es
Feedback
ጠበቃ አዳነ በዛብኽ!!!

ጠበቃ አዳነ በዛብኽ!!!

Ir al canal en Telegram

በዚህ ቻናል፡- የተለያዩ የፌደራልና የክልል ሕግጋት፣ የሰበርና የፌዴሬሽን ም/ቤት ውሳኔዎች እንዲሁም የተመረጡ ሕግ ነክ ጽሑፎች ይቀርቡበታል

Mostrar más
377
Suscriptores
+124 horas
+47 días
+830 días
Archivo de publicaciones
በአጠቃላይ የኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 542 ሌላ ሰው ራሱን እንዲያጠፋ ማነሳሳትን ወይም መርዳትን ወንጀል ለማድረግ የተዘረጋ ሥርዓታዊ እና የሕግ ንድፈ-ሐሳብን የተከተለ መሣሪያ ነው። ራስን ማጥፋትን ከወንጀል ነፃ በማድረግ፣ ሕጉ በከባድ ጭንቀት ውስጥ ያሉ ግለሰቦችን ከመቅጣት ይቆጠባል። ይልቁንም፣ የመንግሥትን የቅጣት ኃይል ወደ ውጫዊ አጥፊዎች እና ደካማነትን ተጠቅመው ጉዳት ወደሚያደርሱ ኃይሎች ያዞራል። በተቀረጸው የቅጣት እርከን አማካኝነት፣ ድንጋጌው በውጤት ላይ የተመሠረተ ተጠያቂነትን እና በመንግሥት የሚደረግን የጥበቃ ጣልቃ ገብነት በጥንቃቄ ያመጣጥናል። ከአገር በቀል ባህላዊ እሴቶች እና ከዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ግዴታዎች ጋር የተጣጣመው አንቀጽ 542፣ የሰውን ክብር ለማስከበር እና በማኅበረሰቡ ውስጥ በጣም ተጋላጭ የሆኑትን ወገኖች ለመጠበቅ የሚቆም ጠንካራ የሕግ ማዕቀፍ ነው። ዋቢዎች  African Charter on Human and Peoples' Rights (adopted 27 June 1981, entered into force 21 October 1986) 1520 UNTS 217 (ACHPR)  Criminal Code of the Federal Democratic Republic of Ethiopia, Proc። No 414/2004  International Covenant on Civil and Political Rights (adopted 16 December 1966, entered into force 23 March 1976) 999 UNTS 171 (ICCPR)  Kenya National Commission on Human Rights & 2 Others v Attorney General, Director of Public Prosecution & 3 Others [2025] KEHC 6 (KLR) (Constitutional Petition E045 of 2022)  Mill JS, On Liberty (first published 1859, Stefan Collini ed, Cambridge University Press 1989)  National Assembly of Kenya, Report of the Departmental Committee on Justice and Legal Affairs on Public Petition No 13 of 2024 Regarding Decriminalization of Attempted Suicide (Parliament of Kenya 2025)  Penal Code of Kenya, Cap 63  Suicide Act 1961 (United Kingdom) ማሳሰቢያ፦ ይህ ጽሑፍ የተዘጋጀው ለትምህርታዊ፣ ለአካዳሚክ እና ለአጠቃላይ መረጃ አገልግሎት ብቻ ሲሆን፣ ሙያዊ የሕግ ምክርን (legal advice) የሚተካ ወይም የሚወክል አይደለም። በጽሑፉ ውስጥ የቀረቡት ትንተናዎች፣ ድምዳሜዎች እና የሕግ ንጽጽሮች የአዘጋጁን ንባብና ምልከታዎች ብቻ የሚያንጸባርቁ ናቸው። አንባቢዎች ይህንን ጽሑፍ እንደ ቀጥተኛ የሕግ መመሪያ ወይም ዋቢነት ከመጠቀም እንዲቆጠቡ እና ከጉዳያቸው ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር ተገቢውን የሕግ መፍትሔ ለማግኘት ፈቃድ ካላቸውና ብቁ ከሆኑ የሕግ ባለሙያዎች (legal professionals) ዘንድ ቀጥተኛ ሙያዊ ምክር እንዲያገኙ እንዲሁም ለምርምር ስራዎች አስተማማኝ ምንጮችን እንዲጎበኙ በጥብቅ ይመከራሉ!!

ይልቁንም የኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ ራስን እንዲያጠፋ ማነሳሳትን ወይም መርዳትን ራሱን የቻለ (sui generis) ወንጀል አድርጎ ይመለከተዋል። በዚህም ምክንያት የረዳቱ ድርጊት ወንጀለኛነት ቀጥተኛ እና መሠረታዊ ሲሆን፣ የሚመነጨውም የሰውን ሕይወት የመጠበቅ እና የመንከባከብን ማኅበራዊ እና ሕጋዊ ግዴታ በመጣሱ ነው። ፬. ባህላዊ እሴቶች እና ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች መዋቅሮች የአንቀጽ 542 መዋቅር የንድፈ-ሐሳብ ውጤት ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያን ማኅበራዊ እና ባህላዊ እሴቶች እንዲሁም ዓለም አቀፍ የሕግ ግዴታዎቿን በጥልቀት የሚያንጸባርቅ ነው ተብሎም ይታመናል። ሀ. ማኅበራዊ-ባህላዊ እና ሃይማኖታዊ እሴቶች በኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ውስጥ ልክ እንደ ሌሎች የአፍሪካ ማኅበረሰቦች፣ የሕይወት ቅድስና መሠረታዊ የሞራል መርሕ ነው። ይህ መርሕ የሰውን ሕይወት የማይደፈር ስጦታ አድርገው በሚመለከቱት በክርስትና እና በእስልምና ሃይማኖታዊ አስተምህሮዎች በጥልቀት የተደገፈ መሆኑ ሲገለፅም ይሰማል፤ ይታወቃልም። ራስን ማጥፋት በአገር በቀል እሴት እንደ ትልቅ ሀዘን ብቻ ሳይሆን በማኅበረሰቡ ላይ እንደተፈጸመ የሞራል ጥሰትም ይቆጠራል። በተጨማሪም የአፍሪካ ሕግ ፍልስፍና በማኅበራዊ ኃላፊነት እና በጋራ መረዳዳት ላይ ያተኩራል። በዚህ መዋቅር ውስጥ ግለሰቦች ሙሉ በሙሉ የተነጠሉ ወኪሎች ሳይሆኑ የጋራ ማኅበረሰብ አባላት ተደርገው ይታያሉ ። ስለዚህ ሕጉ የጋራ እንክብካቤ ግዴታን ያስገድዳል፣ ይህም ኅበራዊ ደህንነትን የሚናጉትንና ሰዎችን ለራስ-ጥፋት የሚያነሳሱትን ይቀጣል። ለ. ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ስምምነቶች ከላይ በንዑስ ፊደል ‘ሀ’ ስር በአጭሩ ከተጠቀሱት የወንጀል ሕግ ፍልስፍናዊ መሠረቶች ባሻገር፣ የድንጋጌው ሰብዓዊና ሕጋዊ ዋጋ ይበልጥ ጎልቶ የሚታየው ከዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ስምምነቶች አንጻር ሲመረመር ነው ። ከዚህ አቅጣጫ ሲታይ፣ አንቀጽ 542 የኢትዮጵያ መንግሥት በዓለም አቀፍ ሕግ ያለበትን ግዴታ የሚወጣበት ዋነኛ መሣሪያ ሆኖ ያገለግላል። በተለይም፣ እንደ ዓለም አቀፉ የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች ቃል ኪዳን (ICCPR) አንቀጽ 6 እና የአፍሪካ የሰዎችና የሕዝቦች መብቶች ቻርተር (ACHPR) አንቀጽ 4 ያሉ መሠረታዊ የሰብዓዊ መብቶች ሰነዶች መንግሥታት የሰውን ሕይወት የመጠበቅ ጥብቅ ግዴታ እንዳለባቸው በግልጽ ይደነግጋሉ። ይህንን ዓለም አቀፋዊ መርሕ ይበልጥ ትርጉም ባለው መልኩ የሚያብራራው የሰብዓዊ መብቶች ሕግ ሥነ-አመክንዮ ሲሆን፣ የመንግሥት ሕይወትን የመጠበቅ ግዴታ አሉታዊ ብቻ ሳይሆን አወንታዊም ጭምር መሆኑን ያስረዳል። አሉታዊ ግዴታው መንግሥት ራሱ ወይም ወኪሎቹ የአንድን ግለሰብ ሕይወት ያለአግባብ ከመቅጠፍ እንዲቆጠቡ የሚፈልግ ሲሆን፤ አወንታዊ ግዴታው ደግሞ መንግሥት ግለሰቦችን በሶስተኛ ወገኖች ከሚደቀኑባቸው ማናቸውም አደጋዎች ለመጠበቅ የሚያስችሉ ተጨባጭ የሕግና የአስተዳደር ዋስትናዎችን በተግባር እንዲያዘጋጅ ያስገድዳል ። በመሆኑም የኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 542 ተጋላጭ የሆኑ ሰብዓዊ ሕይወቶች ላይ ከውጭ የሚሰነዘሩ አደጋዎችን በወንጀል በመቅጣት፣ ይህንን አወንታዊ የመንግሥት የጥበቃ ኃላፊነት በተግባር የሚተርጉም ዋነኛውና ቀዳሚው የሕግ ዋስትና ተደርጎ ሊወሰድ የሚችል ነው። ፭. ንጽጽራዊ ገጽታዎች የኢትዮጵያን የወንጀል ሕግ ድንጋጌዎች ይዘትና ስፋት ይበልጥ ግልጽ በሆነ መልክ ለመገምገም፣ ጉዳዩን ከሌሎች የሕግ ሥርዓቶች ንጽጽራዊ ተሞክሮ አንጻር መመልከት እጅግ ጠቃሚ ነው ። ከዚህ ንጽጽራዊ ትንተና በግንባር ቀደምትነት የምናገኘው የዩናይትድ ኪንግደምን የሕግ ሥርዓት ሲሆን፣ አገሪቱ በ1961 በወጣው የራስ-ማጥፋት ሕግ (Suicide Act 1961) አማካኝነት ድርጊቱን ከወንጀል ሕግ ሙሉ በሙሉ የለየች ቢሆንም፣ በሶስተኛ ወገን የሚደረግን እርዳታ ለመከላከል ግን እስከ 14 ዓመት የሚደርስ ከፍተኛ ጽኑ እስራት አስቀምጣለች። ይህ ዓለም አቀፋዊ አዝማሚያ እንደሚያሳየው አብዛኞቹ ዘመናዊ የሕግ ሥርዓቶች ራስን ማጥፋት የፈጸመውን ግለሰብ ከመቅጣት ይልቅ፣ በድርጊቱ ጀርባ ያለውን የሶስተኛ ወገን ማነሳሳትና መርዳት የሕይወትን ቅድስና ለመጠበቅ ሲሉ በከፍተኛ ሁኔታ መቅጣታቸውን ቀጥለዋል፡፡ ይህንን የግል ነፃነት እና የመንግሥት የጥበቃ ሚና የማመጣጠን ጉዳይ በተመለከተ፣ እንደ ጀርመን እና ካናዳ ያሉ የሕግ ሥርዓቶች ረቂቅና ልዩ የሆኑ አቀራረቦችን ይከተላሉ። ለምሳሌ የጀርመን ሕግ በተደራጀ መልኩ ራስን ማጥፋትን መርዳትን የሚከለክል ቢሆንም፣ የግለሰቡን የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት ከመንግሥት የጥበቃ ግዴታ ጋር ለማመጣጠን ይሞክራል ። በሌላ በኩል ደግሞ፣ የካናዳ ሕግ በሕክምና የታገዘ ሞትን (MAID) ለአዋቂዎች በከፍተኛ ጥንቃቄና በጥብቅ የሙያ ሁኔታዎች ሥር ቢፈቅድም ከዚህ የሕግ ማዕቀፍ ውጭ የሚደረግን ማናቸውንም የራስ-ማጥፋት እርዳታ ግን አሁንም በከባድ የወንጀል ተጠያቂነት ይቀጣል። በምሥራቅ አፍሪካ ቀጠና የጎረቤታችንን የኬንያን የወንጀል ፍትሕ ሥርዓት ተሞክሮ ስንመለከት ደግሞ ጉዳዩ በቅኝ ግዛት ውርስ እና በቅርብ ጊዜ በተደረጉ አበረታች የሕግ ማሻሻያዎች መካከል ያለውን ታሪካዊ ሽግግር በጥልቀት ያሳያል። ለብዙ አሥርተ ዓመታት የኬንያ የወንጀል ሕግ ራስን የማጥፋት ሙከራን እንደ መለስተኛ ወንጀል (misdemeanor) በመቁጠር እስከ ሁለት ዓመት የሚደርስ እስራትን ይደነግግ የነበረ ሲሆን፣ ይህም በስነ-አእምሮአዊ ቀውስ ውስጥ ያሉ ዜጎችን ከደህንነት ይልቅ በድጋሚ ለቅጣትና ለማኅበራዊ መገለል የሚዳርግ ጊዜ ያለፈበት አቀራረብ ነበር። ይሁን እንጂ፣ ጥር 9 ቀን 2025 ዓ.ም (እ.ኤ.አ) የኬንያው ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሕገ-መንግሥታዊ ትርጉም መርሆዎችን መሠረት በማድረግ ይህንን ድንጋጌ ውድቅ ያደረገበትን ታሪካዊ ውሳኔ አስተላልፏል። ፍርድ ቤቱ ራስን የማጥፋት ሙከራን በወንጀል መቅጣት ሰብዓዊ ክብርን፣ እኩልነትን እና ዜጎች በሕገ-መንግሥቱ የተረጋገጠላቸውን ከፍተኛ የጤና ደረጃ የማግኘት መብት የሚጥስ መሆኑን በመወሰን፣ ጉዳዩ ከወንጀል ፍትሕ ይልቅ በሕዝብ ጤና ማዕቀፍ መታየት እንዳለበት ወስኗል። ይህ የፍርድ ቤት ውሳኔ በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ ፓርላማ ውስጥ እየተካሄደ ላለው የሕግ ማሻሻያ ረቂቅ የጀርባ አጥንት በመሆን፣ ኬንያን ከቅጣት ይልቅ ለሰብዓዊ ክብርና ለጤና እንክብካቤ ቅድሚያ ወደሚሰጥ ተራማጅ የሕግ ሥርዓት በማሸጋገር ላይ የሚገኝ መሆኑ እየተገለፀ ይገኛል። ከእነዚህ ዓለም አቀፋዊ ተሞክሮዎች ጋር ሲነጻጸር፣ የኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ ድንጋጌ ልዩ መለያ ሆኖ የሚጠቀሰው በተጎጂው ተጋላጭነት ደረጃ ላይ ያደረገው ግልጽ የሕግ ትኩረት ነው። አብዛኞቹ አገሮች እርዳታ ወይም ማነሳሳትን በጠቅላላ የወንጀል ድንጋጌ ብቻ ሲቀጡ፣ የኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ ግን በተለየ ሁኔታ በተጎጂው አቅመ-ቢስነት (እንደ ሕፃናት፣ የአእምሮ በሽተኞች እና አረጋውያን) ላይ የተመሠረተ ግልጽ የቅጣት እርከን መዘርጋቱ በንጽጽር ሲታይ የላቀ ኅበራዊ ጥበቃን የሚያረጋግጥ ሥርዓታዊ አካሄድ ያሳያል ተብሎ ሊገለፅ የሚችል ነው። ፮. ማጠቃለያ

source #Almaw Wolie(Advocate and Legal Consultants at law) faacebook page. ራስን ከማጥፋት ሙከራ እስከ ሦስተኛ ወገን ተጠያቂነት፡- የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 542 እና የኬንያ አዲሱ የሕግ ሽግግር ፩. መግቢያ የወንጀል ሕግ በተለይም የአንድ ግለሰብ ምርጫ ወደ ራስ-ጥፋት በሚያመራበት ጊዜ፣ በግለሰቡ የግል ነፃነት እና በመንግሥት የጥበቃ ጣልቃ ገብነት መካከል ያለውን የሞራል እና የሕግ ገደብ ለመወሰን ረጅም ዘመናትን የታገለ ጉዳይ ነው። በኢትዮጵያ የሕግ ሥርዓት ውስጥ፣ ይህ ውጥረት በ2004 (1997 ዓ.ም) በወጣው የወንጀል ሕግ አንቀጽ 542 ሥር ሌላ ሰው ራሱን እንዲያጠፋ ማነሳሳት ወይም መርዳትን ወንጀል በማድረግ ጥልቅ በሆነ መንገድ ተቀምጧል። በ1949ኙ የወንጀል ህግም በአንቀፅ 525 ስር ተቀምጦ ይገኝ ነበር፡፡ ራስን የማጥፋት ሙከራን በወንጀል ከሚቀጡ የቀድሞ የኮመን ሎው (common law) እና የሲቪል ሎው (continentallaw) ስርዓቶች በተለየ፣ የወቅቱ የኢትዮጵያ ሕግ ራስን ጥፋት የተለመደ የወንጀል ጥፋት ሳይሆን ከፍተኛ የስነ-ልቦና ቀውስ ውጤት መሆኑን ይገነዘባል። በዚህም ምክንያት የቅጣት መሣሪያው ትኩረት የሚያደርገው በጭንቀት ውስጥ ባለው ግለሰብ ላይ ሳይሆን፣ ድርጊቱን ባመቻቹ ወይም ባበረታቱ ሶስተኛ ወገኖች ላይ ነው። ይህ ጽሑፍ አንቀጽ 542ን የሕግ አካላት፣ የፍልስፍና መሠረቶች እና የቅጣት እርከኖችን ከንጽጽራዊ እና ከሰብዓዊ መብቶች አንጻር በአጭር ይፈተሻል፡፡ ፪.የአንቀጽ 542 አወቃቀርና ይዘት የኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 542 የተጠያቂነትን ወሰን በሁለት መሠረታዊ ንዑሳን ድንጋጌዎች በመክፈል፣ የአጥፊውን የቅጣት ደረጃ በተጎጂው የመወሰን አቅም እና በድርጊቱ የመጨረሻ ውጤት ላይ በመመሥረት ይደነግጋል ። በዚህም መሠረት፣ ንዑስ-አንቀጽ አንድ ሙሉ የሕግ ችሎታና አቅም ያላቸውን አዋቂ ተጎጂዎችን የሚመለከት ሲሆን፣ ድንጋጌው ማነሳሳትን እና መርዳትን/ማገዝን እንደ ሁለት የተለያዩ የራስ-ጥፋት ተባባሪነት ዓይነቶች ይለያል። እዚህ ላ፣ ማነሳሳት ተጎጂው ራሱን እንዲያጠፋ ለማድረግ የታለመ ልዩ የወንጀል ሐሳብን (dolus) በመያዝ ሆን ብሎ ማነቃቃትን፣ ማበረታታትን ወይም ማሳመንን የሚጠይቅ ሲሆን፤ መርዳት ወይም ማገዝ ደግሞ ድርጊቱን ለማመቻቸት ቁሳዊ እርዳታን (ለምሳሌ ገዳይ መሣሪያዎችን ማቅረብ) ወይም የሞራል ድጋፍን መስጠትን ያካትታል። በዚህ መደበኛ ተጠያቂነት ሥር የሚወሰነው ቅጣት በውጤት ላይ የተመሠረተ ነው፤ በተጎጂው የተደረገው ራስን የማጥፋት ሙከራ ሳይሳካ ሲቀር አጥፊው በቀላል እስራት የሚቀጣ ሲሆን፣ ድርጊቱ ተፈጽሞ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ ግን ቅጣቱ እስከ አምስት ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ይከብዳል። በሌላ በኩል፣ ንዑስ-አንቀጽ ሁለት በተጎጂው ስነ-አእምሮአዊ እና አካላዊ ተጋላጭነት ላይ በመመሥረት የተደነገገ ልዩ የቅጣት ማክበጃ ነው። ድንጋጌው ጥበቃ ለሚያስፈልጋቸው እንደ ሕፃናት፣ የአእምሮ በሽተኞች እና በዕድሜ መግፋት (እርጅና) ምክንያት የመወሰን አቅማቸውን ላጡ አቅመ-ቢስ ወገኖች የሚተገበር ሲሆን፤ በእነዚህ ግለሰቦች ላይ የተደረገው ራስን የማጥፋት ሙከራ ለአጥፊው እስከ አምስት ዓመት የሚደርስ ጽኑ እስራት የሚያስከትል ሲሆን፣ ድርጊቱ ተፈጽሞ የመጨረሻውን የሞት ውጤት በሚያስከትልበት ጊዜ ግን የአጥፊው ተጠያቂነት እስከ አሥር ዓመት ጽኑ እስራት እንዲደርስ ይደረጋል ። ይህ የተቀናጀ የቅጣት እርከን ሕጉ ለደረሰው የመጨረሻ ጉዳት ክብደት እንዲሁም ለተጎጂው ተጋላጭነት ደረጃ የሚሰጠውን ጥልቅ እና ሚዛናዊ ትኩረት ያሳያል። ሕግ አውጪው እነዚህን ሁኔታዎች ለይቶ በመደንገግ፣ የአጥፊው የሞራል ጥፋተኝነት ደረጃ ከተጎጂው ተጋላጭነት ስፋት እና ከድርጊቱ የመጨረሻ ውጤት ጋር በቀጥታ የተቆራኘ መሆኑን ያረጋግጣል። ይህንን ዝርዝር የተጠያቂነት እና የቅጣት መዋቅር ተከትሎ የሚነሳው ወሳኝ ጥያቄ፣ ራሱን ያጠፋውን ወይም ለመሞት የሞከረውን ግለሰብ ከቅጣት ነፃ በማድረግ፣ ድርጊቱን ያመቻቸውን ወይም ያነሳሳውን ሶስተኛ ወገን ግን በወንጀል ለመቅጣት የተወሰነበት ሰብአዊና ፍልስፍናዊ መነሻ ምንድን ነው? የሚለው ነው። በዚህ ረገድ የተደነገገውን የሕግ አቅጣጫ በተገቢው መንገድ ለመረዳት፣ ድንጋጌው የተመሠረተባቸውንና የተሟላ ትርጉም የሚሰጡትን በርካታ የወንጀል ሕግ፣ የስነ-ወንጀል ጥናት (criminology) እና የሰብዓዊ መብቶች ንድፈ-ሐሳቦችን በጥልቀት መመርመር አስፈላጊ ይሆናል። ፫. የአንቀጽ 542 ፍልስፍናዊ እና ሰብዓዊ መብቶች መሠረቶች:-ንድፈ-ሐሳቦች ከእነዚህ መሠረታዊ ንድፈ-ሐሳቦች መካከል በግንባር ቀደምትነት የሚነሳው የጆን ስቱዋርት ሚል የጉዳት መርሕ (Harm Principle) ነው። ሚል "በነፃነት ላይ" (On Liberty) በተሰኘው ታዋቂ ሥራው ላይ በግልጽ እንደ አስረዳው፣ መንግሥት በማንኛውም የሰለጠነ ማኅበረሰብ አባል ላይ ካለው ፍላጎት ውጭ የመንግሥትን አስገዳጅ ኃይል በሕጋዊ መንገድ ሊጠቀም የሚችለው በሌሎች ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ለመከላከል ብቻ ነው። ራስን ማጥፋት በራስ ላይ ብቻ የሚደርስ ጉዳት እንደመሆኑ፣ በገዛ ፈቃዱ ሕይወቱን ለማጥፋት በሞከረ ግለሰብ ላይ የሕጉ ጣልቃ ገብነት እንደ ሥልጣን ማለፍ የሚቆጠር ቢሆንም፤ አንድ 3ኛ ወገን ድርጊቱን ሲያነሳሳ ወይም ሲረዳ ግን፣ ሂደቱ ከግል ምርጫነት ባለፈ ውጫዊ እና ጎጂ የሆነ አካል መኖሩን የሚያስተዋውቅበት ሁኔታ ይፈጠራል። በመሆኑም፣ በአንቀጽ 542 ሥር የተደነገገው የመንግሥት ጣልቃ ገብነት ሕጋዊ መሠረት ያገኛል፤ ምክንያቱም ሕጉ ራሱን የጎዳውን ግለሰብ ከመቅጣት ይልቅ፣ ሌላውን ሰው ለከፋ ጉዳት ያጋለጠውን 3ኛ ወገን ለመከላከልና ለመገደብ ያለመ ነው። ይህንን የግል ነፃነት ወሰን ተከትሎ የሚነሳውና ድንጋጌውን ይበልጥ የሚያጠናክረው ሌላው ወሳኝ ጽንሰ-ሐሳብ የወንጀል ጥበቃ (paternalism) እና ተጋላጭ ወገኖችን የመከላከል ግዴታ ነው። ዘመናዊው የወንጀል ሕግ ለግል ነፃነት ክብር ቢሰጥም፣ ይህ ነፃነት ግን ገደብ የለሽ አይደለም ። የሕግ ሥርዓቶች ትክክለኛ፣ ነፃ እና ምክንያታዊ ውሳኔ ለመስጠት የአእምሮ ብስለት፣ የአእምሮ ጤና እና ስሜታዊ መረጋጋት ቀዳሚ መሥፈርቶች መሆናቸውን በጥልቀት ይገነዘባሉ። በመሆኑም፣ እንደ ሕፃናት፣ አረጋውያን ወይም የአእምሮ በሽተኞች ያሉ የግለሰቡ የመወሰን አቅም የሚዳከምባቸው ሁኔታዎች ሲያጋጥሙ፣ መንግሥት የግለሰቦቹን መብት ለመጠበቅ የጥበቃ (paternalistic) አቋም ይይዛል ። በእነዚህ ሁኔታዎች ውስጥ፣ ሕጉ ተጎጂው ለራስ-ጥፋት የሰጠው "ስምምነት" በሕግ ፊት ፈጽሞ ዋጋ እንደሌለው ይቆጥረዋል፤ በዚህም ምክንያት 3ኛውን ወገን እንደ ተራ ወንጀል ተባባሪ ሳይሆን፣ የሰውን ስነ-ልቦናዊ እና አካላዊ ደካማነት ለራስ ዓላማ የተጠቀመ በዝባዥ አድርጎ ይፈርጀዋል። በመጨረሻም የድንጋጌው ልዩ የሕግ ባህሪ ይበልጥ ጎልቶ የሚታየው ከተለመደው የተባባሪነት ንድፈ-ሐሳብ የሚለይበትን መንገድ ስንመረምር ነው። በተለመደው የሕግ አስተሳሰብ፣ የተባባሪ ተጠያቂነት ብዙውን ጊዜ ጥገኛ/ተቀጥላ (derivative) ነው፤ ይህም ማለት ረዳቱ ወይም አነሳሺው የሚቀጣው ዋናው አጥፊ የፈጸመው ድርጊት ወንጀል ሆኖ ሲገኝ ብቻ ነው ። አንቀጽ 542 ግን ከዚህ የጥገኝነት ሞዴል ፍጹም ይለያል። ራስን ማጥፋት በኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ ሥር ወንጀል ስላልሆነ፣ አነሳሺው ወይም ረዳቱ ጥፋታቸውን ከተጎጂው ድርጊት ሊያገኙት አይችሉም።

ይህ በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የተሰጡ አስገዳጅ የወንጀል ሕግ ትርጉም ውሳኔዎችን በየጉዳዩ አደራጅቶ የያዘ ልዩ እትም ነው። እትሙ በየካቲት 2018 ዓ.ም የታተመ ሲሆን፣ ከአውሮፓ ሕብረት በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ በባለሙያዎች ቡድን የተዘጋጀ የመጀመሪያ እትም ነው። ስለዚህ ልዩ እትም ዝርዝር ማብራሪያና ይዘት እንደሚከተለው ቀርቧል፦ 1. የልዩ እትሙ ዋና ዓላማና ጠቀሜታ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት ከበደ በገለጹት መልዕክት መሠረት፣ የሰበር ሰሚ ችሎት አስገዳጅ ውሳኔዎችን አሳትሞ ማሰራጨት የፍርዶችን ይፋዊ ይዘት ለመረዳት፣ ግልጽነትና ተጠያቂነትን ለማስፈን ከፍተኛ ፋይዳ አለው። የዚህ ልዩ እትም ዋና ዋና ጠቀሜታዎች የሚከተሉት ናቸው፦ ወጥ የሕግ አተረጓጎም ማረጋገጥ፦ በመላ አገሪቱ በሚገኙ ማናቸውም ደረጃ ላይ ያሉ የፌዴራልም ሆነ የክልል ፍርድ ቤቶች ዘንድ ወጥና ተገማች የሆነ የሕግ አተረጓጎም ሥርዓት እንዲኖር ያደርጋል። ውጤታማነትና ወጪን መቀነስ፦ የሕግ ክርክሮች በአጭር ጊዜና በአነስተኛ ወጪ እንዲቋጩ ከመረዳቱም በላይ፣ ዐቃቢያነ ሕግ ክስ ከመመስረታቸው በፊት ቀደሞ የተሰጡ ውሳኔዎችን መርምረው ተገቢና ብልህ ውሳኔ ለመወሰን ያስችላቸዋል። የሥነ-ሕግ ዕውቀትን ማዳበር፦ ለሕግ ትምህርት፣ ለምርምር እንዲሁም ሕጎች በተግባር በሰዎች ዕለት ከዕለት ኑሮ ላይ የሚያስከትሉትን ውጤት ለመፈተሽና ለመመርመር ከፍተኛ ሚና አለው። የተደራጀና ተደራሽ መሆን (የእትሙ ልዩ እሴት)፦ ከዚህ ቀደም የሰበር ውሳኔዎች በቅጽ መልክ ሲታተሙ የወንጀልና የፍትሐብሔር ጉዳዮች ተደባልቀው ይወጡ ስለነበር ፈልጎ ማግኘት አስቸጋሪ ነበር። ይህ እትም ግን ውሳኔዎችን በወንጀል ዓይነትና በሕጉ ፍሰት መሠረት በማደራጀት፣ ተመሳሳይ ውሳኔዎችን በአንድ ላይ በማሰናዳትና ተዛማጅ ጉዳዮችን በግርጌ ማስታወሻ በማጣቀስ ተጠቃሚዎች በቀላሉ እንዲያገኟቸው የተለየ እሴት ጨምሯል። 2. የመጽሐፉ መዋቅርና ይዘት መጽሐፉ በባለሰባትና በባለአምስት የሰበር ዳኞች የተሰጡ 86 ማይልስቶን (መሠረታዊ) ውሳኔዎችን ከነሙሉ ይዘታቸው ያካተተ ሲሆን፣ በአራት ዋና ዋና ምዕራፎችና በ45 ክፍሎች የተዋቀረ ነው፦ ምዕራፍ አንድ - የወንጀል ሕግ የጠቅላላ ድንጋጌ ክፍል የሰበር ሕግ ትርጉም ውሳኔዎች፦ ይህ ምዕራፍ በ13 ክፍሎች የተደራጀ ሲሆን፣ የወንጀል ሕግ መርሆዎችን (እንደ አንድ ሰው በአንድ ወንጀል ድጋሚ እንዳይከሰስና እንዳይቀጣ የሚከለክለውን መብትና የሕጋዊነት መርህን)፣ የፍርድ ቤቶችን የስረ-ነገር ሥልጣን፣ የወንጀል አፈጻጸም ደረጃዎችንና ተካፋይነትን፣ የቅጣት አወሳሰን መመሪያዎችን፣ ንብረት መውረስንና ቅጣትን መገደብን (ማገድን) የመሳሰሉ ጠቅላላ መርሆዎችን ያብራራል። ምዕራፍ ሁለት - የወንጀል ሕግ የልዩ ክፍል የሰበር የሕግ ትርጉም ውሳኔዎች፦ በሕጉ ልዩ ክፍል ሥር የተዘረዘሩ የተወሰኑ ወንጀሎችን የሚመለከት ሲሆን፤ በመንግሥትና በሕዝብ ጥቅም ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን (የከበሩ ማዕድናት በሕገ-ወጥ መንገድ ማዘዋወር፣ የሥራ ኃላፊነትን አለመወጣት፣ ሐሰተኛ ምስክርነትና ፍርድ ቤትን መድፈር)፣ በሰው ሕይወት፣ አካልና ነጻነት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን (የሰው ግድያ፣ ከባድና ቀላል አካል ጉዳት፣ ሰዎችን ለሥራ ወደ ውጭ በሕገ-ወጥ መንገድ መላክ)፣ እንዲሁም በንብረትና በሩካቤ ሥጋ ነጻነት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን (ስርቆት፣ እምነት ማጉደል፣ ማታለልና በቂ ስንቅ የሌለው ቼክ ማውጣት) ያካትታል። ምዕራፍ ሶስት - በልዩ ልዩ አዋጆች ላይ የተሰጡ አስገዳጅ የሰበር የሕግ ትርጉም ውሳኔዎች፦ ከዋናው የወንጀል ሕግ ውጭ በልዩ ልዩ አዋጆች ሥር የተደነገጉ ወንጀሎችንና የተሰጡ አስገዳጅ ትርጉሞችን ይዟል። ከነዚህም መካከል የሽብር ወንጀል፣ የሰዎች ዝውውርና ድንበር ማሻገር፣ የሙስና ወንጀል አዋጅ (የተከሳሽን ሐሳብ የማስረዳት ሸክም ወደ ተከሳሹ የሚዞርበትን ሁኔታ)፣ የቴሌኮሙኒኬሽን፣ የታክስ አስተዳደር (ሐሰተኛ የግብር ደረሰኝ) እና የጉምሩክ አዋጆችን፣ የባንክ ሥራ፣ የሊዝ አዋጅ (የከተማ ቦታ ወረራ)፣ የጦር መሣሪያ ቁጥጥር፣ እና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጆችን የተመለከቱ ውሳኔዎች ይገኙበታል። ምዕራፍ አራት - በወንጀል ሥነ-ሥርዓት ሕግ ላይ የተሰጡ የሰበር የሕግ ትርጉም ውሳኔዎች፦ የወንጀል የፍርድ ሂደትን የሚመሩ ድንጋጌዎች ትርጉም ሲሆን፤ የፖሊስ ምርመራን (ለፖሊስ የተሰጠ የእምነት ቃል፣ የኢግዚቢት አመላለስ፣ የብርበራ ሕጋዊነት)፣ የዋስትና መብት መፈቀድና መከልከልን፣ የክስ አዘገጃጀት፣ ማሻሻልና ወደ ሌላ ስፍራ ማዛወርን፣ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያና የእምነት ክህደት ቃልን፣ የማስረጃ አቀራረብና ምዘናን፣ እንዲሁም ተከሳሽ በሌለበት ክርክር ስለመቀጠልና የይግባኝ/ሰበር አቤቱታ ሥነ-ሥርዓቶችን ያጠቃልላል። 3. የመጽሐፉ ልዩ የአጠቃቀም መመሪያዎች ጭብጥና የግርጌ ማስታወሻ፦ በእያንዳንዱ የክፍል ወይም ንዑስ ክፍል ርዕስ ስር የውሳኔዎቹ ዋና ጭብጥ ይገኛል። በጭብጡ መጨረሻ ላይ የተቀመጡት የግርጌ ማስታወሻዎች ከዋናው ውሳኔ ጋር ተመሳሳይ ወይም ተያያዥ የሆኑ ሌሎች የሰበር ውሳኔዎችን ዝርዝር ይጠቁማሉ። ይህ አንባቢው በሌሎች ታተሙ ቅጾችና ድረ-ገጾች ያሉ ተመሳሳይ ውሳኔዎችን በቀላሉ አውጥቶ እንዲጠቀም ጥቆማ ይሰጣል። የተለያዩ የሕግ አቋሞች ማሳያ፦ ምንም እንኳ ያልተለመደ ቢሆንም፣ አልፎ አልፎ በተመሳሳይ ጉዳይ ላይ የተለያየ አቋም የተያዘባቸው የሕግ ትርጉሞች (ለምሳሌ ስለ ተደራራቢ ወንጀሎች ወይም ስለ ቅጣት መገደብ) ሲያጋጥሙ፣ አዘጋጆቹ ለማስተያየት እንዲረዳ በአቋም የተለዩትን ውሳኔዎችም በልዩ ሁኔታ አመልክተዋል። የመፈለጊያ ቃላት (Index)፦ አንባቢዎች ከዋናው ማውጫ በተጨማሪ በመጽሐፉ መጨረሻ ክፍል ላይ ያለውን የቃላት መፈለጊያ እንደ ጠቋሚ በመጠቀም ስለሚፈልጉት ጉዳይ የተጻፈበትን ቦታ በቀላሉ ማወቅ ይችላሉ። ይህ ልዩ እትም ለዳኞች፣ ለዐቃቢያነ ሕግ፣ ለጠበቆች፣ ለሕግ ተመራማሪዎችና ፍላጎት ላላቸው ዜጎች የወንጀል ፍትሕ አስተዳደሩን ሥረ-ነገርና ሥነ-ሥርዓታዊ ሕጋዊ አተረጓጎም በጥራት፣ በግልጽነትና በተደራጀ መልኩ ለመረዳት የሚያስችል ወሳኝ የሕግ መጽሐፍ ነው። ይህንን ልዩ እትም ለማግኘት ቀጥሎ ያለውን ሊንክ ያስፈንጥሩ! https://t.me/j_f125/9725

ይኸው የተሳሳተ የውርስ አቤቱታ ዳኛ ጋር ቀርቦ፣ ውርስ እንዲጣራ ታዞ የተሾመው ውርስ አጣሪ የሟች ሀብት ሙሉ ለሙሉ ለሚስት ይገባል ብሎ አጣርቶ አቀረበ። ዳኛው የውርስ አጣሪውን ሪፖርት እንዳለ አፅደቀውት መዝገቡ ይዘጋል። ይሄ ሁላ ሲሆን ጓደኛዬ መረጃ የለውም። ባለጉዳዩ የፍርድ ቤቱን ውሳኔ ይዘው በባንክ ያለ በሟች ስም ያለ ገንዘብ 100% ለእናት እንዲከፈላቸው ለባንኩ ውሳኔውን ሲያቀርቡ ባንኩ ከ50 % በላይ አልከፍልም አላቸው። ይሄኔ ለጓደኛዬ ደወሉለት። "ምን ይሻላል?" አሉት። የተፈጠረውን ከሰማ በኋላ "የሚሻለውን እርሶ ያውቃሉ" አላቸው። የባንኩን ጉዳይ ተዉትና ይሄስ ምንድን ነው? ይሄ አሁን የዳኛ ስህተት ነው የሚባለው? የአቅም ውስንነት ነው የሚባለው? ወይስ የሥራ ጫና? ገጠመኝ ሦስት በአንድ ክርክር ላይ ውሳኔ ከመወሰኑ 2 ወር በፊት ለእኔ እንደማይወሰን አውቄ የይግባኝ አቤቱታ ባዘጋጅስ? ዳኛ የክርክሩን አውድ ቀድሞ በአግባቡ እና በጥንቃቄ ተረድቶ በጉዳዩ ላይ ቀድሞ አቋም ቢይዝ አይደንቅም። አቋሙ እንዳለ ሆኖ ጉዳዩን በገለልተኝነት አከራክሮ፣ ማስረጃዎቹን በአግባቡ ከመረመረ በኋላ በፍሬ ነገር እና በሕግ ብቻ ላይ ተመሥርቶ በቀደመ አቋሙ መሠረት ፍርድ ቢሰጥም አጃኢብ አያስብልም። ምክንያቱም ጉዳዩን በያዘው አቋም መነፅር ብቻ ሳይሆን ሙያው በሚያዘው አግባብ በገለልተኝነት መርምሮ በእውቀቱ፣ በክህሎቱ እና ሕጉን በተረዳው አግባብ ወስኗልና። ይህ ፍርድ የሕግ ስህተት ወይም ይግባኝ የሚያስብል ቅሬታ ቢያስከትል የዳኛው ስህተት ከእውቀቱ እና ክህሎቱ ማነስ የመነጨ በመሆኑ ዳኛው ተሳስቷል ወይም የከፋ የአቅም ውስንነት ማለት ነው። ያው ባወቀው ልክ ሠርቶ እና ግራ ቀኙን በተቻለው መጠን መርምሮ ተሳስቷል። ዳኛ ቢሳሳት ሰው ነውና አይደንቅም። ዳኛ በሕግ ጉዳይ ላይ የተሳሳተ አቋም ቢኖረው ሰው እና ባለሙያ ነውና አይደንቅም። ዳኛ አከራካሪው ጉዳይ ላይ ክርክሩ ከመጀመሩ አቋም የያዘው አቅሙ እና እውቀቱ በፈቀደ መልኩ ከሆነ ያው የሙያ ሥልጠና ወይም ድጋፍ ያስፈልገዋል ማለት ነው። ዳኛ የክርክሩን አውድ ቀድሞ በአግባቡ እና በጥንቃቄ ሳይረዳ በጉዳዩ ላይ ቀድሞ አቋም ቢይዝ፣ በዚሁ አቋሙ ላይ ተቸክሎ ጉዳዩን በአቋሙ መነፅር ብቻ ያለገለልተኝነት ከመረመረ፣ ተከራካሪዎች ወይም ጠበቆቸው የሚየቀርቡትን ግለፅ እና የሕግ ሀ ሁ የሆኑ፣ የማያሻሙ እና በተገቢ የሰበር ውሳኔዎች የተደገፉ ክርክሮች ለመረዳት ሳይጠር፣ ከሁሉ የከፋው ደግሞ በተከራካሪዎች የቀረቡትን ግልፅ የፅሁፍ ክርክር፣ ማስረጃ እና ያልታተሙ የሰበር ውሳኔዎች ፈፅሞ ሳያነብ፣ ቢያንስ ክርክሮቹን በደፈናው እንኳን አንስቶ ውድቅ ለማድረግ አንዳች ጥረት ሳያደርግ፣ ግልፅ ማስረጃዎችን በአግባቡ ሳይመረምር፣ በቀረበው ፍሬ ነገር እና በሕግ ላይ ሳይመሠረት በቀደመ አቋሙ መሠረት ፍርድ ቢሰጥ ሁለት ነገር ይታየኛል። የቀና ቀና ሰው ሆኜ ሳየው አንደኛ የሚታየኝ ነገር ያው ዳኛው ፅኑ የሥነ ምግባር፣ የዕውቀት እና የብቃት ችግር ያለበት ሰው ነው። አልያም የዳኝነት ሥራን መሠረታዊ ባህርይ የዘነጋ ዳኝነት ለደሞዝ የሚሠራው ሥራ ብቻ የሆነበት ሰነፍ ሰው ነው። ሁለተኛው የሚታየኝ ነገር ግን ያስፈራኛል። ዳኛው ሥራውን በአግባቡ ለመወጣት፣ ነገሮችን ለመገንዘብ፣ ምክንያታዊ የሕግ ትንታኔ ለማድረግ፣ ለማስታወስ፣ በአትኩሮት ለማሰብ እና ሥራውን በብቃት ለማከናወን እንዳይችል የሚያደደረግ ፅኑ ችግር ወይም እክል አለበት ማለት ነው። ይሄ ደግሞ ፅኑ ክትትል፣ ድጋፍ እና እርምጃ ይፈልጋል። ወደ ገጠመኜ ልመለስ። በአንዳንድ ክርክር ላይ ምን እንደሚወሰንብህ የምታውቀው ገና የአንተ ምስክር መሰማት ሲጀምር የችሎቱ ዳኛ የሚጠይቁትን ጥያቄ በመስማት ብቻ ነው። የግራ ቀኙ ክርክር ተሰምቶ ሲያልቅ አላልኩም። ገና የአንተ ምስክሮች አንደበት ሲከፈት ዳኛው ከተሳሳተ የፍሬ ነገር እና የሕግ መረዳታቸው በመነሳት ምስክርህን የሚጠይቁትን የተሳሳተ ጥያቄ ስታይ ምን እንደሚወሰንብህ ታውቃለህ። በዚሁ መሠረት በአንድ መዝገብ ላይ ምስክር ተሰምቶ በቀጣይ ቀጠሮ ፍርድ ከመሰጠቱ በፊት የክርክር ማጠቃለያ ካለን ከቀጠሮ በፊት እንድናስገባ ስንታዘዝ ቤቴ ገባሁና ሁለት ነገር ፃፍኩኝ። አንድ የክርክር ማቆሚያ እና አንድ የይግባኝ ቅሬታዬ። ይግባኝ የሚፃፈው የፍርድ ቤት ውሳኔ ከተሰጠ በኋላ መሆኑ ግልፅ ነው። እኔ ግን ውሳኔውን ቃል በቃል በሚያሰኝ ሁኔታ ቀድሜ ተንብዬ ይግባኜን ፍርድ ቤት ውሳኔውን ከመሰጠቱ ወራት በፊት ፃፍኩት። የክርክር ማጠቃለያዬን ለችሎቱ አስገባሁ። የይግባኝ ቅሬታዬን ለራሴ አስቀመጥኩ። የውሳኔው ቀን ከወራት በኋላ ደርሶ ችሎት ቀርበን ፍርዱ ገና መነበብ ሲጀምር ከውሳኔው ቀድሜ ያዘጋጀሁትን ይግባኝን አንድ መሥመር እንኳን ኤዲት ሳላደርግ ለይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤቱ እንደማስገባው ተገለጠልኝ። ውሳኔው ተነቦ ሲያልቅ እሱን አረጋገጥኩኝ። ከችሎት ስንወጣ የደንበኛዬን የእንባ ጎርፍ እና ተስፋ መቁረጥ ማየቴ ልቤን ደቃው። ጉዳዩን በጥልቀት የማውቀው እኔ ደግሞ ዛሬም የተለመደ ጥያቄዬን ለራሴ ጠየቅኩኝ። "ከ18 ዓመት በላይ በሕግ ሙያ ውስጥ ያለሁት እኔ የደንበኛዬን ጉዳይ ይዤ ፍርድ ቤት መመላለሴ እና ጉዳዩን መከታተሌ ደንበኛዬን ምን ጠቀማት? የእኔ ሕግ ማጣቀስ፣ መራቀቅ እና መተንተን ምን ጠቀማት? እኔስ በዚህ ጉዳይ ጠበቃ ነበር ከሚል ስም በስተቀር ምን አተረፍኩ?" በፍርድ ቤት ክርክር መሸነፍ እና ማሸነፍ በጥብቅና ሙያ ያለ እና የሚኖር ነው። አንድ ባለጉዳይ ጠበቃ ይኑረውም አይኑረውም የሕግ ሀ ሁ በሆነ ጉዳይ ግልፅ ፍሬ ነገር፣ ማስረጃ፣ ሕግ እና የማያሻማ የሰበር ውሳኔ ተጥሶ ሲወሰንበት እና በክርክሩ ስትሸነፍ እና ደንበኛህን የምታስረዳበት አንደበት ስታጣ ግን ስሙ መሸነፍ ብቻ አይደለም። ልብ ይሠብራል። ተስፋ ያስቆርጣል። ጠበቃ ፍትሕ አላገኝም ብሎ ተስፋ ከቆረጠ መጨረሻችን ምንድን ነው? ስንት ወርቅ ዳኞች ባሉበት አገር ጠበቆች በሚገጥሙን እንደነዚህ አይነት ተደጋጋሚ ስብራቶች መነሻነት "የጥብቅናን ሙያ ምን ቀን ነው የገባሁበት?" እያለን በሙያው ውስጥ በቆየን ቁጥር የፍትሕ ሥርዓታችን መጨረሻች ምንድን ነው? ከሁሉ የከፋው ደግሞ ጠበቆች ያሸነፍንባቸውም ሆነ የተሸነፍንባቸው ትክክለኛ፣ ሕጋዊ እና ሊሻሩ የማይገባቸው የብቁ ዳኞች ውሳኔውዎች በይግባኝ ሲሻሩ እያየን እንደነዚህ አይነት የፍርድ ቤት ገበና የሆኑ ውሳኔዎች ግን ይግባኝ ብናቀርብም እስከ ሰበር ሰሚ ችሎት ሲፀኑ ማየታችን ነው። ፍርድ ቤቶቻችንን የሁላችንም ናቸው። የጤናማ ማኅበረሰብ ማገሮች እና ተስፋዎች ናቸው። ፍርድ ቤቶች በወደቁ ቁጥር ችግራችን አሁን ካለበት የከፋ ነው የሚሆነው። ብርቱ ዳኞችን አበርቱ፣ ደግፉ፣ ሸልሙ፣ ሹሙ፣ አሞግሱ፣ ምቹ ሕይወት እና ደስታ ኖሯቸው እንዲሠሩ የምትችሉትን አድርጋችሁ በታሪክ ከፍታ ላይ ኑሩ! የደከሙትን ዳኞች አበርቱ፣ ደግፉ፣ አሠልጥኑ፣ ተቹ፣ ውቀሱ፣ ዳግም እድል ስጡ። የተጣመሙትን ዳኞች አቅኑ፣ ገስፁ፣ ክሰሱ፣ ውቀሱ፣ አባሩሩሩሩሩሩሩሩሩ፣ ቅጡ! የጋራ ቤታችንን አፅዱ!!!! ዳንኤል አረጋዊ ኃይሉ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም"

ከቀናት በፊት በአንድ ቻናል ላይ የተጋራ ነው። በትኩረት ይነበብ "የጋራ ቤታችን የሆኑትን ፍርድ ቤቶች አፅዱልን!!!! በዳንኤል አረጋዊ ኃይሉ ይሄ ፅሑፍ ዳኞች ላይ መሳለቂያም አይደለም። ቧልትም አይደለም። ምፀትም አይደለም። በትጋት እና በሕግ አግባብ ሥራቸውን የሚሠሩ ዳኞችን በጅምላ መፈረጃም አይደለም። ይሄ ፅሑፍ ብዙዎቻች ጠበቆች ከሚገጥሙን ተስፋ አስቆራጭ ገጠመኞች መካከል አንዱ ሰበዝ ነው! ገጠመኞቻችን የሚለያዩት የገጠመንን ጉዳይ እንዲህ በአደባባይ በመከተባችን እና ባለመከተባችን ነው። እንደዚህ በአደባባይ ከተብነውም አልከተብነውም አንድ ነገር ግን እርግጠኛ ነው። በየችሎት አዳራሹ፣ በየኮሪደሩ እና በየካፌው እነዚህ ገጠመኞቻችን ዋና ርዕሰ ጉዳያችን ናቸው። አንዳንድ ገጠመኞቻችን በራሳችን ሙያ ውስጥ በተፈጠሩ ስህተቶች እንድንማር፣ በነውሮቻችን እንድናፍር እና በጠንካራ የክርክር አውዶች እንድንማር ዕድል ይሆኑናል። አንዳንድ ገጠመኞቻችን ግን ከቀናነት ባፈነገጠ መልኩ፣ በስንፍና ወይም በእብሪት በዳኞች በሚሠሩ ስህተቶች እና ጥፋቶች አወንድናዝን፣ ለተጨማሪ እንግልት እንድንዳረግ፣ እንድናፍር እና ተስፋ እንድንቆርጥ ምክንያት ይሆናሉ። ሰሞኑን የገጠሙኝን አይነት የችሎት ገጠመኞች ግን የአንድ ሰሞን ሃሜት፣ የአንድ ቀን ብስጭት፣ የአንድ ቀን ማጉረምረም ብቻ ሆነው አይቀሩም። ይልቅም ዘላቂ ሐዘን የሚፈጥሩ፣ በሙያችን አስፈላጊነት ላይ ጥያቄ የሚያጭሩ፣ ጥልቅ ተስፋ መቁረጥ እና ድባቴ ውስጥ የሚከቱ ናቸው። እንዲህ አይነት ምሬቶች አልፎ አልፎ የሚከሰቱ ናቸው ብለው የሚያስቡ ብዙ ባለሙያዎች እና ዳኞች አሉ። ልክ "አንዳንድ" ብለን እንደምንገልፀው የሚመሰልላቸው። እውነታው ግን አንደሱ አይደለም። "አንዳንድ" ናቸው ብሎ ማሰብ የየዋህ ዕይታ ነው። ለዚህ ማረጋገጫው ደግሞ በውሳኔ ግልባጭ፣ በትዕዛዝ ግልባጭ፣ በመዝገብ ግልባጭ ... የሠፈሩ እና በቀላሉ በማስረጃ መረጋገጥ የሚችሉ ብዙ ጠበቆች የሚገጥሙን፣ በሐሜት፣ በትችት ... እርስ በእርስ ብናወራቸውም ለአደባባይ ማውጣቱ ክብር ለሚገባቸው ብዙ ዳኞች፣ ለፍርድ ቤቶች እና ለአጠቃላይ የፍትሕ ሥርዓታችን መልካም ስም የማይመጥኑ ናቸው ብለን የምንብሰከሰክበቸው ጉዳዮች ቁጥር ስፍር የሌላቸው መሆኑ ነው። ልክ በእኛ በጠበቆች መካከል እንዳሉ የነውር ጥጎች ማለት ነው። ስለዚህ እንዲህ አይነት ለሙያው እና ለፍትሕ የላቀ ክብር ካለው ባለሙያ የሚሰነዘር ትችት በአደባባይ ቢወጣ ለባለቤቱ ባዳ የሆነን ጆሮ ከማንቃት እና ዙሪያችንን ለማየት ከሚረዳ በስተቀር መርዝ አይደለም አይገድልም። ዳኞችንም ሆነ ፍርድ ቤቶችን አያንኳስስም፣ አያሳጣም። ይልቅም ለባለሙያዎች እና ለዳኞች የእርስ በእርስ መማማሪያ ሆኖ ለውይይት በር ይከፍታል። የተቋማቱ መሪዎችም አሠራሮችን ለመፈተሽ ይረዳቸዋል። የአንድ ሳምንት ሦስት ገጠመኞቼን እነሆ። ፍርድ ቤቶቹን፣ ዳኞቹን፣ ጉዳዮቹን እና የዳኞቹን ወይም ሠራተኞቹን ፆታ በዝርዝር ወይም በግልፅ ስለማልጠቅስ ትኩረታችሁ ጉዳዮቹ ላይ ይሁን! ገጠመኝ አንድ ለሁለተኛ ጊዜ "መስቀለኛ ጥያቄ ላይ መሪ ጥያቄ መጠየቅ አትችልም!" ተባልኩ! በአንድ ችሎት ምስክር ሲሰማ የተከሳሽን ምስክሮች መስቀለኛ ጥያቄ ስጠይቅ መሪ ጥያቄ ጠየቅኩኝ። መሪ ጥያቄ ማለት መልሱን የሚጠቁም ወይም ምስክሩ ሲመልስ "አዎ" ወይም "አይ" እንዲል የሚያሰኙ ጥያቄዎች ናቸው። በእንግሊዘኛ Leading Question ይባላሉ። የመስቀለኛ ጥያቄ ዓላማ ምስከሩ የመሰከረውን ነገር እውነተኛነት ማጣራት በመሆኑ መሪ ጥያቄ በዋነኛነት የሚፈቀድበት ጊዜ መስቀለኛ ጥያቄ ላይ ነው። ይሄ ደግሞ የሕግ ትምህርት ቤት ሀ ሁ በመሆኑ አንድ ዳኛ ይሄ ሊጠፋው አይገባም። የሕግ ብቻ ሳይሆን የተፈጥሮ ፍትሕ "Natural Justice" መርህ በመሆኑ የሕግ ባለሙያ ያልሆነ ሰው እንኳን በተለምዶ "በመስቀለኛ ጥያቄ አፋጠጠኝ ወይም አፋጠጥኩት" ሲል መስማት የተለመደ ነው። እና በዚህ አግባብ የተከሳሽን ምስክር መስቀለኛ ጥያቄ ስጠይቅ "ሰነዱ ይጥፋ አይጥፋ አያውቁም አይደል?" ብዬ ጠየቅኳቸው። የችሎቱ ዳኛ አስቆሙኝ እና መሪ ጥያቄ መጠየቅ አይችሉም አሉኝ። መጀመሪያ ጆሮዬን፣ ቀጥዬ ራሴን ተጠራጠርኩ። "መስቀለኛ ጥያቄ ላይ ነን እኮ" ብዬ ለችሎቱ መለስኩ። "እኮ መርተው መጠየቅ አይችሉም" አሉኝ። "የተከበረው ችሎት ምስክሩ እኮ የተከሳሽ ናቸው የእኔ አይደሉም። የምጠይቀው ደግሞ መስቀለኛ ጥያቄ ነው" አልኩ። "እኮ ነገርኮት መሪ ጥያቄ መጠየቅ አይችሉም። ጥያቄውን ያስተካክሉ!" አሉኝ ቆጣ ብለው። ግራ ቢገባኝ በእንግሊዘኛ "Cross Examination ላይ እኮ ነን። መሪ ጥያቄ በዚህ ጊዜ ካልጠየቅኩ መቼ ልጠይቅ ነው?! የሥነ ሥርዓት ሕጉም የሚለው ይሄንኑ አይደል?" አልኩ። .ዳኛው በቁጣ "ነገርኮት እንግዲህ ሲለቋቹ ትፈነጫላቹ። ሌላ ጥያቄ ቀጥሉ!" አሉኝ። ስሜቴን ቆጥቤ "ይመዝገብልኝ እሺ። የጠየቅኩት እኮ ሥነ ሥርዓታዊ ጥያቄ ነው። ይሄ መፈንጨት አይደልም" አልኩ። የዳኛው ቁጣ ባሰ አንተ እያሉ ያወሩኝ ጀመር "ይመዘገብልሃል። አትደንፋብኝ! ሌላ ጥያቄ ካለ ጠይቅ" ብለው አሥፈራሩኝ። ሌላውን ተዉትና ይሄ ጉዳይ ሲገጥመኝ ሁለተኛ ጊዜዬ ነው። በሌላ ችሎትም የባሰ ገጥሞኝ እንዲሁ ተንፍሼው ነበር። ይሄ አሁን የዳኛ ስህተት ነው የሚባለው? የአቅም ውስንነት ነው የሚባለው? የዳኛ እና የጠበቃ ቋንቋ በሕጉ ተፅፏል። እኔ ከተሳሳትኩ በሕጉ አግባብ ልታረም ይገባል። ዳኛው ከተሳሳቱ በሕጉ አግባብ ብይን መስጠት የአባት ነው። "አትደንፋብኝ" ማለት ምን ማለት ነው? ገጠመኝ ሁለት ከሟች ባሏ ጋር የጋራ ልጆች ያሏት እናት አንቺ በሕይወት ስላለሽ የሟች ባልሽን ድርሻ በሙሉ አንቺ እንጂ የጋራ ልጆቻችሁ መውረስ አይችሉም ብትባልስ?! ለመግቢያ ያህል ይቺን ልበል። አይደለም የሕግ ባለሙያ ማንኛውም ኢትዬጵያ ውስጥ ተወልዶ ያደገ ሰው በቀላሉ የሚገባው የውርስ ሕግ ጉዳይ አለ። አባት ልጆች ወልዶ ቢሞት እና ሚስቱ ወይም የልጆቹ እናት በህይወት ካለች የአባት እና የእናት የጋራ ሀብት ለሁለት ይከፈላል። 50% ድርሻ ለእናት የቀረው 50% ድርሻ ደግሞ መውረስ ለሚችሉት ልጆቹ እኩል እኩል ይካፈላል። ይሄም የውርስ ሕግ ሀ ሁ ነው። አንድ ጓደኛዬ ለጓደኛው ቤተሰብ የውርስ ክርክር ጉዳይ በነፃ የሕግ ምክር እና የፅሑፍ አገልግሎት ይሰጣል። ለባለጉዳዩ አስፈላጊውን ማስረጃ አያይዞ ውርስ እንዲጣራ አቤቱታ ፅፎ ይሰጣቸውዋል። ባለጉዳዩ በራሳቸው አንዱ ምድብ ችሎት ቀርበው ፋይል ሲያስከፍቱ ጉዳዩን የያዙት የፍርፍ ቤቱ ሬጅስትራር ጠበቃው የፃፈውን አቤቱታ አዩና "አባታችሁ ናቸው የሞቱት። እናታችሁ በሕይወት አሉ አይደል? ልጆች የአባታችሁን .. እንውረስ ብላችሁ ነው አይደል የምጠይቁት" አሏቸው። ባለጉዳዩ "አዎ" አሉ። ሬጅስትራሩ ቀጠሉ "እና እናት በሕይወት እያለች ነው እናንተ የአባታችሁን ድርሻ ሙሉ ለሙሉ እንውረስ የምትሉት? እናት በሕይወት ካለች የአባታችሁን ድርሻ 100% የምትወርሰው እናት ናት። ስለዚህ የሕግ ባለሙያ አማክሩ እና አስተካክለው ይምጡ" አሏቸው። እኚህ ባለጉዳይ ጠበቃው ጓደኛዬ የውርስ አቤቱታውን የፃፈላቸው በነፃ በመሆኑ የግብር ውጣ ሥራ እንደሠራላቸው አስበው ፍርድ ቤት ሲደርሱ የተባሉትን ሳይነግሩት ፍርድ ቤት ደጅ ላይ ያሉ ፀሐፊዎች ጋር ገብተው በሬጅስትራሩ በታዘዙት መሠረት የሟች አባትን የሀብት ድርሻ 100 % በሕይወት ያለች እናታቸው እንድትወርስ የሚጠይቅ አቤቱታ አፅፈው ፋይሉ ይከፈትላቸዋል።

ይህ አዋጅ በ1968 ዓ.ም የወጣ ሲሆን፤ የወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ሥነ ሥርዐቱንና የፍትሐ ብሔር ሥነ ሥርዓት ሕጉን ለማሻሻል የወጣ ነው። ይህ አዋጅ ግን አሁንም በሥራ ላይ ይሆን? ወይስ ተሽሯል? የምታውቁ አባላት ሐሳብ ስጡበት።

ተሰናባቹ ምክርቤት ሰኔ 17/2018 አ.ም የመረጃ ነጻነት አዋጅን አጽድቋል። ይህ አዋጅ ከአካል ጉዳተኞች መብቶች አንጻር ተራማጅ የሚባል ድንጋጌ ይዟል። አዋጁ በተቋማት ላይ መረጃዎችን ለአካል ጉዳተኞች ሊነበብ፣ ሊታይ ወይም ሊደመጥ በሚችል አግባብ ተደራሽ የማድረግ ግዴታን ይፈጥራል። በሀገራችን የሚወጡአካል ጉዳተኞችን የሚመለከቱ ህጎች ከሚታሙባቸው ምክንያቶች አንዱ ጥርስ አልባ የመሆናቸው ነገር ነው። በዚህ ረገድ የመረጃ ነጻነት አዋጅ ለአካል ጉዳተኛ ሊነበብ፣ ሊታይ ወይም ሊደመጥ በሚችል አግባብ ተደራሽ ለማድረግ ምክንያታዊ ዕርምጃ የመውሰድ ግዴታን ያልተወጣ አካል ከአንድ ዓመት በማይበልጥ ቀላል እስራት ወይም ከ25 ሺሕ እስከ 50 ሺሕ ብር በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ ወይም በሁለቱም እንደሚቀጣ ተደንግጓል። ይህን አዋጅ ለሁሉም ባለድርሻ አካላት ለማስተዋወቅ እና ከአዋጁ ፍሬ አካል ጉዳተኞች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ሰፊ የግንዛቤ ፈጠራ ስራ የማከናወን ተግባር የመንግስት ተቋማት እና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሀላፊነት ነው። ህጉ መውጣቱ ብቻውን ለውጥ ስለማይፈጥር ህጉ የያዛቸውን በረከቶች በተግባር ላይ ለማዋል ሰፊ ስራዎችን በተቀናጀ መልኩ መስራት ያስፈልጋል። ለዚህም የመንግስት ተቋማት እና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች (CSOs) የሚከተሉትን ኃላፊነቶች መወጣት አለባቸው፡- 1. የአዋጁን ይዘት በተመለከተ ለሁሉም ባለድርሻ አካላት ሰፊ የግንዛቤ ፈጠራ ስራ መስራት። 2. አካል ጉዳተኞች ስለ መብታቸው አውቀው ከአዋጁ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማገዝ። 3. ተቋማት መረጃዎቻቸውን ተደራሽ እንዲያደርጉ የቴክኒክና የሙያ ድጋፍ መስጠት። ማስታወሻ፣ የመረጃ ነጻነት አዋጅ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ በሚወጣበት ግዜ ህጉን ተደራሽ ለማድረግ ማህበራችን ከሌሎች አጋር አካላት ጋር በመሆን የተቀናጁ ጥረቶችን ያደርጋል።

906_2014_የነዳጅ_ማደያ_በሌለባቸው_ከተሞች_እና_አከባቢዎች_የነዳጅ_የችርቻሮ_ፈቃድ_አሰጣጥና_የቁጥ.pdf2.97 KB

‎ቀልድ የሚመስል ነገር ግን ትልቅ ቁም ነገር የያዘ ሃሳብ ‎================================== By dessie muliyyei law shelf. ‎የጎረቤቴ ዛፍ ቅርንጫፍ ወደ እኔ ግቢ ዝቅ ቢል "ቆርጬ እጥላለሁ" ማለት ይቻላል? ሕጉ ምን ይላል? ‎ ‎በመኖሪያ ሰፈራችን የጎረቤታችን ዛፍ ቅርንጫፍ ወይም ሥር አጥራችንን አልፎ ወደ እኛ ግቢ ሊገባ ይችላል። በዚህ ጊዜ ብዙ ሰው "የእኔ ግቢ ስለሆነ የፈለግኩትን ማድረግ እችላለሁ" ብሎ ያስባል። ነገር ግን የኢትዮጵያ የፍትሐብሔር ሕግ አንቀጽ 1217 የሚገርም ድንጋጌ አስቀምጧል! ‎ ‎ሕጉ ምን ይላል? ‎ ‎1/ ቅርንጫፎች ወደ እርስዎ ግቢ ከመጡ፦ የጎረቤትዎ ዛፍ ቅርንጫፍ ወደ እርስዎ ግቢ አልፎ ጥላ ቢጥል ወይም ቢረብሽዎ፣ ቅርንጫፉን በራስዎ የመቁረጥ መብት የለዎትም! ‎ ‎ይልቁንም ጎረቤትዎ እንዲቆርጥላቸው የመጠየቅ መብት ነው ያለዎት። ‎ ‎2/  የዛፉ ሥር ወደ እርስዎ ግቢ ከመጣ ግን፦ እዚህ ጋር ሕጉ ይቀየራል! የዛፉ ሥር ወደ እርስዎ መሬት ውስጥ ከገባና እንቅፋት ከሆነብዎት፣ ለጎረቤቱ ሳያሳውቁ ሥሩን የመቁረጥና ለራስዎ የመውሰድ ሙሉ መብት አለዎት! ‎ ‎ በጣም የሚገርመው ነጥብ! (ፍሬው የማን ነው? ‎የጎረቤቱ ዛፍ ቅርንጫፍ ወደ እርስዎ ግቢ ዝቅ ብሎ ቢመጣና ፍሬ ቢያፈራ (ለምሳሌ ማንጎ ወይም ፓፓያ)፦ ‎ቅርንጫፉ የጎረቤት ስለሆነ ፍሬውን መቅጠፍ አይችሉም። ‎ ‎ነገር ግን ፍሬው በራሱ ጊዜ ተለይቶ ወደ እርስዎ ግቢ ከወደቀ፣ ፍሬው በሕግ የርስዎ ይሆናል! ባለቤቱ መጥቶ "የእኔ ዛፍ ፍሬ ስለሆነ መልስልኝ" የመባል መብት የለውም። ‎ ‎ ከዚህ ሕግ ምን እንረዳለን? ‎ ‎ሕጉ የአየር ላይ (ቅርንጫፍ) እና የመሬት ውስጥ (ሥር) ወሰንን ለይቶ ያስቀምጣል። ‎ቅርንጫፉን ባለቤቱ እንዲቆርጠው በማድረግ ሰላማዊ ጎረቤትነትን ያበረታታል። ‎ ‎"ጎረቤትና አጥር አይለወጥም። ሕጉን ማወቅ አላስፈላጊ ጸብን ይቀንሳል። የጎረቤትዎ ዛፍ ፍሬ እስኪወድቅ ድረስ በትዕግስት መጠበቅ ከሕግም ከሞራልም ትክክለኛ መንገድ ነው!" ‎ ‎ፍትህ ለሁሉ! የጎረቤታችሁ ዛፍ አስቸግሯችሁ ያውቃል? ምን አደረጋችሁ? Pacta Sunta Servanda

[forwarded from] Z Getahun1, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ፍ/ቤቶችን ለማቋቋም ዐዋጅ በማርቀቅ ምክክር አደረገች፣ ዐዋጁ በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ጸድቆ ወደ ተግባር ሲገባም ፍ/ቤቶቹ በተከራካሪ ወገኖች ፈቃድ ላይ በተመሠረተ ቅድመ ሁኔታ በጋብቻ፣ በፍቺ፣ በቀለብ አወሳሰን፣ በውርስና ስጦታ ጉዳዮች እንዲሁም ከቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች የሥራ ግንኙነትና ከቀኖናዊ አስተምህሮ ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ላይ የወል ሥልጣን እንደሚኖራቸው ገልጻለች:: ይህ ጥሩ የሚባል ሲሆን በዚህ ሁኔታ የሚቋቋሙት ፍ/ቤቶች የቤተሰብ እና የግል ሕግ ጉዳዮች በሚመለከቱ ጉዳዮች ብቻ ሳይሆን የቅድስት ቤተክርስቲያኒቱ አገልጋዮች የሥራ ግንኙነትና ከቀኖናዊ አስተምህሮ ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ላይም የዳኝነት ሥልጣን የሚኖራቸው ከመሆኑ አኳያ በንጽጽራዊ ዕይታ በይዘት ከሸሪዓ ፍ/ቤቶች የሥልጣን ወሰን ሰፋ ይላል:: እንደሚታወቀው በህገመንግስቱ አንቀፅ 34(5) እና 78(4) መሰረት የሀይማኖትና የባህል ፍ/ቤት ሊቋቋም እንደሚችል ቢደነግግም እስካሁን በእስልምናው ብቻ የሸሪአ ፍ/ቤት ተቋቁሞ ወደ ስራ ተገብቷል። ስለሆነም ይህ የሚበረታታ ተግባር ነው። በቅርቡ የአማራ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የባህል ፍርድ ቤቶችን ማቋቋማቸው አይዘነጋም።@SM

Amhara Region Civil Servants Proc309.pdf2.11 MB

አስገራሚ ህግጋቶች😳 ፨ Messi በተወለደበት Rosario, Argentina ከ2014 ወዲህ በወጣው ህግ መሰረት ወላጆች ለልጆቻቸው "Messi" የሚል ስም ማውጣት ክልክል ነው። ፨ በጀርመን የመንገድ መዘጋጋት እና  መጨናነቅ ከተፈጠረ መኪኖች ዳራቸውን በመያዝ የመሃሉን መንገድ ለአንቡላንሶች ክፍት የማድረግ ግዴታ አለባቸው። ፨በአሜሪካ ግዛት በኦክላሆማ በውሻ ላይ መቀለድ በህግ ያስቀጣል። አንድ ሰው ወደ ውሻ ጠጋ በማለት አስቂኝ 😄 የሆነ ፊት ለውሻው ቢያሳይ በገንዘብ ወይም በእስር እንደሚቀጣ በህግ ተደንግጓል። ፨በ1685 ካናዳ ውስጥ(በዚያን ጊዜ new France ነበር የምትባለው) ከፍተኛ የሆነ ገንዘብ እጥረት አጋጥሞ ነበር። እናም በዚያ ሰዓት የነበሩ ቅኝ ገዥዎች ባለስልጣናት የመጫወቻ ካርድን (ካርታ) እንደገንዘብ እንዲያገለግል ወስነው በካርድ ሰዎች እየተገለገሉ ነበር። ፨በአንድ ወቅት England ውስጥ እራስን ለማጥፋት መሞከር እንደ ወንጀል ይቆጠር ነበር።እሚገርመው እራሱን ለማጥፋት መሞከሩ ከተረጋገጠ የሞት ፍርድ ነበር የሚፈረድበት😂 ፨በሱዳን ውስጥ ከማን ጋር የፍቅር ግንኙነት እንደያዘዎት ጥንቃቄ ማድረግ አለብዎት። አንድ ወንድ ከሴት ጋር ሲተኛ ከተያዘ የቤተሰቧን ክብር ለማዳን ወዲያውኑ ማግባት እንዳለበት የሚደነግግ ህግ አለ። 2006 ሕጉ በፍየልም ላይ ተፈጻሚ ሆነ። 🐐🙄 ቻርለስ ቶምቤ ከፍየል ጋር ግንኙነት ሲፈጽም ተይዞ በህዝብ እንዲዋረድ በሚል ለባለቤቱ ከፍሎ ፍየሏን እንድያገባ ተገዷል። 🤓😁 ፨ በአሜሪካ ኦሪገን ግዛት አንድ ሰው ከ ዝናብ ውሃ ሲደቅን ተገኝቶ በእስር እና 1,500 ዶላር ተቀጥቶ ነበር።ምክንያቱ ደግሞ የመንግስት ንብረት ነው ማስፈቀድ ነበረበት በሚል። ፨ በአውስትራሊያ ቪክቶሪያ ከተማ ውስጥ አምፖል ከተቃጠለ ማንም ሰው ተነስቶ አምፖል መቀየር አይችልም። ኤሌክትሪሻን ወይም የመብራት ሰራተኛ ካልሆነ ፍቃድ ሰው አምፖል መቀየር በህግ ያስቀጣል።🤓

አዲሱ የሼሪአ ፍርድቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ ምን ምን አዳዲስ ነገሮችን ይዟል? ሰላም ተከታታዮቼ...ለዛሬ ሰሞኑን በጸደቀው አዲሱ የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ማቋቋምያ አዋጅ ላይ መጠነኛ የሆነች ማብራርያን የማቀርብላችሁ ይሆናል። ይህም ማብራርያ የአዋጁን ዋና ዋና ይዘቶች፣ ያመጣቸውን አዳዲስ ለውጦች እና ህጋዊ አንድምታዎች ይዳስሳል። 1. ሕገ-መንግሥታዊ መሠረት እና የአዋጁ አስፈላጊነት ይህ አዋጅ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 34(5) እና 78(5) ላይ የተደነገገውን መሠረት በማድረግ የወጣ ነው። ሕገ-መንግሥቱ የግል እና የቤተሰብ ጉዳዮች በተከራካሪዎች ፈቃደኝነት በሃይማኖት ወይም በባህል ሕጎች ሊዳኙ እንደሚችሉ ይደነግጋል። ከሩብ ምዕተ ዓመት በላይ ያስቆጠረውን አሮጌ አዋጅ (አዋጅ ቁጥር 188/1992) በአዲስ መተካት ያስፈለገበት ዋና ምክንያት፣ የፍርድ ቤቶቹን የዳኝነት ነፃነት ለማረጋገጥ፣ ተጠያቂነት የሰፈነበት ሥርዓት ለመዘርጋት፣ ቀልጣፋ የፍትህ አገልግሎት ለመስጠት እና ጠንካራ የፍርድ ቤት አስተዳደር ጉባዔ ለማቋቋም ነው። 2. የዳኝነት ሥልጣን እና የፈቃደኝነት መርህ የሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ሥልጣን በዋናነት በግል እና በቤተሰብ ጉዳዮች ላይ የተገደበ ነው። የጉዳይ ዓይነቶች፡ ጋብቻ፣ ፍቺ፣ ቀለብ፣ የልጆች አስተዳደግ (ሞግዚትነት)፣ የወቅፍ አስተዳደር፣ ስጦታ (ሂባ) እና የውርስ ጉዳዮች ዋነኞቹ ናቸው። በተጨማሪም በግልጽ የሸሪዓ ሕግን መሠረት አድርገው የተመሠረቱ ስምምነቶች በዚህ ፍርድ ቤት ይታያሉ። የፈቃደኝነት መርህ (Consent)፡ ፍርድ ቤቶቹ እነዚህን ጉዳዮች የማየት ሥልጣን የሚኖራቸው ተከራካሪ ወገኖች በሸሪዓ ሕግ ለመዳኘት "ፈቃደኛ" ሲሆኑ ብቻ ነው። ፈቃደኝነት የሚረጋገጥበት መንገድም ግልጽ ተደርጓል፤ አንዱ ወገን አቤቱታ አቅርቦ ሌላኛው በመጀመሪያው ቀጠሮ ፈቃደኛነቱን ከገለጸ፣ ወይም መጥሪያ ደርሶት ሳይቀርብ ከቀረ (በሌለበት እንዲታይ ከተወሰነ) እንደ ፈቃደኝነት ይቆጠራል። የተከራካሪዎች መብት ተተኪ የሆኑ ሶስተኛ ወገኖችም ይህንኑ የፈቃደኝነት መርህ መከተል አለባቸው። 3. የፍርድ ቤቶች አደረጃጀት እና የሥልጣን ክፍፍል አዋጁ የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶችን በሶስት እርከን ያዋቅራል፡ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ሸሪዓ ፍርድ ቤት፡ ግምታቸው እስከ 10 ሚሊዮን ብር የሚደርሱ ጉዳዮችን በመጀመሪያ ደረጃ የማየት ሥልጣን አለው። ችሎቱ በአንድ ዳኛ ይመራል። የፌዴራል ከፍተኛ ሸሪዓ ፍርድ ቤት፡ ግምታቸው ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ የሆኑ ጉዳዮችን በመጀመሪያ ደረጃ፣ እንዲሁም ከመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የሚመጡ ይግባኞችን ያያል። ችሎቱ በሶስት ዳኞች (አንድ ሰብሳቢና ሁለት ዳኞች) ያስችላል። የፌዴራል ጠቅላይ ሸሪዓ ፍርድ ቤት እና የሰበር ችሎት፡ ከፍተኛው እርከን ሲሆን የይግባኝ ሥልጣን አለው። ከሁሉም በላይ አዋጁ ያስተዋወቀው ትልቁ ለውጥ "የሰበር ሰሚ ችሎት" መቋቋሙ ነው። ከ5 ያላነሱ ዳኞች የሚሰየሙበት የሰበር ችሎት የሚሰጠው የሕግ ትርጉም በየትኛውም የሃገሪቱ ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ላይ አስገዳጅነት ይኖረዋል። ይህ ወጥ የሆነ የሸሪዓ ሕግ አተረጓጎም እንዲኖር ይረዳል። 4. የዳኞች መመዘኛ እና የፍርድ ቤቶች አስተዳደር ጉባዔ የፍትህ ሥርዓቱን ታማኝነት፣ ገለልተኝነትና ሞያዊነት ለማሳደግ ጥብቅ መመዘኛዎች ተቀምጠዋል፡ የዳኞች መመዘኛ፡ ሙስሊም ኢትዮጵያዊ የሆነ፣ በሸሪዓ ሕግ ትምህርት ተቋማት የሰለጠነ ወይም በቂ ልምድ ያለው፣ መልካም ስነ-ምግባር ያለው፣ የወንጀል ሪኮርድ የሌለበት፣ ዕድሜው ከ25 ዓመት በላይ የሆነ እና የየትኛውም የፖለቲካ ፓርቲ አባል ያልሆነ መሆን አለበት። ሹመታቸውም በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይጸድቃል። የአስተዳደር ጉባዔ፡ የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች አስተዳደር ጉባዔ መቋቋም ሌላው ቁልፍ አሰራር ነው። ጉባዔው ከፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት፣ ከሸሪዓ ፍርድ ቤቶች አመራሮች፣ ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት (ዑለማ ጉባዔ) እና ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተውጣጡ አባላት ይኖሩታል። የዳኞችን ምልመላ፣ ዲሲፕሊን፣ የደረጃ እድገት፣ እና የበጀት ጉዳዮችን በበላይነት ይቆጣጠራል፤ ውሳኔዎችንም ይሰጣል። 5. ልዩ ልዩ ህጋዊ ድንጋጌዎችና አሰራሮች የአስተዳደር ጉባዔ፡ የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች አስተዳደር ጉባዔ መቋቋም ሌላው ቁልፍ አሰራር ነው። ጉባዔው ከፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት፣ ከሸሪዓ ፍርድ ቤቶች አመራሮች፣ ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት (ዑለማ ጉባዔ) እና ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተውጣጡ አባላት ይኖሩታል። የዳኞችን ምልመላ፣ ዲሲፕሊን፣ የደረጃ እድገት፣ እና የበጀት ጉዳዮችን በበላይነት ይቆጣጠራል፤ ውሳኔዎችንም ይሰጣል። 5. ልዩ ልዩ ህጋዊ ድንጋጌዎችና አሰራሮች ፍርድ ቤትን መድፈር፡ የፍርድ ቤቱን ነፃነት የሚጋፋ ወይም የችሎት ትዕዛዝን አለመፈጸም / መሰናክል መፍጠር ከባድ ቅጣት (እስራትና የገንዘብ መቀጮ) እንደሚያስከትል ተደንግጓል። ውሳኔን ማስፈጸም፡ ፍርድ ቤቶቹ የሚሰጧቸው ውሳኔዎች በመደበኛ ፍርድ ቤቶች አፈጻጸም ሕግ መሠረት በአስፈጻሚ አካላት ተግባራዊ የመሆን ግዴታ አለባቸው። በተለይም በፍርድ ቤቱ የሚወሰኑ የጋብቻ ኩነቶች በድጋሚ ሥነ-ሥርዓት ሳያስፈልግ በቀጥታ በወሳኝ ኩነቶች መዝገብ እንዲሰፍሩ መደረጉ የዜጎችን እንግልት በእጅጉ ያስቀራል። ማጠቃለያ በአጠቃላይ ይህ አዋጅ የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶችን አሠራር ዘመናዊ፣ ተቋማዊ እና ተጠያቂነት ያለው ለማድረግ ሰፋ ያለ ማሻሻያ ያደረገ ነው። በተለይም የሰበር ችሎት መቋቋም፣ የፖለቲካ ገለልተኝነትን በዳኞች ላይ ማስገደድ እና ጠንካራ የአስተዳደር ጉባዔ ማደራጀት፣ የሸሪዓ ፍትህ ሥርዓቱ ከሀገሪቱ የሕግ ማዕቀፍ ጋር ተጣጥሞ በብቃት እንዲሰራ የሚያስችል ትልቅ ህጋዊ እርምጃ ነው።

Repost from Law studies ⚖️
🧬 የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ በቤተሰብ እና ማስረጃ ሕግ: ቁልፍ የሰበር ውሳኔ መርሆዎች ⚖️  1. 🛡 የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ እንደ መከላከያ ማስረጃ እንጂ እንደ ፍርድ ቤት ግዴታ ያለመወሰዱ ➡️ በአባትነት ማረጋገጫ ክስ ላይ ዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ አባትነትን ለማረጋገጥ የሚቀርብ የመከላከያ ማስረጃ እንጂ፣ ፍርድ ቤቱ በራሱ አነሳሽነት ሊያዝ የሚገባው አይደለም። የአባትነት ክስ ሲቀርብ ተከሳሹ መጥሪያ ደርሶት ለመቀበል ፈቃደኛ ሳይሆን ቀርቶ የመከራከር መብቱን ራሱ የተወ ከሆነ፣ ቀርቦ የመከላከያ መብቱን ስላልተጠቀመ የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ የመጠየቅ መብቱን ከክሱን ከመከላከል ጋር እንደተወ ይቆጠራል [ሰ/መ/ቁ 154767]። በመሆኑም ፍርድ ቤቱ በሌለበት ውሳኔ መስጠቱ ስነ ስርዓታዊ አግባብን የጣሰ አይደለም [ሰ/መ/ቁ 154767]። 2. 📜 የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ ትዕዛዝ በሦስተኛ ወገን (ኑዛዜ ተጠቃሚ) ሲጠየቅ ❌ የቤተሰብ ሕግ የአባትነት መካድ ክስ ሊያቀርቡ የሚችሉ ወገኖችን ማንነት ይገድባል። የኑዛዜ ተጠቃሚ የሆነ ሦስተኛ ወገን፣ የመካድ ክስ ለማቅረብ ከተፈቀደላቸው ሰዎች ውስጥ የማይካተት በመሆኑ፣ እንዲሁም የመካድ ክስ ለማቅረብ የሚያስፈልገውን የፍርድ ቤት ፈቃድ አስቀድሞ ባለማግኘቱ፣ ያለምንም ሕጋዊ መሠረት የዘረመል (D.N.A) ምርመራ እንዲደረግ ማዘዙ ከመነሻው በሕጉ የተመለከተውን ሥርዓት ያልተከተለ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ነው [ሰ/መ/ቁ 152719]። 3. 🔨 የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ ትዕዛዝ ባለመፈጸሙ ምክንያት በፍሬ ነገር ላይ መወሰን ⏳ ለቀጠሮ ምክንያት የሆነው ጉዳይ (እንደ ዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ ውጤት) ሳይፈጸም የቀረው ከተከራካሪ ወገኖች በአንዱ ጉድለት ከሆነ፣ ፍርድ ቤቱ የጉዳዩን መፈጸም ሳይጠብቅ የመሰለውን ውሳኔ ለመስጠት ይችላል [ሰ/መ/ቁ 152100]። በመሆኑም፣ ፍርድ ቤቱ ዲ.ኤን.ኤ ምርመራ እንዲደረግ ትዕዛዝ ከሰጠ በኋላ፣ ትዕዛዙን አልፎ በሌሎች ማስረጃዎች (ለምሳሌ በሰው ምስክር ቃል) ላይ ተመስርቶ የሟች ልጅነትን ማጽናቱ መሰረታዊ የሕግ ስህተት አይደለም [ሰ/መ/ቁ 152100]። 4. ⚖️ የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ እንደ ገዥ (Conclusive) ማስረጃ አለመቆጠሩ እና ከሌሎች ማስረጃዎች ጋር መመዘን 🔬 የዘረመል (DNA) ምርመራ ውጤት ብቻውን ፍፁማዊ ገዥ (conclusive) ማስረጃ አይደለም ። አባትነትን የማረጋገጥ ዓላማ ሲኖር፣ የምርመራ ውጤቱ በሌሎች የማስረጃ ዓይነቶች (ለምሳሌ ልጁን እንደ አባት በመንከባከብ፣ የሰው ምስክር ቃል ወይም የልጅነት ሁኔታ) ሊረጋገጥ ከሚችለው ፍሬ ነገር ጋር ተመዝኖ መታየት አለበት ። 5. 👂 የሳይንሳዊ ማስረጃን የመስማት ግዴታ (ለማስተባበል) 🚨 ፍርድ ቤቶች በተከራካሪ ወገኖች የልጅነት ግምትን ለማስተባበል ሲባል የዘረመል ምርመራ እንዲደረግ የቀረበውን አቤቱታ በአግባቡ ማስተናገድ አለባቸው ። 🛑 አንድ ወገን የልጅነት ግምትን ለመቃወም የዲ.ኤን.ኤ ምርመራ እንዲደረግ ጠይቆ እያለ ፣ የስር ፍርድ ቤት ጥያቄውን ሳይመረምር ወይም ውድቅ ያደረገበትን ምክንያት ሳይገልጽ ውሳኔ መስጠቱ ፣ እንዲሁም በሰው ምስክሮች ቃል ላይ ብቻ ተመርኩዞ አባትነትን ማረጋገጡ የሰበር ሰሚ ችሎት ገዥ ትርጉም የሚፃረር መሠረታዊ የሕግ ስህተት ነው ። 📝 በልደት ምስክር ወረቀት ወይም በልጅነት ሁኔታ (circumstantial evidence) የተረጋገጠ የሕግ ግምት በሳይንሳዊ ማስረጃዎች እንደ ዲ.ኤን.ኤ ምርመራ ሊስተባበል ይችላል ። 6. 💵 የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ ወጪ እና የፍትሕ አሰጣጥ 💰 ምንም እንኳን ምርመራውን የጠየቀው ወገን ወጪ የመሸፈን ኃላፊነት ቢኖርበትም ፣ የገንዘብ አቅም አለመኖር ፍትሕን ሊያጓድል አይገባም። ፍርድ ቤቱ የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ ወጪው በማን ይሸፈን የሚለውን ከሕግ አኳያ አይቶ መወሰን ሲገባው፣ ይህን አለማድረጉ ስህተት ነው ። 7. ⭐️ የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ ጥራት እና ተጨማሪ የባለሙያ አስተያየት ⚰️ ከሟች አስክሬን የተወሰደ የዘረመል (DNA) ናሙና በብክለት ምክንያት አስተማማኝ ውጤት መስጠት ባልቻለበት ሁኔታ፣ ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን የበለጠ ግልጽ ለማድረግ ተጨማሪ የልዩ አዋቂ ባለሙያ አስተያየት መስማቱ የፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 136ን የተከተለ በመሆኑ የሚነቀፍ አይደለም ። 8. 👰‍♀️ በጋብቻ ውስጥ ለተወለደ ልጅ የአባትነት ግምት እና የመካድ ክስ 💍 በጋብቻ ውስጥ የተወለደ ወይም የተጸነሰ ልጅ የአባትየው ነው ተብሎ በሕግ ይገመታል ። አባትነት በሕግ በተሰጠው ግምት መሠረት የተረጋገጠ እንደሆነ፣ አመልካች የምርመራውን ውጤት ከመጠየቅ በፊት በቤተሰብ ሕጉ በሚፈቅደው አግባብ የመካድ ክስ ማቅረብ ይኖርባታል ። በፍሬ ነገር ደረጃ በጋብቻ ውስጥ መወለድ መረጋገጡ፣ የዘረመል (DNA) ምርመራ ይደረግ የሚለውን ክርክር ተቀባይነት ያሳጣዋል ። 9. 🗑 በሌላ ማስረጃ አባትነት ሲረጋገጥ የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራን ውድቅ ማድረግ 📄 በልደት ምስክር ወረቀት ወይም በቂ የሰነድና የሰው ማስረጃዎች በመመርመር እናትነት ወይም ልጅነት የተረጋገጠ እንደሆነ ፣ ፍርድ ቤቶች ተጨማሪ የዲ.ኤን.ኤ ምርመራ እንዲደረግ የቀረበው ክርክር ተቀባይነት የለውም በማለት ውድቅ ሊያደርጉ ይችላሉ ።

#የሰራተኞችድምጽ📢 በአማራ ክልል የሚገኙ ዓቃቢያነ ህግ የፌደራል መንግስት ያደረገው ሀገራዊ የደመወዝ ማሻሻያ እስካሁን ተግባራዊ አልተደረገልንም ሲሉ ቅሬታ አቅርበዋል። " በአንድ የፍትህ ሥርአት ውስጥ ለዳኞች የደሞዝ ማሻሻያው ተተግብሮ ለዓቃቢያነ ህግ መቅረቱ አግባብ ያልሆነና በፍትህ ስርዓቱ ላይ ጫና የሚያሳድር ጉዳይ ነው " - የክልሉ ፍትሕ ቢሮ በአማራ ክልል ውስጥ በማገልገል ላይ የሚገኙ ዓቃቢያነ ህግ፣ የፌደራል መንግስት ያደረገው ሀገራዊ የደመወዝ ማሻሻያ እስካሁን ተግባራዊ እንዳልተደረገላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸውን ገልጸዋል። ዓቃቢያነ ህጉ፥ የ2018 በጀት ዓመት የደመወዝ ማሻሻያ መመሪያ ቁጥር 1110/2018 እነሱንም የሚያካትት ቢሆንም፣ የበጀት ዓመቱ ሊጠናቀቅ ጥቂት ቀናት ብቻ እስኪቀሩት ድረስ ምንም ዓይነት ጭማሪ እንዳልተደረገላቸው ገልጸዋል። የፌደራል ዓቃቢያነ ህግ የማሻሻያው ተጠቃሚ በሆኑበት ሁኔታ፣ የክልሉ ባለሙያዎች ተነጥለው መቅረታቸው አግባብ እንዳልሆነና አሳሳቢ የህልውና ጥያቄ በመሆኑ በአስቸኳይ ምላሽ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ የባለሙያዎቹን ቅሬታ ይዞ የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ ዋና ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ጎሽምን በስልክ አነጋግሯል። የክልሉ ፍትህ ቢሮ ዋና ኃላፊ በዝርዝር ምን አሉ ? የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ ሀገራዊ የደሞዝ ጭማሪው ከመታወጁ በፊት በክልሉ የዓቃቢያነ ህግ የደረጃ ማሻሻያ ተደርጎ እንደነበር አንስተዋል። " ከፌደራል የደሞዝ ጭማሪ መጥቷል ሲባል የክልሉ መንግስት ያደረገውን የደረጃ እድገት ማስተካከያን መነሻ ያደረገ ሪፖርት ለፌደራል መንግስት ልከናህ። ይሁን እንጂ ሀገራዊው የደሞዝ ስኬል ማሻሻያ ግን ለክልሉ ዓቃቢያነ ህግ እስካሁን አልተላከም። ለምንድነው እስካሁን ያልመጣው? የሚለው የኛም ጥያቄ ነው። የፌደራል ፍትህ ሚኒስቴሯን ሰብሳቢ ያደረገ ኮሚቴ ተቋቁሟል። የገንዘብ ሚኒስቴር እና ለሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ለጉዳዩ መፍትሄ እንዲሰጡም ጥረት እየተደረገ ነው። የዳኞች የደሞዝ ማሻሻያ በቅርቡ በዚህ አንድ ወር ውስጥ ተግባራዊ ተደርጓል። በአንድ የፍትህ ስርዓት ውስጥ ለዳኞች የደሞዝ ማሻሻያው ተተግብሮ ለዓቃቢያነ ህግ መቅረቱ አግባብ ያልሆነና በፍትህ ስርዓቱ ላይ ጫና የሚያሳድር ጉዳይ ነው። የእኛም አቋም ሀገራዊ ጭማሪው ለዓቃቤ ህግም መምጣት አለበት የሚል ነው " ሲሉ ነግረውናል። የዐቃቢያነ ህግ ጥያቄ የደሞዝ ጭማሪው እስከ ውዝፍ ክፍያው ይከፈለን የሚል መሆኑን ለኃላፊው ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄ ሀገራዊ የደሞዝ ማሸሻያው መመሪያ መስከረም ላይ እንደወጣ አስታውሰው እንደ አማራ ክልል ከመስከረም ጀምሮ ውዝፉም አብሮ ይሰጠን የሚል ጥያቄ ለፌደራል መቅረቡን አሳውቀዋል። በመጨረሻም የፌደራል መንግስት ውሳኔውን አሳልፎ በጀቱን ሲለቅ፣ የክልሉ ፍትህ ቢሮ የዚህን በጀት ዓመት ውዝፍ ክፍያ በቀጥታ ለባለሙያዎቹ ተደራሽ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን አቶ ብርሃኑ ጠቁመዋል። የጊዜ ጉዳይ እንጂ መፍትሄ ማግኘቱ የማይቀር መሆኑን የገለጹት ኃላፊው፣ የፍትህ ሚኒስቴር ማኔጅመንትም በትናንትናው እለት በጉዳዩ ላይ ውይይት ማድረጉንና በቀጣይም ከገንዘብ ሚኒስቴር እና ከሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ጋር የሚደረገውን ንግግር ኮሚቴው አጥብቆ እንደሚከታተለው ተናግረዋል።

Assaf Hailu የሥርዓት የሕይወት መቅረዝ መጥፋት! _______ (የወፍ-በረር ዳሰሳ) የፍትሕ መበስበስና የተቋማት የራስ-ማጥፊያ ጉዞ ከየት ወዴት? 〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️ የአንድ ሥርዓት መሪዎችና አራማጆች የተቋማትን ሁለንተናዊ ፋይዳና ጥልቅ መዋቅር መገንዘብ ሲሳናቸው፣ ተቋማቱ ሕይወት አልባ ወደሆኑ፣ ጥቅምን ወደማያመነጩና የውኃ-ቅዳ ውኃ-መልስ ማዞሪያዎች መለወጣቸው የማይቀሬ የታሪክ እውነት ነው። ይህ ክስተት በፖለቲካ ፍልስፍናው ዓለም “የተቋማት መበስበስ” (Institutional Decay) በመባል የሚታወቅ ሲሆን፣ የአንድን ማኅበረሰብ የጋራ የውል ትስስር ቀስ በቀስ የሚበጣጥስ መርዝ ነው። በተለይ የፍትሕና የዳኝነት ተቋማት ከግዙፉና ከሚታየው መዋቅራቸው በጀርባ ሁለት እጅግ ረቂቅና መሠረታዊ ሚናዎች አሏቸው። መጀመሪያው፣ ሥርዓቱ ከተፈጥሯዊ ወይም ከባሕርያዊ ስህተቶቹ ራሱን በጊዜና በሰላማዊ ሒደት እንዲፈውስና እንዲያርም መንገድ መክፈት ሲሆን፤ ሁለተኛውና ተቀዳሚው ሚናቸው ደግሞ ሕዝብ በሥርዓቱ ላይ ፍጹም አመኔታ እንዲኖረውና ተቋማቱ ሕዝባዊ ቅቡልነት (Legitimacy) እንዲጎናጸፉ ማድረግ ነው። ታዋቂው የሕግ ፈላስፋ ሎን ፉለር (Lon Fuller) “The Morality of Law” በተሰኘው መጽሐፉ ላይ እንደሚያስረዳው፣ አንድ የሕግ ሥርዓት ሕጋዊ ተፈጻሚነት ሊኖረው የሚችለው ውስጣዊ የሞራል መስፈርቶችን ሲያሟላ ብቻ ነው። ከእነዚህ መስፈርቶች መካከል አንዱና ዋናው ደግሞ “በወጡ ሕጎችና በተግባራዊ አስተዳደሩ መካከል ፍጹም መጣጣም መኖር” ነው። ፍርድ ቤቶች ይህንን መጣጣም ማሳየት ካቃታቸው፣ ሕጉ ራሱ ትርጉም ያጣል። የበቀል ስልትና የተቋማዊ ታላቅነት (Integrity) መጥፋት 〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️ ዜጎችን ያለምንም ፍትሕ በየፍርድ ቤቱ በቀጠሮና በይግባኝ ማመላለስ፣ በዕለተ ቀጠሮው “ዳኞች አልተሟሉም” ወይም “መዝገቡ አልተመረመረም” እያሉ ባለጉዳዮችን በደጅ ማስጠናትና ተስፋ ማስቆረጥ፣ በሥርዓቱ ቁንጮዎች ዘንድ እንደ ረቂቅ የመበቀያ ወይም የመቆጣጠሪያ ስልት ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። ሆኖም ይህ እጅግ ተራ፣ ርካሽና አጭር ርቀት የሚጓዝ የፖለቲካ ቁማር ነው። ይህም ተቋማት ያነገቡትን ታላቅ ሕዝባዊና ታሪካዊ ዓላማ ወደ ግላዊና ቡድናዊ የቂም በቀል ማስፈጸሚያነት ማውረድ፣ ከተቋማዊ እሳቤ መምከን የሚመነጭ የዕውቀት ዕጥረት ነው። በታዋቂው የብሪታንያ የሕግ ባለሙያ ቶም ቢንግሃም (Tom Bingham) ጥልቅ ትንታኔ በተሰጠው “The Rule of Law” መርሆ ላይ እንደተጠቀሰው፣ የሕግ የበላይነት ማለት ዜጎች በአስፈጻሚው አካል እንደ እስስት ተለዋዋጭ ይሁንታና "የዘፈቀደ ፍትህ" ሥር መተዳደር ሳይሆን፣ አስቀድሞ በታወቀና ፍጹም ተገማች በሆነ የፍትሕ ሥርዓት መዳኘት መቻላቸው ነው። ተቋማቱ የዚህን ተቃራኒ ሲያደርጉ ግን፣ የሚገዘግዙትና የሚንድቁት የተከሳሾቹን ሕልውና ሳይሆን ራሳቸውን ነው። የሚገዘግዙት ግለሰቦችን ወይም ተፎካካሪ ቡድኖችን የሚመስላቸው የሥርዓቱ ባለአደራዎች፣ በተግባር ግን የራሳቸውን ሥርዓት መሠረት እየናዱ መሆኑን አይረዱትም። ይህ ክስተት የታሪክ ተመራማሪዎች “የሥርዓቶች ራስ-አጥፊነት ባሕርይ” (Systemic Self-Destruction) የሚሉት ግልጽ ማሳያ ነው። የይግባኝ ሥርዓት — የሥርዓቱ ራስን የማከሚያ ፋርማሲ! 〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️ በተለይ የይግባኝ ሰሚ ተቋማትና የከፍተኛ ዳኝነት አካሎች፣ በሕጋዊ መንገድ ሥርዓትን ተከትሎ አቤቱታ ሲቀርብላቸው፣ ባለጉዳዩን ሳያጉላሉና ሳያንገላትቱ ፈጥነው ውሳኔ መስጠት መቻል አለባቸው። አንድ ሰው ጉዳዩን ወደ ይግባኝ ሰሚ ችሎት ወሰደ ማለት፣ በሌላ አነጋገር፡- “ሥርዓቱ የፈጸመውን ስህተት አርሙልኝ፤ ከታች ያሉት መዋቅሮች ‘ቢሳሳቱም’ ወይም ቢበድሉኝም፣ እናንተ በገለልተኝነትና በከፍተኛ የፍትሕ ሚዛን ስህተቱን እንደምታርሙልኝና ተገቢውን ፍርድ እንደምትሰጡኝ አምናለሁ” የሚል የዕምነትና የተስፋ መልእክት ነው። ይህ ዓይነቱ አስተሳሰብ ሁልጊዜ በዜጎች ዘንድ እንዲኖር የሚፈለግ ፍጹም ጤናማ፣ ሰላማዊና ለሥርዓቱ ቀጣይነት ዋስትና የሚሰጥ ትልቅ አደራ ነው። ይግባኝ ማቅረብ ማለት ለፍትሕ የበላይነት መገዛትና የመጨረሻውን የተቋማት ተዓማኒነት መፈተሻ መስኮት ማንኳኳት ነው። ደግሞም ሥርዓቶችና ተቋማት በራሳቸው ነፍስ ዘርተው የሚንቀሳቀሱ ረቂቅ ፍጥረታት አይደሉም። የሚንቀሳቀሱት በሰዎች — በዳኞች፣ በኃላፊዎችና በአቃቢያነ ሕጎች ነው። ተቋማት በሰው አማካይነት የሚንቀሳቀሱ ስለሆኑና በመላእክት ስለማይመሩ፣ የፈለገው ጥንቃቄ ቢደረግ እንኳ ስህተት መሥራታቸው የሰው ልጅ ባሕርይ ነው። ሆነ ብለውም ይሁን ባለማወቅ፣ ሥርዓቶች ይሳሳታሉ። እነዚህን በሰዎች የተሳሳተ ውሳኔ የተነሳ የተዛነፉ መዋቅሮች ለማረምና የሥርዓቱን ሕይወት ለማራዘም ነው የይግባኝ ሥርዓት ያስፈለገው። በአጭሩ፣ ይግባኝ ማለት ሥርዓቱ የራሱን ተቋማት ስህተት፣ በራሱ ተቋማት አማካኝነት የሚያስተካክልበት ውስጣዊ የሕክምና ሂደት ነው። የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኞች የወሰኑት ውሳኔ፣ አሊያም የአቃቤ ሕግ ክስና አካሄድ ስህተት ካለበት፣ ወደ ይግባኝ ሰሚው ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይሻገራል። እዚያም የተበላሸ አካሄድ ካለ፣ ወደ ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ ከዚያም አልፎ መሠረታዊ የሕግ ስህተትን በማሳየት ወደ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ይወሰዳል። በዚህ ዓይነቱ መዋቅር፣ አንድ ሥርዓት ይግባኝ በቀረበለት ቁጥር የራሱን ስህተት ለማረምና ሕዝባዊ አመኔታን ዳግም ለመገንባት የተሰጠው ተጨማሪ ዕድል አድርጎ ሊቆጥረው ይገባል። ከሕክምና ስህተት እስከ ባህላዊ አማራጭ — ንጽጽር! 〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️ ይህን ሒደት በሌላ ምሣሌ ብናየው፣ በአንድ መደበኛ ሐኪም ጥረት ሊድን ያልቻለን ሕመም፣ በሙያው የተሻለ ልምድ፣ ዕውቀትና የሕክምና መሣሪያ ወደላቸው ስፔሻላይዝድ ሆስፒታሎች ሪፈር (Refer) ከመደረጉ ጋር ተመሳሳይ ነው። ሪፈራሉ ከተዘጋ ግን ሕመሙ ተባብሶ በሽተኛው መሞቱ አይቀሬ ነው። ይህ ክስተት በተደጋጋሚ ሲከሰትና ሆስፒታሉ ተስፋ ሲያስቆርጥ፣ ሰው ወደ ሕክምና ተቋማት መሄዱን ያቆምና ፊቱን ሙሉ በሙሉ ወደራሱ ባህላዊና አማራጭ መንገዶች ያዞራል። በፍትሕ ሥርዓትም ውስጥ የሚሆነው ይኸው ነው። የፍትሕና የይግባኝ ሥርዓቱ የተበላሸባት አገር፣ በሥርዓቱ የቆሰሉ፣ በተቋማቱ ተስፋ የቆረጡና በመንግሥት ላይ ቅንጣት ታህል እምነት የሌላቸውን ዜጎች ታመርታለች። ታዋቂው የአሜሪካ የሲቪል መብቶች ታጋይ ማርቲን ሉተር ኪንግ (Martin Luther King Jr.) “Letter from Birmingham Jail” በተሰኘው ታዋቂ መልእክቱ ላይ እንዳለው፡ “Justice too long delayed is justice denied” (እጅግ የዘገየ ፍትሕ፣ እንደተነፈገ ፍትሕ ይቆጠራል)። ዜጎች በፍትሕ ተቋማት ፊት ቀርበው በሥነ-ሥርዓትና በፍትሐዊነት ጉዳያቸው መስተናገድ ሳይችል ሲቀር፣ ከፍትሕ ተቋማት እየሸሹ፣ በራሳቸውና ከተቋማት ውጭ ባሉ የኃይል መንገዶች ፍትሕን ፍለጋ ይገደዳሉ። ፍትሕ ከተቋማት እጅ ወጥታ በግለሰቦች እጅ ስትገባ ደግሞ ተቋማዊ ሥርዓት ያከትምለታል።

የአዋጅ ቁጥር 1261/2013 አንቀጽ 22(1) የምክር ቤቱን ውሳኔዎች «የመጨረሻና አስገዳጅ» ማድረጉ፣ እነዚህ ውሳኔዎች በሀገሪቱ የሕግ ተዋረድ ፒራሚድ ውስጥ ያላቸውን ከፍተኛ ቦታ በግልጽ ያሳያል። ምክር ቤቱ አንድን ሕግ አስገዳጅ በሆነ ሁኔታ የመተርጎም ወይም ከተፈጻሚነት ውጭ የማድረግ ሥልጣን አለው ማለት፣ የእርሱ ውሳኔዎች በሌሎች መደበኛ ሕጎች፣ አዋጆች፣ ደንቦችና መመሪያዎች ሊሻሩ፣ ሊሻሻሉ ወይም ችላ ሊባሉ እንደማይችሉ ማረጋገጫ ነው። ስለዚህ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የሚሰጠው ውሳኔ፣ ራሱን ሕገ-መንግሥቱን ለመተርጎምና ለመጠበቅ የሚወጣ በመሆኑ ከሕገ-መንግሥቱ በታች የሚሰለፍ ሲሆን፣ በሌላ በኩል ደግሞ ሁሉንም የፌዴራልና የክልል አዋጆች፣ ደንቦችና መመሪያዎች የመሻርና የመግራት ፍጹም አስገዳጅነት ስላለው ከሌሎች ሁሉም ዓይነት ሕጎች በላይ ሆኖ በሕግ ተዋረድ ማማ ላይ ይቀመጣል። 🛑የፌደራሉ የገጠር መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 1324/2016 አንቀጽ 64(2) እጣ ፈንታ ምንድን ነው? ✅በገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 1324/2016 አንቀጽ 64(2) እና በፌዴሬሽን ምክር ቤት በመዝገብ ቁጥር 140/2017 (በመስከረም 28/2018 ዓ.ም በተሰጠ) ውሳኔ መካከል ግልጽ የሆነ የሕግ ይዘት መጋጨት መኖሩን መገንዘብ ይቻላል። አዋጁ የአንድ አርሶ አደር መሬት ያለአግባብ በሌላ ሰው ከተወሰደበት መብቱን ለማስከበር ክስ ማቅረብ የሚችለው በ15 ዓመት የይርጋ ጊዜ ውስጥ ብቻ እንደሆነና ካልሆነ ግን መብቱ በይርጋ እንደሚታገድ በግልጽ ይደነግጋል። በአንጻሩ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ያስተላለፈው ውሳኔ መሬት የማይሸጥ፣ የማይለወጥ የመንግሥትና የሕዝብ ሀብት በመሆኑ፣ አንድ አርሶ አደር በሕጋዊ መንገድ ያገኘው የመሬት ይዞታ መብት ለረጅም ጊዜ በሌላ አካል ተይዞ በመቆየቱ (በይርጋ) ሊታገድ እንደማይችልና ሕገ-ወጥ ይዞታም በይርጋ ሊጸድቅ እንደማይችል በማስገንዘብ የይርጋ መቃወሚያውን ፍጹም ውድቅ አድርጎታል። በኢትዮጵያ የሕግ ተዋረድ ሥርዓት መሠረት፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ሕገ-መንግሥታዊ ትርጉም ውሳኔዎች ከአዋጅ በላይ የበላይነትና አስገዳጅነት ያላቸው በመሆኑ፣ በዚህ የሕግ መጋጨት ውስጥ የአዋጁ ድንጋጌ ተፈጻሚነት ሳይኖረው ቀርቶ የምክር ቤቱ ውሳኔ የጸና እና የበላይ ሆኖ ይቀጥላል። ✅ይህንን የምክር ቤቱን የውሳኔ ልዕልና ይበልጥ የሚያጠናክረውና ሕጋዊ ክብደቱን ከፍ የሚያደርገው ሌላው መሠረታዊ ነጥብ፣ ምክር ቤቱ ውሳኔውን የሰጠው አዋጅ ቁጥር 1324/2016 በሥራ ላይ ከዋለ በኋላ መሆኑ ነው። አዋጁ ቀድሞ በ2016 ዓ.ም የወጣ ቢሆንም፣ ምክር ቤቱ ጉዳዩን መርምሮ የመጨረሻ ውሳኔውን የሰጠው መስከረም 28/2018 ዓ.ም በመሆኑ፣ ምክር ቤቱ ውሳኔውን ሲያሳልፍ የአዋጁን መኖርና ይዘት ከግምት ውስጥ አስገብቶ እንደሆነ በሕግ ግምት ይወሰዳል። ይህም ማለት ምክር ቤቱ የአዋጁን የ15 ዓመት የይርጋ ገደብ ድንጋጌ ወደ ጎን በመተው፣ የመሬት ይዞታ መብት በይርጋ ፈጽሞ ሊታገድ እንደማይችልና ሕገ-ወጥ ይዞታም በይርጋ ሊጸድቅ እንደማይችል የሰጠው ውሳኔ የአዋጁን ይዘት በግልጽ የሚሽር (Overriding) ሕገ-መንግሥታዊ ኃይል አለው። በመሆኑም፣ ከአዋጁ መውጣት በኋላ የተሰጠው ይህ አስገዳጅ ውሳኔ የአዋጁን ድንጋጌ ውድቅ በማድረግ የአርሶ አደሩን ሕገ-መንግሥታዊ የመሬት ባለመብትነት መብት ያለ ምንም የጊዜ ገደብ የሚያስከብር በመሆኑ የሕግ ትርጉም የበላይነቱ ሙሉ በሙሉ የተረጋገጠ ነው።

«በሕገወጥ መንገድ የተያዘ የመሬት ይዞታን አስመልክቶ በፌደራል የመሬት አዋጅ ቁጥር 1324/2016 የተቀመጠው የ15 ዓመት የይርጋ ገደብ እና የፌዴሬሽን ምክር ቤት “መሬት በይርጋ አይታገድም” ውሳኔ ተፈጻሚነት ወሰን ክርክር» የትኛው የበላይ ነው? (ጠበቃ አደም ሰይድ ከማል ✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅ መግቢያ በማንኛውም ሕገ-መንግሥታዊ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ውስጥ የሕግ የበላይነትን ማረጋገጥና የሕጎችን ተፈጻሚነት ወጥነት ባለው መልኩ መምራት የሚቻለው ግልጽና ሥርዓታዊ የሆነ የሕግ ተዋረድ (Hierarchy of Laws) ሲኖር ብቻ ነው። በኢፌድሪ ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓት ውስጥ ደግሞ ይህንን የሕጎች ልዕልና የመጠበቅ፣ የመተርጎምና የመጨረሻ ውሳኔ የመስጠት ፍጹም ሥልጣን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ተሰጥቷል። ይህ የሕግ ትንታኔ፣ የኢፌድሪ ሕገ-መንግሥትን እና የፌዴሬሽን ምክር ቤትን ሥልጣን ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1261/2013 መሠረት በማድረግ፣ የምክር ቤቱ ውሳኔዎች ከሕገ-መንግሥቱ በታች፣ ነገር ግን ከማናቸውም የፌዴራልና የክልል አዋጆች፣ ደንቦችና መመሪያዎች በላይ ያላቸውን ማዕከላዊ ቦታ በጥልቀት ይፈትሻል። በተጨማሪም፣ ይህንን የሕግ የበላይነት መርህ በተግባር ለማሳየት፣ በገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 1324/2016 ላይ በተቀመጠው የ15 ዓመት የይርጋ ገደብ እና ምክር ቤቱ በመዝገብ ቁጥር 140/2017 ባሳለፈው "የመሬት መብት በይርጋ አይታገድም" በሚለው አስገዳጅ ውሳኔ መካከል የተፈጠረውን ግልጽ የሕግ መጋጨት በመተንተን፣ የምክር ቤቱ ውሳኔ በአዋጆች ላይ ያለውን የመሻርና የበላይ የመሆን መዋቅራዊ ኃይል በማስረጃ ያሳያል። መልካም ንባብ 🛑ከሕገመንግስቱ አንቀጽ 9(1) አንጻር ሲመዘን በኢፌድሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 9(1)ሥር የተቀመጠው የሕገ-መንግሥቱ የበላይነት የሚደነግገው ድንጋጌ፣ ሕገ-መንግሥቱን የሀገሪቱ የሕግ ሥርዓት ከፍተኛ ማማ እና የሁሉም ሕጎች ሕጋዊነት መነሻ (Grundnorm) ያደርገዋል። በዚህ ሕገ-መንግሥታዊ ሥነ-ሕንጻ ውስጥ፣ በአንቀጽ 82(1) መሠረት ለፌዴሬሽን ምክር ቤት የተሰጠው ፍጹም የትርጉም ሥልጣን፣ ከሕገ-መንግሥቱ ጽሑፍ ውጭ የሚቆም ሳይሆን፣ ራሱን የሕገ-መንግሥቱን ሕያው መንፈስና ድብቅ ፍላጎት የመግለጥ መዋቅራዊ መሣሪያ ነው። ✅ በመሆኑም፣ ምክር ቤቱ የሚሰጣቸው ሕገ-መንግሥታዊ የትርጉም ውሳኔዎች ከራሱ ከሕገ-መንግሥቱ ጽሑፍ ጋር ተዋሕደውና አንድ አካል ሆነው (Constitutionalized) የሚጸኑ በመሆናቸው፣ በባሕርያቸው የሕገ-መንግሥታዊ ልዕልና ተጋሪዎች ናቸው። የትርጉም ውሳኔው የሕገ-መንግሥቱ አካል እስከሆነ ድረስ፣ ከአዋጅ በላይ መሆኑን መከራከር የሕገ-መንግሥቱን የበላይነት ከመቀበል የሚመነጭ ምክንያታዊና ቀጥተኛ የሕግ መደምደሚያ ነው። ​✅ የታችኞቹን ሕጎች ሕጋዊ ሕልውና የመወሰን እና የመሻር ፍጹም ሥልጣን በሕግ ተዋረድ (Hierarchy of Laws) መርህ መሠረት፣ የአንድ ሕግ ደረጃ የሚለካው የታችኛውን ሕግ ይዘት የመግራት፣ የመሻር ወይም የሕልውናውን ወሰን የመወሰን አቅም ሲኖረው ብቻ ነው። በአዋጅ ቁጥር 1261/2013 አንቀጽ 5(2) እና 22(1) ላይ በግልጽ እንደተደነገገው፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔዎች በማንኛውም የፌዴራልም ሆነ የክልል ሕግ አውጪ አካላት የሚወጡ አዋጆችን፣ ደንቦችንና መመሪያዎችን ሕገ-መንግሥታዊ ባለመሆናቸው (Unconstitutionality) ብቻ ሽሮ ከተፈጻሚነት ውጭ የማድረግ ፍጹም አስገዳጅነት አላቸው። አንድ የሕግ መተርጎም ውሳኔ መደበኛውን አዋጅ የመሻር እና የመግራት የቁጥጥር ኃይል ካለው፣ ያ ውሳኔ ከአዋጁ በላይ የላቀ መዋቅራዊና የዳኝነት ልዕልና እንዳለው ማረጋገጫ ነው። ስለሆነም፣ አዋጆች በሕግ አውጪው አካል የሚፈጠሩ መደበኛ ሕጎች ሲሆኑ፣ የምክር ቤቱ ውሳኔ ግን የእነዚህን አዋጆች ሕጋዊ ሕልውና የሚወስን የሕገ-መንግሥቱ የበላይነት መገለጫ በመሆኑ፣ በሕግ ተዋረድ ፒራሚድ ውስጥ ከአዋጆች በላይ ሆኖ በከፍተኛው ማማ ላይ ይሰለፋል። ✅ፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔዎች በሕግ ተዋረድ ላይ ያላቸው ቦታ፡ በኢፌድሪ ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓት ውስጥ የሕግ የበላይነትን እና ሕገ-መንግሥታዊ ልዕልናን (Constitutional Supremacy) ለማረጋገጥ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት የተሰጠው የሕገ-መንግሥት ትርጉም ሥልጣን መሠረታዊ ምሰሶ ነው። በኢፌድሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 62(1) እና 83(1) ላይ በግልጽ እንደተደነገገው፣ ሕገ-መንግሥቱን የመተርጎምና በማንኛውም ሕገ-መንግሥታዊ ክርክር ላይ የመጨረሻ ውሳኔ የመስጠት ሥልጣን የዚሁ ምክር ቤት ነው። ይህንን ሕገ-መንግሥታዊ ሥልጣን ይበልጥ ለማስፈጸም በወጣው አዋጅ ቁጥር 1261/2013 አንቀጽ 4(1) እና 5(1) ሥር የምክር ቤቱ የትርጉም ሥልጣን በድጋሚ የተረጋገጠ ሲሆን፣ በአዋጁ አንቀጽ 22(1) ላይ ደግሞ ምክር ቤቱ የሚሰጠው የመጨረሻ ውሳኔ «አስገዳጅ» መሆኑ ተደንግጓል። ከተጠቀሱት ሕጋዊና ሕገ-መንግሥታዊ ማዕቀፎች የምንረዳው፣ የምክር ቤቱ ውሳኔዎች ከመሠረታዊው ሕገ-መንግሥት ቀጥሎ፣ ነገር ግን በሀገሪቱ ውስጥ ከሚወጡ ማናቸውም የሕግ ዓይነቶች በላይ የበላይነትና የመጨረሻነት ባሕርይ የተጎናጸፉ መሆናቸውን ነው። ✅የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔዎች ከራሱ ከሕገ-መንግሥቱ በታች የሚሰለፉበት ምክንያት የምክር ቤቱ የዳኝነት ሥልጣን ምንጭና መነሻ ራሱ ሕገ-መንግሥቱ በመሆኑ ነው። ምክር ቤቱ አዲስ ሕገ-መንግሥታዊ ድንጋጌዎችን የመፍጠር ወይም ነባሩን የመለወጥ የሕግ አውጪነት ሥልጣን የሌለው ሲሆን፣ ተግባሩ የሕገ-መንግሥቱን መንፈስ፣ መርሆዎችና ፍላጎቶች መግለጥና ማብራራት ብቻ ነው። ስለሆነም፣ በአዋጅ ቁጥር 1261/2013 አንቀጽ 5(2) ላይ እንደተመለከተው፣ ምክር ቤቱ በማንኛውም የትርጉም ሂደት ውስጥ የሕገ-መንግሥቱን የበላይነት የመጠበቅ ግዴታ ያለበት በመሆኑ፣ የእርሱ ውሳኔዎች ምንጊዜም ከሕገ-መንግሥቱ ጽሑፍና መሠረታዊ መርሆዎች በታች ይገዛሉ። ✅ውሳኔዎቹ የሕገ-መንግሥታዊ ትርጉም ውጤቶች እንደመሆናቸው መጠን፣ ከሕገ-መንግሥቱ ጋር ተስማምተውና ተዋህደው የሚኖሩ እንጂ ከራሱ ከሕገ-መንግሥቱ በላይ ሊሆኑ አይችሉም። ✅በሌላ በኩል፣ የምክር ቤቱ ውሳኔዎች በፌዴራልም ሆነ በክልል ደረጃ ከሚወጡ ከማናቸውም ሌሎች ሕጎች በላይ የመሆናቸው ምስጢር፣ ውሳኔዎቹ ያላቸው የቁጥጥርና የመሻር ፍጹም ሥልጣን ነው። አዋጅ ቁጥር 1261/2013 በአንቀጽ 2(3) ሥር «ሕግ» የሚለውን ቃል ሲተረጉም በፌዴራልም ሆነ በክልል ሕግ አውጪ አካላት የሚወጡ አዋጆችን፣ ደንቦችን፣ መመሪያዎችንና የጸደቁ ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን እንደሚያካትት አስቀምጧል። የአዋጁ አንቀጽ 5(2) እና አንቀጽ 7(2) ደግሞ እነዚህ ማናቸውም ሕጎች፣ ልማዳዊ አሠራሮች ወይም የመንግሥት ባለሥልጣናት ውሳኔዎች ከሕገ-መንግሥቱ ጋር የሚቃረኑ ሆነው ሲገኙ፣ የምክር ቤቱ የመጨረሻ ውሳኔ «ተፈጻሚ እንዳይሆኑ» የማድረግ ፍጹም ሥልጣን እንዳለው ይደነግጋል። አንድን ሕግ ይዘቱን መርምሮ ሕገ-መንግሥታዊ ያልሆነ (Unconstitutional) በማለት ውድቅ የሚያደርግ ውሳኔ፣ በባሕርዩ ከተሻረውም ሆነ በሥራ ላይ ካለው ሕግ በላይ የበላይነት አለው፤ ምክንያቱም የታችኞቹን ሕጎች ሕጋዊ ሕልውና የሚወስን በመሆኑ ነው።

የኀላፊዎች ሹመት ምልመላ መመሪያ.pdf3.82 MB