ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
Ir al canal en Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
Mostrar más2 904
Suscriptores
+10524 horas
+3357 días
+33630 días
Archivo de publicaciones
+7
የዓላማ ጽናትና የጀግንነት ተምሳሌቶች ፦ አርበኛ አማረ ታዘዘ አርበኛ ሰይድ ደምስ እንዲሁም አርበኛ ሃብታሙ እና ጓዶቿቸው በግዳጅ ቀጠና በሔዱበት ውብና ማራኪው የአማራ መሬት የተፈጥሮ ፀጋ ጋር!!
ጽናት፦ ለማንኛውም ፈተናና ማስፈራሪያ የማይበገሩ፣ ለህዝቡ ነፃነት ቅድሚያ የሰጡ የጽኑ አቋም ባለቤት የሆኑ። ታሪካዊቷ የሸዋ ምድር እንዲህ ያሉ ለዓላማቸው የታመኑ ጀግኖችን በማፍራት የጸናች ናት። በዚህም ፈጣሪ አርበኛቹን ይጠብቅልን!
የሸዋ መሬት ፍሬ፣ የጀግኖች ተካፋይ፣ አማረ ታዘዘ — የትግሉ ፊት አውራሪና መሪ! በዕውቀት የታነጸ፣ በስልት የበሰለ፣ሴራን አክሻፊ ነው፣ አቋሙ ያልላላ። የህዝብና ሰራዊት አስተሳሳሪ አምድ፣ በጽናት ይጓዛል በነፃነቱ መንገድ። የአማራ ህዝብ አለኝታና ጋሻ፣ ለህዝቡ መቆሙ ነው የዓላማው መድረሻ! ፈጣሪ ይጠብቅህ አርበኛው በርታ፣ አንተና ጓዶቹህ ናቸው የአማራ የህዝብ አለኝታ! ፈጣሪ ይጠብቃችሁ ወንድሞቼ #Dave #Amhara
+1
ሰበር የምሽት ዜና‼️
ባንዳ ተዋበ ጌትነት በቅፅል ስሙ የኔውበት
የአማራን ህዝብ በመክዳት ከአገዛዙ ተልዕኮ ተቀብሎ ከ64ኛ ክ/ጦር በማፈንገጥ የፋኖን ስም ለማጥፋት በዝረፊያ፣ በእገታ በመሳሰሉት ወንጀሎች ተሰማርቶ የነበረ ቢሆንም ባንዳው ከአንዴ ሁለቴ በሰራቸው ወንጀሎች ታስሮ በ64ኛ ክ/ጦር የእርምት እርምጃ እንዲወስድ ተደርጓል።
በመሆኑም ባንዳ ተዋበ መጀመርያ ከሰራቸው ወንጀሎች ባለመማር ከክ/ጦር በድጋሜ በማፈንገጥ በእነማይ ወረዳና ቢቸና ከተማ የሚገኙ ነዋሪዎች ላይ ከፍተኛ ዝርፊያና እገታ በመፈፀም ቢቸና ከተማ የሚገኘው የብልፅግና አገዛዝ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም እጅ የሰጠ ቢሆንም ነሀሴ 25/2018 ዓ.ም በቢቸና ከተማ 03 ቀበሌ ከምሽቱ 3:00 ሰዓት በመኗሪያ ቤቱ ላይ የአፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 201ኛ ኮር አይበገሬው 64ኛ ክ/ጦር አስርጎ በአስገባቸው እስከ ወዳኘው ተሸኝቷል።
ከፋኖ በመክዳት ወደ ዘር ፈጁ የብልፅግና አገዛዝ የገባ የትኛው ባንዳ ከፋኖ እንደማያመልጥ እናሳውቃለን።
አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!
ነሀሴ 25/2018 ዓ.ም
አፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት
የጉባኤ ማጠቃለያ እና የአቋም መግለጫ፡ "የልሂቃን ሚና በአማራ ህልውና"
August 29 እና 30, 2026 በዙም (Zoom) ሲካሄድ የቆየውና በአማራ ህዝብ የህልውና ትግል ላይ በጥልቀት የመከረው ታላቁ የውይይት ጉባኤ በስኬት ተጠናቋል።
የአማራ ህዝብ ዛሬ ላይ እጅግ ፈታኝ፣ ውስብስብ እና አደገኛ በሆነ የታሪክ ምዕራፍ ላይ ይገኛል። ህዝባችን በየአቅጣጫው የተከፈተበትን የህልውና አደጋ ለመመከት ወደር የለሽ ተጋድሎ እያደረገ ቢሆንም፤ መጠነ ሰፊ ማፈናቀል፣ ግድያ፣ የኢኮኖሚ ውድመት፣ እና ሁለንተናዊ የመዋቅር ማግለል የዕለት ተዕለት እውነታው ሆኗል። ይህ የተደራጀና ዘርፈ ብዙ ጥቃት ህዝባችንን በከፍተኛ የህልውና ስጋት ውስጥ የከተተው ሲሆን፣ የተቀናጀና አገር አቀፍ መፍትሄ ባለመገኘቱ ምክንያት ውድ የሆነ የሰው ህይወትና የንብረት ዋጋ እየከፈለ ይገኛል።
ከዚህ መሪርና አሳሳቢ ነባራዊ ሁኔታ አኳያ፣ እኛ የአማራ ምሁራን እና ልሂቃን ቆም ብለን ራሳችንን ስንገመግም፣ ለህዝባችን የሚመጥንና በታሪክም የሚጠበቅብንን ያህል የበኩላችንን የአመራርና የተግባር ሚና እንዳልተወጣን በግልጽ እናምናለን። በህዝባችን ላይ እየደረሰ ያለውን መከራ ለማስቀረትም ሆነ የህልውና ትግሉን በአስተማማኝ መሰረት ላይ ለማቆም፤ በዕውቀት፣ በስትራቴጂ፣ በዲፕሎማሲ፣ እና ህዝብን በማስተባበር ረገድ የነበረን ተሳትፎ ውስን፣ የተበታተነ እና ወቅቱ የሚጠይቀውን ልክ ያላሟላ እንደነበር ጉባኤው በጽኑ ገምግሟል።
ሆኖም ይህ ጉባኤ የታሪክ ማዕዘን መታጠፊያ ነው። ከእንግዲህ ወዲህ የአማራ ምሁራን ከዳር ቆሞ የመመልከትም ሆነ ተበታትኖ የመጓዝ ምዕራፍ በይፋ አብቅቷል። የህዝባችንን ህልውና ለማስጠበቅ፣ ትግሉን በዕውቀት ለመምራት፣ ጠንካራ አንድነት ለመፍጠር፣ እና ለችግሮቹ ሳይንሳዊና ተግባራዊ መፍትሄዎችን ለማምጣት ከመቼውም ጊዜ በላይ በቁርጠኝነት ተነስተናል። አቅማችንን፣ እውቀታችንን እና ጊዜያችንን አሟጦ በመጠቀም ከህዝባችን ጎን በጽናት ቆመን ኃላፊነታችንን ለመወጣት ቃል ገብተናል።
በዚህ የምስረታ ጉባኤና በቅድመ ጉባኤ በአጠቃላይ ለአንድ ወር የአማራ ልሂቃን ባደረግነው ጥልቅ ውይይት መሰረት ትግሉን ወደ ሚገባው የድል ምዕራፍ ለማሸጋገር ወስነናል፣ ይህንን ቁርጠኝነት ወደ ተግባር ለመቀየር አበይት ኃላፊነቶች የተከፋፈሉ ሲሆን በሚከተሉት ስትራቴጂካዊ ዘርፎች ዙሪያ ጠንካራ ስራዎች እንደሚሰሩ ተገልጿል፦
♦️የህዝባዊ ዲፕሎማሲና አለም አቀፍ ግንኙነት፡ ትግሉን ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ በግልጽ የማስረዳት ስራ።
የአለም አቀፍ ህግና የሰብአዊ መብት፡ በህዝባችን ላይ የሚደርሱ ግፎችን በህግ ማዕቀፍ የመከታተልና ፍትህ የመፈለግ ዘርፍ።
♦️የሽግግር ወቅት እቅድና የፍትህ ስርዓት፡ ለቀጣይ የፖለቲካና የፍትህ መዋቅር አስቀድሞ መዘጋጀት።
የታሪክ፣ ባህልና ማንነት ጥበቃ፡ የህዝባችንን እሴቶች የመንከባከብና የማስቀጠል ስራ።
♦️የኮሙኒኬሽን፣ ሚዲያና የትርክት ግንባታ፡ የተበታተኑ ድምጾችን በማሰባሰብ ጠንካራ ትርክት የመገንባት ዘርፍ።
የትብብር፣ ጥምረትና አጋርነት፡ ከሌሎች ሀይሎች ጋር የሚኖረውን ጤናማ ግንኙነት ማስተዳደር።
♦️የህልውና አቅም ግንባታና መረጃ ትንተና ዘርፍ፡ የህዝቡን የመቋቋም አቅም ማጎልበትና ትክክለኛ የመረጃ ፍሰትን ማረጋገጥ።
♦️የፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ፡ ዘላቂ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ፖሊሲዎችን መንደፍ።
♦️የቴክኖሎጂ እና የሳይበር ደህንነት፡ የመረጃ ደህንነትን መጠበቅና በቴክኖሎጂ መታገዝ።
♦️ የዓለም አቀፍ ህግና የሰብአዊ መብቶች ተሟጋችነት ዘርፍ
♦️ የኢኮኖሚ፣ ፋይናንስና የሃብት ማሰባሰብ ዘርፍ በሚል ተቋቁሟል።
"አስተዋይና ብሩህ ህዝብ የማይጠፋ ታሪክ አለው፤ የወደፊት ዕጣ ፈንታውንም እራሱ ይገነባል።" ይህን ታላቅ እውነት ሰንቀን ለጋራ ህልውናችን በአንድነት የምንቆምበት ወሳኝ ሰዓት አሁን ነው። የተጋረጡብንን የህልውና ስጋቶች በተቀናጀ መንገድ ለመመከትና ለህዝባችን የተሻለ ነገን ለመፍጠር፣ መላው ህዝባችን በነዚህ በተዋቀሩት ዘርፎች ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የድርሻውን አዎንታዊ አሻራ እንዲያሳርፍ በአክብሮት ጥሪያችንን እናቀርባለን።
እንተባበር! እንወያይ! እንገንባ!
የዓለም አቀፍ የአማራ ሊህቃን መማክርት ምስረታ ጉባኤ!
ነሐሴ 24 ቀን 2018 ዓ.ም
ከአፋብን ሊቀ መንበር አርበኛ ዘመነ ካሴ የተላለፈ የዕለቱ መልዕክት❗️🦅
ይድረስ ለመላው ኢትዮዺያዊያን።
ቀን ፦24/12/2018 ዓም ለአማራ ህልውና በድጋሜ የወጣ የስልጠና ጥሪ ማስታወቂያ
የአማራ ህዝብ እየደረሰበት ያለውን የህልውና አደጋ ለመቀልበስ የአማራ ፋኖ ወደ ትጥቅ ትግል ከገባ 37 ወራትን ያስቆጠረ መሆኑ ይታወቃል።
=======================
ስለሆነም በሶስት አመት በነበረን የትግል ቆይታችን የአብይ አህመድን መንግስት ፍርስርሱን በማውጣት ከነፍስ ወከፍ መሳሪያ እስከ ቡድን መሳሪያ እስከ አፍጫችን መታጠቃችመታጠቃችኔን የአደባባይ ሀቅ መሆኑ ወገን ቀርቶ ጥላት ይመሰክራል :: በመሆኑም ይህንን የፈራረሰ ስርዓት ግብዓተ መሬት በመፈፀም ህዝባዊ መንግስት በማቋቋም ሀገራችንን ኢትዮጵያን የቀደመ ክብሯን እና ገናነቷን አስጠብቆ ለማስቀጠል ከትግላችን ጎንለጎን ማሰልጠቅንና ማስቲጠቅ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ምክንያት የአፋብን፤ ቴዎድሮስ 2ኛዕዝ ፤206ኛ ኮር 14ኛ ክፍለ ጦር ፤ አዲስ ምልምል ሰልጣኞችን ተቀብሎ ለማሰልጠን ዝግጁቱን አጠናቆ እናንተን በመጠበቅ ላይ ይገኛል።
የመመልመያ መሰፈርት፦
👉 በአማራ ብሔርተኛነት የሚያምን 👉🏼የታደሰ የቀበሌ መታወቂያ ማቅረብ የሚችል:
👉 ዕድሜ ፦ ከ 18 ዓመት - 28 ዓመት
👉 የትምህርት ደረጃ ፦ ከ 5ኛ ክፍል በላይ
👉 ፆታ :- አይለይም
👉 ምንም አይነት የጤና ችግር የሌለበት ፤
👉 ምንም አይነት ወንጀል የሌለበት በማህበረሰቡ ዘንድ በስነምግባሩ የተመሰከረለት፤
👉 ከማንኛውም ደባል ሱስ ነፃ የሆነ
👉 ስልጠና ካጠናቀቀ በኋላ ለድርጅቱ ታማኝ የሚሆን በሚመደብበት የትኛውም ቦታ ተንቀሳቅሶ ግዳጅ ለመወጣት ዝግጁ የሆነ፤
👉 ከጠላት ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የሌለው : ይህ ማስታወቂያ
ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ መስከረም05/01/ 2019 ዓ.ም
ድረስ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት
ደብረ ማርቆስ ከተማ
አስተዳደር /ንጉስ ተክለሃይማኖት ) ጊዜያዊ መንግስት አሰተዳደር ጎዛምን ወረዳ ጎዛምን ህ/መንግስት አስተዳድር ዘወትር በስራ ስዓት በአካል በመቅረብ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን ##ለበለጠ መረጃ:-በ14ኛ ክ/ጦር በ24ኛ ክ/ጦርበ34ኛ ክ/ጦር እንዲሁም በ206ኛ ኮር የህዝብ ግንኙነት መምሪያ የማህበራዊ ሚዲያ ድህረገጾች በመከታተል በውስጥ መስመር መረጃወችን ማግኘት ትችላላችሁ:: #ማሳሰቢያ :- ያለን ቦታ ውስን ስለሆነ በፍጥነት በመመዝገብ ህልውናችሁን አረጋግጡ:: 👉🏼ከላይ የተዘረዘሩት መስፈርቶች ማሟላት የማይችል የማናስተናግደው መሆኑንን በድጋሜ እናሳስባለን!
አዲስ ትውልድ!
አዲስ አስተሳስብ!!
አዲስ ተስፋ!!!
👉ህልውናችንን በተባበረኸሾ ክንዳችን💪💪💪
የአፋብን:ቴዎድሮስ ዕዝ/206ኛ ኮር/የ14ኛ/ክፍለጦር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
የንድፈ-ሐሳብና የተግባር ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ 322 የምልምል ኮማንዶ አባላት በድምቀት ተመረቁ
▬▬▬▬▬▬▬❁✿❁▬▬▬▬▬▬
ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም
ለተከታታይ አራት ወራት ያህል ሲከታተሉት የቆዩትን ጠንካራ የኮማንዶ ሥልጠና በስኬት ያጠናቀቁ ምልምል ሠልጣኞች ዛሬ በተካሄደ ደማቅ ሥነ-ሥርዓት ተመረቁ።
በቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 102ኛ ኮር 33ኛ ክፍለ-ጦር አዘጋጅነት ሲሰጥ የቆየውንና "አንድነት ኮርስ" የተሰኘውን የኮማንዶ ሥልጠና በስኬት ያጠናቀቁት እነዚህ 322 አዳዲስ ተመራቂዎች፣ በቆይታቸው በሁለት ዋና ዋና ዘርፎች የተቃኙ ሥልጠናዎችን ወስደዋል።
#የንድፈ-ሐሳብ ሥልጠና፦ በውጊያ ስልት፣ በውጊያ መሪነት፣ በወታደራዊ ሳይንስ፣ በግብረ-ገብነት፣ በስነ-ልቦና ዝግጅትና በታማኝነት መርኆዎች ላይ ያተኮሩ ትምህርቶች፤
#የተግባር (Practical) ሥልጠና፦ የአካል ብቃት ማጎልበት፣ የነፍስ ወከፍና የቡድን መሣሪያዎች አጠቃቀም፣ ድንገተኛ አደጋዎችን የመቋቋም፣ የደፈጣና የፀረ-ደፈጣ ውጊያዎች እንዲሁም አስቸጋሪ የመሬት አቀማመጦችን የማሸነፍ ተግባራዊ ክህሎቶች።
በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ የተገኙ የዕዙ፣ የኮሩ እና የክፍለ-ጦሩ ከፍተኛ አመራሮች እንደገለጹት፤ የ"አንድነት ኮርስ" ተመራቂዎች በዐማራ የሕልውና ትግል ግቡን ያሳካ ዘንድ ከፍተኛ ድርሻ ይኖራቸዋል።
ሠልጣኞቹ በስልጠና ወቅት ያሳዩትን ከፍተኛ ጽናት፣ ዲሲፕሊንና የወንድማማችነት መንፈስ በግዳጅ ቀጠናዎች ላይም በተግባር ማሳየት እንዳለባቸው በቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ ወታደራዊ አዛዥ ሻለቃ የኔዓለም ዘለቀ ታዟል።
በዕለቱ በተካሄደው የምረቃ ፕሮግራም ላይ ተመራቂዎቹ በወታደራዊ የሰውነት ብቃት፣ በሰው ሠራሽና በተፈጥሮ እንቅፋቶች አሻግሮ የመዋጋት፣ እንዲሁም የጠበበ ውጊያ ማሳያዎችን ለታዳሚው አቅርበዋል።
በሥልጠና ቆይታቸው ከፍተኛ ለውጥ ላሳዩ ተመራቂዎች፣ ለአሠልጣኞች እና ለሥልጠናው መጠናቀቅ አስተዋጽኦ ለነበራቸው አካላት የገንዘብና የዕውቅና የምሥክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።
እነዚህ 322 አዳዲስ የኮማንዶ አባላት የተሰጣቸውን የሕዝብ ግዳጅ ለማከናወን ሙሉ ዝግጁነታቸውን በማረጋገጥ ወደተለያዩ የግዳጅ ቀጠናዎች ይሰማራሉ ሲል ክፍለ-ጦሩ አሳውቋል።
የዐፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ ወታደራዊ አዛዥ ሻለቃ የኔዓለም ዘለቀ፣ ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ ሥልጠና መምሪያ ሓላፊ ሻምበል ጌትነት ንጉሤ፣ የቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ ልዩ ዘመቻ ሓላፊ ፻ አለቃ ማርቆስ አሞኘ፣ የቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ ትምህርት እና ሥልጠና ምክትል ሓላፊ አርበኛ ዘውዳለም አዱኛ፣ በየደረጃው የሚገኙ የኮር እና የክፍለ-ጦር አመራሮች፣ እንዲሁም የተመራቂ ኮማንዶ ቤተሰቦችና የትግሉ ደጋፊዎች የዚህ ታላቅ በዓል ተሳታፊዎች ነበሩ።
+1
አህያ ሲሰለጥን እንዲህ ነው AI በደንብ ችላችሁበታል ወደዳችሁ ጠላችሁም አማራ ያሸንፋል። አለቀ አፋብን ድርጅታችን!!
የብልፅግና አገዛዝ 101ኛ አየር ወለድ ኮማንዶ ክፍለ ጦር ክፉኛ መመታቱ ተገለፀ!!
ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም
የአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ አፄ አምደጽዮን ኮር አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር መርሐቤቴ ዓለም ከተማ መሽጎ የነበረው 101ኛ አየር ወለድ ኮማንዶ ክፍለ ጦር፣ ለኃይል ቅያሪ እንቅስቃሴ እያደረገ ባለበት ሰዓት በፋኖ የደፈጣ ጥቃት ከፉኛ መመታቱን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ኃላፊ አስታወቀ።
የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር፣ ጠላት ከዓለም ከተማ ተነስቶ ወደ ኮላሽ ቀበሌ የኃይል ቅያሬ ለማድረግ ሲንቀሳቀስ፣ የወገን ኃይል ልዩ ቦታው ከማጋስ መሳለሚያ እስከ አበርጅት ድረስ ደፈጣ በመያዝ፣ ጠላት አቅዶት የነበረውን የኃይል ቅያሬ እቅድ እዳያሳካ ሲደረግ የሰውና የንብረት ኪሳራ ማስተናገዱን ታውቋል።
ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት ጀምሮ የተከፈተው ጥቃት እስከ ቀኑ 07:00 ሰዓት ድረስ የዘለቀ ሲሆን፣ መጀመሪያ ከተደረገው የደፈጣ ጥቃት ወደ ተሟላ የግንባር ውጊያ በመቀየር፣ የጠላትን እቅድ ያከሸፈ፣ የንብረትና የኃይል ውድመት ያደረሰ ውጊያ መካሔዱን አክሎ ገልጿል።
በዚሕ ኦፕሬሽን በርካታ የጠላት ኃይል የተደመሰሰና የቆሰለ ሲሆን፣የተመታው ኃይል አሁንም ድረስ እዳልተነሳና ቁስለኛዎችን ብቻ ወደ ዓለም ከተማ እናት ሆስፒታል እያመላለሰ እንደሚገኝ ከስፍራው ባለን መረጃ አረጋግጫለሁ ብሏል። በደረሰበት ድንገተኛ ጥቃት የተደናገጠው የጠላት ኃይል፣ የዋርኝና የኮራ ተራሮችን በዶሽቃና በዙ-23 ከባድ መሣሪያዎች እየደበደበ እደሚገኝ ገልጿል።
"ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!"
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!"
የአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ 202ኛ ኮር ዞብል ጃኖ ክፍለ ጦር በጠላት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ አደረሰ።
ነሐሴ 25/ 2018 ዓ.ም
ነሐሴ 24/2018 ዓ.ም ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ላይ ጠላት ከአራት የተለያዩ አቅጣጫዎች፣ ማለትም ከቡሆና በጉንትር፣ ከጫንድባ በኳክ፣ ከጯሂት በሳንኪሳ እንዲሁም ከቆላድባ በባርካው በኩል የተቀናጀ ጥቃት ለመፈጸም እንቅስቃሴ አድርጎ ነበር። ሆኖም ግን የጠላትን እንቅስቃሴ አስቀድመው ሲከታተሉ የነበሩት የክፍለ ጦሩ የቃኝ ቡድኖችና ጀግኖች የሰጡት ፈጣን እና ብቁ ምላሽ የጠላትን እቅድ አክሽፎታል።
በተለይም በጫንድባ-ሽመልድባ ቀጠና ተንከል ምድር ላይ በተሰነዘረበት ድንገተኛና ከባድ ጥቃትና ምት ጠላት ከፍተኛ ስብራት አስተናግዶ፣ ሳይሳካለት ወደ መጣበት የመመለስ ግዴታ ውስጥ ወድቋል። ይህም የቃኝዎችን የላቀ የመረጃ የበላይነትና የክፍለ ጦሩን ዝግጁነት በግልጽ ያሳየ ውጊያ ነበር።
በተመሳሳይ በተንከል-ቀንወጣ ምድር የመሸገውን የጠላት ኃይል እስከ አይከል ጭልጋ ድረስ በማስጠጋት ከፍተኛ ምት ያረፈበት ሲሆን፣ በዚህ የተበሳጨው ዘረ ፈጅ ስርዓት በደንቢያና በጭልጋ የነበረው የጠላት ኃይል በአካባቢው ማህበረሰብ ላይ ጥቃት ሲፈጽምና ንብረት ዘርፎ ወደ መጣበት አቅጣጫ ተመልሷል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን በላይዘለቀ 3ኛ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
የጠላቶቻችንን የከፋፍለህ ግዛ ሴራ ያከሸፈ ታሪካዊ ህዝባዊ ውይይት በላይ አርማጭሆ ተካሄደ!
ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም
በላይ አርማጭሆ ወረዳ ጃኒከው ንዑስ ወረዳ በአፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ 305ኛ ጎቤ መልኬ ኮር አዘጋጅነት የቅማንት ማህበረሰብ የሃይማኖት አባቶችና የአካባቢው አባላት በተገኙበት ሰፊና ታሪካዊ የሕዝብ ውይይት ተካሄደ።
በመድረኩ አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ 305ኛ ኮር የቀጣና 1 ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ መምህር አበባው ወርቁ እና የ52ኛ ክፍለ ጦር ባብየው የሻለቃ ዋና አዛዥ አርበኛ ማሩ ኪዴ ሰፊ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን፤ የፋኖነትን ታሪካዊ ዳራ እና የትግል መነሻ ምክንያቶች ፣ የትግሉን ዋና ዋና አላማዎችና ግቦች፣የአማራና የቅማንት ህዝብ ማህበራዊ መስተጋብርን በተመለከተ ለተወያዬቹ በዝርዝር አስረድተዋል። የአማራ ፋኖ ትግል ዘር፣ ቀለም፣ ሃይማኖትና ጎጥ ሳይለይ ሁሉንም አቃፊ የሆነ፣ የሕዝቦችን እኩልነት የሚያረጋግጥና አገራዊ አንድነትን የሚያስከብር የነጻነት መንገድ እንጂ ሕዝብን ከሕዝብ የሚለይ እንዳልሆነ በአጽንኦት አስገንዝበዋል።
በተደጋጋሚ በጠላቶችና በፖለቲካ ቁማርተኞች ሲሰራበት የነበረው የማንነት ውጥረት፣ የከፋፍለህ ግዛ ሴራና በሁለቱ ማህበረሰቦች መካከል መጠራጣርን የመፍጠር እኩይ አጀንዳ እና ስሁት አካሄድ መሆኑን መረዳት አስፈላጊ ነው ተብሏል።
በመድረኩ ላይ የተሳተፉት አስተያየት ሰጭዎች የአማራና የቅማንት ሕዝብ በደም፣ በጋብቻና በሃይማኖት የተጋመደ አንድ ሕዝብ በመሆኑ ለፖለቲካ ትርፍ ሲሉ ክፍተት እና ስንጥቅ ለመፍጠር የሞከሩ አካላት ጥረት እንዳልተሳካ ገልጸዋል። ቀደም ሲል በሁለቱ ሕዝቦች መካከል እገታ፣ የከብት ዝርፊያ፣ የህዝብ መፈናቀልና የብጥብጥ ድራማ በመስራት ሕዝባዊ ዕረፍት ለመንሳት ሲሰሩ የነበሩ ሌቦችና የብልጽግና ስርዓት ተላላኪዎች፤ ፋኖ ወደ ቀጠናው መንቀሳቀስ ከጀመረበት ጀምሮ ይፈጠሩ የነበሩ የሰላም እጦት መመለሱን የመድኩ ተሳታፊዎች አረጋግጠዋል።
በመጨረሻም፣ ሁለቱ ወንድማማች ሕዝቦች የጋራ ጠላት እንዳላቸውና አጠቃላይ የከፋፍለህ ግዛው አጀንዳ የውጭና የውስጥ ጠላቶች ስልት መሆኑን በመገንዘብ፣ ለሴረኛው ስርዓት በር ሳይከፍቱ አጋጣሚዎችን ሁሉ በጋራ ለመመከት ሙሉ መግባባት ላይ ደርሰዋል።
የጃኒከው ንዑስ ወረዳ ሕዝብ እናትና አባትን፣ ወንድምና እህትን የሚለይ ምንም ዓይነት ተፈጥሯዊ ኡደት በሌለበት እና ማህበራዊ ውቅር ውስጥ የገቡ አካላትን አሳፍሮ መመለሱን በመግለጽ፤ ፋኖ ለቆመለት ፍትሃዊ ትግል ሙሉ ድጋፍ እንደሚሰጥ፣ በማንኛውም ጊዜና ሰዓት ከጎን እንደሚሆኑና ሰላማቸውን በጋራ ለመጠበቅ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል ሲል መረጃውን ያደረሰን የኮሩ ህዝብ ግንኙነት ነው።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን በላይዘለቀ 3ኛ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
በወለጋ አማራዎች ላይ መጠነ ሰፊ ጭፍጨፋ እያካሔደ ያለው የሸመልስ አብዲሳ ሸኔና የኦሮሚያ ገዳ ልዩ ኮማንዶ ጥምረት "በአንድ መድረክ ላይ ተቀምጠው" የሚያሳይ ተጨባጭ ፍቶግራፍ የአማራው ቄራ ከሆነችው ከወለጋ ሰማይ ስር!
25/12/2018 ዓ.ም
የአገዛዙ ጄኔራሎችና ኮሎኔሎች በዲማ ጊዮረጊስ ገዳም፣ በዲማና ደብረፅሞና ኗሪዎች ላይ ከፍተኛ ውድመትና ዝርፊያ ፈፅሞል!!
64ኛ ክ/ጦር ነሀሴ 24/018 ዓ.ም
አገዛዙ በም/ጎጃም ዞን እነማይ ወረዳ ዲማ ጊዮረጊስ ገዳም፣ በዲማ ከተማ እና ደብረፅሞና ቀበሌ ኗሪዎች ላይ ከፍተኛ የሆነ እንግልት፣ ድብደባ፣ዛቻ፣ ፆታዊ ጥቃት፣ ውድመት፣ ዝርፊያና ንፁሃንን በመረሸን በአለም ላይ ተፈፅመው የማይታወቁ አሰቃቂ ወንጀሎችን በዲማ ከተማ በመፈፀም ወደ መጣበት ቦታ ተመልሶ ሄዶል።
ለሰው ልጆች ዕርህራሄ የሌላቸው የብልፅግና አገዛዝ አስፈፃሚ አካላት ጄኔራል ሶፊያ በክሪንና ጄኔራል ብረሃኑ ጥላሁን እና ኮሎኔል ፀጋየ በም/ጎጃም እነማይ ወረዳ ታላቁ ዲማ ጊዮረጊስ ሜካናይዝድ፣ መድፍ፣ BM፣ ዙ23፣ ሞርተር፣ ዲሽቃና በረካታ የእግረኛ ሰራዊት በመያዝ ከጥዋቱ 1:30 እስከ ምሽቱ 12:00 ሰዓት በቅዱሳን ምድር እና በአርበኞች መፍለቂያ የሆነችው ዲማ ከተማ የሚገኙት የደጅ አዝማች በላይ ዘለቀ ልጆች ጋር ባካሄደው ውጊያ ከፍተኛ ኪሳራ በማስተናገዳቸው ምክንያት ይዘውት የገቡትን ወራሪ ሀይል ትዛዝ በመስጠት በታላቁ ዲማ ጊዮረጊስ ገዳም፣ በዲማና ደብረፅሞና ቀበሌ ኗሪዎች ላይ እንግልት፣ ውድመትና ዝሪፊያ እንዲፈፀም ትዛዝ በመስጠት የባንዳነት ስራቸውን ለህዝባቸው እንዲህ አሳይተዋል።
በዲማ ከተማ የገባው አገዛዙ ጥምር ጦር በታላቁ ዲማ ጊዮረጊስ ገዳም የሚገኙ አባቶችን በማሰር፣ በማንገላታት፣ ዛቻ በመፈፀም፣ በገዳማ የሚኖሩ መነኩሳት ውስጥ 6 የገዳሙ አባቶችና እናቶች ከፍተኛ ቁስለኛ አድርጓል። አገዛዙ በተኮሳቸው ከባድ መሳሪያዎች የገዳሙ መጠለያ ቤቶችና ዲማ ጊዮርጊስ ሙዚየም ከፍተኛ ጉዳት አስተናግዶል። በዲማ ከተማ እና ደብረፅሞና ቀበሌ የሚገኙ ኗሪዎች መኗሪያ ቤት ወድሞል፣ ቤት ውስጥ ይጠቀሙበት የነበረው የቤት ዕቃ ወድሟል። ቤት ውስጥ ይጠቀሙበት የነበረው እህል፣ ዱቄት፣ ሽሮ በረበሬና ሙሉ የቤት ዕቃ በማውደም እና በመዝርፍ በዲማ ከተማና ደብረፅሞ ቀበሌዎች የሚገኙ ኗሪዎች ላይ ከፍተኛ ወንጀሎችን ፈፅሞል።
በመጨረሻም በዲማ ከተማ ሰፍሮ የነበረው ከጎጃም የተለያዩ ቦታዎች የተሰባሰበው የሶስት ክ/ጦሮች ጥምር ጦር በአይበገሬዎቹ የ64ኛ ክ/ጦር ሰራዊት ቀለበት ውስጥ መግባታቸውን ሲያረጋግጡ ነሀሴ 21/2018 ዓ.ም ከሌሊቱ 7:00 ሰዓት ጨለማን ተገን አድርገው ወደ መጣበት ቦታ ተመልሶ ወጥቷል።
አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!
ነሀሴ 24/2018 ዓ.ም
አፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት
