ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
Ir al canal en Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
Mostrar más2 945
Suscriptores
+1624 horas
+127 días
+37730 días
Archivo de publicaciones
አገዛዙ ያወደማቸው የት/ት ተቋማትን መልሶ የመጠገን ስራ ተሰረቷል!!
64ኛ ክ/ጦር ሰኔ 08/2018 ዓ.ም
ሰኔ 08/2018 ዓ.ም በእነማይ ወረዳ ስር እየሱስ ቀበሌ በአገዛዙ ሰራዊት የወደሙ የት/ት ተቋማትን በ64ኛ ክ/ጦር እና የወረዳ ጊ/መንግስት አመራሮች ከቀበሌው ማህበረሰብ ጋር የመልሶ ጥገና ስራ ተሰረቷል።
64ኛ ክ/ጦር ከአማራ ህዝብ የህልውና ትግል ጎን ለጎን በመሰረተ ልማት ስራዎች ህዝባችንን ተጠቃሚ ለማድርግ በገጠር ቀበሌዎች ተጀምረው የነበሩ በገጠር የንፁህ ውሃ መጠጥ ፕሮጀክቶች፣ ከኦል መሬት ህግ ማስከበር፣ የተዘጉ መንገዶችን እና በአገዛዙ ሰራዊት የወደሙ ተቋማት ላይ ማህበረሰቡን እያወያዩ እየሰራ ይገኛል።
የትጥቅ ትግላችን ለህልውናችን! የመሰረት ልማታችን ለህዝባችን ተጠቃሚ እናደረጋለን!!🙏🙏🙏
አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!!
ሰኔ 08/2018 ዓ.ም
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት
ተጠናክሮ በቀጠለው የብልፅግናው ሰራዊት ፍልሰት ዛሬም ፲አለቃ ገለታ አብዲሳ የተባለው የ103ኛ ኮማንዶ ክፍለጦር ጋንታ መሪ አንድ ዘመናዊ ስናይፐር በመያዝ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደ ፅዮን ኮር የ7ለ70 ክፍለጦርን መቀላቀሉን ኮሩ በላከው መረጃ አስታውቋል።
አፋብን ሸ/ጠ/ግ/አ/ዕዝ
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ያወጣውን የምህረት አዋጅ ተቀብሎ ከሁለት ወር በፊት ፋኖን በተቀላቀለው የትግል ጓደኛው አማካኝነት ስለ ፋኖ እውነተኛ ማንነት የተነገረው የኦሮሞ ብሔር ተወላጁ ፲አለቃ ገለታ አብዲሳ አንድ ዘመናዊ ስናይፐር ከ95 በላይ ተተኳሽ በመያዝ ከነ ሙሉ ትጥቁ ፋኖን ሲቀላቀል በአፄ አምደ ፅዮን ኮር 7ለ70 ክፍለ ጦር አመራሮች ስለተደረገት አቀባበል ላቅ ያለ ምስጋናውን ያቀረበ ሲሆን ወቅታዊ የአገዛዙ ሰራዊት ግዳጅን የመፈፀም አቅሙ እንደተዳከመና በሰራዊቱ ውስጥ ከፍተኛ የእርስ በእርስ መከፋፈል መፈጠሩን ገልጿል።
''ክብር ለትግሉ ሰማዕታት''
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
ሰኔ 08/2018ዓ.ም
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር በሁሉም ቀጠናዎች የ 6ኛ ክፍል ፈተናዎችን አስጀምሯል።
ትምህርት የግለሰቦችን ብቻ ሳይሆን አንድን ማህበረሰብ በዕውቀትና በሥነ-ምግባር ታንጸው ለአገራቸውና ለወገናቸው የሚጠቅም አዎንታዊ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ከማስቻሉም በላይ፣ ማህበራዊ ፍትህንና ኢኮኖሚያዊ ለውጥን ለመገንባት ቀዳሚውን ሚና ይጫወታል። በመሆኑም ተቋማችን አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር የበጀት ዓመቱን የትምህርት መማር ማስተማር ስርዓት በሰላማዊ መንገድ እንዲከወን የበኩሉን ድርሻ በመወጣት በትውልድ ላይ የሚሰራ እውቀትና ክህሎት የነገዋን አገር በጽኑ መሰረት ላይ ማቆም መሆኑን በመረዳት፣ በማንኛውም አስገዳጅና ፈታኝ ሁኔታዎች ውስጥም ሆኖ የትምህርት ሂደትን ሳያቋርጡ ማስቀጠል የነጻነትና የጀግንነት ክብር አድርጎ ይወሰዳል።
በመሆኑም ይህንን የትምህርትን ታላቅ ፋይዳ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር ስር በሚገኙ በሁሉም ቀጠናዎች የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በስኬት ተጀምሯል።
ይኸው የ2018 በጀት ዓመት ማጠቃለያ ፈተና ተማሪዎች በዓመቱ ውስጥ የቀሰሙትን ዕውቀትና ያዳበሩትን ብቃት የሚመዝኑበት ታላቅ መድረክ ነው። ፈተናው በተሟላ የጸጥታ ጥበቃና በከፍተኛ ጥንቃቄ መጀመሩ፣ የወደፊት አገር ተረካቢ የሆኑ ወጣቶች ያለምንም ስጋትና እንግልት የደከሙበትን የዕውቀት ውጤት እንዲያገኙ በማድረግ ረገድ ትልቁ እቅዳችን የተሳካበት ማሳያ ነው።
በመጨረሻም፣ ይህ የ6ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና በሁሉም ቀጠናዎች እንዲጀመር የተደረገበት የተቀናጀ ጥረት፤ ለኮራችን ትልቅ ስኬት በግልጽ ያሳያል። ኮራችን ለአካባቢው ማህበረሰብ ደህንነትና ለነገው ትውልድ እጣ ፈንታ የቆመ መሆኑን ያረጋገጠበት ሲሆን፣ ፈተናው በሰላም ተጀምሮ በስኬት እንዲጠናቀቅ ሁሉም ክፍለ ጦሮቻችን፣ መምህራን፣ ወላጆችና መላው ማህበረሰብ እያደረጉት ያለው ድጋፍ ሊበረታታ ይገባል።
ይህ ሂደት ተማሪዎች በቀጣይ የትምህርት ደረጃቸው ከፍ ያለ ስኬት እንዲያስመዘግቡና ኩራት እንዲሆኑ ትልቅ መነሳሳትን ይፈጥርላቸዋል።ፈተናውም በሰላም ተጀምሮ በሰላም እስኪጠናቀቅ ድረስ አሰፈላጊውን የጸጥታና የጥንቃቄ ስራዎችን አጠናክረን እንቀጦላለን።
ድል ለአማራ ህዝብ !!!
ድል ለአማራ ፋኖ !!!
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር ቃል አቀባይ ክፍል!!!
የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት ዓሳምነው ዕዝ ዓፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር የነጎድጓድ ክፍለ ጦር ሁለት አባት አርበኞች የአብይ አህመድ ሰራዊት ድባቅ መቱት!!
መንዲዳ — ሰኔ 08/2018 ዓ/ም
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ በአፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር የነጎድጓድ ክፍለ ጦር ቁጥጥር ስር በምትገኘው በመንዲዳ ከተማ መሽጎ የሚገኘው የአገዛዙ ጦር፣ ትናንት ምሽት በደረሰበት ከፍተኛ ድንጋጤ ሌሊቱን ሙሉ በውር ድንብር ሲተኩስ ማደሩ ታወቀ።
በዚህም በትናንትናው ዕለት በባሶና ወረና ወረዳ "እሑድ ገበያ" በተባለ ቦታ፣ መነሻውን ከመንዲዳ ካደረገው የኦሮሚያ ልዩ ኃይል፣ መከላከያ እና ሚሊሻ ጥምር ጦር ጋር የተጋፈጡት ሁለት አባት አርበኞች ነበሩ። ጀግኖቹ አስቀድሞ በደረሳቸው መረጃ መሠረት በወሰዱት የደፈጣ ጥቃት እርምጃ፣ በቁጥር በውል ያልታወቁ የጠላት ኃይሎችን ሙትና ቁስለኛ አድርገዋል።
ይህንን ተከትሎ "ፋኖ መጣብኝ" በሚል ፍርሃትና ጥርጣሬ ውስጥ የወደቀው የብልፅግና ጦር፣ ከምሽቱ 02:30 እስከ ሌሊቱ 10:00 ሰዓት ድረስ በከባድ መሣሪያ እሑድ ገበያ አካባቢን ሲደበድብና ሲተኩስ ማደሩን የአካባቢው አባት አርበኞች አረጋግጠዋል።
በሌላ ዜና በሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዘርያዕቆብ አንደኛ ኮር ስር የሚንቀሳቀሰው ስመ-ጥር የብሩኬ ደምሴ ክፍለ ጦር፣ ለአዲሱ የነፃነት ምዕራፍ የሚመጥን ታሪካዊና ጥልቅ ግምገማ አጠናቀቀ። ሆኖም ክፍለ ጦሩ በነበረው ጠንካራ ግምገማ ላይ መሠረት በማድረግ፣ ለቀጣዩ ወሳኝ ትግልና ግዳጅ አቅሙን ይበልጥ የሚያጎለብት ታላቅ የአመራር ሪፎርም (ሽግግር) አድርጓል።
ይህንን ተከትሎም መላው የክፍለ ጦሩ አባላትና አመራሮች መንፈሳዊና ወታደራዊ ተሃድሶ በማድረግ፣ ማንኛውንም የጠላት ኃይል ለመደምሰስና የተጣለባቸውን ታሪካዊ ኃላፊነት ለመወጣት ሙሉ በሙሉ ዝግጁ መሆናቸውን በይፋ አውጀዋል። የብሩኬ ደምሴ ክፍለ ጦር አመራሮች እንደገለጹት፣ ይህ አዲስ የሪፎርም እና የተሃድሶ ምዕራፍ ለጠላት መርዶ፣ ለሕዝቡ ደግሞ የድል ዋስትና የሚሆን አዲስ የትግል ወጤት የሚያስመዘግብ መሆኑን በአንክሮት ገልፀዋል።
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!!!
ህልዉናችን በተባበረ ክንዳችን!!!
የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግኑኝነት መምሪያ!!!
በስቦ ማስከዳት የመከላከያ አመራሮችና አባላት ስናይፐርና ክላሽ በመያዝ ምኒልክ ዕዝን ተቀላቅለዋል!
መነሻቸውን ከላስታ ወረዳ ብልባላ ከተማ እና ከዋግኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን አዚላ ያደረጉ ሁለት የመከላከያ አመራሮችና ሁለት መሠረታዊ ወታደሮች በድምሩ አራት የአገዛዙ ሰራዊት አባላት አገዛዙን በመቃወም ሰኔ 08 ቀን 2018 ዓ/ም የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር 30ኛ ክፍለ ጦር ቃኝዎችን ተቀላቅለዋል።
የተቀላቀሉ አባላትም:-
1. ሃምሳ አለቃ መኩሪያው አባትይሁን ከ38ኛ ክፍለ ጦር መሐንዲስ
2. አስር አለቃ ይረፍ ደምሴ ከ38ኛ ክፍለ ጦር መሐንዲስ
3. ናትናኤል አቤል የሻለቃ ኦርዲናንስ
4. መሰረታዊ ወታደር ደረጀ አሸናፊ ሲሆኑ
👉 አንድ ጥቁር ስናይፐር
👉 ሦስት ጥቁር ክላሽ
👉 አንድ ሀይተር መገናኛ
👉 ሦስት የስናይፐር ካዝና
👉 አራት የደረትና የወገብ ትጥቅ
👉 420 የክላሽ ተተኳሽ
👉 56 የስናይፐር ተተኳሽ
👉 ስምንት የእጅ ቦምብ በመያዝ ተቀላቅለዋል።
የመከላከያ አባላቱም ፋኖን ሲቀላቀሉ የ30ኛ ክፍለ ጦር ፋኖ ከፍተኛ አመራሮችና አባላት ደማቅ አቀባበል ያደረጉላቸው ሲሆን በተደረገላቸው አቀባበልም ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀዋል።
አባላቱ አያይዘውም የብልፅግና መንግስት ሃገራችን ኢትዮጵያን ወደ መቀመቅ እየከተታት መሆኑን ዘግይተን ብንረዳውም አሁንም አልረፈደምና የአማራን ህዝብ ለመካስ ብሎም ኢትዮጵያን ከመፍረስ ለማዳን ከፋኖ ጎን ሆነን የስርዓቱን ግብዓተ መሬት እናፋጥናለን ሲሉ ቃላቸውን ሰጥተዋል።
በአንድ ወር ጊዜ ውስጥም በአውደ ውጊያ ከተማረከው ውጭ ሦስት ጥቁር ስናይፐር፣ ከ20 በላይ ጥቁር ክላሽና ሌሎች ትጥቆች ከመከላከያ በመውጣት ወደ 30ኛ ክፍለ ጦር ካዝና ገቢ ሆኗል ሲል የ303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃውን አድርሷል ።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያ እና ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ!!
ሰኔ 8/2018ዓ.ም
በሐረጎ የተከሰተው አስደንጋጭ አደጋ፡
የ28 ወገኖቻችን ሕይወት በአሰቃቂ ሁኔታ አለፈ
ዛሬ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ማለዳ ላይ ከደሴ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበረ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ በደሴ እና በኮምቦልቻ ከተሞች መካከል ልዩ ስሙ «ሐረጎ» በተባለው አካባቢ በደረሰበት ከባድ የትራፊክ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት ወዲያውኑ አልፏል።
አውቶቡሱ በድንገት መንገዱን ስቶ ወደ 100 ሜትር በሚጠጋ ጥልቀት ባለው ገደል ውስጥ በመግባቱ ነው ይህ አሰቃቂ አደጋ ሊከሰት የቻለው። በጉዞው ላይ በነበሩ ሌሎች በርካታ መንገደኞች ላይም ቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።
በአሁኑ ወቅት ከአደጋው የተረፉትን ተጎጂዎች በፍጥነት ወደ ሕክምና ተቋማት ለማድረስ ከፍተኛ የነፍስ አድን ርብርብ እየተደረገ እንደሚገኝ ፖሊስ አስታውቋል። ይህንን ልብ ሰባሪ አደጋ ያስከተለውን ትክክለኛ መንስኤ ለማወቅም ፖሊስ ጥብቅ ምርመራ እያካሄደ ይገኛል።
ለሟች ቤተሰቦችና ወዳጅ ዘመዶች መጽናናትን፣ ለተጎዱትም ፈጣን ማገገምን እንመኛለን።
+3
ተወዳጁ እና አንጋፋው የአምሓርኛ ባህላዊ ሙዚቀኛ ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው (ሰሜ ባላገሩ) ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው የተለያዩ ባህላዊ እና ሌሎች ይዘቶቸ ያሏቸው የሙዚቃ ሥራዎችን ለአድማጭ ተመልካች አበርክቷል፡፡
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ባለትዳር እና የአራት ልጆች አባት ነበር።
ነፍስ ይማር😪
ሜ/ጀኔራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ስር ጉና ክፍለ ጦር በሚያስተዳድራቸው ቀጠናዎች የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ማጠቃለያ ፈተናዎች ያለምንም የፀጥታ ስጋት በስኬት ሰላማዊ በሆነ መንገድ መጀመራቸው ተገለፀ።
=======================
ሰኔ 8/10/2018/
➜ ፈተናው በሰኬት እንዲጀመር የተደረገበትን ዝርዝር ሁኔታና ሂደት እንደሚከተለው በአጭሩ ተዳሷል።
፩. የፈተና ቁሳቁስ ስርጭትና የፀጥታ ጥበቃ
የፈተና ወረቀቶችና ተያያዥ ቁሳቁሶች ያለምንም በጓተትና የፀጥታ ስጋት ወደየፈተና ጣቢያዎች ከፍተኛ ጥንቃቄ በተላበሰ መልኩ እንዲደርሱ ተደርጓል።
ጉና ክፍለ ጦር በሚያስተዳድራቸው ዋና ዋና መዳረሻዎች ማለትም ፦ በአንዳቤት ወረዳ፣ በእስቴ ወረዳ፣በስማዳ ወረዳ፣ በፋርጣ ወረዳ እንዲሁም የዞኑ ዋና ከተማ ደብረታቦር ጨምሮ የሚገኙ የፈተና ጣቢያዎች ሙሉ ቁሳቁስ በጀግናው ፋኖ ሙሉ እጀባና ጥበቃ ተደርጎላቸው በሰላም ደረሰዋል።
ፈተና ከመጀመሩ በፊት የነበሩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችም ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቁ መቆየታቸው እና ፋኖ ትምህርት እንዲጀመር መፍቀዱም የሚታወስ ነው።
፪. የፋኖ ፣የተማሪዎች፣ የወላጆችና የመምህራን ቅንጅት
በታሪክ አጋጣሚ ለየት የሚያደርገው የዘንድሮው የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ያለምንም "ህፀፅ" እንዲጀመር በየ ቀጠናው ያለው ጀግናው ፋኖ የአንበሳውን ድርሻ አበርክቷል።
ይህ ስኬት ሊመዘገብ የቻለው ፋኖ ከተማሪዎች፣ ከወላጆች እና ከመምህራን ጋራ ባለፉት ተከታታይ ወራቶች በተሰሩ ስልታዊ ውይይቶች በመሆኑ፣ ተማሪዎች በስነ- ልቦና ሳይሸበሩ፣ በትምህርት ገበታቸው ላይ ብቻ ትኩረት አድርገው ውጤታማ እንዲሆኑ እና ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ጉና ክፍለ ጦር አይተኬ ሚና ነበራት።
በአጠቃላይ በአሁኑ ሰዓት ጉና ክፍለ ጦር በፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ መምህር አርበኛ አማረ እንደግ እየተመራ ሁሉም ስራ አስፈፃሜ ፣በስሯ ያሉት ከአምስት ብርጌዶች እና የወረዳ ጊዜያው የፋኖ መንግስት የተውጣጣ ግብር ሃይል የስራ ስምሪት በመስጠት ፈተናዎች በሰላምና በመረጋጋት እየተሰጡ የሚገኝ ሲሆን፣ ይህም የፀጥታና ክትትል ስራ ፈተናው ሙሉ በሙሉ እስኪጠናቀቅ ደረስ የሚቆይ ሲሆን ፣ በተፈጠረላቸው አስተማማኝ ሰላም ምክንያት ተማሪዎች አቅማቸውን እንዲያሳዩ ትልቅ በር ከፍቷል።
ሜ/ጀኔራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ጉና ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ
መምህር ያሬድ ገደፍው✍️
+5
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር በሚያስተዳድራቸው 5 ወረዳ ትምህርት ቤቶች 6ኛ ክፍል ፈተና እንዲህ አስጀምሯል
የብልፅግና ቤት በየቀኑ እየፈራረሰ ነው 3 ፓራ ኮማንዶ አባላት እና 1 የመከላከያ አባላት 201ኛ ኮር 74ኛ ክፍለ ጦርን ተቀላቅለዋል።
==========================
.....ሰኔ 08/2018 ዓ.ም
ከደብረ ወርቅ ከተማ በመውጣት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 74'ኛ ክፍለ-ጦርን ተቀላቅለዋል ።
1 : ፈንታ ምትኩ = ፓራ ኮማንዶ
2 : ጎዴ ዘሪሁን = ፓራ ኮማንዶ
3 : ይህነው ተሜ = ፓራ ኮማንዶ
4 : ዘውዱ አብየ = መከላከያ ሲሆኑ አባሉ ምንም አይነት የመዋጋት ስነ ልቦና የሌለው መሆኑን ተናግረዋል። በክፍለ ጦር አመራሮቻችን በጀግና አቀባበል ተደርጎላቸዋል ።
ጊዜው አልረፈደም አሁንም ወደ ማንነታቹህ ወገኖቻቹህ ኑ ተመለሱ
የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
የአማራ ህዝብ የትጥቅ ትግል ያለበትን ወቅታዊ ሁኔታ እና በቀበሌ የህዝብ አስተዳደር ስራዎችን ላይ ሰፊ ውይይት ተካሂዶል!!
64ኛ ክ/ጦር ሰኔ 07/2018 ዓ.ም
በእነማይ ወረዳ ዘብች/እየሱስ ቀበሌ ከሚገኙ የማህበረሰብ ክፍል በአማራ ህዝብ የህልውና ትግል ወቅታዊ ሁኔታዎች እና በህዝብ አስተዳደር ስራዎች ላይ ሰፊ ውይይት ተካሂዶል።
የ64ኛ ክ/ጦር እና የእነማይ ወረዳ ጊ/መንግስት አመራሮች በመሩት የስብሰባ መድርክ ስለ አማራ ህዝብ የህልውና ትግል ያለበት ወቅታዊ ሁኔታ ሰፊ ግንዛቤ በመስጠት በቀበሌ ፍትህ አሰጣጥ፣ የቀበሌ መልካም አስተዳደር ፀጥታ፣ ህገወጥ የኦል መሬት ማስከበር፣ የፋይናስ እና ሎጀስቲክ አሰባሰብ በተመለከተ በሰፊው በመወያየት ለቀበሌ ጊ/መንግስት አቅጣጫ ተሰጥቷል።
በውይይት መድረኩ የተገኙት ማህበረሰብ እንደተናገሩት የአብይ አህመድ አምባ ገነን አገዛዝ በአማራ ህዝብ ላይ ከፍተኛ የሆነ በደል እና ጭቆና እያደረሰ ቢገኝም ይህንን አምባ ገነን ስረዓት ለመገርሰስ መስዋትነት እየከፈለ የሚገኘው የአማራ ፋኖ ጎን እንደሆኑ ተናግረዋል።
አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!
ሰኔ 07/2018 ዓ.ም
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት
