Amharic book store
رفتن به کانال در Telegram
እዚህ Channel ላይ ያስተምራሉ ያዝናናሉ ብለን የምናስባቸውን መፅሀፎች ማግኘት ይችላሉ 🎯ተከታታይ ልቦለድ 🎯ግጥም 🎯ፍልስፍና 🎯ምክር የተለያዩ PDF መፅሐፍት ለማግኘት ይቀላቀሎ ቻናሉን ማጋራት አይዘንጋ 🙏 🙏 🙏
نمایش بیشترکشور مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
458
مشترکین
+424 ساعت
+217 روز
+20530 روز
آرشیو پست ها
ብዙ ወንዶች "ሃብታም ከሆንኩ ሴቶች ይወዱኛል" ብለው ያስባሉ። ለዚህም ቀን ከለሊት ይለፋሉ። አዎ፣ ገንዘብ ሴቶችን ያመጣል፣ ግን ፍቅርን አያመጣም።
በገንዘብህ የመጣች ሴት፣ የምትወደው አንተን ሳይሆን ገንዘብ የሚፈጥረውን ምቾት ነው። ልክ ገንዘቡ ሲጎድል፣ ወይም ካንተ የበለጠ ሃብታም ሲመጣ፣ፍላጎቷም አብሮ ይጠፋል ወይም ያድጋል። ገንዘብ መኖር አለበት፣ ግን ሴቷ አንተን እንድትፈልግህ የሚያደርገው የእራስህ ማንነት ፣ ጥንካሬ እና መሪነት ነው።
📕 ርዕስ: ወንዶች ከማርስ፣ ሴቶች ከቬነስ
✍️ ደራሲ: ጆን ግሬይ
https://t.me/Amharic_Books_storee
አንቺ ጨካኝና ክፉ መሬት ሆይ! ለምንድን ነው ውብ፣ ንጹሕና ቅን የሆኑትን ምርጥ ልጆቻችንን በፍጥነት ወደ ሆድሽ የምታስገቢያቸው? ለምንድን ነው ክፉ፣ ምቀኛ፣ ውሸታምና ጨካኝ የሆኑትን ሰዎች ግን በላይሽ ላይ በነፃነት እንዲመላለሱና ዓለምን እንዲያቆሽሹ የምትፈቅጂላቸው? ለምንድን ነው አበቦቻችንን አርግፈሽ፣ እሾሃማ ቁጥቋጦዎችን የምታለመልሚው? መሬት ግን ምንም ምላሽ አልሰጠችኝም፤ በዝምታዋ ብቻ ቀጠለች። ያኔ ነው የገባኝ፤ ዓለማችን ውበትንና ንጽሕናን መሸከም የማትችል የሥቃይ ቦታ መሆኗን። ምርጦቹ ልጆቻችን በፍጥነት የሚሞቱት፣ ነፍሳቸው ከዚህች ክፉ ምድር ጋር መኖር ስላልቻለችና ቀድማ እረፍትን ፍለጋ ወደ ሰማይ ስለሸሸች ነው። እኛ የቀረነው ግን በዚህች ክፉ ምድር ላይ እርስ በርሳችን እየተቆራቆስን እንድንኖር ተፈርዶብናል።"
📕 ርዕስ፦የተሰበሩ ክንፎች
✍🏻 ደራሲ፦ካህሊል ጂብራን
https://t.me/Amharic_Books_storee
የማንን ሃሳብ፣ በማን ጭንቅላት እያሰባችሁ ነው?
( ብዙ ጭንቅላቶች ቢኖሩም፣ ብዙ ሀሳቦች የሉም)
የሰው ልጅ አሳቢ ፍጡር ነው ቢባልም አብዛኛው ግን አይደለም፡፡ ብዙሃኑ ታስቦ ያለቀ አሳብ እራሱ ላይ ጭኖ የሚሄድ መንገደኛ ነው፡፡ ግቡ መሄዱ እንጂ መድረሱ አይደለም፡፡ “ለምን” የሚባል ጥያቄ ጠላቱ ነው፡፡ በሰዎች ምላስ ጣዕምን ይለካል እንጂ፣ የራሱ ምላስ(የጣዕም ልኬት) የለውም፡፡ ኬክ ጣፋጭ ነው! አዎ ነው!! እንትን ነውር ነው! አዎ ነውር ነው!! የእንትና መፅሐፍ አሪፍ ነው! አዎ በጣም ብዙ ሰው ይወደዋል አሪፍ ነው! እንዲህ ነው ብዙሀኑ-ገደል ማሚቱ!
የያዛችሁትን ሀሳብ ለምን ያዛችሁ ? ብዙሀን ስለተከተሉት? ብዙሃን ስለተከተሉት በቡዝሀን ሀሳብ ብቻ ትክክል ሆኖ የሚያውቅ ሀሳብ አለ፡፡ ትክክል በመሆኑ ብዙዎች የተከተሉት ሀሳብ ይኖር ይሆናል፣ ብዙሃን ስለተከተሉት እውነት የሆነ ሀሳብ ግን በፍፁም! የያዝከውን ሀሳብ ትጠይቃላችሁ? ለምን እንዲህ አመንኩ ብላችሁ ትጠይቃላችሁ ወይስ ለምን ከሚባል ጥያቄ እስከ አለም ጥግ ትሸሻላችሁ፡፡
ሃሳባችሁ ማን ሰራሽ ነው? ሃይማኖት ሰራሽ? ማህበረሰብ ሰራሽ? ቤተሰብ ሰራሽ? ነው ቅልቅል? ግርር ብሎ ማሰብ ትልልቅ ሰዎችን ፈጥሮ አያውቅም- ባለህበት እርገጥ እንጂ፣ ወደ ፊት! የለውም፡፡ ታላቅነት “ለምን” በምትል ጥያቄ ውስጥ ነው የሚወለደው፡፡ ነፃ መሆን፣ ወይም የብዙሃኑ ቡችላ መሆን የግለሰቡ ምርጫ ነው፡፡ እንደተመረጠልህ መኖር ወይስ እንደመረጥከው መጓዝ፡፡
ትልቁ ጥያቄ- የያዝከውን አቋም የመፈተሸ ድፍረት አለህ ወይ? ለሃይማኖትህ መልስ የምትሰጠው ከሰባኪያን ከለቀምከው ቃል ነው ወይስ የሀይማኖት መፃሕፍትህን መርምረህ ከደረስክበት? መፀሐፍቱን ስታነብስ አራት ነጥብ እያደረክ ነው የምታነበው ወይስ ጥያቄ ምልክት ታስቀምጣለህ በመሃል? ያለመጠየቅ ሙቀት ይሻልሀል፣ የመጠየቅ ገነት? ሳይጠየቁ የኖሩ አዲስ እውነት አፍጦ በመጣባቸው ጊዜ ያብዳሉ፡፡
“ ያልተመረመረ ህይወት ዋጋ ቢስ ነው” ይላል ጋሽ ሶቅራጥስ፡፡ የኛው ሌሊሳ ደግሞ፣ “ ሕይወትን ሂስ ማድረግ የማይችል ዘመን የፈጠራ መንፈስ አይኖረውም” ይላል በአፍሮ ጋዳ መፅሐፉ፡፡ ዘመን ብቻ ሳይሆን ሕይወቱን ሂስ የማያዳረግ ሰውም እንደዛው ነው፡፡ እርግጥ በመመርመር የሚመጡብህ ቅጣቶች አሉ፡፡ አንደኛው የለውጥ ስቃይ ነው፡፡ የቀደመ አስተሳሰብን መለወጥ ለብዙዎች ስቃይ ነው፡፡ አንዳንዱ እዚህ ድረስ መጥቼ እንዴት እመለሳለው ብሎ፣ በጀመረው የስህተት መንገድ መንጎድ ይመርጣል( አዲሱ መንገድ ትክክል እንደሆነ ቢያውቅም፣ የኖረበትን መንገድ መልቀቅ ሞቱ ነው)፣ ሌላኛው በስቃይም ቢሆን አዲሱን እውነት ይቀበላል፡፡
ታዋቂው የክርስቲያን ፈላስፋ የሆነው፣ “ቅዱስ ኦውግስቲን” የመጀመሪያ እምነቱ “Manicheism” የሚባል እና ከክርስትና ጋር ምንም እህል ውሃ የሚያባብል ግንኙነት የሌለው ነበር፡፡ ነገር ግን ይህን እምነቱን ትቶ ወደ ክርስትና ለመለወጥ፣ በብዙ ጭንከት እና ውዝግብ ውስጥ ካለፈ በኋላ በ387 ተጠምቆ ክርስቲያን ሆነ፡፡ ከዚያ በኋላ ደግሞ ክርስትናውን የማይለውጠው አቋሙ አደረገው፡፡ ምን አልባት ትንሽ እድሜ ቢሰጠው… በለመደው ውዝግብ እና ጭንቀት ውስጥ አልፎ ሌላ ሃይማኖት ውስጥ ልናገኘው እንችል ነበር፡፡ ይሄ ሰው ቀድሞ ያመነበትን( ያወቀውን ነገር ከመቀየር ምን ያህል እንደሚከብደው ማሳያ ሊሆነን ይችላል) እናንተ የየትኛው ዘመን ሃሳብ ባሪያዎች ናችሁ? ለየትኛው ሰው? ለየትኛው ድርጅት?….
መንግድህ እያሳየህ ያለው ከሌሎች ባትሪ የሚወጣው ብርሀን ነው ወይስ የራስህ ባትሪ አለህ? ስንት ሃይማኖት መርምረህ ያንተ ሃይማኖት ልክ መሆኑን አወክ? ስንት ማህበረሰብ አይተህ አንተ ያለህበት ማህበረሰብ አስተሳሰብ ልክ መሆኑን አመንክ? የስንት ህዝብ ባህል ፈትሸህ፣ የባህልህ ተገዢ ሆንክ? “ባህላችን” ስትል ምን ማለትህ ነው? ሙሉ ለሙሉ እንከን የማይወጣለት ባህል አለኝ ነው የምትል ወይስ ባህሉ “የአንተ ስለሆነ” ብቻ ልክ ነው? የትኛው ባህልስ ነው ልክ? ባህል እንደሚሻሻል እንደሚለወጥ ታምናለህ ወይስ ለአያቶችህ መንፈስ የመታመን እዳ በላይህ ላይ ጭነሃል?
የማን ሆናችኋል? ማን እየሾፈራችሁ፣ ማን እየዘወረን ነው? “ መሬት አየር ሰማይ” የሚለው አዲሱ የሌሊሳ መፅሐፍ ላይ፣ እንዲህ የሚል ገፀባህሪ አለ፤ “ እኔ ነኝ ሀገሬ” እንዲህ ሲል ይቀጥላል ይሄ ገፀባህሪ፤
“………. ሀገር ብቀይር አንጎሌ ማሰብ አያቆምም፣እግሬ መራመድ፣ ጨጓራዬ መፍጨት፣ ልቤ ማፍቀር፤…እኔ ከሌለሁ ሀገር የለም… አዎ! እኔ ነኝ ሀገሬ፡፡ ….”
እናም፣ አንተ ነህ አገርህ፣ አንቺ ነሽ አገርሽ! እራስን ያላከተተ መንገድ ሁሉ…. ፈረሱን ከልክሎ “ያውልህ ሜዳው ጋልብበት” የማለት ያህል ነው፡፡ ምንም ፈረስ በሌለበት፣ ፈረስ ካልጋለብኩ እንደማለት ነው፡፡
ጥያቄው የማንን ጭነት ተሸክማችኋል ነው፡፡ የራሳችሁን ሸክም ነው የሌላውን የተሸከማችሁት? …… ሸክማችሁ የከበደ እናንተ ሸክማችሁን ጣሉ….! የራሳችሁን ሸክም ብቻ ተሸከሙ፡፡ ማንነታችሁንና ዘመናችሁን በማይመጥን ሸክም ትከሻችሁን አታጉብጡ፡፡
“እኛ” ብላችሁ ከማውራታቹህ በፊት፣ “እኔ” ማለትን ልመዱ፡፡ ብዙ ያማሩ ጭንቅላቶችን፣ ብዙ ያማሩ ቡድኖች ውስጥ ገድለን ቀበርን እኮ- ያ አይበቃም?! ብዙ ሃሳብ ያላቸው ጥቂት ሰዎች እንጂ፣ ጥቂት ሃሳብ ያላቸው ብዙ ሰዎች ምን ይረቡናል? በእኛ ውስጥ የሚጨፈለቀው እኔ ለራሱም ለሌላውም የሚፈይደው የለውም፡፡ እንዲያ ማለት አብዝተህ እራስህን ውደድ አይደለም፣ የሌሎችን ህልውና ጨፍልቅ አይደለም! – የራህን ጫማ አድርግ ማለት ነው፡፡ ያባትህ ጫማ ያንተ አይደለም- ላንተም አይደለም! መንገድ ላይ ከርፈፍ ከርፈፍ እያልክ ከመሄድ ውጪ የሚያተርፍልህ የለም፡፡ አንቺም የእናትሽን ጫማ አውልቀሽ ጣዪ፡፡ ማን እንደሰራው ከማታውቂው፣ ከሚያወለካክፍሽ ጫማም እራስሽን ጠብቂ፡፡
በመጨረሻም፣ እራሳቸውን ችለው የሚያስቡ ጭንቅላቶች ያብዛልን እያልን ወደራሳችን እንሄድ ዘንድ
https://t.me/Amharic_Books_storee
ንታዊቷ ጃፓን አንድ ወጣት ነበር። ይህ ወጣት በጣም ብሩህ አዕምሮ ቢኖረውም አንድ ትልቅ ችግር ነበረበት። እጅግ በጣም ሰነፍና ነገሮችን ነገ 'አስራለሁ እያለ' ስራዎችን የሚያሳድር ነበር።
...
አባቱ አንድ ስራ ሲሰጡት "ነገ ጠዋት በጊዜ ተነስቼ እሰራዋለሁ" ይላል። ጠዋት ሲሆን ደግሞ "ከሰዓት በኋላ ብሰራው ይሻላል" ይላል። በዚህ ሁኔታ ቀኖቹ በከንቱ ያልፋሉ።
...
አንድ ቀን አባቱ ወጣቱን ወደ አንድ ትልቅ ኮረብታ ወሰዱት። ኮረብታው ላይ ሲደርሱ አባቱ ለወጣቱ አንድ ባዶ የሻይ ኩባያ ሰጡትና "ይህንን ኩባያ እስከ ምሽት ድረስ እጅህን ሳታወርደው ይዘህ ቁም" አሉት።
...
ወጣቱም "ይህማ ቀላል ነው፤ ኩባያው ባዶ ነው፣ ምንም አይከብድም" ብሎ አሰበ። የመጀመሪያው አንድ ሰዓት ቀላል ነበር። ነገር ግን ሁለት ሰዓት፣ ሦስት ሰዓት እያለ ሲሄድ ያ ባዶ ኩባያ እንደ ድንጋይ እየከበደው መጣ።
...
እጁ መንቀጥቀጥ ጀመረ፣ ትከሻውም በህመም ሊቀደድ ደረሰ። በመጨረሻም አባቱ መጥተው "እንዴት ነው? ኩባያው ከበደህ?" ብለው ጠየቁት።
...
ወጣቱም በስቃይ ሆኖ "አባቴ! ኩባያው ባዶ ቢሆንም፣ ረጅም ሰዓት ስለያዝኩት ሊገድለኝ ነው!" ሲል መለሰ።
..
አባቱም ኩባያውን ከእጁ ላይ አንስተው እንዲህ አሉት።
"ሰንፍናም ልክ እንደዚህ ኩባያ ናት። አንድን ስራ ዛሬውኑ ሰርተህ ብታሳርፈው ቀላል ነው። ነገር ግን 'ነገ እሰራዋለሁ' እያልክ በጭንቅላትህ ውስጥ ተሸክመኸው ስትዞር፣ ስራው ባይሰራም እንኳ ክብደቱና ጭንቀቱ በየቀኑ እየጨመረ ይሄዳል። ሰነፍ ሰው ከሚሰራው ሰው በላይ ይደክማል፤ ምክንያቱም የሚሰራው ሰው ስራውን አውርዶ ሲያርፍ፣ ሰነፉ ግን ያልተሰራውን ስራ በሃሳቡ ተሸክሞት ይውላል።"
...
ሰንፍና ማለት እረፍት ማለት አይደለም። ያልተሰራ ስራ በውስጣችን የሚፈጥረው ጭንቀትና ጸጸት፣ ከስራው ድካም በላይ አእምሮአችንን ያደክመዋል።
...
ዛሬ መደረግ ያለበት ነገር ዛሬውኑ መከናወን አለበት።
https://t.me/Amharic_Books_storee
ትችት ልክ ብልግና ቃላት እንደመናገር ሁሉ ልማድ ሊሆን የሚችል መጥፎ ድርጊት ነው፡፡ መጥፎ ነገር ከመናገር የዘለለ ትርጉም የለውም፡፡ ልማድ ሆኖብን ግን ብዙ ጊዜ ሳናስብ እናደርገዋለን፡፡
📕ርዕስ፦ቀላሉን ነገር አታካብደው
✍️ትርጉም:- ዶክትር ዮናስ ላቀው
https://t.me/Amharic_Books_storee
ሁለት ሰዎች ከእኛ ሱቁ ፊት ለፊት ተቀምጠው ያለማቋረጥ እየሳቁ ነበር። አንድ የሰፈራችን የመንግስት ባለስልጣን በአጠገባቸው ሲያልፍ ስለሚያውቃቸው በሳቃቸው ተገርሞ ለምን እንደሚስቁ ጠየቃቸው።
እነርሱም፦“ጌታዬ ለዚህች ሀገር ችግር መፍትሔ አለን።”
ባለስልጣኑ በጉጉትና በግርምት ጠየቃቸው፦“መፍትሔው ምን ይሆን?”
መለሱለት፦“ሕዝቡን በጠቅላላ ሰብስበን እንቀብራቸዋለን። ከሕዝቡ ጋር አንድ አህያ አብረን እንቀብራለን”
ባለስልጣኑ፦“አህያውን ለምንድነው ከእነሱ ጋር አብረን የምንቀብረው?”
ሁለቱም ሰዎች ከቅድሙ ይብስ ጮክ ብለው እየሳቁ አንደኛው ለሌኛው እንዲህ አለው፦“አየህ አልነገርኩህም ነበር ማንም ስለሕዝቡ አይጠይቅም
https://t.me/Amharic_Books_storee
አሁን እጆቻችን ላይ የተደላደሉ የመሰሉን ፀጋዎች የእኛ አለመሆናቸው የሚገባን ጊዜ ይመጣል። ገንዘባችን..ስልጣናችን..ዝናችን በእኛ ላይ የሚሸጋገሩ የዓለም ንብረቶች ናቸው።ለቀጣይ ተረኛ እናስረክባቸዋለን።
📕ርዕስ፦ጥሪ ወደ ሞት
✍️ደራሲ፦አህመድ ሁስ(ሻድ)
https://t.me/Amharic_Books_storee
የሆነ ቦታ ላይ በጣም በፍጥነት የሚፈስ ግዙፍ ወንዝ አለ ብዬ አስባለሁ። በዚያ ወንዝ ውስጥ ሁለት ሰዎች አሉ። እርስ በእርሳቸው እንዳይወሰዱ አጥብቀው ተቃቅፈዋል፣ ነገር ግን የወንዙ ጉልበት በጣም ጠንካራ ስለሆነ መለያየታቸው ግድ ነው። በመጨረሻም እጃቸውን ለቅቀው በየራሳቸው አቅጣጫ በውሃው ይወሰዳሉ። የኛም ህይወት እንደዚሁ ነው። እስከመጨረሻው አብረን ለመቆየት ብንመኝም፣ ጊዜና እጣ ፈንታ እንደዚያ ወንዝ ነጥቀው ይወስዱናል። ማንም ሰውን ለዘላለም ይዞ ማቆየት አይችልም።"
📕 ርዕስ፦የተሰበሩ ክንፎች
✍🏻 ደራሲ፦ካህሊልጂብራን
https://t.me/Amharic_Books_storee
#የገንዘብ_ሳይኮሎጂ
The Psychology of Money በሚል ርእስ በሞርገን ሀውስል የተጻፈውና አለም አቀፍ ሽያጭ የተቀዳጀው መጽሐፍ
ከ ሀምሳ በላይ በሆኑ ቋንቋዎች የተተረጎመው ይህ መጽሐፍ በብዙ ታላላቅ ሰዎችና በታላላቅ ሚዲያዎች እንዲህ ተሞካሽቷል፡-
የገንዘብ ሳይኮሎጂ መጽሐፍ በሚያስደምሙ ሀሳቦችና በገሃዱ አለም ሊተገበሩ በሚችሉ አስተምህሮዎች የተሞላ ነው። ከገንዘብ ጋር የተሻለ መስተጋብር እንዲኖራቸው ለሚፈልጉ ሁሉ እጅግ መነበብ ያለበት ነው። ሁሉም ሰው ይህ መጽሐፍ ሊኖረው ይገባል!
#ጄምስ_ክሊር
(በሚሊዮን ኪፒ የተሸጠው #የአቶሚክ_ሀቢትስ መጽሐፍ ደራሲ)
ለሃያ አንደኛው ክፍለዘመን የሚያስፈልግ ምርጥ የገንዘብ ሳይኮሎጂ መጽሐፍ
#ብሉምበርግ
ተደጋግሞ የሚነበብ፣ በቢዝነስ አለምም ውስጥ እግራቸውን ማስገባት ለሚፈልጉ ሁሉ የሚሆን
#ዘ_ኮሌጅ_ኢንቨስተር
በዓመታት መካከል የተገኘ ምርጥ እና ኦርጅናል ሀሳብን የያዘ ፋይናንስ መጽሐፍ
#ዘ_ዎል_ስትሪት_ጆርናል
እውነተኛና የማይረሱ ታሪኮችን በውስጡ ይዟል፤ ይህም መጽሐፉን ያለመሰልቸት እንዲነበብ አድርጎታል።
#ፎርቹን
ለሁሉም ስኬቶች እና ውድቀቶች ምክንያት ምን እንደሆነ በሚገባ የሚያሳይ መጽሐፍ
#ፎር_ሚኒት_ቡክስ
ሞርገን ሀውስል ብሩህ አእምሮ ካላቸው የፋይናንስ ጸሐፊያን መካከል አንዱ ነው። በሁሉም እድሜ ላይ ላሉ ሰዎች የሚሆን መጽሐፍ፤ ገንዘብን የማግኘት ሃሳብ ካለህ ከዚህ ጀምር!
https://t.me/Amharic_Books_storee
በዓለም ዙሪያ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎችን ሕይወት የቀየረው "The Power of Now" መጽሐፍ ደራሲ ኤክሃርት ቶሌ በየወሩ ከዚህ መጽሐፍ ብቻ ስንት እንደሚያገኝ ታውቃላችሁ?
አንድ ደራሲ ከእያንዳንዱ መጽሐፍ ሽያጭ ከ7.5% እስከ 10% ያገኛል። በዚህ ስሌት መሠረት፣ ኤክሃርት ቶሌ ከዚህ መጽሐፍ ብቻ በየወሩ በአማካይ ከ$30,000 እስከ $50,000 ዶላር ወይም ከ3 ሚሊዮን ብር በላይ ቋሚ ገቢ ያገኛል።
ይሄ መጽሐፍ እስካሁን በ33 ቋንቋዎች ተተርጉሞ ከ16 ሚሊዮን ኮፒ በላይ ተሽጧል።ከታተመ 20 አመታት ቢያልፉትም እስካሁን ድረስ በየወሩ በአማካይ በአሥር ሺዎች የሚቆጠሩ ኮፒዎች በአማዞን እና በመጽሐፍ መደብሮች ይሸጣል።
የሚገርመው ኤክሃርት መጽሐፉ የሰጠውን ዝና ተጠቅሞ ሌሎች 3 ትልልቅ የገቢ ምንጮች ፈጥሯል።
1,"Eckhart Tolle Now" የተባለ የቪዲዮ መድረክ አለው። ተከታዮቹ የእሱን አዳዲስ ትምህርቶች ለማየት በወር 20 ዶላር ወይም በዓመት 180 ዶላር ይከፍላሉ። ይህ መድረክ ብቻ በየወሩ በመቶ ሺዎች የሚቆጠር ዶላር ያስገኝለታል።
2,የሚያዘጋጃቸው የኦላይን ኮርሶች ዋጋቸው ቀላል አይደለም። አንዳንድ ልዩ ስልጠናዎቹ እስከ $5,000 ዶላር ያወጣሉ።
3,በተለያዩ ትልልቅ መድረኮች ላይ ተጋብዞ ለጥቂት ሰዓታት ንግግር ለማድረግ ብቻ ከ$150,000 እስከ $299,000 ዶላር ክፍያ ይጠይቃል።
በአጠቃላይ እነዚህ ሁሉ የገቢ ምንጮች ተዳምረው የኤክሃርት ቶሌ ጠቅላላ የተጣራ ሀብት በአሁኑ ጊዜ ከ150 ሚሊዮን ዶላር በላይ ደርሷል።የኢትዮጵያ ደራሲዎችስ ስንት ያገኛሉ?
መጽሐፉ በአማርኛ "የአሁን ኃይልነት" ተብሎ ተተርጉሟል።እንዲለቀቅ ከ300 በላይ ሪያክት ያስፈልጋል👍
https://t.me/Amharic_Books_storee
አንድ ሰው ጠዋት 12፡30 ላይ በአላርም ተቀስቅሶ፣ ከአልጋው ዘሎ ወርዶ፣ ልብሱን ለብሶ፣ በግድ በልቶ፣ የትራፊክ መጨናነቅ ውስጥ አልፎ... በመጨረሻም ለሌላ ሰው ብዙ ገንዘብ ወደሚያስገኝበት ቦታ ሄዶ ቀኑን ሙሉ ሲደክም ይውላል። ከዚህም አልፎ ደግሞ ይህን በማድረጉ እና ይህን ስራ በማግኘቱ አመስጋኝ መሆን እንዳለበት ይጠየቃል። ታዲያ አንድ ሰው በዚህ ዑደት ውስጥ እያለ እንዴት ብሎ ነው ህይወትን ሊደሰትባት የሚችለው? ሁላችንም በገዛ ፈቃዳችን የገባንበት ዘመናዊ እስር ቤት ውስጥ ነን።
📕 ርዕስ፡- ፋክቶተም(ትርጉም)
✍🏽 ደራሲ፡- ቻርለስ ቡኮውስኪ
https://t.me/Amharic_Books_storee
እናንተ የሰው ልጆች ህግጋትን ማውጣት እጅግ ያስደስታችኋል፤ ነገር ግን ያወጣችሁትን ህግ ራሳችሁ መጣሱ ደግሞ የበለጠ ያስደስታችኋል። እናንተ ማለት በባህር ዳርቻ ላይ አሸዋ እየሰበሰቡ ግንብ እንደሚሰሩ፣ ከዚያም ያንኑ ግንብ በሳቅ እያፈረሱ እንደሚጫወቱ ሞኝ ህፃናት ናችሁ። ይህን የውሸት ስርአት እና ህግ ስትገነቡም ሆነ ስታፈርሱ፣ ያ ዘላለማዊው የህይወት ውቅያኖስ በሞኝነታችሁ ይስቃል። የሰው ልጅ የፈጠረው ማህበረሰብ፣ ፍትህ እና ስርአት... ሁሉም በውሸት ላይ የተገነቡና ነፋስ የሚያፈርሳቸው የአሸዋ ቤቶች ናቸው።"
📕 ርዕስ፡- ነቢዩ
✍🏽 ደራሲ፡- ካህሊል ጂብራን
https://t.me/Amharic_Books_storee
Eat That Frog!" በብራያን ትሬሲ የተጻፈ፣ በዓለም ዙሪያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን የሥራ ሕይወት የለወጠ መጽሐፍ ነው። መጽሐፉ 21 የሚሆኑ የጊዜ አጠቃቀምና የሥራ ቅልጥፍና ዘዴዎችን ይዟል።
"ጓጉላዋ" የምትለው በጣም ከባዱን፣ ልታደርገው የምትፈራውን ግን ደግሞ ትልቁን ውጤት የሚያመጣውን ሥራህን ነው።
. "ጓጉላዋን" ለይተህ እወቅ
ብዙ ጊዜ ሰዎች ቀኑን ሙሉ ቢለፉም ውጤታማ አይሆኑም። ምክንያቱም ትንንሽና ቀላል ሥራዎች ላይ ስለሚጠመዱ ነው። መጽሐፉ እንደሚለው፦
ሁለት ጓጉላዎችን መብላት ካለብህ (ሁለት ከባድ ሥራዎች ካሉህ)፣ ትልቁንና አስከፊውን ቀድመህ ብላ።
ጓጉላ መብላት ካለብህ ደግሞ ቁጭ ብለህ አትመልከተው (ሥራውን አትፍራው፣ ዝም ብለህ ጀምረው)።
🎴. የ "ABCDE" ዘዴ
ይህ ዘዴ ሥራዎችህን በደረጃ እንድትለይ ይረዳሃል፦
(በጣም አስፈላጊ)፦ ካላደረግከው ከባድ ጉዳት የሚያመጣ (ይህች "ጓጉላዋ" ናት)።
(አስፈላጊ)፦ ባታደርገው መጠነኛ ችግር የሚያመጣ
(ቢደረግ ጥሩ ነው)፦ ባታደርገውም ምንም ችግር የማይመጣ (ለምሳሌ ከጓደኛ ጋር ቡና መጠጣት)።
(አስወግድ)፦ ምንም ፋይዳ የሌላቸውን ሥራዎች ከዝርዝርህ ውስጥ ሰርዝ።
🎴. ቁርጥራጭ ማድረግ (Salami Slicing)
አንድ ሥራ በጣም ትልቅና የሚያስፈራ ሲሆን "ጓጉላውን" ሙሉውን ለመዋጥ ይከብዳል። መጽሐፉ የሚመክረው ሥራውን ወደ ትናንሽ ቁርጥራጮች እንድትከፋፍለው ነው። አንዲት ትንሽ ቁራጭ ስትጨርስ የሚሰማህ የድል ስሜት ወደ ቀጣዩ እንድትሄድ ይገፋፋሃል።
🎴የነገውን ሥራ ዛሬ ማታ ዘርዝር።
ከዝርዝሩ ውስጥ ትልቁንና ከባዱን ሥራ (ጓጉላውን) ለይ።
ጠዋት እንደተነሳህ ሌላ ምንም ነገር ሳትነካ (ስልክ ሳታይ) ያንን ሥራ ጀምረህ ጨርስ።
https://t.me/Amharic_Books_storee
Eat That Frog!" በብራያን ትሬሲ የተጻፈ፣ በዓለም ዙሪያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን የሥራ ሕይወት የለወጠ መጽሐፍ ነው። መጽሐፉ 21 የሚሆኑ የጊዜ አጠቃቀምና የሥራ ቅልጥፍና ዘዴዎችን ይዟል።
"ጓጉላዋ" የምትለው በጣም ከባዱን፣ ልታደርገው የምትፈራውን ግን ደግሞ ትልቁን ውጤት የሚያመጣውን ሥራህን ነው።
. "ጓጉላዋን" ለይተህ እወቅ
ብዙ ጊዜ ሰዎች ቀኑን ሙሉ ቢለፉም ውጤታማ አይሆኑም። ምክንያቱም ትንንሽና ቀላል ሥራዎች ላይ ስለሚጠመዱ ነው። መጽሐፉ እንደሚለው፦
ሁለት ጓጉላዎችን መብላት ካለብህ (ሁለት ከባድ ሥራዎች ካሉህ)፣ ትልቁንና አስከፊውን ቀድመህ ብላ።
ጓጉላ መብላት ካለብህ ደግሞ ቁጭ ብለህ አትመልከተው (ሥራውን አትፍራው፣ ዝም ብለህ ጀምረው)።
🎴. የ "ABCDE" ዘዴ
ይህ ዘዴ ሥራዎችህን በደረጃ እንድትለይ ይረዳሃል፦
(በጣም አስፈላጊ)፦ ካላደረግከው ከባድ ጉዳት የሚያመጣ (ይህች "ጓጉላዋ" ናት)።
(አስፈላጊ)፦ ባታደርገው መጠነኛ ችግር የሚያመጣ
(ቢደረግ ጥሩ ነው)፦ ባታደርገውም ምንም ችግር የማይመጣ (ለምሳሌ ከጓደኛ ጋር ቡና መጠጣት)።
(አስወግድ)፦ ምንም ፋይዳ የሌላቸውን ሥራዎች ከዝርዝርህ ውስጥ ሰርዝ።
🎴. ቁርጥራጭ ማድረግ (Salami Slicing)
አንድ ሥራ በጣም ትልቅና የሚያስፈራ ሲሆን "ጓጉላውን" ሙሉውን ለመዋጥ ይከብዳል። መጽሐፉ የሚመክረው ሥራውን ወደ ትናንሽ ቁርጥራጮች እንድትከፋፍለው ነው። አንዲት ትንሽ ቁራጭ ስትጨርስ የሚሰማህ የድል ስሜት ወደ ቀጣዩ እንድትሄድ ይገፋፋሃል።
🎴የነገውን ሥራ ዛሬ ማታ ዘርዝር።
ከዝርዝሩ ውስጥ ትልቁንና ከባዱን ሥራ (ጓጉላውን) ለይ።
ጠዋት እንደተነሳህ ሌላ ምንም ነገር ሳትነካ (ስልክ ሳታይ) ያንን ሥራ ጀምረህ ጨርስ።
https://t.me/Amharic_Books_storee
ውድቀትን ወደስኬት መቀየሪያ ስልቶች
✓ ‹‹ለድርጊትህ ያለፈውን ውድቀትህንና ያጣሃቸውን ነገሮች እንደመነሻነት ተጠቀምባቸው››
✓ ‹‹ውድቀት ማለት መጥፎ ስህተት የሠራ ሰው ነው፡፡ ነገር ግን ይህ የሚሆነው ውድቀትን ወደ ትምህርታዊ ልምድነት መመንዘር ሳትችል ስትቀር ነው››
✓ ‹‹ብልሃትን ከስኬት ይልቅ ከውድቀታችን ነው የምናገኘው››
✓ ‹‹ውድቀት እንደገና ለመጀመር ብቸኛው አማራጭ ነው፤ በዚህ ጊዜ ብቻ ነው ብልሀተኛ የምትሆነው››
✓ ‹‹ሁሉም የእኔ ስኬቶች የተገነቡት በእኔ ውድቀቶች ላይ ነበር››
✓ ‹‹ስኬት ማለት የአንተን ደስታ በማይነጥቅ መልኩ ከውድቀት ወደ ውድቀት የመጓዝ ችሎታ ነው፡፡ (ሰር ዋንስተን ቸርችል )
📙ቢዝነስ ስትራቴጂ
https://t.me/Amharic_Books_storee
#ፉክክራችን_ከራሳችን_ጋር_ይሁን!
"አምና ከነበርኩት እኔ ምን ጨምሬያለሁ?"
እዚህ ምድር ላይ ፈጣሪ ሲያመጣን እጅግ የተለያየ አድርጎ ነው። የጣት አሻራችን፣ የአይን አሻራችን አለም ላይ ያለን የቢሊዮናችንም ሰዎች የተለያየ ነው። የመንትዮች ሳይቀር የተለያየ ነው። ስለዚህ አበርክቷችንም የተለያየ ነው ማለት ነው። ይህ በሆነበት ሁኔታ ራስን ከሌላው ጋር ማነፃፀርና ህይወትን በዛ ቅርፅ መምራት ብዙ ሰው ላይ የሚስተዋል በሽታ ነው።
➢ራሱን ከሌላ ጋር የሚያነፃፅር ሰው ሁሌም ተሸናፊ ነው። ምክያቱም በዛ ሰው የተቀደመ ጊዜ የውስጥ ሰላሙን ያጣል ፤ የቀደመ ጊዜ ደግሞ መጨረሻው ያ መስሎት እንዲቆም እና ከዕድገት እንዲገታ ያደርገዋል። ከሌላ ጋር መወዳደር የጀመርን ጊዜ እዛው ላይ ተሸንፈናል!
ስለዚህ ወዳጆቼ ፉክክራችን ውስጣችን ካለው አቅም ጋር እና ከቀደመ ማንነታችን ጋር ይሁን። "አምና ከነበርኩት እኔ ምን ጨምሬያለሁ?" ብለን ራሳችንን እንጠይቅ።
https://t.me/Amharic_Books_storee
"ሁልጊዜ ከሰዎች የማነስ ስሜት የሚሰማህ ከሆነ የቅናት ማዕከላት የሆኑትን የማሀበራዊ ሚዲያዎች መጠቀም አቁም 🚫"
ATOMIC HABIT
https://t.me/Amharic_Books_storee
የመነመነ ማንነት
በአካል ከተለያችኋቸው ወራትና ዓመታት ካስቆጠራች በኋላ፣ እንደገና እንደማታገኟቸው እያወቃችሁ በሃሳባችሁና በስሜታችሁ ለመለየት ያልቻላችኋቸው ሰዎች ጉዳይ ሕይወታችሁን ያመነምነዋል፡፡
በቀን ውስጥ ሳታስቧቸው መዋል ካቃታችሁ . . . ስለ እነሱ ስታስቡ ስሜታችሁ የሚወርድባችሁ ከሆነ . . . ከእነሱ ውጪ ኑሮ የማይገፋ ከመሰላችሁ . . . የሌላ ሰውና ሁኔታ ነገር አልጥም ካላችሁ . . . ተስፋ ቢስነት ከተጫጫናችሁ . . . አስቡበት!
ለመነሻ የሚጠቅሟችሁ ሃሳቦች
• ከእነሱ ውጪ መኖር እንደምትችሉ ራሳችሁን አሳምኑ፡፡
• ራሳችሁን በጤናማ ልምምድና ዓላማችሁን በመከተል “Busy” አድርጉ፡፡
• እነሱን የምታስታውሱባቸውን ነገሮችና ሁኔታዎች ማየትን፣ መስማትን . . . ለመቀነስ ሞክሩ፡፡
• እነሱን ለመርሳት ስትሉ በሚገባ ካላሰባችሁበት ግንኙነትና ሁኔታ ራሳችሁን ጠብቁ፡፡
• ወደፊት እንድትራመዱ የሚደግፏችሁን ሰዎች ለይታችሁ እወቁና ከእነሱ ጋር አዘውትሩ፡፡
ራሳችሁን አትጣሉ! ስሜታችሁንና ሃሳባችሁን መለስ አድርጉ! ቀና በሉ!
ይህቺ ሕይወት የተሰኘት ሂደት ገና ብዙ ነገር እንደገና እንድትጀምሩ የማድረግ እውነታ ስላላት እንደገና መጀመርን ልመዱ!
https://t.me/Amharic_Books_storee
"አዎን።የራሳችን ዋነኛ ጠላት ራሳችን ነን።ስለራሳችን የማናውቀውን ማወቅ ያሰፈራናል።"
📓ርዕስ፦አለማወቅ
✍️ደራሲ፦ዳዊት ወንድምአገኝ
https://t.me/Amharic_Books_storee
ሴት በወንድ ሕይወት ውስጥ ሦስት መልክ አላት፦ እናት፣ እህትና ሚስት። እናት መጀመሪያው ናት፣ እህት መንገዱ ናት፣ ሚስት ደግሞ መድረሻው ናት። ሴት ማለት የሕይወት መዝሙር፣ የወንድ ልጅ የልብ ትርታና የነፍሱ መስታወት ናት።
📕 ርዕስ፦የጥበብ መንገድ
✍🏻 ደራሲ፦ካህሊል ጂብራን
https://t.me/Amharic_Books_storee
