es
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

Ir al canal en Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

Mostrar más
2 936
Suscriptores
-124 horas
+3307 días
+38330 días
Archivo de publicaciones
ብልሆች ህይወታቸውን እያተረፉ ነው በዛሬው እለት የፓራ ኮማንዶ አባላቱ እና ዲሽቃ ምድብተኛው ፋኖን ተቀላቅለዋል። ◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍ .......ሐምሌ 02/2018 ዓ.ም ከፈለገ ብርሀን ከደብረወርቅ ከሞጣ ፣ከግንደወይን እንዲሁም ከድጎፅዮን በመውጣት ከዚህ በሗላ ለስርአቱ መጠቀሚያ መሆን በቃን በማለት 201ኛ ኮር 74ኛ እና 54ኛ ክፍለ ጦርን ተቀላቅለዋል። 1.ገብሬ ሆነ........ፓሊስ ኮሪያ 2.ፈንታሁን ስማቸው.... ዲሽቃ ምድብተኛ 3.ክንድ ግዛ ...........ፓራ ኮማንዶ 4.እባብየ ድረስ..........ሚሊሻ 5.ወለላው ጌጤ.....ሚሊሻ 6.ገበያው አስቻለ ....ፓራኮማንዶ ጓድመሪ 7.አመት የቆየ..........ፓራኮማንዶ 8.ድንበሩ አበበ.........ሚሊሻ በክፍለ ጦር አመራሮች አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን ሁላቹህም ይኸን የተሻለ አጋጣሚ በመጠቀም ወደ ትክክለኛው ማንነታቹህ እንድትመለሱ ጥሪያችን እናስተላልፋለን። < ኑ መተኪያ የሌለው ህይወታቹህን አትገብሩ ራሳቹህን አትርፉ> የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

54ኛ ክ/ጦር የህዝብ ጥያቄወችን በመለየት የመሠረተ ልማት የመንገድ ስራዎች ጥገና እንደቀጠሉ ናቸዉ። ◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍ .....ሐምሌ 01/2018 ዓ.ም በአፋብን ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴወድሮስ 201ኛ ኮር 54ኛ ክ/ጦር ከአዉደ ዉጊያ ጎን ለጎን በቢቡኝ ወረዳ ኮረብታ ንዑስ ከተማ ወይም ከደብረ ማርቆስ ዋብር ኮረብታ ንዑስ ከተማ የሚወስደዉን መንገድ ጠጠር በመድፋት መንገዱን በማስጠገን የህዝብን መሰረተ ልማት ጥያቄ እየፈታ ይገኛል። አምባገነኑ የአብይ አህመድ ስርዓት ለአማራ ህዝብ እንደ መሰረተ ልማት ያቀረበለት በምድር ሞርተርና መድፍ በሰማይ ደግሞ ድሮን መሆኑ ይታወቃል። ነገር ግን የአማራ የቁርጥ ቀን ልጅ የሆነዉ ፋኖ በአማራ ህዝብ ላይ በይፋ የታወጀዉን ህገ_መንግስታዊ ፣ መዋቅራዊና መንግስታዊ የዘር ማጥፋት(genocide)፣የዘር ማፅዳት(Ethnic cleaning)፣ፊት ለፊት ከመመከትና ከመቀልበስ ባሻገር የአማራ ህዝብ ጥያቄዎች በተገቢዉ መንገድ የህዝብ መሰረተ ልማት ስራዎችን እየፈታና ስራ ላይ እያዋለ ሲሆን በቢቡኝ ወረዳ ከድጓ_ፅዮን ኮረብታ ንዑስ ከተማ ወይም ከደብረ ማርቆስ ዋብር ኮረብታ ንዑስ ከተማ የሚወስደዉን መንገድ በቢቡኝ ወረዳ ጊዚያዊ መንግስት አስተዳደርና አስፈፃሚ ኮሚቴዎች አስተባባሪነት ከአዉደ ዉጊያዉ ጎን ለጎን የመንገድ ጥገና ስራዎች ተሰርተዋል። የኮረብታና ዋብር አካባቢ ኗሪ ማህበረሰብ ለዘመናት ሲጠይቅ የነበረዉ የመንገድ ጥገና ስራ ማህበረሰባችን በሚፈልገዉ መልኩ መንቀሳቀስ እንዳልቻለና በዚህ ሰዓት በበጎ አድራጎት ስራ እንዲሰራላቸዉ ለቢቡኝ ወረዳ ጊዚያዊ መንግሰት ባቀረቡት የትብብር ጥያቄ መሰረት መመለስ ተችሏል። ይሁንና የአካባቢዊ ማህበረሰብ ትብብራችሁ ተጠናክሮ ይቀጥልልን በማለት ከዚህ በኋላ አንዳንድ የንግድ ስራዎችን ለመስራት የመኪና እንቅስቃሴ ገትቶባቸዉ እንደነበር ገልፀዉ የንግድ እቃዎችም ኮረብታ ከተማ ድረስ በቀጥታ እንደሚደርስና መንገዶች እንደተስተካከሉ እዉቅና ፍጠሩልን የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል። አዲስ ትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስተስፋ የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 54ኛ ክ\ጦር የቢቡኝ ወረዳ ጊዚያዊ መንግስት ሚዲያና ግንኙነት

#ሰበር ዜና❗️21 የሚሊሻ አባላት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደ ፅዮን ኮርን ተቀላቀሉ! ሃምሌ 01/2018ዓ.ም ህዝባቸውንና የነፃነት ታጋይ ፋኖ ልጆቻቸውን ያስቀደሙ የአገዛዙን የሴራ ፖለቲካ በሂደት ጠንቅቀው የተረዱ ፣ ከሰሞኑ በርካታ የሚሊሻ አባላትን ወደ መከላከያ ሰራዊት ለማካታት በአስገዳጅ ሁኔታ ወደ ማሰልጠኛ ተቋም መላክ መጀመሩን ተከትሎ ዛሬ ሃምሌ 01 ቀን 2018ዓ.ም ቁጥራቸው 21 የሚሆን የሚሊሻ አባላት የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የአፄ አምደ ፅዮን ኮር አካል የሆኑ ክፍለጦሮችን መቀላቀላቸውን ኮሩ በመረጃው አስታውቋል። በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሀቤቴ አውራጃ መነሻቸውን ከሚዳ ወረዳ መራኛ ከተማ ያደረጉ 17 የሚሊሻ አባላት የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦርን ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ሲቀላቀሉ፣ ከሞረትና ጅሩ ወረዳ እንዋሪ ከተማ የተነሱ 3 የሚሊሻ አባላት እንዲሁም ከእንሳሮ ወረዳ ለሚ ከተማ የወጣ አንድ የሚሊሻ አባል የራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦርን ከነ ሙሉ ትጥቃቸው መቀላቀላቸውን የአፄ አምደ ፅዮን ኮር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል በላከው የግንባር መረጃ ገልጿል። የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ከአገዛዙ ጋር እስካሁን ድረስ አብረው ለተሰለፉ የፀጥታ ሀይሎች ያቀረበውን ተደጋጋሚ ወንድማዊ ጥሪ ተከትሎ በርካታ የሚሊሻ፣ የአድማ ብተና እንዲሁም የፖሊስ አባላት የዕድሉ ተጠቃሚ መሆናቸውን እየገለፀ ዛሬም ዕዙ የምህረት እጆቹ የተዘረጉ መሆኑን ይገልፃል። "ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!" የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

በእብሴ ሳርምድር ወረዳ ሁለት ቀበሌወች ህዝባዊ ውይይቶች እንደቀጠሉ ናቸው፨ ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ....ሐምሌ 01/2018 ዓ.ም የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦር የእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ ጊዚያዊ መንግስት ከይጠፈት (021) ቀበሌ እና ቀንዳች (017) ቀበሌ ህዝብ ጋር ሰፊ ውይይት አድርገዋል። በውይይቱም ላይም የጊዚያዊ መንግስቱ አመራሮች የተገኙ ሲሆን የትግሉን አሁናዊ ቁመና እና የድርጅቱን አቅም በማስረዳት አሁን ላይ ከጠላት የተሻለ ቅቡልነትን በመፍጠር ቀጠናዊና አለማቀፋዊ ተቀባይነቱም በመጨመሩ በርካታ አጋር ሀይሎችንም በማፍራቱ በአጭር ጊዜ ድል ማድረግ እንደሚችል አብራርተዋል በማህበረሰቡም በኩልም በርካታ ሀሳቦች የተነሱ ሲሆን በአመራሮቹ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል። በቀበሌው መዋቅር አመራሮች ላይ ከአገልግሎት አሰጣጥ አኳያ የአገልግሎት አሰጣጥ እና የአሰራር አኳያ የታዩ ክፍቶችን በመለየት የማስተካከል ስራ በመስራት የቀጣይ የስራ አቅጣጫ መስጠት ተችሏል ። የአማራ ህዝብ የትግሉ ባለቤት በመሆኑ በየጊዜው በመገኘት የማህበረሰብ ችግሮችን እያወያዩ በመለየት አስቸኳይ መፍትሄዎችን የመስጠት ሂደቱንም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በአፅኖት ተናግረዋል። አፋብን ቴዎድሮስ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

ከሰኔ 01_ሰኔ 30/2018 ዓ.ም ከጠላት ወደ 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦር የተቀላቀሉ የአብይ አህመድ ሰራዊት አባላት ================================= ......ሰኔ30/2018 ዓ.ም ብልሆች የመሪያችን የምረት አወጅ በመጠቀም በዚህ ወር ከሰኔ 1___30/2018 ዓ.ም ከጠላት በመውጣት ወደ 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦርን የተቀላቀሉ የጠላት ኃይል ፦ 1.ይልቃል አባየሁ ...... ፓራኮማንዶ 2.ጥጋቡ የሺ .........ፓራ ኮማን 3.ሐብቴ ቁሜ............ፓራኮማንዶ 4.አበበ ጌታሁን..............ፖሊስ 5.ተመስገን ደመቀ......... ፖሊስ 6.አለማየሁ ጨመር...ፓራ ኮማንዶ 7.ደረጀው ተረፈ............ ሚሊሻ 8.ይርጋ ደርጀው.............ሚሊሻ 9.አበበ አንላይ......... ፓራኮማንዶ 10.አብርሐም አየልኝ .......ፖሊስ 11.የሽዋስ ታድሎ.......አድማብተና 12.አየነውመንግስት...አድማብተና 13.ምኒችል ገደፋው..........ሚሊሻ 14.ደግዋለ አይተነው........ሚሊሻ 15.ዘለቀ ጸሐይ........ አድማብተና 16.ሞላ ዋለ......... አድማብተና 17.በላቸው አባተ...... አድማብተና 18.ገበያው ሞላ........ፓራኮማንዶ. 19.ተስፋው አንሙት....ፓራኮማንዶ 20.እንድሪስ ሙሉጌታ..........ፖሊስ 21.ፈንታምትኩ..........ፓራኮማንዶ 22.ጓዴ ዘሪሁን.......... ፓራኮማንዶ 23.ይኸነው ተሜ........ፓራኮማንዶ 24.ዘውዱ አብየ..........መከላከያ 25.ብልሐቱ ካሳ......... ሚሊሻ ሲሆኑ ከመቸውም ጊዜ በላይ ድርጅታችን ያቀረበውን የምረት አዋጅ በመጠቀም ሁሉም አማራን እናደድን የሚል መልክት የተቀመጠ ሲሆን፦ <<<< ተያይዘን ትውልድ የማዳን ሀላፊነታችን እንወጣ ...>> የአፋብን ቴውድሮስ ዕዝ201ኛ ክር ህዝብ ግንኙነት

ዳግማዊ ቴዎድሮስ 5ኛ ኮር በሊቦ ከምከም ያደረገው አውደ ውጊያ‼️                      [ሐምሌ 01/2018ዓ.ም] 👉01. ሊቦ ከምከም/አምቦ ሜዳ             የአገዛዙ አራዊት ሰራዊት መነሻውን ከሊቦ ከምከሟ አዲስ ዘመን አድርጎ ወደ እብናት ከተማ ሲንቀሳቀስ የነበረው ሐገር አጥፊ የአቢይ አሕመድ የግል ታጣቂ ኃይል ''#አምቦ_ሜዳ'' ላይ ከጠዋቱ ጀምሮ በዳግማዊ ቴዎድሮስ 5ኛ ኮር ውጊያ ተተከፍቶበታል። የዳግማዊ ቴዎድሮስ 5ኛ ኮር አካል የሆኑት አፄ ኢያሱ ክፍለ ጦር፣ ታድሎ ብርሐን ክፍለ ጦር፣ አባ ማዕበል በለሳ ክፍለ ጦር እና ጥቁር አንበሳ ክፍለ ጦር በጋራ ጠላትን በመስበር ባለበት እንዲቆም እና ካሰበበት ግዳጅ ቀጠና እንዳይደርስ ማድረግ ተችሏል። በተባበረ የ5ኛ ኮር ክንድ የጠላት ኃይል እየተመታ ሲሆን አውደ ውጊያው አድማሱን አስፍቶ ከአምቦ ሜዳ ከተማ ወደ ሻሞና ወደ ሌሎች መዳረሻዎች ተስፋፍቷል።                         አማራነትን በክቡር መስዋዕትነቱ ለማረጋገጥ የሚደክመው የ5ኛ ኮር ሰራዊት ብርቱ ክንዱን በጠላቶቹ ላይ ማሳረፉን አጠናክሮ ይቀጥላል። 👉02.ሊቦ ከምከም/ጭብጪባ             የሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ሰራዊት ዓለም በር ከተማ ውጊያ ማድረጉን ተከትሎ አዲስ ዘመን የነበረው መከላከያ በጎን ለሆድ ዘመዱ እንዳይደርስ ለማድረግ ከአዲስ ዘመን በጭብጪባ በኩል የተንቀሳቀሰውን የጠላት ሰራዊት የዳግማዊ ቴዎድሮስ 5ኛ ኮር ሰራዊት አካል የሆኑት ጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር እና አፄ ኢያሱ ክፍለ ጦር በጋራ የጠላትን አከርካሪ በመስበር ወደመጣበት እንዲመለስ አድርገዋል።       በዚህ ውጊያም ጠላትን በተባበረ ክንድ መምታት የተቻለ ሲሆን ጠላት አንዱ ለአንዱ ደራሽ እንዳይሆን ተደርጓል። በጠላት ላይም ከፍተኛ የሆነ የአካል ኪሳራና የዕቅድ መዛባት እንዲደርስበት ተደርጓል። ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን❗ ©አፋብን ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ ዳግማዊ ቴዎድሮስ ፭ኛ ኮር! 01/11/2018 ዓ.ም

በተጉለት አውራጃ ደረፎ ክላስተር የገዥው ጥምር ጦር በንጹሃን ላይ ዘረፋ ሲፈፅም፡ አድማ ብተና ሀይሎች ፋኖን ተቀላቅለዋል!! 01/11/2018 ዓ.ም ከደብረ ብርሃን ተነስቶ ወደ አንኮበር ቀጠና ደረፎ ቀበሌ ያመራውና ራሱን "ጥምር ጦር" ብሎ የሚጠራው የመከላከያና አድማ ብተና ሰራዊት፣ የፋኖ ኃይላችን በሌሉበት የህዝብ ንብረት መዝረፉ ታወቀ። ሰራዊቱ ሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም በየቀበሌው በመግባት አርሶ አደሮች ለክረምት ዝግጅት ያከማቹትን 10 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ እንዲሁም አቶ ኪዳኔ ከተባለ አርሶ አደር ቤት በመግባት ሥስት(3) ጭነት ባቄላ ዘርፎ መውሰዱ ተረጋግጧል። በዚህ የዘረፋ ተግባር ላይ ለሆዳቸው ያደሩ የአካባቢው ሚሊሻዎችም የተሳተፉበት መሆናቸው ተረጋግጧል። ድርጊቱ እንደተሰማ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፣ መሐመድ ቢሆነኝ ኮር እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር በፍጥነት ወደ ስፍራው ቢያመራም፣ የገዥው አካል ጦር የዘረፈውን ንብረት ጭኖ ወደ ደብረ ብርሃን ለመፈርጠጥ ተገዷል። ይሕ በእንዲሕ እዳለ አገዛዙ በንፁሀን ላይ የሚፈፅመውን ግፍና ዘረፋ የሠሙት የአገዛዙ ደጀን የነበሩት አድማ ብተና ኃይሎች ፋኖን ተቀላቅለዋል። በዚሕም ሁለት የአድማ ብተና አባላት የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደጽዮን ኮር ራንቦ ክፍለ ጦርን ከነ ሙሉ ትጥቃቸው በቀን 01/11/2018 ዓ.ም ተቀላቅለዋል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

የአማራ ልጅ ​በለምለሟና በታሪካዊቷ ምድር ላይ፣ ፀሐይ ስትወጣና ስትጠልቅ የምታያቸው ድንቆች ብዙ ናቸው። ነገር ግን ከሁሉም በላይ የሚያስደንቀውና ምቀኞችን በእንቅልፍ ማጣት የሚቀጣው የአንድ ማህበረሰብ ልጅ ማንነትና ተፈጥሮአዊ ጥበብ ነው። እርሱ በሄደበት ሁሉ ቅርጹን፣ እውቀቱንና ኃይሉን እንደየአስፈላጊነቱ የሚቀያይር የጥበብ አልማዝ ነው። ​በማንኛውም አቅጣጫ ብታየው፣ በአንድ አካል ውስጥ ሺህ ህይወትና ሺህ እውቀትን አዝሎ ታገኘዋለህ። ​1. ከታች ዝቅ ስትል፦ አራሽ፣ ቀዳሽ፣ ተኳሽ ​ወደ ምድር ዝቅ ብለህ፣ አፈሩንና እርሻውን ስትመለከት እዚያው ታገኘዋለህ። ​አራሽ ነው፦ በእጆቹ ላይ ያሉት ፎረፎሮችና ጠባሳዎች የምድርን ልብ ሰንጥቀው ሀገርን የመቀለብ ተጋድሎዎቹ ምስክሮች ናቸው። ላቡን ወደ ምድር እያፈሰሰ፣ ኩሩነቱን ሳያጣ ጎንበስ ብሎ ያርሳል። ​ቀዳሽ ነው፦ እሁድ ማለዳ በቤተክርስቲያን አውደ ምህረት ላይ ነጭ ማዕተቡን አስሮ፣ በእርጋታና በቅድስና ቆሞ ፈጣሪውን ሲያመሰግንና ህዝቡን ሲባርክ ታየዋለህ። ​ተኳሽ ነው፦ ያው ያረሰውና የቀደሰው እጅ፣ የሀገርና የወገን ክብር ስትደፈር ግን ወደ ኋላ አይልም። ማጭዱንና መስቀሉን አስቀምጦ፣ የነፃነት መሣሪያውን ሲያነሳ ግን ኢላማ የማይስት፣ በጠላት ላይ መብረቅ የሚጥል ጀግና ተኳሽ ይሆናል። ​2. ከላይ ከፍ ስትል፦ ዶክተር ​የምድርን ስቃይና በሽታ ለማስታገስ ወደ ላይ ከፍ ብለህ ስትመለከት ደግሞ ሌላ ማንነቱን ታገኛለህ። በዘመናዊው የህክምና ሳይንስ የላቀ፣ ነጭ ጋውኑን ለብሶ በሽተኞችን የሚታደግ ዶክተር ሆኖ ታየዋለህ። ህመምተኞች የእሱን ፈገግታና እውቀት ሲያዩ ተስፋቸው ይለመልማል። እርሱ ህይወትን የሚቀጥል የፈውስ እጅ ነው። ​3. ከጎን ዞር ስትል፦ ፕሮፌሰር ​ወደ እውቀትና ፍልስፍና አደባባይ ዞር ስትል ደግሞ በዩኒቨርሲቲዎች መድረክ ላይ ታገኘዋለህ። ሰፊውን ግንባሩን አሳብቦ፣ የዓለምን ታሪክና የተወሳሰቡ የሳይንስ ንድፈ-ሀሳቦችን በቅልጥፍና ሲተነትን ፕሮፌሰር ሆኖ ታየዋለህ። የእርሱ አእምሮ በጥልቀት የሚያስብ፣ የትውልድ መቅረዝ ነው። ​4. ከጀርባ (ከኋላ) ዞር ስትል፦ ኢንጂነር ​ወደ ልማት፣ ህንጻና መሰረተ-ልማት ስትመለከት ደግሞ ከጀርባው ሆኖ ትልልቅ ድልድዮችንና መንገዶችን የሚቀይስ ኢንጂነር (መሀንዲስ) ሆኖ ታገኘዋለህ። የፈረሱትን የሚጠግን፣ የማይቻሉ የሚመስሉ የተራራ ቁልቁለቶችን በጥበብ ቀምሮ መንገድ የሚያወጣ የዕድገት ቁልፍ ነው። ​5. ከፊት ዞር ስትል፦ ፓይለት ​ፊቱን ወደ ሰማይ አቅንተህ ከፊት ለፊት ስትመለከተው ደግሞ ደመናትን ሰንጥቆ፣ በሰማያት ላይ የሚቀዝፍ እና ሀገሩን ከፍታ ላይ የሚያስቀምጥ ፓይለት (አብራሪ) ሆኖ ታየዋለህ። እርሱ በምድር ላይ ብቻ ሳይሆን በሰማይም ላይ የበላይነት ያለው የዓላማ ሰው ነው። ​"ለዚህም እኮ ነው የሚጠሉት!" ​ይህንን ሁሉ ተአምር በአንድ ሰው ላይ ማየት ለጠላቶቹ ሊሸከሙት የማይችሉት ከባድ እውነት ነው። ​እነሱ በአንድ መስክ እንኳን መድረስ ያልቻሉትን ከፍታ፣ እርሱ ግን ፋኖ ሆኖ በአንድ ጊዜ በሁሉም ዘርፍ ተክኖታል። በጥላቻ ሊያጠፉት የሚፈልጉት ስለበደላቸው ሳይሆን፣ የሱ መኖርና ሁለገብነት የእነሱን ታናሽነትና ድክመት አጋልጦ ስለሚያሳይ ብቻ ነው። እርሱ ግን በጥላቻቸው ሳይበገር፣ በሁሉም አቅጣጫ እንደ ከዋክብት እያበራ መኖሩን ይቀጥላል። Dave Amhara

ሰበር ባሕርዳር አሁን በዚህ ሰአት  ባህርዳር  ፈለገህይወት ሆስፒታል የአንድ ፖሊስ አመራር አስክሬን ገብቶ  ፖሊሶቹ የሆስፒታሉን ግቢ በጥይት እየበጠብጡት እንደሚገኙ ምንጮች በውስጥ ልከውልናል

#_3_የፓራ_ኮማንዶ አባላት ፋኖን ተቀላቀሉ የብልጽግና ካምፕ ባዶ ራቁቱን ቀርቷል !! ~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~ ....... ዛሬ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም ብልሆቹ የምረት ጥሪውን ተቀብለው
+4
#_3_የፓራ_ኮማንዶ አባላት ፋኖን ተቀላቀሉ የብልጽግና ካምፕ ባዶ ራቁቱን ቀርቷል !! ~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~ ....... ዛሬ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም ብልሆቹ የምረት ጥሪውን ተቀብለው ህይወታቸውን በማትረፍ ላይ ናቸው የፓራ ኮማንዶ አባላቱ በዛሬው እለት ከግንደ ወይን እና ከደብረ ወርቅ ከተማ በመውጣት 201ኛ ኮር 74ኛ ክፍለ ጦርን የተቀላቀሉ ሲሆን፦ 1.ይልቃል አባየሁ....ፓራኮማንዶ 2.ጥጋቡ የሺ......ፓራ ኮማንዶ 3.ሐብቴ ቁሜ.....ፓራ ኮማንዶ በዛሬው እለት የተቀላቀሉ ሲሆን በክፍለ ጦር አመራሮች አቀባበል ተደርጎላቸዋል። ሁሉም እንደተናገሩት ከሆነ ማንም እዛ ውስጥ መቆየት አይፈልግም የትጥቅ ችግር ስለነበረብን ፍላጎታችን አሳክተን ወደ ወንድሞቻችን ተመልሰናል በማለት ተናግረዋል። ጊዜው አልረፈደም አሁንም ቢሆን ወደ ማንነታቹህ ተመለሱ ኑ እንቀበላቹሀለን እንደማንኛውም ሰው መደበኛ ህይወታቹሁ መኖር የምትችሉ መሆኑን ድርጅታችን ጥሪ አቅርቦላቹሀል። የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት