Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union
Ir al canal en Telegram
This is the official Channel of Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union.
Mostrar más4 477
Suscriptores
Sin datos24 horas
+117 días
+1030 días
Archivo de publicaciones
በመመረቂያ አዳራሽ ሜዳልያ የተነፈገችዋ የአንቦ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪ ! ! !
በትምህርት ስሟ መቅደስ በቀለ (ከሰለመች ቡሃላ ሁዳ በቀለ) በዲኗም በትምህርቷም ተምሳሌት ተደርገው ከሚጠቀሱ የአምቦ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች መካከል ነች። 12ተኛ ክፍል ሳለች እስልምናን ተቀብላ፤ ጀመዓውን ከተቀላቀለች ቡሃላ ደግሞ ቁርዓንን እስከ መሐፈዝ ደርሳለች። በአንስቴዥያ ዲፓርትመንት 3.93 በማምጣት እንደ ኮሌጅ ከሁሉም ተማሪዎች ልቃ የተገኘች ቢሆንም ስሟ ከመድረክ ሳይጠራ ቀርቷል። ከእርሷ በታች ያመጡ ተማሪዎች ሲሸለሙ የእርሷ ሽልማት ግን የሗላ ሗላ ቅሬታ ካቀረበች ቡሃላ ከሪጅስትራር ቢሮ እንዲሰጣት ሆኗል። ሆኖም ግን ካሸነፈችው ሜዳልያ አንፃር የተሰጣት አንዱ ብቻ ነው። ምክንያቱም አንደኛነቷ እንደ ሴትም፤ እንደ አጠቃላይም ነውና።
በመጀመሪያ ደረጃ በአደባባይ የተነፈገ እውቅና በአደባባይ ነው ሊስተካከል የሚችለው። ዩኒቨርስቲው ስህተቱን አምኖ የሚገባትን እውቅና በአደባባይ ሊሰጣት ይገባል። ሲቀጥል ተማሪዋ በአሸነፈችበት መድረክ ሁሉ የሚገባትን ሽልማቶች ማግኘት ይገባታል።
Share it ! ! !
@MohammadamminKassaw
Repost from AAU - Muslim Students Union
ታላቁ የቲክቶክ መድረክ ደረሰ _ ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ ! ! !
ስለኒቃብ መጠየቅ በምርቃት ቀን እስከ ማሳሰር ከመድረሱ በፊት ጀምሮ ስላለው የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥሰት ታሪካዊ ዳራ በሰፊው ይዳሰሳል። ሕገ- መንግስቱን ጥሰው ስለሚጥሱት መብት ሕጋዊ ቦታ በሰፊው ይተነተናል። ከእኛ ስለሚጠበቀው ነገርም በደንቡን ውይይት ይደረጋል።
ሙባረክ አደም፦ በድምፃችን ይሰማ የመብት ትግል እንቅስቃሴ ፈርቀዳጅ ታጋይ፤ አክቲቪስት፤ ቲክቶከር፤ ተፅዕኖ ፈጣሪ ስብዕና፤ የሂባ ፋውንዴሽን መስራች ነው። ፕሮግራማችንን በመድረክ መሪነት የሚያስተናብርልን ይሆናል።
ሙስጠፋ ሺፋ፦በድምፃችን ይሰማ የመብት ትግል እንቅስቃሴ ወቅት ለታሰሩት ጠበቃ ሆኖ አገልግሏል፤ አሁንም በጥብቃና ሙያው አንቱታን ካተረፉ ባለሙያዎች መካከል ነው። ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ ሕጋዊ መሠረት ያብራራልናል።
የሕያ ኢብኑ ኑሕ፦የንፅፅር ትምህርት መምህር፤ የሒዳያ ኢስላማዊ ማህበር መስራች እንዲሁም ተፅዕኖ ፈጣሪ ስብዕና ነው። ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥሰት ታሪካዊ ዳራ ያብራራልናል።
ሁሴን ዩሱፍ፦የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ፀሐፊ ሲሆን ከማን ምን ይጠበቃል የሚለውን በዝርዝር ያስቀምጣል።
መቅረት አይታሰብም። ጀመዓዎች በቻናሎቻችሁ ላይ አሰራጩት። ሁሉም ለሁሉም ያድርስ። በአንድነት በአንድ መድረክ ተሰባስበን ስለመብቶቻችን እውቀትን እንጨብጥ።
🗓 ቀን፡ ሰኞ፣ ሰኔ 22 (Monday, 29 June)
⏰ ሰዓት፡ ከምሽቱ 03፡00 ሰዓት
እውቀትን መፈለግ መብት ነው፤ እምነትንም በክብር መተግበር እንዲሁ!
የቲክቶክ ገፃችንን Follow በማድረግ ዝግጅቱን ይጠብቁ፦
https://www.tiktok.com/@aaumsu
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
@aaumsu
የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ኒቃቢስቷ ጀግና አህት ኢማን ዲልሰባ ከ Health college ከሴቶች ከፍተኛ ውጤት በማምጣት የዩኒቨርሲቲው የሜዳሊያ ተሸላሚ ሆናለች!! 🎓🥇
እህታችን እንኳን ደስ አለሽ! 🎉
ኒቃብ ፊትን እንጂ አእምሮን አይሸፍንም!! ✨
Repost from AAU - Muslim Students Union
የታሰሩት ሙሉ ለሙሉ ተፈተዋል።
ዝርዝሩን ይዘን እንመለሳለን።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
@aaumsu
+2
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተመራቂ ተማሪዎች ታሰሩ ! ! !
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የተማሪዎች ምረቃ ፕሮግራምን እያካሄደ ባለበት ወቅት በምርቃታቸው ቀን የመረጡትን፤ የሚያስደስታቸውን፤ የምርቃት ቀኔ መልዕክት ይሁን ያሉትን በሪቫን እና ባይንደር ላይ አሳትመው ባሉበት እና የደስታ ቀናቸውን እያሳለፉ ባለበት ወቅት የግቢ በር አካባቢ ላይ ሳሉ 10 ገደማ ልጆችን ወደ ፖሊስ ጣቢያ ወስደዋል። እንደ ምክንያትም "ሪቫኑ ላይ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሎጎ የለም!" - የሚልን አቅርበዋል።
ይህ ፈፅሞ ትክክል ያልሆነ፤ የተማሪዎችን ነፃነት የሚጋፋ፤ የደስታ ቀናቸውን የሚያደፈርስ እና ከአንድ አንጋፋ ዩኒቨርስቲ የማይጠበቅ እኩይ ተግባር ነው። መሠል የሙስሊም ተማሪዎችን ነፃነት የሚጋፋ ተግባር ኒቃብ መልበስን በመመሪያ ከመከልከል ጀምሮ እየተደጋገመ ያለና ጥሩ ወዳልሆነ አቅጣጫ የሚያመራ ነው።
ስለሆነም የታሰሩት ሙስሊም ተማሪዎች በቶሎ ተፈተው ወደ ቤተሰባቸው እንዲመለሱ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ እንጠይቃለን።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !!!
@aaumsu
Look at the image
በዛሬው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ምርቃት ፕሮግራም ላይ ነው
ሪባኑን ተመልከቱት
ባይንደሩን ተመልከቱት
"She will wear her niqab, She will also attend her education --- እንደለበሰች ትማራለች። We have a question, and we want an answer --- ጥያቄ አለን መልስም እንፈልጋለን።" - የሚል መልዕክት ነው።
በሁሉም ቦታ ስለመብታችን እንጠይቃለን። መጠየቅም ሆነ መልበስ መብታችን ነው። ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣም እንጠይቃለን።
@aaumsu
"ፍትሕ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች!" - በሰመራ ዩኒቨርስቲ የዋንጫ ተሸላሚ የሆነው ዶክተር ሙሐመድ ሐሰን
በሰመራ ዩኒቨርስቲ የወርቅ ሜዳልያ እና ዋንጫ ተሸላሚ ሆኖ የተመረቀው ዶክተር ሙሐመድ ሐሰን በሐይማኖታቸው ምክንያት በደል እየደረሰባቸው ላሉ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች እና ለአክሱም ሙስሊሞች በምርቃቱ ቀን ድምፁን አሰምቷል። "ኒቃብ ፀጉርን እንጂ አዕምሮን አይፈንም!" - የሚልን መልዕክት ያስተላለፈው የዋንጫ ተሸላሚው ዶክተር ሙሐመድ ሙስሊም ተማሪዎችን የማያገል፤ ሁሉንም ኢትዮጵያዊ በእኩልነት የሚያስተዳድር፤ ፍትሕን የሚያሰፍን መመሪያ እንዲወጣ ጥሪ አቅርቧል። በሙስሊም ተማሪዎች ላይ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጀምሮ እየደረሱ ያሉ የመብት ጥሰቶች ቆመው ፍትሕ ይሰፍን ዘንድ የሚመለከታቸው አካላት ሀላፊነታቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርቧል።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
Repost from AAU - Muslim Students Union
ታላቅ የፓናል ውይይት ... በቲክቶክ መድረክ ! ! !
ድምፃችንን ከፍ አድርገን የምናሰማባቸውን መድረኮች አብዝቶ ለፈጠረው አምላክ ምስጋና ይገባ። ታሪካዊውን የፓናል ውይይት በመስጂድ ልናከናውን ቀጠሮ የያዝን ቢሆንም የመሰብሰብ እና የመወያየት መብታችንን በመንፈግ እንደተከለከልን የሚታወስ ነው። ሆኖም እነርሱ ከለከሉን ማለት ዝም ብለን እንቀመጣለን ማለት አይደለም። በሰፊው፣ ሁሉም በያለበት ሆኖ ይታደም ዘንድ በተመቻቸ ሁኔታ፤ ርዕሶቹም ሰፋ ብለው፤ በቅርቡ በቲክቶክ ታላቅ የፓናል ውይይት የሚኖረን ይሆናል።
የክብር እንግዶቻችን እንዳሉ ሆነው፤ መምጣት ሳይችሉ ቀርተው ሲቆጩ የነበሩት ባሉበት ሆነው እንዲሳተፉ በሚያስችል መድረክ፤ በውጭ ሀገርም ሆነው በሀገር ውስጥ ያሉ ተማሪዎች እና መላው ሕዝበ ሙስሊም የሚሳተፍ ይሆናል።
እስከዚያው መልዕክቱን ለሁሉም አድርሱ። የቲክቶክ ገፃችንን https://www.tiktok.com/@aaumsu?_r=1&_t=ZS-97D9UHuTcGO በመግባት Follow አድርጉ።
የሚታፈን ድምፅ የለም ! ለበዳዮች እጁን የሚሰጥ ትውልድም አይኖርም !!
ጥያቄ አለን ... ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
@aaumsu
+1
አማናችሁን አድርሰናል _ ለወሎ ዩኒቨርስቲ ጤና ካምፓስ ሙስሊም ተማሪዎች መስጂድ ማሰሪያ _ 25145 ብር ! ! !
በወሎ ዩኒቨርስቲ ለሚገኙ ሙስሊም ወንድሞቻችን መስጂድ ማስጨረሻ እንረባረብ ዘንድ ጥሪ አቅርበን በአካውንታችን ያስገባችሁትን 25145 ብር አድርሰናል። ወንድሞቻችንም ባደረጋችሁት አስተዋፅዖ ተደስተው በአላህ ስም አመስግነዋል። በአላህ ፈቃድ መሰሉን መልካም ተግባር የምንቀጥል ይሆናል።
አሁንም ቢሆን የሚያስፈልጋቸው ብዙ ነውና ለወንድም እህቶቻችን መስጂድ በማስገንባት፤ የአኼራ ቤታችንን እየሰራን ለትውልድ የሚሻገርን ኸይር ስራ መስራት ይምትፈልጉ ካላችሁ ላይ በአካውንታቸው አስገቡ።
አካውንት:- 1000695672814 (Wollo Univ TCC Muslim Students Jemaa)
አላህ በጀነተል-ፊርደውስ ይሰብስበን!
አላህ ለመልካም ለውጥ ሰበብ ያድርገንም!!
"በመብት ጥያቄ ወቅት ጊዜያዊ መፍትሄ ማለት ዋናውን መፍትሔ ማስረሻ ነው።"
ፖድካስቱ በዲኑ ዓሊ Youtube ተለቋል። ገብታችሁ ተመልከቱ። ለሌሎችም Share አድርጉ።
ሊንኩ https://youtu.be/SNmZcifBpw0?si=BDRMcJHqVEfLmstR ነው።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !
"እንደ ልጅ አድርገህ አስተምርልኝ ብዬ የላኩለት መምህር ልጄን እስከ ምሽት 4:30 ድረስ ልጄን ብርድ፣ ቁር ላይ ትቷት ምላሽ ካልሰጣት የሁለተኛ ወላጅ ሚናን ረስቷል ..... !" - ጋዜጠኛ ዲና ዓሊ
"ሀላፊነቱን ተሸክማችሗል። ውይይት የተባለውን ነገ በተባለው መሠረት ይካሄድ፤ መፍትሔ ይምጣ። የምንፈልገው ሌላ ነገር አይደለም።" - ሙሐመድአሚን ካሳው
ነገ ቅዳሜ ምሽት 3:00 በጋዜጠኛ ዲኑ ዓሊ ዩቲዩብ ቻናል ይጠብቁ። ብዙ ነጥቦች ተዳሰዋል።
@aaumsu
ትምህርት ሚኒስቴር ከኢድ ዋዜማ እና ማግስት ሊሰጥ የነበረውን የሪሜድያል ፈተና ወደ ግንቦት 27 መራዘሙን ገልጿል።
ቢዘገዩም ማስተካከላቸው ኸይር ነው። ይህንን ስህተት ግን በየአመቱ ባይደግሙት ኸይር ነው። ቋሚ የሆነ አሰራር እና መፍትሔም ሊቀመጥለት ይገባል።
@MohammadamminKassaw
+3
በትላንትናው እለት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቅጥር ግቢ ውስጥ የተከሰተውን ክስተት አስመልክቶ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የወጣ መግለጫ
“መብት በልመና አይገኝም!”
ይህ በታላቅ ትዕግስትና ፅናት ያለፉትን 19 ወራት (ከ620 ቀናት በላይ) መዋቅራዊ በደልና ማግለል የተጋፈጠው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ድምፅ ነው ። ህገ-መንግስታዊ መብትን በሚጥስና በተለይም የሙስሊም ሴት ተማሪዎችን ሂጃብና ኒቃብ በግቢው ውስጥ ሙሉ በሙሉ በሚከለክል አድሏዊ መመሪያ ምክንያት እህቶቻችንና ወንድሞቻችን በየቀኑ ሲንገላቱ፣ አካዳሚያዊና ስነ-ልቦናዊ ጥቃት ሲፈጸምባቸው ኑረዋል ። ትናንት ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ.ል. በዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ፊት ለፊት በሰላማዊ መንገድ በመሰባሰብ፣ በብርድ፣ በጨለማና በረሃብ ውስጥ ሆነው የታየው የመቶዎች ፅናት ይህ ትውልድ ማንነቱን፣ እምነቱንና ክብሩን ለምንም አሳልፎ የማይሰጥ መሆኑን በተግባር ያረጋገጠበት ታሪካዊ ክስተት ነው ። ከሃይማኖት መሪዎቻችን (መጅሊስ) ጋር በተደረገው ስምምነትና በተሰጠው ቃል መሠረት ጉዳዩን በኃላፊነት እንዲይዙት ሌሊት ላይ ተማሪው ወደ ማደሪያው ቢበተንም ፣ ይህ ትግሉ ተጠናቀቀ ማለት ሳይሆን መመሪያው በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲሻሻል የተሰጠ የጊዜ ገደብ ነው ። መብታችን በግልፅ ተረጋግጦ፣ የታተመ የመመሪያ ለውጥ በይፋ እስካልመጣ ድረስ ሰላማዊ ትግላችን በበለጠ ስፋትና ጉልበት ይቀጥላል! መላው ፍትህ ፈላጊ ማህበረሰብም ከተበደሉ ተማሪዎች ጎን እንዲቆም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን ። በዱዓ፣ በንቃትና በአንድነት ቆመን የመጨረሻውን ፍሬ እናያለን!
“ጥያቄ አለን! መልስም እንፈልጋለን!”
@aaumsu
ከቀኑ 7:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ አሁን ምሽት 2:40 ሰዓት ድረስ፣ ተማሪዎቻችን በብርዱና በጨለማው ውስጥ ቁጭ ብለው ለጥያቄዎቻችን ምላሽ እየጠበቁ ይገኛሉ። መብትንና ክብርን ለማስከበር የሚደረግ ጉዞ መራራና ዋጋ የሚያስከፍል ቢሆንም፣ የእነዚህ ወጣቶች ጽናት ግን የፍትሃዊነታቸው ትልቁ ማረጋገጫ ነው።
📌 ለተማሪዎቻችን፦ በዚህ ብርድ በበዛበት ምሽት እያሳያችሁት ያለው ተስፋ አለመቁረጥና ቁርጠኝነት ታሪክ የማይረሳው ታላቅ የጽናት መዝገብ ነው። ቅስናችሁ አይሰበር፣ ሞራላችሁ አይውረድ። በዚህ አስቸጋሪ ሰዓት የምታሳዩት ትዕግስት (ሰብር) እና አንድነት ለነገው ድላችሁ መሰረት ነው። አላህ እውነተኞችንና መብታቸውን በሰላማዊ መንገድ የሚጠይቁትን መቼም ቢሆን አይጥልም።
📌 ለሚዲያ አካላት፦ እነዚህ ወጣቶች የነገዋ ሀገር ተስፋዎች እንጂ የሁከት አራማጆች አይደሉም። ሰላማዊ በሆነ መንገድ፣ ህጋዊና ሰብአዊ መብቶቻቸውን ይዘው መልስ ፍለጋ በብርድ ላይ ተቀምጠዋል። ለነዚህ ተማሪዎች ድምጽ በመሆን ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ እናሳስባለን።
📌 ለዩኒቨርሲቲው አመራሮችና ለሚመለከታቸው የመንግስት አካላት፦ ተማሪዎች በሰላማዊ መንገድ ላነሷቸው ጥያቄዎች አፋጣኝ፣ ግልጽና ፍትሃዊ ምላሽ መስጠት የሀላፊነት ሁሉ መጀመሪያ ነው። ጉዳዩን በቸልተኝነት መመልከት ወይንም ማዘግየት መፍትሄ አይሆንም። አሁንም ጥያቄያችን ግልጽ ነው! ከምላሹ መሸሽ አይቻልም!
📌 ለመጅሊስ፦ የናንተ የመጀመሪያ ኃላፊነት የሙስሊሙን መብት ማስጠበቅ ነው። ሰላማዊው ጥያቄያችን በፍትሐዊ መንገድ ይመለስ ዘንድ ስሩ። ሴት ልጅ ብርድ ላይ አትደር፤ ተማሪዎች እንቅልፍ አጥተው ሜዳ ላይ አይደሩ። ስለፍትሕ ቁሙ! ታሪክ እየተፃፈ ነው!!
📌 ለሙስሊም ማህበረሰብ፦ እነዚህን በብርድና በጨለማ ውስጥ ያሉ ልጆቻችሁን በዱዓና በሞራል ከጎናቸው ቁሙ።
@aaumsu
ግቢው እብደቱን ቀጥሏል!
ምግብም ወደግቢ እንዳይገባ ከልክሏል! ውጭ ያሉ ተማሪዎችም አትገቡም ብሎ እያስፈራራ ነው። መጾም ለኛ አጅር እና ክብር እንደሆነ አላወቁም!
@aaumsu
እዚያ ያለውን ተማሪ ማስነሳት ሲያቅታቸው ተማሪዎች ወደግቢው እንዳይገቡ እየከለከሉ ይገኛሉ።
አሁንም መፍትሄው የተማሪን ድምጽ ማፈን ሳይሆን ለተጠየቀው ጥያቄ ተገቢውን ምላሽ መስጠት ነው።
ጥያቄ አለን! መልስም እንፈልጋለን!
Video: አሁን ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ፊት ለፊት
@aaumsu
+2
ፌደራል ፖሊሶች ተማሪውን እንዲበተን ለማድረግ እየሞከሩ ቢሆንም ተማሪው አሁንም በእምቢታው ቀጥሏል።
@aaumsu
አቋማችን ግልጽ ነው!
ማደር ካለብን አይደለም አንድ ሌሊት ቀናትን እናድራለን፤ መዋል ካለብን ሳምንታትን እንውላለን! መጾም ካለብን ወራትን እንጾማለን! ነገር ግን ለጥያቄያችን መልስ ሳይሰጠን ወዴትም አንሄም!
@aaumsu
+1
መብት በትግል እንጂ በልመና አይገኝም!
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ከ20 ወራት ቡሃላ ጥያቄያቸውን ለማቅረብ ከፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ተሰባስበዋል።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !
@MohammadamminKassaw
"አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ 2 ሶስት ቀን ኒቃብ አይከለከልም ቢል መፍትሔ መጣ አንልም። ምን ማለት ነው? እኛ የምንፈልገው በመመሪያ የፀና መብት ነው። ነገ የት ነው የምታስጮሁን ብለን ልንጠይቅ ነው?!" -
@aaumsu
