ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
Ir al canal en Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
Mostrar más2 938
Suscriptores
+1424 horas
+3877 días
+38530 días
Archivo de publicaciones
የዳዊትና የጎልያድ ትንቅንቅ በደጋ ዳሞት ምድር!
አስራ አንድ የጦር መኮንኖች በአንድ ሻለቃ ፊት ግራ ሲጋቡ! የጦር ሜዳ ሳይንስንና የኃይል ሚዛንን ሙሉ በሙሉ ያቃወሰው የደጋ ዳሞቱ ታሪካዊ ፍልሚያ!"
ዛሬ በታሪካዊቷና በቆራጦች ምድር በደጋ ዳሞት፣ ታሪክ በደማቅ ቀለም ዳግም ተጽፏል። የአራት ኪሎው አገዛዝ ያለ የሌለ ኃይሉን አሰባስቦ፣ በርካታ ከባድ መድፎችን፣ የታንክ ሰራዊትንና ዘመናዊ መሣሪያዎችን አስፎክሮ የላካቸውን 4 ጀነራሎች እና 7 ኮሎኔሎችን በአጠቃላይ 11 የጦር መኮንኖችን በአማራ ፋኖ ኩራት በሆነው በጀግናው ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው የሚመራው የቴዎድሮስ ዕዝ አፈር ድሜ አብልቷቸዋል።
የመደበኛ ውትድርና ስልጠና የወሰዱት፣ የብረትና የመሳሪያ ብዛትን ተማምነው የመጡት እነዚህ አስራ አንድ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች፤ የደጋ ዳሞትን ምድር በቁጥጥር ስር ለማዋል ትልቅ ዝግጅት አድርገው ነበር። ነገር ግን የጦር ስልትና የብረት ኃይል ብቻውን ውጊያን እንደማያሸንፍ የደጋ ዳሞቱ ፍልሚያ አስመስክሯል! የጠላት ዝግጅት፦ አራት ጀነራሎችና ሰባት ኮሎኔሎች፣ በከባድ መሳሪያዎችና በሰው ኃይል ታጅበው ገቡ። የፋኖ ምላሽ ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው፣ የሕዝብን እውነተኛ የነጻነት ስሜትና የቴዎድሮስን ወኔ አንግቦ በጥቂት ታጋዮች የጠላትን ሰራዊት መላቅጡን አጠፋው!
አራት ጀነራሎችና ሰባት ኮሎኔሎች ተደማምረው በአንድ የፋኖ ሻለቃ አመራር ፊት መቆም አቅቷቸው ሲጨነቁ፣ ሲጠበቡና ወደኋላ ሲያፈገፍጉ ውለዋል። ይህ ክስተት የጦር መሳሪያ ብዛት ሳይሆን የሞራል የበላይነትና የታጋዩ እውነተኛ ወኔ ድል አድራጊ መሆኑን ለአለም አቀፍ ማህበረሰብ በግልጽ ያሳየ ህያው ምስክር ነው!
ይህ ተአምራዊ ድል በወታደራዊ ስልት ብቻ የተገኘ አይደለም፤ በደጋ ዳሞት አርሶ አደርና ቆራጥ ሕዝብ የማይወላወል ደጀንነት እንጂ! ሕዝቡ፦ ቀለቡን አዘጋጅቶ፣ መረጃውን አቅርቦ፣ ልቡንና ጸሎቱን ሰጥቶ ከጎን ቆመ! የቴዎድሮስ ዕዝ፦ የሕዝቡን አደራ አንግቦ የጠላትን ግርማ ሞገስ አፈር ድሜ አበላው!
የደጋ ዳሞት ምድር ዛሬም እንደ ትላንቱ የጀግኖች መብቀያ እንጂ የፈሪዎችና የአብይ አህመድ ወንበር አስጠባቂ መፈንጫ አትሆንም! የጀግናው ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው ክንድና የፋኖዎች ወኔ ነገም አዲስ ታሪክ መስራቱን ይቀጥላል። ታሪክ አይረሳም! የእውነትና የነጻነት ጉዞ በደማቅ ድል መታጀቡን ይቀጥላል!
🔥 ድል ለአማራ ህዝብ
⭐️ ከፍታና ዝና ለጀግናው ሻለቃ ዝናቡ ልንገረውና ለቴዎድሮስ ዕዝ! አድርሱልኝ Dave Amhara
የድምሰሳ_ፕሮፓጋንዳው_ከሽፏል‼️ (ሰፋ ያለ እና የተሟላ ትንተና)
በጎጃም ምድር የተካሄደውን ወቅታዊ የጦርነት ሁኔታ እና የጠላትን እንቅስቃሴ በተመለከተ የሚከተሉት ዋና ዋና ነጥቦች ጎልተው ወጥተዋል።
1. የጠላት የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ እና የከባድ መሳሪያ ድብደባዎች
ምንም አይነት ወታደራዊ ድል ማስመዝገብ ያልቻሉት የሌተናል ጄኔራል መሐመድ ተሰማ (የምስራቅ ዕዝ) እና የሜጄር ጄኔራል ብርሃኑ ጥላሁን (የ6ኛ ዕዝ) የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ሙሉ በሙሉ መክሸፉ ተገልጿል።
የጥቃቱ ስፋት፡ በጎጃም ምድር ከ275 በላይ የመድፍ ጥቃቶች ተፈጽመዋል።
የተሰማሩ የጦር መሳሪያዎች፡ ቢኤም (BM)፣ ዘ-23 (ZSU-23) እና ሞርተሮች ጥቅም ላይ ውለዋል።
የዒላማው ሁኔታ፡ ጥቃቶቹ ከ40 እስከ 20 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኙ ንጹሐን መንደሮች ላይ ያነጣጠሩ ነበሩ።
2. የአገዛዙ ሰራዊት አቋም እና የውጊያ ሁኔታ
የአገዛዙ እግረኛ ሰራዊት በሜዳ ላይ ምንም ዓይነት የውጊያ ፍላጎት እንደሌለው ተመላክቷል። ራሱን በረጅም እርቀት አስቀድሞ ለመከላከል ሲል በእያንዳንዱ እንቅስቃሴው መድፎችን እና ቢኤም (BM) በመጠቀም ያለ ምንም ትክክለኛ ውጊያ የንጹሐንን ሕይወት እየቀጠፈ ይገኛል። በዚህም የተነሳ በሰራዊታችን ላይ የደረሰ ምንም ዓይነት ጉዳት የለም፤ ይልቁንም የሜካናይዝድ ጥቃቱ ሙሉ በሙሉ በንጹሐን ዜጎች ላይ ያነጣጠረ ነው።
3. ከባድ መሳሪያ ጥቃት የተፈጸመባቸው አቅጣጫዎች እና አካባቢዎች
ሀ. የምስራቅ ዕዝ (ሌተናል ጄኔራል መሐመድ ተሰማ) የተንቀሳቀሰባቸው መስመሮች፦
ከአዲስ ቅዳም - ፋግታ - ፍኖተ ሰላም - ገነት አቦ - ጉጥልማ - ፈረስ ቤት
ከአዴት - ብር አዳማ - ጠጠር ማርያም - ሃሙስ ገበያ
ከአዴት - ዋሸራ - ገረገራ - አስተርዮ
ለ. 6ኛ ዕዝ (ሜጄር ጄኔራል ብርሃኑ ጥላሁን) የተንቀሳቀሰባቸው መስመሮች፦
ከደንበጫ - በአንጀኔ - ፈረስ ቤት
ከደንበጫ - ገሊላ - ዋዳን - ኮረብታ - ውሃበር
ከደብረ ማርቆስ - አማኑኤል - ደብረቀለሞ - ደጋሰኝ - ረዕቡ ገበያ
ከደብረ ማርቆስ - ረዕቡ ገበያ - ደብረዘይት
ከትኖራ - መርጡለ ማርያም - ሞጣ - ድጎፂዮን - ውሃበር
ከቁይ - ጎዛምን - ደባይ ጥላት ግን ደጋማ ክፍል
4. የሰራዊታችን አጸፋዊ እርምጃዎች እና ድሎች
የጠላትን ስልታዊ እቅድ ውድቅ በማድረግና ከሚጠበቀው ውጪ ጀብድ በመፈጸም ረገድ፦
206ኛ ኮር 34ኛ ክ/ጦር በኮርክ ከተማ ድል አስመዝግቧል።
102ኛ ኮር 33ኛ ክ/ጦር ደግሞ በምርኮ የቀጠለውን ውጊያ በዋሸራ አቅጣጫ አጠናክሮ ቀጥሎበታል።
በአንጀኔ፣ ገሊላ፣ ዋሸራና ገረገራ ቀጠናዎች የአገዛዙ ጦር ከባድ ኪሳራ አስተናግዶ ማፈግፈጉና የአካባቢዎቹ በፋኖ ቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተገለጸ
በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ ሥር የሚንቀሳቀሱ ክፍለጦሮች በተለያዩ ወታደራዊ ቀጠናዎች ባካሄዱት መጠነ-ሰፊ የመልሶ ማጥቃት እርምጃ የአንጀኔና የገሊላ ከተሞችን ጨምሮ በርካታ ስትራቴጂካዊ ቦታዎችን ሙሉ በሙሉ በቁጥጥራቸው ሥር ማዋላቸውን ገለጹ።
የዕዙ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ይፋ ባደረጋቸው ወታደራዊ መረጃዎች መሠረት፣ በኢንጂነር ክበር ተመስገን ሻለቃ፣ በ102ኛ ኮር 33ኛ ክፍለጦር እና በሌሎች አርበኞች የተቀናጀ ተጋድሎ የአገዛዙ ጦር ከአንድ ሻለቃ በላይ ሰራዊት ተደምስሶበት ወደ ኋላ እንዲያፈገፍግ ተደርጓል።
የቴዎድሮስ ዕዝ 109ኛ ኮር፣ 99ኛ ክፍለጦር ኢንጂነር ክበር ተመስገን ሻለቃ ከሐምሌ 09 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በሦስት አቅጣጫ ሜካናይዝድ ኃይል በማሰለፍ ተንቀሳቅሶ የነበረውን የአገዛዙን ጦር ለ5 ቀናት ያህል በተካሄደ ከባድ ትንቅንቅ መደምሰሱ ተገልጿል።
ጠላት በአንጀኔ፣ ገሊላና ከቢቡኝ በኩል አልማ ሽፋን በመስጠት የጀግኖችን ቀዬ እይዛለሁ ብሎ ቢንቀሳቀስም፣ በአንጀኔ ገናላ ጊዮርጊስ፣ ዳባ እና ዋዳን በተባሉ ቦታዎች በተደረገ አውደ ውጊያ ከአንድ ሻለቃ በላይ የአገዛዙ ኃይል ተደምስሶ ቀጠናው ሙሉ በሙሉ በፋኖ ቁጥጥር ሥር ውሏል።
በዚህ ውጊያ የአገዛዙ አዋጊ መኮንኖች የተደመሰሱ ሲሆን፣ ወደ መግደያ ዞን ገብቶ ከባድ ሰብዓዊ ኪሳራ የደረሰበት የአገዛዙ ጦር ከፍኖተ ሰላምና ከደብረ ብርሃን/ደምበጫ የተጫነ ተጨማሪ ኃይልና ዙ-23 ከባድ መሣሪያዎችን በመጠቀም የተረፉ አባላቱን ይዞ ለመውጣት ተገደዳል። በሌላ በኩል ደግሞ የደምበጫ ማኅበረሰብ በጡሩንባ በመውጣት የአገዛዙን ጦር ፊት ለፊት በመጋፈጥ ከፍተኛ ሕዝባዊ ጀብድ መፈጸሙ ተጠቅሷል።
በሌላ ወታደራዊ ቀጠና፣ ከቋሪት ጠጠር ማርያም ተነስቶ ዋሸራን ለመያዝ የተንቀሳቀሰው የአገዛዙ ጦር በ102ኛ ኮር 33ኛ ክፍለጦር ተቀጥቅጧል። ትናንት ምሽት በገረገራ ከፍተኛ ኪሳራ አስተናግዶ የነበረው ሰራዊት ከቋሪት ተጨማሪ ኃይል አግተልትሎ ወደ ዋሸራ ቢገባም፣ በወንዳወክና በዮሐንስ ዓለማየሁ አርበኞች በተሰነዘረበት የእጅ በእጅ ውጊያ አቅሙን አጥቶ ወደ ኋላ በማፈግፈግ ላይ ይገኛል።
በተጨማሪም የ102ኛ ኮር 33ኛ ክፍለጦር በፈጸመው ድንገተኛ ማጥቃት ጎንጂ ቆለላ ገረገራን በወገን ቁጥጥር ሥር ማዋል ተችሏል። በዚህም ሳቢያ በጎንጂ ቆለላ ከተማ የተጠራቀመው የአገዛዙ ሰራዊት እርስ በርሱ ሲተኳኮስ ማደሩ የተገለጸ ሲሆን፣ በተለይም የተጠረነፈው ሚሊሻ "ወደ ሰሜን ግባ" መባሉን ተቃውሞ አልሄድም በማለቱ በፈነዳው የእርስ በእርስ ውጊያ ከሦስት በላይ የአገዛዙ አባላት መወገዳቸው ታውቋል።
በሁሉም አቅጣጫ መውጫ ያጣውና በፋኖ የመልሶ ማጥቃት የተቀጠቀጠው የአገዛዙ ጦር፣ የደረሰበትን ከባድ ወታደራዊ ኪሳራ ለመበቀል በንጹኃን አርሶ አደሮች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ፈጽሟል። ሰራዊቱ መድፍ፣ ዙ-23 እና 107 ሮኬት በመጠቀም ከሕፃናት እስከ አዛውንቶች ያሉ ሰላማዊ ሰዎችን ከእርሻ ቦታቸውና ከቤታቸው በማውጣት የከባድ መሣሪያ ድብደባና ጭፍጨፋ ማካሄዱ ተገልጿል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ በናዝሬት በተካሄደ የብልጽግና አገዛዝ የግምገማ መድረክ ላይ "ወደ ሰሜኑ ጦርነት ስንሄድ ሙሉ ሚሊሻና አድማ ብተና ወደ ፋኖ ስለሚቀላቀል፣ መሣሪያቸውን ተቀብለን በምክንያት መደምሰስ አለብን" የሚል ውሳኔ መተላለፉን የቴዎድሮስ ዕዝ ከውስጥ ባገኘሁት መረጃ አረጋግጫለሁ ብሏል።
በመሆኑም አድማ ብተናና ሚሊሻው በአገዛዙ ሴራ ከመበላቱ በፊት አስቀድሞ ወደ ሕዝቡና ወደ ሕልውና ትግሉ እንዲቀላቀል ዕዙ ጥሪውን አስተላልፏል።
ሰበር ዜና!!
2 አዛዦችን ጨምሮ ከ70 በላይ የጠላት ጦር ተደመሰሰ/ 51 ክላሽ ተማረከ!
በአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ 104ኛ ኮር ስር የ23ኛ ክ/ጦር አርበኞች ከትናንት ሃምሌ አመሻሽ ጀምሮ እስከ ዛሬ ሃምሌ 14/2018 ዓ/ም ደርስ ባደረጉት ከባድ ተጋድሎ ከወታደራዊ አዛዦች ጀምሮ የጠላትን ጦር ቆርጦ በመደምሰስና ለሕልውና ትግሉ ወሳኝ የሆኑ የቡድንና የነፍስ ወከፍ የጦር መሣሪያዎችን በመማረክ አንፀባሪቂ ድል ተቀዳጅተዋል።
በአምባሰል ወረዳ መነሻውን ከውጫሌ ከተማ አድርጎ እዛው ውጫሌ ከተማ በተጠመደ ከባድ መሣሪያ ሽፋን በመታገዝ በሚኒሻ መሪነት በአበት በኩል አቆራርጦ ወደ ሚለዋ አከባቢ ተንቀሳቅሶ የነበረው የጠላት ጦር ነው በፋኖ ቀለበት ውስጥ ገብቶ ዳሽቆ የቀረው።
የጠላት ጦር ትናንት ሃምሌ 13/2018 ዓ/ም መነሻውን ውጫሌ በማድረግ በዛው ውጫሌ ከተማ ተጠምዶ ወደ ሚለዋና አከባቢው በሚወረወር ከባድ መሣሪያ ሽፋን በመታገዝ ወታደራዊ ቁሳቁሱን በግመልና በአህያ ጭኖ በሚኒሻ መንገድ መሪነት በአበት ተራራ በኩል ወደ ሚለዋ አከባቢ ተንቀሳቅሶ ነበረ።
የጠላት ኃይል ወደ አከባቢው በሚገባበት ወቅት ምንም አይነት እርምጃ ያልወሰዱትና ቀድመው ቁልፍ ወታደራዊ ቦታዎችን በመቆጣጠር አድፍጠው የነበሩት የ23ኛ ክፍለጦር አርበኞች፡ ጠላት ወጥመዳቸው ውስጥ መግባቱን ካረጋገጡ በኋላ መውጫ መግቢያ በሮችን ክርችም አድርገው በመዝጋት የጥቃድ ዶፍ አውርደውበታ።
የጠላት ኃይል ወደፊት እንዳይገፋምሆነ ወደ ኋላ እንዳይመለስ መውጫ ማምለጫ በሮች በሙሉ ተቆልፈውበት፡ ከትናንት ሃምሌ13/2018 ዓ/ም ጀምሮ እስከ ዛሬ አመሻሽ ድረስ በተወሰደበት ከባድ እርምጃ ዳሽቋል።
የፋኖ ልዩ የጦር ንድፍና የማጥቃት አቅም በታየበት በዚህ ተጋድሎ፡ ከ70 በላይ የአገዛዙ ወታደሮች ሲደመሱ፡ ቀሪው ኃይል ዛሬ ከሰዓት በኋላ መተንፈሻ በር አግኝቶ በርካታ ቁስለኞቹን በወሳንሣ ተሸክሞ ሸሽቷል።
በተጋድሎው እርምጃ ከተወሰደባቸው የጠላት ኃይሎች መካከል የሃምሣ አለቃነት ማዕረግ ያለው አንድ የሻምበል አዛዥና የአሥር አለቃነት ማዕረግ ያለው የመቶ መሪ እንደሚገኙበት ነው ለማረጋገጥ የተቻለው።
የፋኖ ልዩ የቆረጣ ማጥቃት ብቃት በታየበት በዚህ ተጋድሎ ሦስት ብሬን መትረጌስን ጨምሮ 51 ክላሽንኮቭ መሣሪያ፣ እስካሁን በውል ተቆጥሮ ያላለቀ የብሬንና የክላሽ ተተኳሽ እንዲሁም በርካታ የደረትና የወገብ ትጥቅ ከጠላት ተማርኳል።
በተጨማሪም፡ 11 ወታደሮች እጅ ከፈንጅ ተማርከው የአለም አቀፍ የምርኮኛ አያያዝ ሕገደንብ እንዲሁም አማራዊ እሴትና ባህልን ባከበረ መልኩ እንብካቤ እየተደረገላቸው ይገኛል።
እገዛ ለማድረግ ተጨማሪ ከወደ ውጫሌ ከተንቀሳቀሰው የጠላት ኃይል ጋር ውጊያው በዚህ ምሽትም በፋኖ የበላይነት እየተመራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያ እና ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ!!
ሀምሌ 14/ 2018 ዓ/ም።
ሰበር ዜና ‼
የአፋብን ቢዛሞ አይሻ ሰይድ ዕዝ በምስራቅ ወለጋ ዞን ጉቶ ጊዳ እና ስቡ ስሬ ወረዳ በተደረገ ውጊያ ልጎ እና መርካቶ ከተሞችን ተቆጣጠረ !!
የጠላት ጥምር ጦር ላለፉት በርካታ ወራት በእነዚህ ከተሞችና ቀበሌዎች መሽጎ በአካባቢው በሚኖረው የአማራ ማህበረሰብ ላይ ግድያ፣ ዝርፊያ፣ እንዲሁም ከገበያ በሚመለሱ ነዋሪዎች ላይ ኬላ በመጠበቅ እንግልትና ንብረት ማውደም ቢፈጽም መቆየቱን ተከትሎ ነው።ዛሬ ሐምሌ 14 ቀን 2018 ዓ.ም. ከሌሊቱ 11፡00 ሰዓት ጀምሮ የተካሄደው ይህ ኦፕሬሽን፣ ከኡኬ አየር ማረፊያ ከ4 እስከ 5 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኙት መርካቶ እና ልጎ ከተሞች ላይ ያነጣጠረ ነበር።
ከዕዙ ምክትል ጦር አዛዥ እና የየክፍለ ጦሮቹ አዛዦች ጋር በከፍተኛ ቅንጅትና መናበብ የጠላትን ምሽግ በመሰባበር የከተማ ሽምቅ ውጊያ አካሂደዋል።
ለስድስት ተከታታይ ሰዓታት (እስከ ጠዋቱ 5፡00 ሰዓት) በተደረገው በዚህ ውጊያ፣ የአንሻ ሰይድ አናብስቶች ሁለቱንም ከተሞች ሙሉ በሙሉ በመቆጣጠር በድል አጠናቀዋል። የተሸነፈው የጠላት ጥምር ጦር ሙትና ቁስለኛውን እያዝረከረከ ወደ ኡኬ ከተማ ያፈገፈገ ሲሆን፤ በአሁኑ ወቅትም አፈግፍጎ ከገባበት ሆኖ በመድፍ፣ በዙ-23 እና በሞርተር ነዋሪው የሚገኝባቸውን ከተሞች እየደበደበ ይገኛል።
በዚህ ከባድ ውጊያ በምርኮ የተገኙ የሰው ኃይል እና ቁሳቁሶች፦
• 15 የጠላት እግረኛ ጥምር ጦር አባላት
• 28 የክላሽንኮቭ ጠመንጃዎች
• 19 የኤፍ-ዋን (F-1) የእጅ ቦምቦች
• 24 ካዝናዎች እንዲሁም 26 የደረትና የወገብ ትጥቆች
• 730 የብሬንና የክላሽንኮቭ ጥይቶች እና የተለያዩ ወታደራዊ ሻንጣዎችን ማርከዋል።
"ግፍ የወለደን፤ ግፈኞችን የምንቀጣ የአንሻ ሰይድ ወንድሞች ነን!"
ምንጭ፡- ዳዊት አማረ፣ የአፋብን ወለጋ/ቢዛሞ አንሻ ሰይድ ዕዝ የህዝብ ግንኙነት መምሪያ
ከደብረ ማርቆስ ሆስፒታል ወደ ጦር ኃይሎች(አ.አ) ለከፍተኛ ህክምና 12 የአድማ ብተና አባላት እና ሹፌሮች ሪፈር ተልከዋል።
ሐምሌ14/2018 ዓ.ም
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
በትናትናው እለት 206ኛ ኮር 34ኛ ክ/ጦር በኮርክ ከተማ በመሸገው እና ከየጁቤ ተነስቶ ድጋፍ ለመስጠት በተንቀሳቀሰው የጠላት ኃይል ላይ አስደናቂ ጀብድ ከፈፀመ በኋላ፦
1. አብነህ ሹመት
2. ፈንታ አባተ
3 .ሰንታየሁ ታሪኩ
4. ዋሰይሁን አድማሰ
5. ይታያል ተረፈ
6. እያሱ መለሰ
7. ይታያል አለሙ
8. ባድማው ዋሌ
9. ወንድም ማናየ
10. ሃይሉ አባተ
11. ጥላሁን ልንገር ፦ በቅርቡ የግሉን የጭነት ማመላለሻ FSR ገዝቶ በስራ ላይ እያለ በግዳጅ ተይዞ ወደ ባሶሊበን ኮርክ ተጨማሪ ኃይል ጭኖ ሲንቀሳቀስ ከሰራዊቱ ጋር ጉዳት አስተናግዶ ከተላኩት መካከል ሲሆን ተሽከርካሪው ከጥቅም ውጭ ሁኗል። በዚህም መሰረት ከየጁቤ ሆስፒታል ሪፈር ተብለው ደብረ ማርቆስ ሆስፒታል ከተላኩት 18 የአድማ ብተና መካከል 12ቱ ወደ ጦር ኃይሎች ለከፍተኛ ህክምና መሔዳቸው ተረጋግጧል።
አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ ! አዲስ ተስፋ!
የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
የብረት ጽናትና የጀግንነትን ታሪክ የተላበሰው የአማራ ልጅ ፋኖ የአርበኛ ኮማንዶ ታድሎ ንጉሤ ተጋድሎ ከማሰልጠኛ እስከ አውደ ውጊያ!!
የወታደራዊ ስትራቴጂ፣ የጽናትና የመስዋዕትነት ህያው ምስክር የሆነው አርበኛ ኮማንዶ ታድሎ ንጉሤ፣ በአማራ ወታደራዊ ታሪክ ውስጥ ጉልህ ስፍራ የሚሰጠውንና ለዓመታት ያካበተውን የውጊያና የስልጠና ተጋድሎ በቀድሞው የሸዋ ዕዝ የወታደራዊ ስልጠና ኃላፊ፣ በኋላም በነበረው የአፋብኃ የአሳመነው ዕዝ ዋና ልዩ ዘመቻ መሪነት ያገለገለዉ አርበኛ ታድሎ፤ በአሁኑ ስዓት በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳመነው ዕዝ በምክትል ልዩ ዘመቻ መሪነት አገራዊና ህዝባዊ ግዳጁን በብቃት እየተወጣ ይገኛል። በጥበብና በፅናት በተሞሉ ዓይኖቹ የጦር ሜዳውን የሚቃኘው አርበኛ ኮማንዶ ታድሎ፤ በልቡ ላይ ያሉት ጠባሳዎች ዝም ብለው የተሰፉ ቁስሎች ሳይሆኑ በየውጊያው አውድማ ላይ የተጻፉ የጀግንነት ታሪኮች እንደሆኑ ያስመስክራል።
በ2013 ዓ.ም በሀገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል ተከስቶ በነበረው ከባድ ጦርነት ወቅት፣ ጠንካራና የሰለጠነ የሰው ኃይል መገንባት ወሳኝ ነበር። አርበኛ ኮማንዶ ታድሎ ንጉሤ በጠባሴ ማሰልጠኛ በመገኘት የወታደራዊ ስልጠና አዛዥነቱንና መሪነቱን ተረክቧል። በዚህ ማሰልጠኛ ቅጥር ግቢ ውስጥ ሌትና ቀን ሳይል ባደረገው ከፍተኛ ጥረት፣ በሶስት (3) ተከታታይ ዙሮች ከ5,000 በላይ የሚሆኑ ወጣት ተዋጊዎችን በልዩ የኮማንዶ ስልጠና አዘጋጅቷል። እነዚህ የሰለጠኑ የኮማንዶ አባላት በስነ-ልቦና፣ በታክቲክ እና በውጊያ ብቃት የላቁ እንዲሆኑ በማድረግ ለሀገር አለኝታነታቸውን ያስመሰከሩበትን መሰረት ጥሏል።
በ2014 ዓ.ም በኦሮሚያ ክልል ውስጥ ወታደራዊ እንቅስቃሴ በሚደረግበት ወቅት፣ አርበኛ ታድሎና ጓዶቹ እጅግ ፈታኝ ከሆኑ የጠላት ኃይሎች ጋር ፊት ለፊት ተገናኝተዋል። ከሸኔ ታጣቂዎች ጋር በተደረገው በዚህ ፍልሚያ፣ ውጊያው ተራ የሩቅ ተኩስ ሳይሆን እስከ አካላዊ የቅርብ ርቀት (አንገት ለአንገት) የደረሰ አደገኛና አታጋይ በማድርግ ደረጃ በዚያ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆኖ የኮማንዶ ስትራቴጂዎችን በመጠቀም፣ የጠላትን ግስጋሴ የመከከተ እና ወታደራዊ ብቃቱን ያረጋገጠበት የጀግንነት ምዕራፍ ተመዝግቧል።
ሚያዝያ 3 ቀን 2015 ዓ.ም በጠባሴ ቀጠና የተካሄደው ውጊያ በአርበኛ ታድሎ የውጊያ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ቦታ ይይዛል። በዕለቱ ከአማራ ጠሉ ከአብይ ኮማንዶ ጋር በተደረገው ከፍተኛ ፍልሚያ፣ የጦር ሜዳው በእሳትና በጥይት እራፊ የተሸፈነ ነበር። አርበኛ ታድሎ በእንደዚህ ዓይነት ከባድ ከበባና ፍልሚያ ውስጥ ሆኖ፣ የወደቁትን የትግል ጓዶቹን እየደገፈ፣ የተበተነውን ኃይል በቆራጥነት በመሰብሰብና የፊት ለፊት መሪነቱን በመውሰድ አውደ ውጊያውን በድልና በጽናት መወጣት ችሏል።
በተከታታይ የስልጠና ዘመቻዎችና አዳዲስ አበቦች 2015 - 2016 ዓ.ም ውጊያን ከተግባራዊ ስልጠና ጋር አጣጥሞ የሚመራው አርበኛ ታድሎ፣ በውጊያ መካከል እንኳን ተተኪ ኃይል ማፍራቱን አላቆመም በ2015 ዓ.ም በተጉለት ቀጠና በመገኘት 3 ዙር የልዩ ኮማንዶ ስልጠና ሰጥቷል። በ2016 ዓ.ም፦ በሳሲት፣ በፈላ እና በጋወና ቀጠናዎች በመንቀሳቀስ 2 ዙር ተጨማሪ የኮማንዶ ስልጠናዎችን በመስጠት በመቶዎች የሚቆጠሩ አዳዲስ ተዋጊዎችን አፍርቶ ለግዳጅ አብቅቷል። የማይረሱት የትግል አጋሮችና የወደፊቱ ራዕይ አርበኛ ኮማንዶ ታድሎ ንጉሤ ስለተጎናጸፋቸው ድሎችና ስለተወጣቸው ግዳጆች ሲናገር፣ ከሁሉም በላይ ቀደመው የሚመጡበት በየሳሲት ገደሎች፣ በፈላና በጋወና ዳገቶች አብረውት ደምና ላባቸውን ያፈሰሱ የትግል ጓዶቹ እንደሆኑ ይገልጻል።
ይህ ሁሉ ድልና ጽናት የብቸኛ ጥረት ውጤት አይደለም። ጀግና ማለት ብቻውን የሚያሸንፍ ሳይሆን ከጎኑ ያሉትን ጀግኖችን አብሮ ወደ ድል የሚያመራ ነው! በየቀኑ አብረውኝ በየመሬቱ ደፋ ቀና የሚሉትን፣ በብርድና በሐሩር የሚጋፈጡትን እና መስዋዕትነት የሚከፍሉትን ውድ የትግል አጋሮቼን (ጓዶቼን) ሁልጊዜም በታላቅ ክብርና ፍቅር አስባቸዋለሁ ይለናል።
በአሁኑ ሰዓት አርበኛ ኮማንዶ ታድሎ ንጉሤ በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳመነው ዕዝ በምክትል ልዩ ዘመቻ መሪነት በተሰጠው ኃላፊነት ላይ ይገኛል። Dave Amhara
+9
በጥዋት ዜና እወጃችን የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዓፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር በነጎድጓድ ክ/ጦር በተካሄደው የአንጨቆረር ከተማ ጀብድ የምርኮ ዝርዝር ይፋ እንደሚከተለው አቅርበናል!!
ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ቀን 14/11/2018 ዓ.ም በዛሬው ዕለት ጠዋት በወጣው ዜና በሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዘርያዕቆብ ኮር ነጎድጓድ ክ/ጦር በአገዛዙ ሀይል ላይ በወሰደው እርምጃ የአገዛዙ ጅምላ ተጋላቢ የሚሊሻ አባላት ላይ አመርቂ ድል መቀዳጀቱ ይታወሳል። አሁን ከሰዓት በደረሰን ተጨማሪ መረጃ መሠረት የተማረኩ አካላት እና የቁሳቁስ ዝርዝር መረጃ ይፋ ሆኗል።
የተማረኩ አካላት እና ቁሳቁሶች ዝርዝር
1ኛ.የተማረኩ የሚሊሻ ብዛት 5 አባላት
2ኛ.12 ክላሽኒኮቭ ጠመንጃዎች
3ኛ.4 ኤስ-ኬ-ኤስ (SKS): ጠመንጃ
4ኛ.1 መትረዬስ ክላሽ
5ኛ. ልዩ ልዩ የወገብ ትጥቅና ተተኳሾች ናቸው።
የኮሩና ክ/ጦሩ አመራሮች እንዳስታወቁት፣ በዚህ አውደ ውጊያ ላይ ለተሳተፉ አመራርና ሰራዊት አባላት ምስጋናቸውን በማቅረብ ይህና መሰል ስራዎችን ተጠናክረው በመቀጠል የድርጅታችን አፋብንን ጥሪ ባልተቀበሉ የአማራ ህዝብ ጠላቶች ላይ ሁሉ እርምጃው ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግኑኝነት መምሪያ
በጉቶ ጊዳ ወረዳና ስቡ ስሬ ወረዳ የአንሻ ሰይድ ክ/ጦሮች የተናበበ መብረቃዊ ጥቃት በመፈፀም ድል ተቀዳጁ‼️
ሐምሌ 14ቀን 2018ዓ.ም
በአፋብን ወለጋ/ቢዛሞ አንሻ ሰይድ ዕዝ የሚንቀሳቀሱት
1 ጌጤ ግርማ መብረቅ ክ/ጦር
2 አበጀ ጥበቡ ነበልባል ክ/ጦር
3 አንገር ጉትን ክ/ጦርና
4 ታፈረ አለሙ ሳተናው ክ/ጦር
የአንሻ ሰይድ ዕዝ ምክትል ጦር አዛዥና የየክፍለ ጦሮች ጦር አዛዦች ጋር በመናበብ ደማቅ ወታደራዊ ገድልና የድል ታሪክ በመፃፋ ዛሬም በደመቀ ሁኔታ ቀጥለውበታል።
ላለፉት በርካታ ወራቶቺ በምስራቅ ወለጋ ዞን ጉቶ ጊዳ ወረዳ ልጎ ቀበሌና በምስራቅ ወለጋ ዞን ስቡ ስሬ ወረዳ መርካቶ ቀበሌ ላይ ለበርካታ ወራቶች ካምፕ በማድረግ የአማራውን ማህበረሰብ በግፍ ሲጨፈጭፍ ፣ሲገል ፣ ሀብት ንብረቱን ሲዘርፍ እንዲሁም የሀይማኖት አባት ጨምሮ በአሰቃቂ ሁኔታ በመግደል የአማራ የጥላቻውን ጥግ ባደባባይ ሲያራምድ የቆየ፤በተጨማሪም ወደ ሁለቱም ከተሞች ማለትም በመርካቶ ከተማና በልጎ ከተማ ለገበያ ከገጠር የሚገቡ አማራዎች ላይ የሚገዙትን ነገር ሸምተው ሲመለሱ ኬላ ላይ በመጠበቅ ሀብት ንብረታቸውን በመቀማትና ፈሳሺ ነገሮችን ከዘይት ጀምሮ በማፍሰስ የተለያዩ የግፍ ድርጊቶቺን ሲፈፅም ቆይቷል።
ዛሬ ከንጋቱ 11:00 ሰዓት በምስራቅ ወለጋ ዞን ጉቶ ጊዳ ወረዳና ስቡ ስሬ ወረዳ ከኡኬ ኤርፖርት አየር ማረፊያ በ4 እና በ5 ኪሎ ሜትር ውስጥ የሚገኙት መርካቶ ከተማና ልጎ ከተማ ላይ ለወራቶች መሽጎ የነበረን የጥላት ጥምር ጦር በነዚህ ከተሞች ላይ ሰርጎ በመግባትና ምሽጎችን በመሰባበር 4ቱም ክፍለጦሮች የተናበበ የከተማ ሽምቅ ውጊያ በማድረግ ሁለቱንም ከተሞች በመቆጣጠር በጥላት ላይ አንፀባራቂ ድል ተቀዳጅተዋል።
በመጨረሻም ውጊያው ከጠዋቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ቀኑ 5:00 ሰዓት ለስድስት ሰዓታት የተደረገ ሲሆን በየግዜው ወለጋ ምድር ላይ ታሪክን በጃቸው መፃፍ የለመዱት የአንሻ ሰይድ አናብስቶቺ በድል ተጠናቋል።
የጥላት ጥምር ጦሩም ሙትና ቁስለኛውን በማዝረክረክ ወደ ኡኬ ከተማ በመፈርጠጥ የፈሪ ደዱላውን በመድፍ፣በዙ23ና ሞርተር አማሮች የሚኖሩበትን ከተሞች እየደበደበ ይገኛል።
በዚህ ከባድ ጦርነት ጀብደኞች በምርኮ ያገኛቸው ቁሳቁሶች
👉15 የእግረኛ ጥምር ጦር አባላት
👉28 ክላሺ እኮብ
👉19 ኤፍዋን ቦምብ
👉24 ካዝናና 26 የደረትና የወገብ ትጥቅ
👉730 የብሬንና የክላሽ ተተኳሽ የተለያዩ ወታደራዊ ሻንጣዎች የተማረኩ ሲሆኑ የተገኙ ድሎቺን በፎቶና በቪድዮ የምናቀርብ ይሆናል።
ግፍ የወለደን:ግፈኞቺን የምንቀጣ የአንሻ ሰይድ ወድሞች ነን!!!
©አፋብን ወለጋ/ቢዛሞ አንሻ ሰይድ ዕዝ ህ/ግንኙነት መምሪያ!
14/11/2018 ዓ.ም
+4
የምኒልክ ዕዝ ልዩ ዘመቻ መምሪያ የአጫጭር ስልጠናዎች እና የደንብ ልብስ የማልበስ ተሀድሶና ምርቃት አደረገ!!
ዘመናዊ ወታደር በመገንባቱ ረገድ ግንባር ቀደም በመሆን እየሰራ የሚገኘው (አፋብን) ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ልዩ ዘመቻ መምሪያ የሰራዊቱን የግዳጅ አፈፃፅም አቅም የሚያሳድጉ አጫጭር ስልጠናዎችን ሲሰጥ ቆይቶ ትላንት ሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም በደማቅ ሁኔታ አስመርቋል።
የልዩ ዘመቻ መምሪያው አጫጭር ስልጠናዎቹን ከሰራዊቱ የደንብ ልብስ ተሀድሶ ጋር በማጣመር ያዘጋጀ ሲሆን፣ የምረቃ መርሃ ግብሩ በየደረጃው ያሉ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በድምቀት ተካሂዷል።
በእለቱ የተገኙት አመራሮች ለተመረቁት ሰራዊቶች የቀጣይ የግዳጅ አፈፃፀም መመሪያና የተለያዩ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን፣ በስልጠናቸውና በግዳጅ ወቅት የላቀ አፈፃፀም ላሳዩ የሰራዊቱ አባላትም የዕውቅናና የሽልማት አሰጣጥ ስነ-ስርዓት ተከናወኗል።
ይህ ስልጠናና የደንብ ልብስ ተሀድሶ ሰራዊቱ የተጣለበትን ህዝባዊ ኃላፊነት በላቀ ዝግጁነት፣ በፅናትና በብቃት ለመወጣት የሚያስችለውን አቅም በእጅጉ እንደሚያጎለብተው ተገልጿል ሲል የልዩ ዘመቻ መምሪያ ህዝብ ግንኙነት ክፍል መረጃውን አድርሷል።
ጀግንነትና አሸናፊነት ከርህሩህነት ጋር= አማራነት!
ይህንን ቻናላችንን አሁኑኑ ሰብስክራይ ላይክ (Like) እና ሼር (Share) በማድረግ አጋርነታችሁን አሳዩ፤ ! 💪ለሁሉም ያድርሱት። በትብብራችን ትግላችን ያሸንፋል!አብረን እንቁም
🔗 ሊንኩን ተጭነው ቤተሰብ ይሁኑ፡
የምኒልክ ዕዝ ወታደራዊና ሲቪል አመራሮች ከላስታ ወረዳ ማህበረሰብ ጋር ስትራቴጂካዊ ውይይት አካሄዱ!
በአፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ስር የሚገኙ ከፍተኛ ወታደራዊና የሲቪል መዋቅር አመራሮች ከላስታ ወረዳ ማህበረሰብ ጋር በትግሉ ሂደት፣ በወታደራዊ ስምሪትና በሲቪል አስተዳደር ቅንጅት ዙሪያ ሰፊ ውይይት አካሂደዋል።
መድረኩ የትግሉ አሁናዊ ደረጃ፣ የሕዝብና የሠራዊት ትስስር እንዲሁም የአገዛዙን <የምክክር መድረክ> ሴራ ማጋለጥን ጨምሮ በ5 ዋና ዋና አጀንዳዎች ላይ በጥልቀት በመምከር የቀጣይ ነፃነት ጉዞውን ስትራቴጂካዊ በሆነ መንገድ ለመምራት የሚያስችል መሠረት መጣሉ ታውቋል።
በዚሁ ታላቅ መድረክ ላይ የምኒልክ ዕዝ የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ፣ የዕዙ ዕቅድ ዝግጅትና ግምገማ መምሪያ ኃላፊዎች፣ የ303ኛ ኮር እና የ14ኛ ጥራሪ ክፍለ ጦር አመራሮች በግንባር ቀደምትነት ተገኝተዋል።
በተጨማሪም የሕዝብን ደጀንነትና የዕለት ተዕለት አስተዳደራዊ ሥራዎችን የሚመሩ የወረዳ፣ የንዑስ ወረዳና የቀበሌ የሲቪል መዋቅር ተወካዮች ከየአካባቢው ተወጣጥተው ተሳትፈዋል።
ስብሰባው በዕዙ ሥር ባሉ ወታደራዊና ሲቪል መዋቅሮች መካከል ያለውን የመረጃና የሥራ ቅንጅት ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ ነው።
በውይይቱ የተዳሰሱ 5 ዋና ዋና አጀንዳዎች፦
1. የአማራ ትግል መነሻ፣ የደረሰበት ደረጃና መዳረሻ፦ ሕዝቡ ሕልውናውን ለማስከበር ወደ ትግል የገባበት አስገዳጅ ምክንያቶች፣ ትግሉ አሁን የደረሰበት የላቀ የጥንካሬ ደረጃና እየተመዘገቡ ያሉ ድሎች ተብራርተዋል።
እንዲሁም ትግሉ ዘላቂ ሰላም፣ እኩልነትና አስተማማኝ ደህንነት የሚያረጋግጥበት የመጨረሻ ግብ ተመላክቷል።
2. ወታደራዊና ሲቪል አደረጃጀትን ማጠናከር፦ የወረዳ፣ የንዑስ ወረዳና የቀበሌ የሲቪል አመራሮችን ሚና ከግንባር አዋጊዎች ጋር ማስተሳሰርና የዕቅድና ዝግጅት ሥራዎችን በተደራጀ መልኩ መምራት በሚቻልበት ስልት ላይ ውይይት ተደርጓል።
3. የሕዝብና የሠራዊት የማይበጠስ ትስስር፦ የፋኖ ሠራዊት የሕዝብ ልጅ በመሆኑ ያለ ሕዝብ ደጀንነት ትግሉ ግቡን ሊመታ እንደማይችል በመጠቆም፡ በሕዝቡና በሠራዊቱ መካከል ያለውን መተማመንና ትብብር ይበልጥ ማሳደግ እንደሚገባ ተገልጿል።
4. ትግሉን ከውስጥና ከውጭ ሴራዎች መጠበቅ፦ የትግሉን አቅጣጫ ለማስቀየር <ከአብይ አማሮች> እና ከሌሎች አካላት የሚሰነዘሩ የፖለቲካና የደህንነት ሴራዎችን በንቃት መከላከል እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል።
5. የአገዛዙን <የምክክር መድረክ> ማጋለጥ፦ አገዛዙ ሕዝቡን በድሮንና በከባድ መሣሪያ እየጨፈጨፈ ባረፈበት ወቅት በ«ምክክር መድረክ» ስም ያመጣው ሀሳብ ማደናገሪያና ሴራ መሆኑ ተብራርቷል።
አገዛዙ ሳይወገድ ምንም ዓይነት መፍትሔ ያለው ምክክር ሊኖር እንደማይችልና ትግሉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ግንዛቤ ተፈጥሯል።
በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ ከተሳታፊዎች ለተነሱ በርካታ ጥያቄዎችና ስጋቶች በዕዙ ከፍተኛ አመራሮች ዝርዝርና አጥጋቢ ምላሽ ተሰጥቶባቸው ውይይቱ በስኬት ተጠናቅቋል።
