es
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

Ir al canal en Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

Mostrar más
2 945
Suscriptores
+1624 horas
+127 días
+37730 días
Archivo de publicaciones
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት ይፋትና ጥሙጋ አውራጃ አባት አርበኞች ድል ተቀዳጁ ሰኔ 09/2018 ዓ.ም የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዓፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር ዓጼ ይኩኖ አምላክ ክፍለ ጦር ስር የሚያስተዳድሩት አባት አርበኞች በአጥቦ አይለብሴው ሚሊሻ ላይ ጥቃት ፈፀሙ። በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ በማጄቴ ዙሪያ የተደራጁት ከከነዓን ብርጌድ፣ ከውባተ አባተ ብርጌድ፣ ከምኒልክ ብርጌድ ፣ የተውጣጡ የአባት አርበኛ ቃኝወች ከኦሮሞ ብሔረሠብ ልዩ ዞን ጨፋ-ሮቢት ተቀምጦ አማራንና ኦሮሞን እያተራመሠ ከሚገኘው ሚሊሻ ጋር ከባድ ውጊያ አካሒዶ አንፀባራቂ ድል ተቀዳጀ። ይሕ የጠላት ሀይል ከአሁን በፊት የማጀቴ ና አካባቢዋን አርሶ አደር ሰብል በማቃጠልና የኢኮኖሚ ድቀት አላማ አስፈፃሚው ከብልፅግና የተሠጠውን ተልዕኮ በማስፈፀም የሚታወቅ መሆኑ ግልፅ ነው። ሆኖም ለማውደም፣ ለመዝረፍና ለማቃጠል አልሞ የዘመተው የጠላት ኃይል ከኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ሚሊሻ፣ ፖሊስና መከላከያ ሰራዊት ጥምረት በመፍጠር በአካባቢው አርሶ አደሮችና አባት አርበኞች ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት ለመሰንዘር ሲሞክር፡ ካሁን በፊት በዚህ ቀጠና ሰርጎ በመግባት 442 ከብቶችን ና 72 የጤፍ ፈጠጥ ጨምሮ በርካታ የሙዝ፣ የፓፓያ፣ የአቮካዶና የማንጎ አትክልቶችን ጨፍጭፎ እንደሔደው የሚቀናው መስሎት የተግተለተለው ሀይል ዛሬም ይህንኑ የተለመደ የጥፋት ተግባር ለመድገም በከፍተኛ ዝግጅት ቢመጣም፣ የአባት አርበኞቹ ጨፋ ደረስ ዘልቀው በመግባት አጥቅተውና መክተው ድላቸውን አጣጥመዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ትላንት ከማለዳው ጀምሮ እስከ ምሽቱ 1:00 ሰዓት ድረስ በቆየው አውደ ውጊያ የአካባቢው የአባት አርበኞች ባደረሱት ጉዳት በውል ያልታወቀ ሙትና ቁስለኛ አስከ ኬሚሴ ሆስፒታል እዳጨናነቁ በውስጥ መረጃዎቻችን አረጋግጠናል። አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ የአባት አርበኞች የፊት መስመር ኃይል ከኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን በቅርብ ርቀት ላይ ወደምትገኘው ጭሬ ቀበሌ እና ማጄቴ ቆላ አካባቢ ከፍተኛ ውጥረት ላይ ይገኛል። ​የማጄቴና የአካባቢው ማህበረሰብ "መሬታችንና ሰብላችን አይደፈርም!" በሚል ፅኑ እምነት እራሱን የመከላከል እና በጠላት ላይ ጠንካራ ክንዱን የማሳረፍ ታሪክ ሰርቷል። በቀጣይ የሚኖሩ አዳዲስ መረጃዎችንና ዝርዝር ዘገባዎችን ይዘን የምንመለስ ይሆናል። "ክብር ለትግሉ ሰማዕታት! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ​የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ጉድ ሳይሰማ መስከረም አይጠባ እንደተባለው የፋኖን ክንድ መቋቋም ያቃተው በኮለኔል ማቲዎስ ማዴቦ የሚመራው የአየር ወለድ ቅልብ ሰራዊት ቁጥራቸው 395 የሚሆኑ እማወራ እናቶችን ወደ ፋኖ የተቀላቀሉ ባሎቻችሁን አምጡ በሚል በግፍ መታሰራቸውን የአፄ አምደ ፅዮን ኮር ለዕዙ በላከው መረጃ ገለፀ። ሰኔ 09 ቀን 2018ዓ.ም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሀቤቴ አውራጃ የሬማ ከተማና አካባቢው ነዋሪዎች ላይ ከፍተኛ ግፍ በመፈፀም የሚታወቀው የብልፅግናው የግል ሰራዊት 101ኛ አየር ወለድ ክፍለጦር ቁጥራቸው 395 የሚሆኑ የአካባቢው ነዋሪዎች እማወራዎችን ከሚጠቡ ህፃናት ጋር በመያዝ ባሎቻችሁ 94,000ብር በልተው መሳሪያችንን ይዘው ፋኖን ተቀላቅለዋልና "ወይ እንዲመጡ አድርጉ! ካልሆነም በተሃዲሶ መልክ ደብረ ብርሃ ከተማ ወስደን የሰጠናቸውን ገንዘባችንን እና መሳሪያችንን ይመልሱልን!" በሚለው የዓመቱ ምርጥ ቀልድ ርካሽ ምክነያት ትላንት ሰኔ 08 ቀን 2018ዓ.ም እናቶችና በርካታ የሬማ ከተማ ነዋሪዎችን የፋኖ ደጋፊ ናችሁ በሚል በግፍ ማሰሩን የተበዳይ ቤተሰቦች መናገራቸውን የአፄ አምደ ፅዮን ኮር ገልጿል። በተለያዩ ምክነያት በአገዛዙ ቤት ቆይተው ስርዓቱ በአማራ ህዝብ ላይ የሚፈፅመውን ግፍ በውል ተረድተው በቆይታቸው ባለማወቅ በህዝባቸው ላይ ለፈፀሙት በደል ይቅርታ ጠይቀው በቀጠናው የሚገኘውን የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደ ፅዮን ኮር አካል የሆነውን የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦርን የተቀላቀሉ የቀድሞ የአገዛዙ የሚሊሻ አባላት ቁጥራቸው ከ650 በላይ መድረሱን ተከትሎ ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ የገባው የብልፅግናው ኃይል፣ በሬማ ከተማና ዙሪያውን ከፍተኛ የአፈሳ ዘመቻ ከፍቶ ነፍሰ ጡር እናቶችን፣ ህፃናት የሚያጠቡ እናቶችን እንዲሁም ዕድሚያቸው የገፋ አዛውንት እናቶችን በግፍ ሰብስቦ በሬማ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ ቅጥር ግቢ ውስጥ አስሮ እያሰቃየ ይገኛል ሲል ኮሩ የገለፀ ሲሆን ከታሰሩት እናቶች መካከል ዛሬ አዳራቸውን ከለሊቱ 9:00 ላይ ሁለት ነፍሰ ጡር እናቶች በደረሰባቸው ከፍተኛ እንግልት ታመው በከተማው ጤና ጣቢያ ለህክምና መግባታቸውን ኮሩ በመረጃው አረጋግጧል። አማራ በባህሉ በሴት ልጅ ላይ ክንዱን የማያነሳ ጨዋ ህዝብ በመሆኑ፣ ይሕን የመሰል ነውር በብልፅግናው አገዛዝ የተፈፀመውን የውንብድና ድርጊት የአካባቢውን ህዝብ ክፉኛ ያስቆጣ ሲሆን፣ የህዝብ ልጅ የሆነው ጀግናው ሰራዊታችን የአፄ ዳዊት ክፍለጦር አሃዶች ድርጊቱ ከተፈፀመ በሰዓታት ልዩነት ውስጥ በሬማ ከተማ ቅርብ ርቀት ላይ ተወርውረው በመድረስ በፈፀሙት የአፀፋ ርምጃ አንድ መንገድ መሪ ያልነቃ የሚሊሻ አባልና የ101ኛ አየር ወለድ ክፍለጦር ሁለቱ አባላቱ ሲገደሉ በርካቶቸን በሰርጎ ገብ ኦፕሬሽን ለከፍተኛ አካላዊ ጉዳት ማድረሱን ኮሩ የገለፀ ሲሆን የአገዛዙ ጀበና ሰባሪ ሰራዊት የፋኖን ክንድ መቋቋም ሲያቅተው በግፍ ያሰራቸውን እናቶቻችን በአስቸኳይ የማይለቅ ከሆነ የከፋ የአፀፋ ርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል።      ''ክብር ለትግሉ ሰማዕታት''    ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

የሰሚን ልብ የሚሰብር፣ የሰውን ልጅ ህሊና በእምባና በሃዘን የሚያናውጥ እውነተኛ ሰቆቃ!! ​ዕድሜዋ ገና 23 ነው። ገና የህይወትን ውበት ሳታይ፣ ለነገ ያነገበቻቸውን የብሩህ ተስፋ ህልሞች ሳታሳካ የጨለማ መጋረጃ የተጋረደባት የቁም ስቃይ ሰለባ መቅደስ ባንቴ ትባላለች። ሆኖም ​ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከምትወዳቸው ቤተሰቦቿ ከባህርዳር ተነስታ ወደ አዲስ አበባ ስትጓዝ፣ ልቧ በሰላም የመድረስና ሰርታ ራሷን የመቀየር ተስፋ ተሞልቶ የነበረችው መቅደስ ደብረወርቅ ከተማ ላይ ጉዞዋ በድንገት ወደ ጨለማ ተቀላጠፈ። የአብይ አህመድ ወንበር አስጠባቂ አራዊት ሰራዊት አባላት መኪናዋን አስገዳጅ በሆነ ሁኔታ አስቁመው በመኪናው ውስጥ የነበሩትን ወንድ ተጓዦች በሙሉ በዛቻና በዱላ እያሳደዱ ካባረሩ በኋላ፣ ይህችን ምስኪን እህታችንን ብቻዋን አስቀሯት። ማንም በሌለበት፣ ረዳት ባጣችበት በዚያ አስፈሪ ሰዓት፣ ዮሐንስ እና ፍልፍሉ የተባሉ የስርዓቱ ዙፋን አስጠባቂዎች ከመኪናው አውርደው ደብረወርቅ ከተማ ውስጥ ወደሚገኘው "አዝመራ ግሮሰሪ እየጎተቱ አስገቧት። በሩ በኃይል ተቆለፈባት። ​ከግንቦት 24 ቀን እስከ ዛሬ ሰኔ 08 ቀን 2018 ዓ.ም... ለተከታታይ 15 ረጅም ቀናትና ሌሊቶች! ይቺ የ23 ዓመት ንፅህት እህታችን በዚያች ጠባብና ጨለማ ክፍል ውስጥ ታስራ ሰነበተች። እነዚያ ሁለት አውሬዎች በእያንዳንዱ ቀንና ሌሊት እየተፈራረቁባት ሰብአዊ መብቷን ረገጡት፤ ክብሯን አረከሱት። የጭካኔያቸውን በትር አሳረፉባት። ​በእያንዳንዱ ሰከንድ የምታፈሰው ዕንባ፣ የምታሰማው የድረሱልኝ ጩኸት በግሮሰሪው ግድግዳዎች ላይ ተደፍኖ ቀረ። ሰሚ አልነበረም። የ23 ዓመት ሙሉ ክብሯ፣ የወጣትነት ውበቷና ተስፋዋ በነዚያ አውሬዎች እጅ ደቀቀ። ​በዚህም. ሰኔ 08 ቀን... እነዚያ ጨካኞች ሰብአዊነት የጎደለው ስሜታቸውንና አውሬነታቸውን በእህታችን ላይ ጨርሰው ካረኩ በኋላ፣ አካሏን አድክመውና ነፍሷን አቁስለው ሜዳ ላይ ጥለዋት ሄደዋል። መቅደስ ዛሬ ተለቃለች፤ ነገር ግን የቀድሞዋ መቅደስ አይደለችም። በቁሟ የሞተች፣ ተስፋዋ የተነጠቀና ክብሯ የተዘረፈባት ህያው በድን ሆናለች። ​ይህ በንፁሃን ዜጎቻችንና በእህቶቻችን ላይ እየተፈጸመ ያለው ታሪክ የማይረሳው ግፍ፣ ለአገዛዙ ማክተሚያ የቁም ምስክር ነው! ​የቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር የሕዝብ ግንኙነት ክፍል!!

#ቻው_ኮሎኔል‼️ በጀብደኛው ምኒልክ ዕዝ የተደመሰሰው ኮ/ል በዚህ መልኩ ስርዓተ ቀብሩ ተፈፅሟል። የአብይ አህመድ ጋሻ ጃግሬዎችን፣ምርኮኛ ጀኔራሎችን እና ኮረኔሎችን የማስወገድ ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል። አጀንዳችን በብልፅግና መቃብር ላይ የአማራን ህዝብ ህልውና ማረጋገጥ ነው። አማራዊ ትብብራችን ለህልውና ትግላችን ተቀዳሚ የትኩረት ማዕከላችን ሲሆን ስትራቴጅካዊ ግባችን ደግሞ ብልፅግናን ማስወገድ ነው። 08/10/2018 ዓ.ም

የስመጥሩው ጀግና (50 አለቃ አደም አሊ (አባ ናደው)) መታሰቢያ እለት፤ ሰኔ 8 ቀን 2017 ዓ.ም በእለተ እሁድ ማለዳ ታላቅ የጦር ሜዳ ጀብዱ ፈጽሞ በጀግንነት የተሰዋው እውነተኛው ታጋይ 50 አለቃ አደም አሊ (አባ ናደው) ሁሌም የሚታወስ የትግል አርማችን ነው:: የአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ በወርሀ መስከረም ለተከታታይ 16 ቀናት በጀግናው ታጋይ ስም ዘመቻ አውጆ በጠላት ላይ ከፍተኛ ሰብአዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ ማድረሱ ይታወቃል:: የ50 አለቃ አደም አሊ (አባ ናደው) ህያውነት የሚረጋገጠው በስሙ ሰራዊታችን ታሪክ መስራት ሲችል መሆኑ አያጠራጥርም:: በጦር ሰፈሩ ውስጥ ልጅ አዋቂው ይወደዋል፤ ያከብረዋል:: ጠላት እጅጉን ይፈራዋል:: 50 አለቃ አደም አሊ (አባ ናደው)) የሀገሩ ከራማ ነበር ሲሉ አባ ናደውን የሚያውቁት ይናገራሉ:: ይህም ብቻ አይደለም: እንዳው በስሙ እና በግርማ ሞገሱ ብቻ ጠላት ይንቀጠቀጥ ነበር ይላሉ:: በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ለጋምቦ ወረዳ 09 ቀበሌ አራጣ ዳገት ላይ 14 የጠላት ኃይልን ማርኮ ለልዩ ኃይል አዛዦች አስረክቦ ስለነበር በጀግንነቱ ተደንቀው ከልዩ ኃይል ጋር ተቀላቅሎ እንድዋጋ ፈቀዱለት:: በዚህ አጋጣሚ የልዩ ኃይል አባል ሆነ:: ወደ ሰሜን ወሎ ተጉዞ ቃሊም ላይ ምሽግ ሰብሮ የልዩ ኃይል አመራሮች የ50 አለቃነት ማዕረግ ሰጡት:: ከመሰዋቱ ጥቂት ደቂቃዎች ቀደም ብሎ ስናይፕር ከአጃቢው ተቀብሎ በመተኮስ ጠላትን አንገት ማስደፋት ችሎ ነበር:: ከእሱ ህልፈት በኋላ ማለትም ውሎ አድሮ ወደ ፋኖ የመጣ የጠላት ኃይል አባል ምስክርነቱን ሲሰጥ " ያኔማ እጅ ልንሰጥ ስንል ሰውዬው ተመታልን እሩሀችንም ተረፈ፤ መመታቱን አላወቅንም ነበር ውጊያውን አቁመው ጥለውን ሲሄዱ ነው የተረፍነው" ብሏል:: አባ ናደው የፋኖ ሰራዊት አባት ነበር:: ሰራዊትን በጥብቅ ድስፕሊን መገንባት ያውቅበታል:: ፋኖዎች ምሽግ እያዙበት ቦታ ድረስ በመሄድ ይጎበኝና አንድ የፋኖ አባል በልክ ምሽግ ይዞ ካልተኛ በእግሩ ይረግጠዋል:: ውጊያ የሚገባው ከሁሉም ቀድሞ ሲሆን የሚወጣው ደግሞ መጨረሻ ላይ ነው:: እሱ በቃ እንዲህ ነው:: የትግል ጓዶቹ: እረ እባክህ ከፊት አትግባ ሀገሩን ባዶ ልታስቀረው ነው ሲሉት እሺ ይላቸውና ተኩስ ሲጀመር ግን ዘሎ ከፊት ይገባል:: ምነው ሲሉት: አያስችለኝም ነው መልሱ:: የአባ ናደው ህልፈት ሲሰማ የወረዳ አመራሮች ደስታቸውን ሲገልፁና መከላከያዎችም ሲጨፍሩ አንድ የአድማ ብተና አባል በበኩሉ ቀጣፊ ቅዘናም ሁላ የጀግና ሞት አያስደስተኝም:: ሌላ ጠላት ቢመጣ እኮ አንድ በር ዘጊ ነበር:: እሱ ሞተ ብላችሁ ነው የምትተኩሱት" እንዳላቸው የውስጥ ምንጮች በወቅቱ ተናግረው ነበር:: አባ ናደው ለአማራ ህዝብ ህልውና መረጋገጥ ሲል ለአመታት በፅናት ቆሞ የታገለ እና ያታገለ ግንባር ቀደም ጀግና ነው:: ከደሴ ከተማ በስተምዕራብ ባለው ቀጠና ማለትም በለጋምቦ፣ መሀል ሳይንት፣ መካነሰላም፣ ከላላ፣ አማራ ሳይንት፣ ወግዲ እና አካባቢው ይንቀሳቀስ የነበረው የፋኖ ኃይልን ከሌሎች ጓዶች ጋር በመምራት መራር ተጋድሎ ሲፈጽም የነበረው አርበኛ 50 አለቃ አደም አሊ የሰሜን ምስራቅ ዕዝ 801ኛ ኮር በርካታ ሰራዊት፣ አድማ ብተና፣ ፓሊስ እና ሚሊሻን ላለፉት 2 አመታት በፅናት እና በጀግንነት በመፋለም እልቆ ቢስ የጠላት ኃይል አባላትን የደመሰሰ ቆፍጣና አርበኛ ነው:: 'ሁለተኛ አማራ አልሆንም፤ አትግደሉኝ" ያለችውን ህፃን የጭንቅ ድምፅ እያስታወሰ እና በየቦታው የሚገደለውን አማራ ደም ለማፈስ በማሰብ ጠብመንጃ ያነሳው አርበኛ 50 አለቃ አደም አሊ ከሰሜኑ ጦርነት ወዲህ በተጀመረው የፋኖ ትግል ሂደት አይደፈሬ የተባለውን በመድፈር በተደጋጋሚ ፊልም የሚመስሉ ጀብዱዎችን መፈፀም የቻለ ነው። ለአብነት ያክል በምዕራብ ወሎ ቀጠና ለጋምቦ ወረዳ ውስጥ በገነቴ ግንባር የሰሜን ምስራቅ ዕዝ 801ኛ ኮር 45ተኛ ክፍለ ጦር ሰራዊት ተሽከርካሪዎችን በማጋየት ተደጋጋሚ ድል የተቀዳጀ ደፋር ጦረኛ ነው። 45ተኛ ክፍለ ጦር በእነ ኮሎኔል ብርሀኑ እየተመራ አርበኛውን ለመደምሰስ ለጋምቦ ገብቶ ሰበር ሰካ ሲል ጀግናው አርበኛ አደም አሊ እና ሰራዊቱ ባደረሱበት ሰብአዊ ኪሳራ የተነሳ ለጋምቦ ወረዳ ከሚገኙት 3 ከተሞች አንዷ የሆነችው ጊምባ ከተማ ውስጥ የ45ተኛ ክፍለ ጦር ካምፕ የሆነው መካነየሱስ ግቢ ጀርባ የጅምላ መቃብር በመቆፈር በርካታ ኃይሉን ሲቀብር ከርሟል። የጠላት ኃይል በየጊዜው ለግዳጅ ሲወጣ የራሱን አስከሬን ጭኖ የሚመለሰው በጦር ጠበብቱ አርበኛ አደም አሊ የውጊያ ፍልስፍና እና ብቃት ነው:: 50 አለቃ አደም አሊ ወግዲ ወረዳ ጎረንጅ ቀጠና ውስጥ በሽርጥ ቦንብ ታቅፎ ወደ መከላከያ ሰራዊት ምሽግ በመጠጋት አስፈሪውን የጎለሌ ምሽግ መስበር የቻለው ይህ ደፋር አርበኛ በጨለማ ጭምር ባትሪ እያበራ በድፍረት ተስቦ ጠላትን በመጠጋት ቦንብ በመጣል ይታወቃል። በቦንብ ውርወራ ወደር የለሽ የተባለው አርበኛ አደም አሊ ከላላ ወረዳ ዋርጃ ተብሎ የሚጠራ ቀጠና ውስጥ ጠላት ከቦት ሳለ በጀግንነት ከበባ ሰብሮ በርካታ ጠላት ደምስሶ መውጣቱም ይታወሳል። በአማራ ሳይንት ወረዳ በለጡማ ግንባር፣ በመካነሰላም በኩል ደግሞ ሙዲለላ ታዳጊ ከተማ ላይ እንዲሁም በከላላ ወረዳ ውስጥ በደገር እና ወርቄ ቀጠናዎች የጠላትን አከርካሪ የሰበረ የጥምር ጦር መቅሰፍት መሆኑንም ልብ ይሏል። ገነቴ ከተማ አቅራቢያ የአድማ ብተናዎችን ምሽግ ከጥቂት አጃቢዎቹ ጋር ሆኖ በመስበር አድማ ብተናዎችን አፈር ያስጋጠ እና ከላላ ውስጥ ብስቁልል ላይ ከ4 ወረዳ የተውጣጣን ጠላት በመመከት ከ60 ያላነሰ ሰራዊት ደምስሶ በርካቶችን ያቆሰለ ነው። በጥቅሉ ለአማራ ህዝብ እና ለትግሉ የታመነ፣ ገንዘብ እና ጥቅም የማያታልለው እንዲሁም ፅኑ እና ቆራጥ አርበኛ ነው። ፅኑ እና ጀግናውን አርበኛ በዚህ መራር የትግል ሂደት መሀል ድንገት ብናጣውም ድል ያለ መስዋዕትነት ጦርነት ያለ ተኩስ አይሳካምና ዋናው ቁምነገር የእሱን ፈለግ ተከትሎ ጀግንነቱንም አስቀጥሎ አላማውን ማሳካት ስለሆነ እኛ የትግል ጓዶቹ እና የስጋ ወንድሞቹ ለዚህ ሁሌም እንደታጠቅን በፅናት እንቆማለን ጦርነቱንም በድል እንወጣዋለን የሚለው የሁልጊዜም ቃላችን ነው:: 50 አለቃ አደም አሊ በንፅህና እና በጀግንነት ታግሎ ያረፈ ባለ ታሪክ ነው:: ጀግንነትን እና ለሀቅ ኖሮ በሀቅ መሰዋትን ያስተማረን የትግል አባታችን ምንም እንኳን በአካል ከመካከላችን ባይኖርም ስሙ የማይፋቅ የልብ ማህተም እና የማይደበዝዝ የደም አሻራ ሆኖ ዝንታለም ሲታወስ ይኖራል::

በአማራ ደም ፤አማራነት ይቅደም!! ወታደራዊ የስርፀት ስራችን ተጠናክሮ ይቀጥላል። መራራውን የአማራ ህዝብ ተጋድሎ በድል ለመቋጨት በሚደረገው ድርብርብ አማራዉ ሃይላችንን በበቂ ሁናቴ ማደራጀት፣መሰብሰብ፣ማብቃት እና የፀና ስራዊት መፍጠር የግድ ነው። ዓላማውን ጠንቅቆ የሚያውቅ ሃይል ስትራቴጅካዊ ግብ እና መድረሻውን ያውቃል። አማራዊ አቅማችንን በማሰባሰብ እና ዳግም በማንነቱ የሚጨፍጨፍ ህዝብ እንዳይኖር የጀመርነው አብዮት በአማራዉ ተጋድሏችን አሸናፊነት ይቋጫል። ዝንታለም አማራ ወይራው አማራ

ወንድማችን ተዋቸው ትግሉ ከተጀመረ ጀምሮ. ህዝቡን በማንቃት ደረጃ ትልቅ ስራ እየሰራ ይገኛል ኪነት አንዱ የውጊያ መሳሪያ ነው ወንድማችን በርታልን በቅርብ ቀን ዋርካው አማራ የተሰኘውን ነጠላ ዜማ ይ
ወንድማችን ተዋቸው ትግሉ ከተጀመረ ጀምሮ. ህዝቡን በማንቃት ደረጃ ትልቅ ስራ እየሰራ ይገኛል ኪነት አንዱ የውጊያ መሳሪያ ነው ወንድማችን በርታልን በቅርብ ቀን ዋርካው አማራ የተሰኘውን ነጠላ ዜማ ይለቃል አበረታቱት!!

ወራሪው ቡድን ካንፕ አድርጓቸው የነበሩ የጤና ተቋማት በአዲስ እና በጥገና መልክ እየተሰሩ ነው!! 🕯🕯🕯🕯🌷🌷🕯🕯🕯🕯 በሜጀር ጀኔራል ተሾመ አበባው የሚመራው 204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር
+2
ወራሪው ቡድን ካንፕ አድርጓቸው የነበሩ የጤና ተቋማት በአዲስ እና በጥገና መልክ እየተሰሩ ነው!! 🕯🕯🕯🕯🌷🌷🕯🕯🕯🕯 በሜጀር ጀኔራል ተሾመ አበባው የሚመራው 204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር  ዛሬም እንደ ትላንቱ ህዝባዊነቱን እያሳየ ነው!! ከዚህ በፊት ወራሪው እና የግለሰብ ወንበር ጠባቂው  መከላከያ ተብየ ካንፕ አድርጎት የነበረው የመቀጠዋ ወረዳ የአጊሳ ጤና ጣቢያ ብዙውን ነገር በማውደም ጸረ አማራነታቸውን አሳይተው ነበር ። ነገር ግን የትግላችን አካል የሆነውን ማህበራዊ አገልግሎት መስጫ ተቋማትን መጠበቅ; መንከባከብ; ደህንነታቸውን መጠበቅ; አቅም በፈቀደ ድጋፍ ማድረግ; ማሰራት; ማስጠገን እና የመሳሰሉትን ተግባራት የእቅዳችን አካል በማድረግ በአጊሳ ጤና ጣቢያ የመጸዳጃ ቤት; የእናቶች ማረፊያ እና ሌሎች በአዲስ እና በጥገና እንዲሰራ ለአገልግሎትም ምቹ እንዲሆን እያደረግን እንገኛለን!! ከዚህ በፊት የትምህርት; የመንገድ እና ሌሎች መሰረተ ልማቶችን መደገፋችን የሚታወስ ነው "በእሳት የተፈተነው በተግባር የሚገለጠው 204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር"!! አፋብን ጎጠግበላይ ዕዝ 204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል!!

የአማራ ክልል ሰላም ካውንስል ነኝ የሚለው የፖለቲካ ደላላ ቡድን ገና እንደተመሰረተ ተነቅቶበት መፈራረሱ ይታወቃል። ብልፅግና ቤት አጀንዳ ሲጠፋ ከስድስት ወር በፊት ናይሮቢ ላይ ከፋኖ ተወካዮች ጋር
የአማራ ክልል ሰላም ካውንስል ነኝ የሚለው የፖለቲካ ደላላ ቡድን ገና እንደተመሰረተ ተነቅቶበት መፈራረሱ ይታወቃል። ብልፅግና ቤት አጀንዳ ሲጠፋ ከስድስት ወር በፊት ናይሮቢ ላይ ከፋኖ ተወካዮች ጋር ተነጋግሬ ነበር የሚል ዜና አሰርቷል። የአማራ ክልሉ ኦባሳንጆ😂 ለመሆን እየጣረ ያለው የያህራድ እና ጓደኞቹ ስብስብ የፕሮጀክት ብር ከማወራረድ ያለፈ ሚና እንደሌለው ገና ከጥንስሱ ገልፀናል። በህዝብ ደም ላይ እያላገጡ መኖር አይቻልም። መሬት ላይ ያለው ሐቅ ሌላ ነው። አብይ አህመድ የብልፅግናን "የፓርክ አብዮት" የሚጠብቅ አብዮታዊ ዘብ እያቋቋመ ነው። በሹማ አብደታ ኮማንዶ፣ በይልማ መርዳሳ ጀቶች፣ በኢምሬቶች አኪንች ድሮኖች፣ በብርሃኑ ጁላ እልፍ እግረኛ መተማመን ተስኖት ራሱ የሚመራው ኃይል እያሰለጠነ ነው። አርበኛ አስረስ ማረ ዳምጤ

የድል ዜና !! መሀመድ ቢሆነኝ ኮር አስቴ ጎማ ተራራ ክ/ጦር በመኮይ ከተማ በሚገኙ የብልፅግና ኃይሎች ላይ መብረቃዊ ጥቃት አደረሰ !! ሰኔ 08 ቀን 2018 ዓ.ም። በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፣ በመሃመድ ቢሆነኝ ኮር ስር የሚንቀሳቀሰው ጀግናው የአስቴጎማ ተራራ ክፍለጦር፣ በይፋት አውራጃ አንፆኪያ ገምዛ ወረዳ መኮይ ከተማ መደበቂያቸውን ባደረጉ የብልፅግና የካድሬ፣ የሚሊሻ፣ የፖሊስና የኮማንዶ ስብስቦች ላይ የተቀናጀ መብረቃዊ ጥቃት ተፈፀመ። ክፍለጦሩ በከተማዋ በሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ ላይ ባደረገው የሚካናይዝድ ሞርተር ጥቃት፣ የፀረ-አማራው የብልፅግና ስብስብ አባላት የሆኑ 10 ታጣቂዎችን ድባቅ መምታት ችሏል። ከደረሰባቸው ከፍተኛ ጉዳት የተነሳም 4ቱ በአሁኑ ወቅት በደሴ ሪፈራል ሆስፒታል በጽኑ ሕክምና ላይ እንደሚገኙ ታውቋል። የብልፅግና አስተዳደር ላለፉት ሦስት ዓመታት ወደ ወታደራዊ ካምፕነት ቀይሮት በነበረው በመኮይ ከተማ የሙያና ቴክኒክ ማሰልጠኛ ኮሌጅ ውስጥ መሽጎ በነበረው የልዩ ዘመቻ አየር ወለድ ኮማንዶ ሰራዊት ላይም ወታደራዊ  ኢላማውን በጠበቀ መልኩ የሞርተር መብረቃዊ ጥቃት ተፈጽሟል። በዚህ ጥቃት ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ በርካታ የአገዛዙ ታጣቂዎች ላይ ከፍተኛ የአካልና የቁሳቁስ ጉዳት መድረሱ ተረጋግጧል። ክብር ለትግሉ ሰማዕታት! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!!

የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ስር ባሉ አካባቢዎች መጀመሩ ተገለጠ፤ ለ8ኛ ክፍል ፈተናም ዝግጅት መጠናቀቁ ተመልክቷል ​ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት በአሳምነው ዕዝ ቁጥጥር ስር በሚገኙ ሁሉም አውራጃዎችና ቀጠናዎች የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ያለምንም የፀጥታ ስጋት በሰላም መሰጠት መጀመሩን የዕዙ የማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ አስታወቀ። መምሪያው በሸዋ ጠቅላይ ግዛት በሁሉም አካባቢዎች የትምህርት መማር ማስተማር ሂደቱ በአግባቡ እንዲቀጥል ሲደግፍ መቆየቱን ጠቅሶ፤ በአሁኑ ወቅትም ተማሪዎች በአማራ ህዝብ ላይ ከተከፈተው ጦርነት ጎን ለጎን ከትምህርት ገበታቸው ሳይስተጓጎሉ ክልላዊ ፈተናቸውን መውሰድ እንዲችሉ ሁኔታዎችን ማመቻቸቱን ገልጿል። ​በተያያዘ ዜና፣ በዚህ ሳምንት ሐሙስ ዕለት ለሚጀመረው የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ዕዙ ከፍተኛ ዝግጅት ማድረጉ ተገልጿል። ፈተናውን የሚያስፈትኑ መምህራን ሙሉ በሙሉ ስጋት በሌለው መንፈስ ስራቸውን ማከናወን እንዲችሉ አስፈላጊው ሁሉን አቀፍ ድጋፍና ጥበቃ እንደሚደረግላቸውም የማህበራዊ ጉዳይ መምሪያው በሰጠው ማረጋገጫ አመልክቷል። ክብር ለትግሉ ሰማዕታት ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም

አገዛዙ ያወደማቸው የት/ት ተቋማትን መልሶ የመጠገን ስራ ተሰረቷል!! 64ኛ ክ/ጦር ሰኔ 08/2018 ዓ.ም ሰኔ 08/2018 ዓ.ም በእነማይ ወረዳ ስር እየሱስ ቀበሌ በአገዛዙ ሰራዊት የወደሙ የት/ት ተቋማትን በ64ኛ ክ/ጦር እና የወረዳ ጊ/መንግስት አመራሮች ከቀበሌው ማህበረሰብ ጋር የመልሶ ጥገና ስራ ተሰረቷል። 64ኛ ክ/ጦር ከአማራ ህዝብ የህልውና ትግል ጎን ለጎን በመሰረተ ልማት ስራዎች ህዝባችንን ተጠቃሚ ለማድርግ በገጠር ቀበሌዎች ተጀምረው የነበሩ በገጠር የንፁህ ውሃ መጠጥ ፕሮጀክቶች፣ ከኦል መሬት ህግ ማስከበር፣ የተዘጉ መንገዶችን እና በአገዛዙ ሰራዊት የወደሙ ተቋማት ላይ ማህበረሰቡን እያወያዩ እየሰራ ይገኛል። የትጥቅ ትግላችን ለህልውናችን! የመሰረት ልማታችን ለህዝባችን ተጠቃሚ እናደረጋለን!!🙏🙏🙏 አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!! ሰኔ 08/2018 ዓ.ም አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት