Eotc Task Force
Ir al canal en Telegram
7 369
Suscriptores
+524 horas
+617 días
+35230 días
Archivo de publicaciones
7 371
ወድሜ ሰላም እንደምነህ ትናት 25/8/2018አርሲ ስሆን መረቲ ወረዳ አቦምሳ ከተማ ቀጤ ቀበሌ ለይ አንድ ንፅ ክርስትያን ሲገደል ሸሞ ቀበሌለይ ወደ አባጀማ ሲጓዝ የነበሩ በርካት ክርስቲያናች ታግተዋል አረባካችሁ ድምፅ ሁኑን
7 371
7 371
"ከአርሲ : ኦርቶዶክሳዊያንን : አጥፍተው : የቀሟቸውን ፡ የእርሻ : መሬቶች ፡ በስጦታ ፡ ተሰጡ !!
"በአርሲ : የኦርቶዶክሳዊያን : ላይ : የዘር : ማጥፋት : ጭፍጨፋ : በመፈፀም : ከኦርቶዶክሳዊያን : ላይ : የተቀሙ : መሬቶች : በስጦታ : ተሰጡ !!
" 100,000 ካሬ : ሜትር : የአርሲ : ዞን : አስተዳደር : አቶ : ኢብራሒም : ከድር : እና : የአሰላ : ከተማ : ከንቲባ : ለሐጂ ኢብራሒም ቱፋ : ለመስጅድ እና : ለእስላማዊ ዩኒቨርሲቲ : በተጨማሪም : ለሌሎች : ጉዳዮች : መስርያ ቦታ : እንዲሆን : ተብሎ : የለገሱ : ሲሆን : የዚህ : ቦታ : ስፋት : በአለም : አቀፍ : ምልከታ : ብንመለከተው ፦
" ወደ 14 የሚጠጉ : መደበኛ : ዓለም : አቀፍ : የእግር : ኳስ : ሜዳዎችን : (ስታዲየሞችን) : ጎን : ለጎን : መስራት : የሚያስችል : ግዙፍ : መሬት : ነው ።
" በአርሲ ዞን : ላይ : የሚደረገው : ተራማጅ : የኦርቶዶክሳውያን : ጥቃት : በመዋቅር : የሚታገዝ ጭፍጨፋ : እንጅ : የአንድ : ተራ : ሽፍታ : የዝርፊያ : ውጥን : እንዳልሆነ ፡ በገዛ ፡ ሀገራቸው : ለመኖር ፡ ስለፍትሕ ፡ የሚጠይቁ ፡ ኦርቶዶክሳዊያንን ፡ የመንግስት ፡ ተቃዋሚ ፡ አስመስሎ ፡ በመሳል ፡ ድምፃቸው ፡ እንዳይሰማ ፡ በማድረግ ፡ በተቃራኒው ፡ ደግሞ ፡ ከኦርቶዶክሳዊያን ፡ የተቀሙ ፡ መሬቶችን ፡ ለሌላ ፡ ሃይማኖት ፡ በችሮታ ፡ መስጠት ፡ በቂ ፡ ማሳያ ፡ ነው ።
"ከዚህም ፡ በላይ ፡ ከሚያሳውቁ ፡ ምልክቶች ፡ መሃከል ፡በአንድ ፡ ሣምንት ፡ ውስጥ ፡ 25 ፡ ኦርቶዶክሳውያን ፡ እንደ ፡ ከብት ፡ ታር*ው እየተገ*ሉ "ማንም ፡ አልሞተም ፡ ውሸት ፡ ነው" የሚል ፡ መረጃ ፡ መንግስታዊ ፡ መዋቅርን ፡ የሚመራው ፡ አካል ፡ የአርሲ ዞን አስተዳደር አቶ ኢብራሒም ፡ ከድር ፡ በድፍረት ፡ ሲሰጥ ፡ እና ፡ በጭፍጨፋው ፡ ለጨፍጫፊዎቹ ፡ ሽፋን ፡ በመስጠት ፡ ድምፁን ፡ አጥፍቶ ፡ የሰራውን ፡ የተቀናጀ ፡ የኦርቶዶክሳዊያንን ፡ የዘር ፡ ማጥፋት ፡ ስራ ፡ ውጤት ፡ የሆነውን ፡ ከኦርቶዶክሳዊያን ፡ ነፃ ፡ የተደረገ ፡ ግዙፍ ፡ መሬትን ፡ ለማስረከብ ፡ ሲገለጥ ፡ ስትመለከት ፡ ነገሩ ግልፅ ፡ ይሆንልሃል ይህም ጅሃድ ይባላል ።
7 371
አይ አርሲ
ከተማ የኑሮ ውድነት ሲያሳስበው መኖር ውድ የሆነባቸው የገጠር ክርስቲያኖች የመከራ ምድር
ሁሉም ቤት ሀዘን ገብቶ
ማን ለጎረቤቱ ያለቅሳል?
ማን ማንን ያጽናናል?
ሙሉ ቤተሰብ አልቆ ለቅሶ ማይደረስበት፤ትናንት የተገደሉትን ሲቀብር ውሎ ዛሬ የሚቀበር ያለባት።
ለገዳይ መብትን የሰጠ የገዳይ ምስለኔ
አስተዳደር፤መንፈሳዊ ስልጣን ይዞ ፍትሕን የማይጠይቅ አደራ በላ (ለውጭ አልጋ ፤ለቤት ቀጋ) መዋቅርን የገለጠች የስቃይ ስፍራ አርሲ !
———————————————————
ማነው ተረኛ ነገ ሚሸኘው
ወንድሙ ሲሞት ዝም ብሎ ያየው
ከተማ ገብቶ ምን ገዶኝ ያለው
አይደለም እሩቅ ለሱም ቅርብ ነው
ገ/ማርያም-ጅማ-ኢትዮጵያ
7 371
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
ኦርቶዶክሳውያን ሆይ፦
👉 አባቶቻችን አጥንታቸውን ከስክሰው ደማቸውን አፍስሰው ነፍሳቸውን ገብረው ባቆዩልን በገዛ ሀገራችን ላይ ሁሌ እየተገደልንና እየተሰደድን መኖሩ አይበቃም ወይ?
👉 እስከ መቼ በጎጥ፣በስፈር፣በ ክልል ፣በዘር፣በቋንቋ ተቧድነን ኅብረታችንን አጥተን ተራችንን እየጠበቅን በጠላቶቻችን ተጨፍጭፈን እንለቅ?
✍ እስከ መቼ የአደንዛዥ ሰባኪያንን ግራህን ለሚመታህ ቀኝህን አዙርለት ስብከት ፣ እየተወያየን ነው እየተነጋገርን ነው ወዘተ...የምንደኛ እረኞችን ዉሸት፣የመዝሙር ነጋዴዎች እየሞትን እንበዛለን ፣የሉም ሞተዋል ሲሉን ኖረን ወዘተ...የእንጀራ መብያ መዝሙር እየሰማን እየደነዘዝን የእርድ ቀናችን እየተጠባበቅን እንኖራለን?
👉 ይመራናል ያልነው ሥርዐት እስከመጩረሻው ላጥፋችሁ ብሎ ተነስቶ ስምንት ዓመት ሙሉ ሲገድለን ሲያፈናቅለን ዝም ብሎ ማየቱ ተባባሪ መሆን አይደለም ወይ?
👉 ይጠብቁናል ያልናቸው እረኞች ለገዳዮች ሽፋን እየሰጡ እያስፈጁን ነው።እና ከማን ነው መፍትሔ እየጠብቅን ያለነው?
👉ግፉ አልበዛም ወይ?
👉መቼ ነው ራሳችንን ለመታደግ በአንድነት የምንነሳው?
https://t.me/Eyo21e
7 371
ዛሬም የኦርቶዶክሳዊያን ሞትና መከራ እንደቀጠለ ነው
በዛሬው እለት ሚያዚያ 21/2018ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00ሰአት በአርሲ ሮቤ ወረዳ ሰዲቃ ቀርሳ ቀበሌ 1ሰው ገድለው 4ሰው አግተው ወስደዋቸዋል እባካችውን ድምጽ ሁኑን አሁንስ መከራችን በዛ ወዴት እንሂድ ተወልደን ያደግንበትን ሀገር ለቀን ወዴት እንሂድ ለማንስ እንጨው የታጠቁት ሃይል ከመንግስት አካላት ጋር አብርው በመሆን አንድ በአንድ እየጨረሱን ነው እባካችውን ግፍና መከራችንን ለዓለም አቀፍ መሐበረሰብ አሳውቁልን።
1. ባይሳ ጅማ በአሰቃቂ የተገደለ በዛሬው እለት
ታግተው የተወሰዱ:
1. መጎስ መኮንን
2.ደሴ ስዩም
3.አቢቾ እንግዳ
4.ገዙ ሀይሉ
