fa
Feedback
Amharic book store

Amharic book store

رفتن به کانال در Telegram

እዚህ Channel ላይ ያስተምራሉ ያዝናናሉ ብለን የምናስባቸውን መፅሀፎች ማግኘት ይችላሉ 🎯ተከታታይ ልቦለድ 🎯ግጥም 🎯ፍልስፍና 🎯ምክር የተለያዩ PDF መፅሐፍት ለማግኘት ይቀላቀሎ ቻናሉን ማጋራት አይዘንጋ 🙏 🙏 🙏

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
458
مشترکین
+424 ساعت
+217 روز
+20530 روز
تعداد پست‌ها

در حال بارگیری داده...

واکنش‌ها
نظرات
ستاره‌های تلگرام
بهترین پست‌ها بر اساس

در حال بارگیری داده...

تجزیه و تحلیل انتشار
پست ها
ديناميک بازديد ها
https://t.me/poethaymi
25000Loading...
Trump Strategies For Real Estate .pdf
1000Loading...
ማሳሰቢያ ይህ መጽሀፍ ከመጭበርበሩር ዠጄዎች ለመከላከል እንጂ ሰውን ለማጭበርበር አይደለም የተጻፈው ዳርክ ሳይኮሎጂ (Dark Psychology) ወይም ስውር ሥነ-ልቡና፣ ሰዎች ሌሎችን ለግል ጥቅማቸው ሲሉ ለመቆጣጠር፣ ለማታለልና ተፅዕኖ ለማሳደር የሚጠቀሙባቸውን ድብቅ እና ተንኮል አዘል ዘዴዎች የሚያጠና የሥነ-ልቡና ዘርፍ ነው። በዚህ ርዕስ ዙሪያ የሚጻፉ መጽሐፍት ዋና ዓላማ አንባቢዎች የማጭበርበር (Manipulation) ሰለባ እንዳይሆኑ ራሳቸውን እንዲከላከሉና የሰዎችን ድብቅ ማንነት እንዲረዱ ማገዝ ነው። የዳርክ ሳይኮሎጂ መጽሐፍትን ይዘትና ዋና ዋና ነጥቦች በጥንቃቄ የተነተነ ዳሰሳ ከዚህ በታች ቀርቧል። 1. የዳርክ ሳይኮሎጂ አራት ምሶሶዎች (The Dark Tetrad) መጽሐፍቱ የሰዎችን ክፉ ባህሪ ለመረዳት አራት ዋና ዋና የስብዕና ጉድለቶችን (Personality Traits) ያስረዳሉ፦ ናርሲሲዝም (Narcissism): ራስን ብቻ መውደድ፣ ከመጠን በላይ ታዋቂነትን መፈለግ እና ለሌሎች ስሜት ግድ አለመስጠት። ማኪያቬሊያኒዝም (Machiavellianism): የራስን ፍላጎት ለማሳካት ማንኛውንም ዓይነት ማታለል፣ ውሸት እና ስውር ዘዴ መጠቀም ህጋዊ ነው ብሎ ማመን። ሳይኮፓቲ (Psychopathy): ለሌሎች ሰዎች ምንም ዓይነት ርኅራኄ ወይም የጥፋተኝነት ስሜት አለማሳየት እና ጨካኝ መሆን። ሳዲዝም (Sadism): ሌሎች ሰዎች ሲጎዱና ሲሰቃዩ በማየት መደሰት። 2. መጽሐፍቱ የሚያጋልጧቸው ዋና ዋና የማታለያ ታክቲኮች (Manipulation Techniques) በነዚህ መጽሐፍት ውስጥ ሰዎች ሌሎችን ለመቆጣጠር የሚጠቀሙባቸው ስውር ስልቶች በዝርዝር ይዳሰሳሉ፦ ጋዝላይቲንግ (Gaslighting): ተጎጂው ስለ ራሱ ማስታወስ ችሎታ፣ አስተዋይነት ወይም እውነታ ጥርጣሬ እንዲያድርበት በማድረግ አእምሮን የመቆጣጠር ዘዴ። የፍቅር ቦምብ መጣል (Love Bombing): መጀመሪያ ላይ ከመጠን በላይ ፍቅር፣ ስጦታ እና ትኩረት በመስጠት ሰውን ማጥመድ እና በኋላ ላይ ግንኙነቱን ለመቆጣጠር ያንን መከልከል። ጥፋተኝነትን ማጋባት (Guilt Tripping): አንድ ሰው ሁልጊዜ ስህተት እንደሰራ እንዲሰማው በማድረግ የሚፈልጉትን ነገር እንዲያደርግ ማስገደድ። የዝምታ ቅጣት (Silent Treatment): ከሰውየው ጋር መነጋገር በማቆም ከፍተኛ የጭንቀት ስሜት መፍጠር እና እጅ እንዲሰጥ ማድረግ። 3. የመጽሐፍቱ ጠቀሜታ (The Value) ራስን መከላከል፦ ስውር ጥቃቶችን እና የማታለያ ወጥመዶችን ቀድሞ በመንቃት ከአእምሮ ብዝበዛ መዳን። የሰዎችን ባህሪ ማንበብ፦ በቃላት ከሚነገረው በስተጀርባ ያሉትን እውነተኛ ፍላጎቶች እና የሰውነት ቋንቋዎችን መረዳት። ግልጽ ድንበር ማበጀት፦ በግንኙነቶች ውስጥ ተገቢ ያልሆኑ ተፅዕኖዎችን በመለየት "አይሆንም" የማለትን ጥበብ ማዳበር። 4. ሊወሰዱ የሚገቡ ጥንቃቄዎች (The Critical Caveat) የዳርክ ሳይኮሎጂ መጽሐፍትን ሲያነቡ ትልቁ አደጋ፣ እውቀቱን ሰዎችን ለመጉዳት ወይም ለመበቀል መጠቀም መጀመር ነው። ዋናው ግብ የመከላከያ ጋሻ መታጠቅ እንጂ ሌሎችን የሚያጠቃ "መሣሪያ" መያዝ መሆን የለበትም ። https://t.me/Amharic_Books_storee ማሳሰቢያ ይህ መጽሀፍ ከመጭበርበሩር ዠጄዎች ለመከላከል እንጂ ሰውን ለማጭበርበር አይደለም የተጻፈው 📚 ማጋራት አይዘንጋ !
120003Loading...
ድንጋዩ፣ ከግዙፍ አለት ወደ ብይ እያነሰ መጥቶ፣ ከዛም የተሰወረ ቢመስለውም፣ ነገር ግን፣ በሆነ የማይታይ ቅርፅ ማንነቱን ቀይሮ በህልውና መኖር መቀጠሉን ጠረጠረ። ከዚህ መነሻ ነው ወደ "Theory of the small" ትኩረቱን ያዞረው። 'በዐይን የማይታይን ነገር እምን ላይ ላንከባለው?'ብሎ አንድ የእውቀት ተራራ ፈጠረ። ተራራውም አሁን "Particle phys-ics" ተብሎ የሚጠራው መሆኑ ነው። ይህ የሌሊሳ ግርማ ትርጓሜ ሲሲፈስን ከጥንታዊው አፈታሪክ አውጥቶ ወደ ዘመናዊው የሳይንስ እና የፍልስፍና አድማስ ያሸጋገረበት መንገድ እጅግ ረቂቅ ነው። ሲሲፈስን ከጉልበት ሰራተኛነት ወደ "Theoretical Physicist" የቀየረበት ጥበብ አዝናንቶ ያስደምመኛል። ​ ​ድንጋዩ ሟምቶ ሲያልቅ ሲሲፈስ የደረሰበት መደምደሚያ "Theory of the Small" መሆኑ ደሞ ሌላ አጃኢብ ነው። ይህም ቁስ (Matter) አይጠፋም፣ ቅርፁን ይለውጣል እንጂ የሚለውን የሳይንስ ህግ ያስታውሰናል። ሲሲፈስ ግዙፍ ድንጋይ መግፋት አቁሞ የማይታይ "Particle" ላይ ትኩረቱን ማድረጉ፣ ከሥጋዊ ድካም ወደ አእምሯዊ ሽግግር ማድረጉ ቢሆንስ። ​በጥንቱ ታሪክ ተራራው የዙስ ቅጣት ነበር፤ በዚህኛው ትርጓሜ ግን ተራራው የእውቀት ተራራ ሆኗል እያለን ቢሆንስ? ሲሲፈስ አሁንም ይገፋል፣ ነገር ግን አሁን የሚገፋው ድንጋይ ሳይሆን ጥያቄዎችን ወይም ሀሳቦችን ነው። ◉በአሁኑ ዘመን የሰው ልጅ እንደ ጥንቱ ድንጋይ በመሸከም ብቻ ሳይሆን፣ የማይታዩ ረቂቅ ነገሮችን በመመርመር ላይ ተጠምዷል ነው ሌሊሳ እያለን ያለው። ሌሊሳ ሲሲፈስን ድንጋዩ ሟምቶ ካለቀ በኋላ ወደ "Theory of the Small" እና "Particle Physics" ትኩረቱን እንዳዞረ አድርጎ መሳሉ፣ የዘመናችንን ሳይንሳዊ ግስጋሴ አይወክልም ነው የምትሉት? የሌሊሳ ትርጓሜ ሲሲፈስን ከግሪክ ተራራ አውጥቶ በዘመናዊው የሳይንስ ላብራቶሪ ያስቀምጠዋል። የአሁኑ ዘመን የሰው ልጅ መከራን ወደ ልምድ፣ ችግርን ደግሞ ወደ ብቃት የመቀየር አቅሙን የሚያጎላ ነው። ስራው "ገድለ ሲሲፈስ" መባሉ ራሱ ይህንን በጽናት የመታገልና የመለወጥ ሂደትን የሚያንፀባርቅ ነው። © [ Mesoud ]
193003Loading...
ሕይወትህን በቁጥጥርህ ስር ማድረግን ጀምር! (“ጀምሮ መጨረስ” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ ማሞ መጽሐፍ የተወሰደ) “መጀመር አቁምና መጨረስ ጀምር” – Unkwon Source የጥንቱ ፈላስፋ አሪስቶትል እንዲህ ሲል ጽፏል፡- “የሰው ዘሮች ውጤትና ዓላማ-ተኮር ፍጥረቶች (teleological organisms) ናቸው፡፡ ይህም በቀላሉ ሲተረጎም የሰው ልጆች ዓላማ-መር ፍጥረቶች ነን እንደ ማለት ነው፡፡ ይህም ማለት በሕይወትህ ደስተኛነት የሚሰማህና ሕይወትህን በቁጥጥርህ ስር እንዳዋልክ የሚሰማህ በየቀኑ ወደፊት እንድትራመድ የሚያደርግህ ግልጽ የሆነ ግብ ሲኖርህ ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የእድሜ-ልክ ግብ አውጪና ያወጡትን ግብ ተከታይነት በሕይወትህ ልታዳብራቸው ከምትችላቸው ዲሲፕሊኖች መካከል እጅግ ወሳኙና አስፈላጊው ነው” (Trace, Page 86)፡፡ በሕይወታቸው አንድን ዓላማ ይዘውና ከዚያ ዓላማ አንጻር ግብን አውጥተው ሁለንተናቸውን በመሰብሰብ ከዚያ ዓላማ ጀርባ የሚሰለፉ ሰዎች የሚኖራቸው የመኖር ጉጉት፣ የደስተኛነት ስሜትና በራስ መተማመን ይህ ነው አይባልም፡፡ ይህንን ፈጣሪ በሰው ልጆች ውስጥ ገጥሞና አስተካክሎ ያስቀመጠውን በግብና በዓላማ የመርካት ሕግ የሚለማመዱ ሰዎች ግን ቁጥራቸው እጅግ አናሳ ነው፡፡ ይህንን ለማወቅ ከፈለግን በሕይወታቸው ምን ማድረግ እንደሚገባቸው ባለማወቅ ግራ የመጋባት ስቃይ ውስጥ የሚገኙ ሰዎች ቁጥር የመበራከቱን ሁኔታ ማጤን በቂ ነው፡፡ አንድ ሰው የሕይወቱን ራእይ፣ ዓላማ ወይም ግብ በሚገባ ሲያውቅ ሕይወት ራሷ በሚያስገርም የትኩረትና የጉጉት ቅብብሎሽ ውስጥ ታሳልፈዋለች፡፡ በቅድሚያ በውስጡ ያለውን ዓላማ መቼ እንደሚጀምረው በመጓጓት ይነሳሳል፡፡ ወደ ዓላማው የሚወስደውን ጎዳና አንድ ብሎ ከጀመረ በኋላ ደግሞ የጀመረው ጉዞ በየጊዜው የሚወልደው አዳዲስ ነገር የጓጓዋል፡፡ ከዚህም የተነሳ ቀጣይነቱን ለማረጋገጥ የሚኖረው የውስጥ ተነሳሺነት ለየቀን ኑሮው ትርጉምና መጓጓትን ይሰጠዋል፡፡ ይህንን የቀጣይነት ጉዞ እያጣጣመ ሳለ ደግሞ ዓላማውን አሳክቶ የማየትና የመጨረስ ፍላጎቱ ይቀበለዋል፡፡ እንዲህ እያለ ነው እንግዲህ አንድ ሰው ከዓላማ-ቢስነት የአሰልቺ ኑሮ አዙሪት ወደ ዓላማ-መር የደስተኛነት ኑሮ የሚሸጋገረው፡፡ በሉ እንግዲህ ወደ አዲሱ ዓመት ውስጥ ስገባ እለወጣለሁ ያልነው የለውጥ ጉዞ እንጅመር፣ አደርገዋለሁ ያልነውን ተግባር መተግበር እንጀምር፣ አቆመዋለሁ ያልነውን አጉል ልማድ የመቆምን እንቅስቃሴ እንጀምር . . . እነዚህን ነገሮች ደግሞ እንደጀመርን እንቀጥላቸው፣ እንቀጠልናቸው ደግሞ እንጨርሳቸው! ይህንን አዲስና አስገራሚ ዓመት ይህንን “ጀምሮ መጨረስ” የሚለውን መጽሐፍ በማንበብና ያንን ክህሎት በማዳር እንድትጀምሩት ላነሳሳችሁ፡፡ መልካም የአዲስ ዓመት ጅማሬ ይሁንላችሁ! https://t.me/Amharic_Books_storee
964301Loading...
Who is the first person to land on the moon
1000Loading...