ህፃን ያቀፈች አንዲት ሴትም አለች ፦ " ስለ ህፃናት ንገረን? " እሱም አላት ፦ ፧ " ህፃናት ልጆቻችሁ የእናንተ ልጆች አይደሉም ። ህይወት ለራሷ ላላት ናፍቆት ሳባል የተወለዱ ወንድና ሴት ልጆቻችሁ እንጂ...በእናንተ በኩል መጡ እንጂ ከእናንተ አልመጡም ። ከእናንተ ጋር ቢኖሩም የእናንተ ንብረት አይደሉም...እናንተ ፍቅርን እንጂ ሀሳቦቻችሁን ልትሰጧቸው አትችሉም ። የየራሳቸው ሀሳቦች አሉዋቸውና... 📖📖📖 ✅እናንተ ለሥጋቸው መጠለያ ቤት ትሆኑዋቸው ይሆናል እንጂ ለነፍሶቻቸው ቤቶች አይደላችሁም ። ነፍሶቻቸው የሚኖሩት እናንተ ልታዩት በማትችሉት ፣ በህልማችሁ እንኳን ልትጎበኙት በማይቻላችሁ በነገ ቤት ውስጥ ነውና...እናንተ እንደ እነርሱ ለመሆን ሞክሩ እንጂ እነሱ እንደ እናንተ እንዲሆኑ አትፈልጉ ። ህይወት ወደኋላ ይመለሳልን? ትናንት ላይ ቆሞስ ይቀራልን...? ✅እናንተ ህፃናት ልጆቻችሁ ህይወት እንዳላቸው ቀስተኞች ሆነው ወደፊት የሚመነጠቁባቸው ደጋኖች ናችሁ ። ቀስት ወርዋሪው መጨረሻ በሌለው ጎዳና ላይ ያለውን ኢላማውን ያተኩራል ፤ ቀስቶች ተወናጭፈው ርቀው ይሄዱ ዘንድ በታላቅ ኃይል እናንተን ያጎብጧችኋል ። በቀስት ወርዋሪው እጅ መጉበጣችሁንም በደስታ ተቀበሉት ፤ ለበጎም ይሁን ። እሱ የሚወነጨፈውን ቀስት የሚያፈቅረውን ያህል የረጋውን ደጋን አያፈቅረውምን? " የጥበብ መንገድ ደራሲ ፦ ካህሊል ጂብራን https://t.me/Amharic_Books_storee

ታሪኩ ሩስያ ውስጥ ነው። የሩስያው ዛር ጴጥሮስ አንድ ጠባይ ነበረው። እስርቤቶችን ይጎበኝና ነጻ ሊያወጣው የወደደው እስረኛ ካለ ይለቀዋል። ያልተገደበ ስልጣን ስላለው ማንም አይቃወመውም። አንድ ቀን
ታሪኩ ሩስያ ውስጥ ነው። የሩስያው ዛር ጴጥሮስ አንድ ጠባይ ነበረው። እስርቤቶችን ይጎበኝና ነጻ ሊያወጣው የወደደው እስረኛ ካለ ይለቀዋል። ያልተገደበ ስልጣን ስላለው ማንም አይቃወመውም። አንድ ቀን ይህንኑ ተግባሩን ለመፈጸም ወደ እስር ቤት ጎራ አለ። ከባባድ ወንጀለኞች፣ ነፍሰገዳዮችች፣ አስገድዶ ደፋሪዎች ወዘተ እንዲህ ይሉታል፦ "እባክህ ንጉሥ ሆይ! እኔ ምንም አላጠፋሁም! ነጻ ሰው ነኝ። በስህተት ተፈርዶብኝ ነው። እባክህ ነጻ አውጣኝ" አንድ ነፍስ አጥፍቶ እድሜ ይፍታህ የተፈረደበት ወንጀለኛ ብቻ እንዲህ አለው፦ "እኔ ነፍሰገዳይ ነኝ። ወንጀሉን ፈጽሜያለሁ። እንዲያውም የተጣለብኝ ቅጣት በቂ አይደለም። እባክህ ጨምረህ ቅጣኝ" ዛር ጴጥሮስ ወዲያውኑ፦ "ይህንን ወንበዴ ቶሎ ልቀቁት። ሌሎቹንም ይበክላቸዋል። ከሱ በቀር ሁሉም ንጹህ ናቸው። እሱ ብቻ ነው ወንበዴ" https://t.me/Amharic_Books_storee

እሷ የክፍላችን ቁጥር አንድ ጎበዝ ተማሪ ናት። እኔ በቅርብ ርቀት እከተላታለሁ። አንድ ቀን የፊዚክስ የቤት ስራ ተሰጥቶን የኔና የሷን መልስ ስናነጻጽረው እርስበእርሱ ተቃራኒ ነው። እኔ እሷ ናት ትክ
እሷ የክፍላችን ቁጥር አንድ ጎበዝ ተማሪ ናት። እኔ በቅርብ ርቀት እከተላታለሁ። አንድ ቀን የፊዚክስ የቤት ስራ ተሰጥቶን የኔና የሷን መልስ ስናነጻጽረው እርስበእርሱ ተቃራኒ ነው። እኔ እሷ ናት ትክክል ብዬ መልሴን ወደሷ መልስ ቀየርኩ። ለካ እሷም ተሳስቻለሁ ብላ መልሷን ወደኔ መልስ ቀይራዋለች። መምህሩ ደብተራችንን ተቀብሎ መልሱን ሲያመሳክር የሷ መልስ ትክክል፣ የኔ ደሞ ስህተት ሆኖ ተገኘ። ይህ ማለት የኔ የመጀመሪያ መልስ ልክ ነበር። እሷ ደግሞ ስህተተኛ ነበረች። ታዲያ በአእምሮዬ ሁሌም የሚፈጠር ጥያቄ አለ።  እኔ ትክክለኛ የነበረውን መልሴን የቀየርኩት መል,ሷ አሳምኖኝ አልነበረም። በደረጃ ስለምትበልጠኝ ብቻ እሷ አትሳሳትም ከሚል በራስ ካለመተማመን የመጣ ድርጊት ነበር። ይህ አጋጣሚ ታዲያ ትልቅ ቁምነገር አስተማረኝ፦ "መቼም ቢሆን በሰዎች ሃሳብ ልክ ከመሆን በራስ ሃሳብ ስህተት መሆን ተመራጭ ነው" https://t.me/Amharic_Books_storee

🔶ጥላቻ አሲድ ነው። ወሳኙ የሕይወታችን ማዕከል በጣጥሶ ድራሹን ያጠፋዋል። ስለ ማርቲን ሉተር ኪንግ ደግመህ ደጋግመህ አስበው፤ “ጥላቻ ሊሸከሙት የማይገባ ሸክም ነው፤ ፍቅር ነጻነት ነው!” እያለ ይ
🔶ጥላቻ አሲድ ነው። ወሳኙ የሕይወታችን ማዕከል በጣጥሶ ድራሹን ያጠፋዋል። ስለ ማርቲን ሉተር ኪንግ ደግመህ ደጋግመህ አስበው፤ “ጥላቻ ሊሸከሙት የማይገባ ሸክም ነው፤ ፍቅር ነጻነት ነው!” እያለ ይሰብክ ነበር። ፍቅር ሁሉንም ነገር ወደ ላይ ያሸጋግራል፤ ጥላቻ ሁሉንም ያዋክባል። 🔷በውስጣችን ያለው የሚያንቀን ራስ ወዳድነታችን ቆዳውን ገፈን እርቃኑን በማስቀረት እንዳይጎዳን ማድረግ ይጠበቅብናል። ምክንያቱም ሉተር እንዳለው “በየትኛውም ነጥብ ላይ ጥላቻ የነቀርሳ በሽታ ሲሆን፤ ወሳኙ የሚያስከብረን ቦታችንን በመከልከል ነብሳችን ለስቃይ ይዳርገዋል። ኑሯችንና ሕይወታችንን ያቃውስብናል። ለማንኛውም ትልቁ ጠላታችሁ ኢጎያችሁ ነው https://t.me/Amharic_Books_storee

እይታ - ዶር እዮብ ማሞ.pdf30.99 MB

🔘አሪፍ ጸሐፊ አሪፍ መጽሐፍ መጻፍ ብቻ ሳይሆን በአሪፍ ደራሲ የተጻፉ መጽሐፍቶችን በሚስላቸው የተለያዩ ገፀባሕርያት ክላሲክ የሆኑ መጽሐፍቶችን ይጠቁምሃል። ✔️ሳቤላ መጽሐፍን የጠቆመኝና እንዳነበ ያደረገኝ ይህ የDr ምህረት ደበበ “ ሌላ ሰው ” የሚለው መጽሐፍ ነው። ሌላ ሰውን መጽሐፍ ያነበባችሁ ትዝ የሚላችሁ ከሆነ ከዶክተር ሲራክ ጋር የምትቀማጨለው ቆንጅዬዋ ሴተኛ አዳሪ አስታወሳችኋት ?” 📕ዶክተር ሲራክ ስምሽ ማነው ብሎ ሲጠይቃት “ ሳቤላ ” ትለዋለች» እሱም የስሟን ትርጉም ለማወቅና በምን ምክንያት እንደወጣለት ሲጠይቃት እንዲህ ብላ ነበር የመለሰችለት ፦ አባቴ «ሳቤላ» የሚል መጽሐፍ ውስጥ ያለችው ዋና ገፀባህርይ “ሳቤላን” ስለሚወዳት ነው በሷ ስም የሰየመኝ ትለዋለች ( ቃል በቃል አይደለም ) 📕እኔ ከርታታው ሌላ ሰው መጽሐፍን አንብቤ እንደጨረስኩ የመጀመሪያ ስራዬ የሆነው ሳቤላ መጽሐፍን ገዝቶ ያቺ በስሟ ፣ አባት የልጁን ስም እንዲሰይም ያደረገችው ድንቅ ገፀባህርይ ማን እንደሆነች ማወቅ ሆነ። እውነትም ደግሞ የምትወደድ እና የሚታዘንላት ከርታታ የሆነች ገፀባህርይ ናት። አስባችሁታል ንግስት የነበረችበት ቤት ውስጥ ሰራተኛ ሁና ስትቀጠር ?” ብቻ መጽሐፉን ያነበባችሁት ስሜቴን ትጋሩኛላችሁ ብዬ አስባለሁ። 📕በዚሁም የማክለው ነገር ቢኖር ፦ መጽሐፉን ያላነበባችሁት መጽሐፍት ወዳድ ጓደኞቼ ሆይ ይህንን ዘመን አይሽሬ ክላሲክ የሆነ መጽሐፍ አንብባችሁ ትደሰቱበት ዘንዳ ጥቆማዬ ነው። Pdf ትፈልጋላችሁ? https://t.me/Amharic_Books_storee

“ጤናማ” ስህተቶች! (የሕይወት ጸጸቶች” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ ማሞ መጽሐፍ የተወሰደ) በፈረንጆቹ አቆጣጠር በ1886 አንድን መድሃኒት ለመፈልሰፍ በሙከራ ላይ የነበረ ጆን (John Pemberton) የተሰኘ ሰው በሙከራ ምርምር ውስጥ ንጹህ ውኃ እጨምራሁ ብሎ በስህተት ጋዝ ያለው ውኃ (Carbonated water) ጨመረበት፡፡ መሳሳቱን ለማወቅ ብዙም ባይፈጅበትም በስህተቱ ምክንያት የተፈጠረውን ነገር ለማወቅ ፈልጎ ሲቀምሰው አስገራሚ ጣእም ያለውና አርኪ ስሜት ሰጪ መጠጥ ሆኖ አገኘው፡፡ ብዙም ሳይቆይ ኮካ ኮላ በመባል የታወቀ ዝነኛው መጠጥ ወደመሆን እንደመጣ ይነገራል፡፡ ስህተት ወደ ስኬት ሲለወጥ! ከብዙ መቶ አመታት በፊት ሸን (Shen Nung) የተሰኘ የቻይና ገዢ ከቤቱ ወጣ ብሎ በግቢው ውስጥ ተቀምጦ ውኃ በማፍላት ላይ እያለ በአካባቢው ከነበሩ ዛፎች ከአንዱ ላይ የረገፈ ቅጠል በድንገት በሚያፈላው ውኃ ውስጥ ወድቆ ይገባበታል፡፡ ገጠመኙን ባይወደውም ውሃውን ሲቀምሰው ቅጠሉ ለውኃው የሰጠውን አዲስ ጣእም ወደደው፡፡ ሻይ የተሰኘው በአለማችን ተወዳጅ የሆነው መጠጥ የተጀመረው በዚያው እንደሆነ ይታመናል፡፡ አላስፈላጊ ገጠመኝ ወደ አስፈላጊ ግኝት ሲቀየር! በፈረንጆቹ አቆጣጠር በ1928 አሌክሳንደር (Alexander Fleming) የተሰኘ አንድ ሰው ለብዙ ቀናት ከሄደበት የእረፍት ጉዞ ወደቤቱ ሲመለስ በወጥ ቤቱ ውስጥ አንድን የሻገተ ነገር ተመለከተ፡፡ ያንን ሻጋታ ለማስወገድ ከመቸኮል ይልቅ ቀረብ ብሎ ለማጥናት ፈለገ፡፡ ጊዜን ወስዶ ሲመራመር ዛሬ ፔኒሲሊን (Penicillin) በመባል የታወቀውን የብዙ በሽታ መድሃኒት የሆነውን ግኝት ደረሰበት፡፡ አላስፈላጊ የተፈጥሮ ክስተት ወደ ጥቅም ሲያድግ! ከላይ ያነበብናቸው ሶስት አጫጭር ታሪኮች በየእለት ኑሯችን ከሚከሰቱ ድንገተኛ ሁኔታዎችና ስህተቶች፣ እንዲሁም ደግሞ አዳዲስ ነገሮች ውስጥ ለመግባት በምንወስዳቸው እርምጃዎች የሚገጥሙንን ገጠመኞች የሚጠቁሙ ናቸው፡፡ እነዚህን መሰል ስህተቶች ወይም ገጠመኞች “ጤናማ የስህተት ገጽታዎች” ብለን ልንሰይማቸው እንችላለን፡፡ እንደዚህ አይነት ሁኔታዎች እንዳይከሰቱ ሕይወትን መኖርና ማጣጣም ማቆም አለብን፤ የምንወደውን ነገር ከማድረግ ራሳችንን መግታት አለብን፤ ችግር እንዳይፈጠር በሚል ፍርሃት መንቀሳቀስን መተው አለብን፡፡ ስህተት እሰራለሁ ወይም ያልተጠበቀ ነገር ይፈጠራል በሚል ፍርሃት ኑሮን ከመኖርና አዳዲስ ነገሮችን ከመጀመር አትገታ፡፡ ተፈጥሯዊ ስህተቶች የአዳዲስ ምእራፍ ደጆች ናቸውና! https://t.me/Amharic_Books_storee

አዲስ ምድር ✍ኤክሃርት ቶሌ (Eckhart Tolle) ትርጉም:- ኦስማን መሐመድ "አዲስ ምድር፡ ለህይወትህ አላማ መነቃቃት" በኤክሃርት ቶሌ የተፃፈ እና በ2005 የታተመ መንፈሳዊ ራስን አገዝ መፅሃፍ ነው። የመፅሃፉ ማዕከላዊ መነሻ የሰው ልጅ ኢጎ የብዙ ስቃያችን ምንጭ ነው እና ኢጎን በማለፍ ውስጣዊ ሰላም አግኝተን የበለጠ አርኪ ህይወት መኖር እንችላለን የሚል ነው። ቶሌ ኢጎ ከሀሳቦቻችን፣ ከስሜታችን እና ከውጫዊ ሁኔታዎች ጋር በመለየት ላይ የተመሰረተ የውሸት የራስነት ስሜት እንደሆነ ይሞግታል። ስለ ኢጎአችን በማወቅ እና ያለፍርድ ማክበርን በመማር ከእሱ መለየት እንጀምራለን እና ከእውነተኛ ተፈጥሮአችን ጋር መገናኘት እንችላለን ይህም ንጹህ ንቃተ ህሊና ነው። በመጽሐፉ ውስጥ ቶሌ በዕለት ተዕለት ሕይወት ውስጥ መገኘትን እና ጥንቃቄን ለማዳበር ተግባራዊ ምክሮችን እና ልምምዶችን ይሰጣል። መጽሐፉ የጋራ ኢጎን ጽንሰ-ሀሳብም ይዳስሳል፣ እሱም በህብረተሰቡ ውስጥ ያለውን የጋራ ማንነት እና የእምነት ስርዓቶች። ቶሌ የጋራ ኢጎን በማለፍ እና ከእውነተኛ ተፈጥሮአችን ጋር በመገናኘት በፍቅር፣ በመተሳሰብ እና በአንድነት ላይ የተመሰረተች አዲስ ምድር መፍጠር እንደምንችል ይጠቁማል። በአጠቃላይ፣ "አዲስ ምድር" የበለጠ አርኪ እና ትርጉም ያለው ህይወት ለመኖር ተግባራዊ መመሪያ የሚሰጥ አሳቢ እና አበረታች መጽሐፍ ነው። ለግልጽነቱ፣ ቀላልነቱ እና የለውጥ ኃይሉ የተመሰገነ ሲሆን በዓለም ዙሪያ ያሉ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አንባቢዎች ውስጣዊ ሰላም እና መንፈሳዊ መነቃቃትን እንዲያገኙ ረድቷል። ማጋራት መተሳሰብ ነው! https://t.me/Amharic_Books_storee

አብልቸው ልሙት “በሰው ልብ ውስጥ ራእይ ብቻ ሊሞላው የሚችል ባዶነት አለ” በአንዲት ከተማ ውስጥ አንድ ከቤተሰቦቹ ኃብትን የወረሰ ባለጠጋ እንደነበረ ይነገራል፡፡ ይህ ሰው የፈለገውን ያህል ወጪ በፈለገው ጊዜ ለማውጣት የሚያስችለው በቂ ገንዘብ ነበረው፡፡ ጥሩ ቤት፣ ጥሩ መኪናና የተሟላ ሁኔታ ነበረው፡፡ በዚህ ምቹ ሕይወት ብዙ አመታትን ኖሯል፡፡ ሆኖም ኑሮ የሕይወት ድግግሞሽ አዙሪት ሆኖበታል፡፡ ይበላል፣ ይጠጣል፣ ከወዳጆቹ ጋር ይጫወታል፣ እቤቱ ይገባል፣ ይተኛል፣ እንደገና ደግሞ ጠዋት ይነሳል፡፡ የሚቀጥለውም ቀን ያንኑ ይደጋግመዋል፡፡ ከቁጥር በላይ ጓደኞች አሉት፡፡ ሰውየው ይህ የኑሮ ዑደት ሰለቸውና ወደ ግራ መጋባት መጣ። የስሜት ቀውሱ ሲበዛበት አንድ ቀን፣ “ራሴን አጠፋለሁ” ብሎ ተነሳ፡፡ ራሱን በምን መልክ ሊያጠፋ እንደሚችል ሲያስብ በአካባቢው ያለ አንድ ትልቅ ድልድይ እንዳለ ትዝ አለው፡፡ ወደዚያ ድልድይ ሄዶ ራሱን በመጣል ራሱን ሊያጠፋ መንገድ ጀመረ፡፡ የሚያስፈራ ከፍታ ባለው በዚያ ድልድይ ጫፍ ላይ ቆሞ ራሱን ሊጥል ሲዘጋጅ በድንገት አንድ ድምጽ ሃሳቡን ሰረቀው፡፡ የሚያሳዝን የሕጻን ልጅ ድምጽ ነው፡፡ ዘወር ብሎ ሲመለከት አንድ ህጻን ተመለከተ፡፡ ይህ ሕጻን እርቦት በጣም ከስቷል፡፡ እዚያ ድልድይ ጋር ማን ትቶት እንደሄደ አይታወቅም፡፡ ይህ ራሱን ሊያጠፋ የነበረ ሰው ይህንን ሕጻን ጠጋ ብሎ ሲያየው ከረሃብ የተነሳ መገርጣቱን ተመለከተና በጣም አዘነለት፡፡ በልቡም እንዲህ ሲል አሰበ፣ “ይህንን የከሳ ሕጻን አንድ ቀን እንኳን አብልቸው ልሙት”። ስለዚህም፣ ራሱን የማጥፋት ቀጠሮውን ለበኋላ አስተላለፈው፡፡ ሕጻኑን አቅፎ አነሳውና ወስዶ ካጠበው፣ በደንብ ካበላውና ካጠጣው በኋላ ራሱን ወደማጥፋት እቅዱ ለመመለስ መንገድ ቀጠለ፡፡ በመንገድ ላይ ሲሄድ ግን የዚህ ሕጻን ሁኔታ ከአይኑ አልለይ አለው፡። ደግሞ እንዲህ ሲል አሰበ፣ “እኔ ከሞትኩ በኋላ ይህንን ህጻን ማን ሊያበላው ነው? ገና በአንድ ቀን ምግብ ፊቱ መለስ ብሏል”፡፡ ይህንን ካሰበ በኋላ ስላላስቻለው ህጻኑን ትቶ ወደ መጣበት አካባቢ በመመለስ እንደገና ሊያበላው ወሰደው፡፡ ሌላ ቀን ጨመረለት። እንደገናም ሌላ ቀን አበላው፡፡ እንዲህ እያለ ለጥቂት ቀናት ካበላው በኋላ ልጁን ሲያየው ነፍሱ ተመልሳለች፡፡ አሁን ይሄ ባለጠጋ ተመልሶ ራሱን ስለማጥፋት ማሰብ ሲጀምር የዚህ ልጅ የወደፊት ሕይወት ይታየው ጀመረ፡፡ ይህ ልጅ አድጎ ጥሩ ደረጃ ላይ ሲደርስ ለማየት መናፈቅ ጀመረ፡፡ ለመኖር ጓጓ፤ የሚኖርለት ትርጉም አግኝቷልና፡፡ ከዚያም በኋላ ዳግም ራስን ስለማጥፋት አስቦም አያውቅ፡፡ ሰው የሚከስረው ንግድ አልሳካ ሲለው አይደለም፣ ራእይ ሲያጣ ነው … ሰው ብቸኝነት የሚሰማ ብቻውን ሲሆን አይደለም፣ ራእይ ሲያጣ ነው። ሰው ዝቅተኝነት የሚሰማው ከሌሎች ስላነሰ አይደለም፣ ራእይ ሲያጣ ነው። ሰው ወዲ ወዲያ የሚንከራተተው መንገዱ ሲጠፋው አይደለም፣ ራእይ ሲያጣ ነው … ሰው በማይመለሱ ጥያቄዎች የሚሞላው መልስ ሲያጣ አይደለም፣ ራእይ ሲያጣ ነው … ሰው ስራ የሚያጣው ስራ ሲጠፋ አይደለም፣ ራእይ ሲያጣ ነው … ዶ.ር እዮብ ማሞ አዎ! እሱ ጋ ያመኛል ! ማጋራት መተሳሰብ ነው! https://t.me/Amharic_Books_storee

"The Story of My Experiments with Truth"—በዓለማችን ላይ ካሉ እጅግ ተደናቂ የሕይወት ታሪኮች አንዱ ነው። ማህተማ ጋንዲ (Mahatma Gandhi) በዚህ ግለ ታሪኩ ውስጥ የነበረውን የሐቀኝነት ደረጃና የሰላማዊ ትግል (Non-violence) ፍልስፍናውን ቁልጭ አድርጎ ያሳየበት ድንቅ ስራ ነው። ይህ መጽሐፍ የአንድን መሪ ታሪክ ብቻ ሳይሆን፣ አንድ ግለሰብ በራሱ ላይ በሚያደርገው Self-transformation (ራስን የማሳደግ ሂደት) ዓለምን እንዴት መለወጥ እንደሚችል የሚያሳይ መመሪያ ነው። እሄን መጽሐፍ አንብበህ ስትጨርስ የሚሰማህ ስሜት Albert Einstein እንዳለው እንዲህ ያለ ሰው በዚህች ምድር ላይ በሥጋ ተመላልሷል ብለን ለሚቀጥለው ትውልድ መናገርም ሆነ ማሳመን እንዴት ይቻለናል የሚለው ስሜት ይሆናል። የአሜሪካው የሲቪል መብቶች ታጋይ ማርቲን ሉተር ኪንግ፣ የጋንዲን የሰላማዊ ትግል ስልት ለራሱ ትግል እንደ መመሪያ (Manual) ተጠቅሞ አለምን ያነቃነቀ ትግል አድርጎበታል።"Christ gave us the goals and Mahatma Gandhi the method." (ክርስቶስ ግቡን ሰጠን፣ ጋንዲ ደግሞ ግቡ ላይ የምንደርስበትን መንገድ አሳየን በማለት ስለጋንዲ ሰላማዊ ትግል መስክሯል። የጋንዲን መንገድ የሚከተለው ሉተር ብቻም አልነበረም እንደነ ኔለሰን ማንዴላ ያሉ ለደቡብ አፍሪካ ነጻነት ሲታገሉ የነበሩ ታጋዮች የጋንዲ ትምህርቶች ትልቅ ስንቅ እንደሆናቸው ደጋግመው ምስክር ሲሰጡ ነበር። ይህ መጽሐፍ ጋንዲን እንደ ፍጹም ሰው (Perfect human) ሳይሆን፣ እንደማንኛውም ሰው ስህተት የሚሠራ፣ የሚፈተን ነገር ግን በራሱ ላይ "ሙከራዎችን" (Experiments) እያደረገ ወደ እውነት የተጠጋ ሰው አድርጎ ያቀርበዋል እንጂ እንዲሁ መሬት ላይ በሌለ እውነት አይሰብክህም። መጽሐፉ ( Moral Courage ) ከጠመንጃ ይልቅ የሞራል የበላይነት እንዴት ዓለምን እንደሚቀይር ትልቅ ትምህርት ይሰጥሃልና ጊዜ ማጋራት መተሳሰብ ነው! https://t.me/Amharic_Books_storee

ዐገቱኒ! ከበቡኝ ከመወለዴ ተከበብኩ - በብዙ ጥያቄዎች። ከልጅነቱ መጠየቅን ደፍርኩ፤ መጠ'የቅን ግን ፈራሁ። ጥያቄዎቼ የውስጤ፣ የራሴ ይመስሉኝ ነበር።ግን ዙሪያውን ተከብቢያለሁ - በጥያቄዎች። ከውጪም እንደከበቡኝ የገባኝ ዘግይቶ ነው - ገብቶኝ ከሆነ። ብዙ ጊዜ አንድ ነገር የገባኝ መስሎኝ ሳይገባኝ ቀርቷል። እንደውም አሁን አሁን የገባኝና የመሰለኝ ተቀላቅለው፥ አንድ ሆነዋል። ጥያቄዎች ግን የከበቡኝ ግን ለምንድን ነው? እንዳልኳችሁ፥ ጥያቄዎቹ ለምንድንስ ነው የውስጤ የመሰሉኝ? ገና ሲጀመር "የውስጤ" ማለት ምን ማለት ነው? የ'እኔ' ማለት ይሁን? እኔና ውስጤ አንድ አይደለንም? ነን? እኔንጃ አላውቅም! 'ውይ...... አላውቅም አልኩ?' ሳላስበው። ልጅ እያለሁ አላስብም ነበር፥ በመሆኑም አላውቅም ማለት አያሳፍረኝም ነበር። ካደኩኝ በኋላ ማሰብ ጀመርኩኝና አምታታሁት፥ ማሰብ መጀመርን ከማወቅ ጋር። አቤት.... አቤት! አወረድኩት ይኼን መቀበጣጠር፥ ግን እንዲህ ነኝ። እጠይቃለሁ፤ ምክንያቱም በጥያቄዎች ተከብቤ-አለሁ። 📓 ርዕስ፦ አለማወቅ ✍️ ደራሲ፦ ዳዊት ወንድምአገኝ(ዶ/ር) ማጋራት መተሳሰብ ነው! https://t.me/Amharic_Books_storee

ምርጥ አባባሎች "ሌሎችን ሰዎች ለመምሰል ራሱን የሚቀይር ሰው ብዙም ሳይቆይ ራሱን ሸራርፍ ይጨርሰዋል።" (Roymnod hull) "እራሳችሁን ታማኝ አድርጉ። የዛኔ በአለም ላይ ያሉ የቀጣፊዎች ቁጥር በአንድ እንደቀነሰ እርግጠኛ ትሆናላችሁ።" (thomas carlyn) "አንድ ሰው ለሰው ዘር ሊያበረክተው የሚችለው ትልቁ ስጦታ ሩሱን መቀየር ነው።" ( frank herbert) "ክረምቱ መጥቶ በበጋው ወራት ምን ስታደርግ ከረምክ ብሎ ሚጠይቅህ ጊዜ ይመጣል።" (henry clay) "ለራሳችን ያለንን ክብር አሳልፈን ካልሰጠናቸው በቀር ሰዎች ሊወስዱብን አይችሉም።" (Gandii) "አንድን ነገር ለታይቶ መስራት ሞኞች የፈለሰፉት የመክበር ሙከራ ነው።" (Bruce lee) ምንጭ፦ google ማጋራት መተሳሰብ ነው! Join https://t.me/Amharic_Books_storee