cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

ቤተ-ሀብተማርያም(Bete-Habtemariam)

በዚህ የቴሌግራም Channel: የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክን ዶግማና ቀኖና፣ ትውፊትና ሥርዓትን የጠበቁ #ስብከቶች #መዝሙሮች #የአብነት-ትምህርቶች #ዜማዎች #መጽሐፍት #ሥነ-ቃሎች #ሥነ-ጽሑፎች #ሌሎችም... ........................ ይለቀቁበታል። ቤተሰብ በመኾን ይተባበሩ!

Mostrar más
Publicaciones publicitarias
212
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

#ሥላሴ_ቅኔ ፡ ዘአብርሀ ( አፈ -ንቡረ- እድ ዘአክሱም ) ኢይባእ ቤተ መቅደስ ተከልአ ዕፅ በአበሳሁ ! አምጣነ በዕፅ አዳም መዋቲ እመንበረ ክብሩ ሰሰለ፤ ወሕያው አምላከ አዳም ዲበ ዕፅ ተሰቅለ፤ ወኢይምሰሎ ለእብን ገፋዒ ክበደ ጌጋዩ ቀሊለ፤ ውስተ ቤተ መቅደስ እመ ተልዕለ፤ አምጣነ የዋህ አቤል በእብን ተቀት፤ ወበእብን ኤርምያስ ተሀጕለ ። #ትርጉም ቤተ መቅደስ እንዳይገባ እንጨት በበደሉ ተከለከለ፣ ሟች አዳም በእንጨት ከክብር ወንበሩ ተወግዷልና፣ ህያው የአዳም አምላክም በእንጨት ተሰቅሏልና ፤ በቤተ መቅደስም ከፍ ቢል ለገፊ ድንጋይ የበደሉ ክብደት ቀላል አይምስለው፤ ተላላ (ገር) አቤል በድንጋይ ተገድሏልና፤ ኤርምያስም በድንጋይ ጠፍቷልና ። #ምስጢር ነውረኛ የሆነ ካህን ቤተ መቅደስ እንዳይገባ ይከለከላል ፤ እን ዲሁም የቅድስት ማርያም ቤተ መቅደስ ያለ እንጨት በድንጋይ ብቻ ተሰራ። አዳም በበለስ እንጨት ምክንያት በመጎዳቱና ክርስቶስም በእንጨት ላይ በመሰቀሉ እንጨት ለቤተ መቅደስ ስራ አልዋለም ። "ሌላው ካህንም በቤተ መቅደስ ከፍ ቢል ደህና የሆንሁ አይምሰለው ። በሱ ምክንያት ንፁህ ሰው ተገድሏል፣ የዋሁ ሰው ጠፍቷል" እንደሚባል' ድንጋይ ደግሞ ያለ እንጨት ብቻውን ቤተ መቅደስ ሆኖ ስለተሰራ አቤልና ኤርምያስ በዚሁ በድንጋይ በመግደላቸው እንደ እንጨት መወገድ ነበረበት በማለት ባለቅኔው ፍርድ ነክ አስተያየታቸውን በምስጢር ሰንዝረዋል ። #ታሪክ ንጉስ ላሊበላ በላስታ ያሳነፀው ቤተ መቅደስ እንደሌሎቹ ቤተ መቅደሶች በድንጋይና በጭቃ የተገነባና የእንጨት ጣሪያ ያለው ሳይሆን' ገሃው መሬት እየተፈለፈለና ውስጡ እየተከፈለ የተሰራ አስደናቂ ስራ ነው ። ነቢዩ ኤርምያስ ልዩ ልዩ መከራን ከመቀበሉም በላይ በድንጋይም ተወግሯል ( ኤርም. 20 1 2 )። ከግእዝ ቅኔያት ቅጽ 2
Mostrar todo...
👍 1👏 1
✍️✍️✍️✍️ #የሚለጠጡ_አገልጋዮች_ያስፈልጋሉ! ✍️✍️✍️ እመቤታችን በዐረገች በ4ኛ ዓመት ጳውሎስና በርናባስ ፊልጵስዩስ ገብተው አስተማሩ፤ ሕዝቡም አምነው ተጠመቁ "እንግዲህ_ወደ_ቤተ_ጣዖት_አትሒዱ" አሏቸው። የለመድነውን ከከለከላችሁንማ መካነ ጸሎት ስጡን አሏቸው፡፡ እንዲህ ብንላቸው እንዲህ አሉን ብለው ወደ ጴጥሮስና ዮሐንስ ላኩ። "አልቦ ዘትገብሩ ወኢምንተኒ ዘእንበለ ትእዛዙ ወምክሩ ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ" ዮሐ 15። "ያለጌታችን ፈቃድ አንዳች ልታደርጉ አይገባም እናንተም ጸልዩ እኛም እንጸልያለን" ብለው ላኩባቸው፡፡ ሱባዔ ሲጨርሱ በዚህ ዕለት ጌታ በሩቅም በቅርብም ያሉ ደቀመዛሙርቱን በደመና ጠቅሶ ፊልጵስዩስ ሰበሰባቸው፡፡ ዮሐንስ ጌታዬ ለምን ሰበሰብከን ብሎ ጠየቀ። ጌታም በእናቴ ስም ጽንፍ እስከ ጽንፍ አብያተ ክርስቲያናት እንዲታነጹ ፈቃዴ ነውና ሕንጻ ቤተክርስቲያን ላሳያችሁ ሥርዓት ላስተምራችሁ ነው አለው፡፡ ይህንን ብሎ ወደ ምሥራቅ ወሰዳቸው ተራርቀው የነበሩ 3 ደንጊያዎች ነበሩ፡፡ በተአምራት አቀራርቦ ቁመቱን ወርዱን መጥኖ ሠጣቸው ‹‹ወአዕባንኒ ይለመልሙ በእዴሆሙ›› ይላል እሳት እንዳየው ሰም ከእጃቸው እየለመለሙ /እየተሳቡ/ ቁመቱን 24 ወርዱን 12 ክንድ አድርገው ሠርተውታል፡፡ ‹‹ወይእዜኒ አንትሙኒ ከመዝ ግበሩ›› እንግዲህ እናንተም እንዲህ አድርጋችሁ ሥሩ ብሏቸው ዐረገ፡፡ በማግሥቱ ሰኔ 21 እመቤታችንን መንበር፣ ጴጥሮስን ተራዳኢ ካህን፣ እስጢፋኖስን ሠራዒ ዲያቆን አድርጎ ቀድሶ አቁርቧቸዋል፡፡ ዳግመኛም ጴጥሮስን እጁን ጭኖ ፓትርያርክ አድርጎ ሾሞታል፡፡ በዚህም ጊዜ ሰማያውያን መላእክት ምድራውያን ሐዋርያት አንድ ሆነው አመስግነዋል፡፡ ቅድስት ቤተክርስቲያናችን በእደ ልቡናቸው ዘርንና ጎጥን፣ ሙስናን፣አድርባይነትን፣ ጥላቻን፣ ድንንቁርናን፣ ትዕቢትን፣ ወዘተ ባነገቡ ግለሰቦች ምክንያት ከፈራረሰች ብዙ ዘመናት አልፈዋል፡፡ ይህ እንደለ ሆኖ "ላለፈው ክረምት ቤተ አይሰራም" እንደተባለው ሁሉ አሁን ላይ ለቤተክርስቲያን የሚለጠጡ ድንጋዮች ያስፈልጓታል ማለትም፦ ☞ለክህደት ሳይሆን ለእምነት የሚለጠጡ ☞ለሙስና ሳይሆን ለታማኝነት የሚለጠጡ ☞ለጥላቻ ሳይሆን ለፍቅር የሚለጠጡ ☞ለትዕቢት ሳይሆን ለትህትና የሚለጠጡ ☞ለድንቁርና ሳይሆን ለዕውቀት የሚለጠጡ ☑️ምዕመናን ☑️ዲያቆናት ☑️ያሬዳውያን ☑️ካህናት ☑️መነኮሳት ☑️ጳጳሳት ያስፈልገናል፡፡ ለመልካም ክርስቲያናዊ ምግባር ለመለጠጥ ያብቃን፡፡ መጋቤ ብሉይ ወሐዲስ ቆሞስ አባ ጸጋዘአብ
Mostrar todo...
#ሕንጸተ ቤታ ለእግዝትነ( ሕንጸታ ለቤተ መቅደስ) ዘመኑን "እመቤታችን በዐረገች በ4 ዓመት፣ ይኸውም ታሪኩ የተፈጸመው በ53 ዓ.ም ነው።" ይላል መዝገበ ታሪክ የመጀመሪያይቱ ቤተ መቅደስ የታነጸችበት ቀን ታሪኩም እንዲህ ነው፤ ይኸውም ጳውሎስና በርናባስ በአሕዛብ ውስጥ በሰበኩ ጊዜ በክርስቶስ አመኑ። ያንጊዜ ቅዱስ ቁርባን የሚቀበሉበት ቤተክርስቲያን አልነበረም። ሐዋርያትም በወንጌላዊ የማርቆስ እናት ቤት ተሰብስበው ጸሎት ያደርጉ ነበር እንጂ። 'ወእምዝ ሖረ ቤተ ማርያም እሙ ለዮሐንስ ዘተሰምየ ማርቆስ ኀበ ሀለው ብዙኃን አኃው ግቡአን ወይጼልዩ፤ ከዚህም በኋላ በአስተዋለ ጊዜ ብዙዎች ወንድሞች ተሰብስበው ይጸልዩበት ወደ ነበረው ማርቆስ ወደ ተባለው ወደ ዮሐንስ እናት ቤት ወደ ማርያም ቤት ሄደ፤ ' እንዳለ ሐዋ 12 ፤12። ስለዚኽም ወደ ጴጥሮስና ወደ ዮሐንስ ወደ ሐዋርያት ሁሉ ስለ ቤተክርስቲያን መታነጽ ጉዳይ ወደ ፈጣሪያቸው በጸሎት እንዲለምኑ መልእክቱን ላኩ። ሐዋርያትም እንዲህ ብለው መለሱላቸው። ያለ ጌታችን ፈቃድ ምንም አንሰራም። ግን የምንሰራውን እስኪያስረዳን ድረስ ወደ እግዚአብሔር እየጸለዩና እየማለዱ አንድ ሱባኤ ይፈጽሙ ዘንድ ወደ ሃይማኖት የተመለሱ ሰዎችን አዘዟቸው። ሱባዔ ገቡ። ወደ ሱባዔውም ፍጻሜ ክብር ይግባውና ጌታችን ተገለጸላቸው። በየሐገሩ ያሉትን ሐዋርያት ኹሉ በፊልጵስዩስ በደመና ሰበሰባቸው። ከርሳቸውም ጋር ጳውሎስና በርናባስን ጌታችን ባረካቸው። እንዲህም አላቸው፤ በዚኽች ዕለትም በእናቴ በማርያም ሥም በአራቱ ምዕዘነ አለም ቤተክርቲያኖች እንዲታነጹ የፈቀድኩባት ናት አለ። ' ስለዚኽ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤እነሆ በጽዮን ድንጋይን ለመሠረት አስቀምታለሁ፤ ዋጋው ብዙ የኾነውን የተመረጠውን የከበረውን መሠረቱ የጸናውን የማዕዘን ድንጋይ አኖራለሁ።' እንዳለ በነቢዮ ኢሳይያስ ኢሳ 28,፤ 16 ። ከዚህ በኋላ ከከተማዋ በስተምሥራቅ በኩል አወጣቸው። የቤተክርስቲያኒቱንም ቦታና መሰረቷን ወሰነላቸው( ቁመቱን 24፣ ወርዱን 12 ክንድ አድርገው ሰርተውታል፤ ይላል)። ከርሳቸውም ጋር የእግዚአ ብሔር ኃይል ነበር። ጌታችንም ሦስት ድንጋዮች አስቀርቦ ባረካቸው። አንዱን መቅደስ፣ አንዱን ቅድስት፣ አንዱን ቅኔ ማሕሌት እንዲሆኑ አድርጓቸዋል። የቤተ ክርስቲያኒቱ ህንጻዋ እስኪፈጸም ድረስ ድንጋዮች በሐዋርያት እጆች ውስጥ እንደ ሰም እየቀለጡ፤ እየተሳቡ፤እየለመለሙ፣እየተለጠጡ ለአንድ ቤተክርስቲያን በቅተዋል። ከዚህ በኋላ ሰኔ 21 ቀን ጌታችንም ነዋየ ቅድሳቱን፣ አልባሳቱንና መሰዊያውን አዘጋጀ። ከዚህ በኋላ ጌታችን እጁን በጴጥሮስ እራስ ላይ ጭኖ በአራቱ ማዕዘነ ዓለም ውስጥ ስራ ብሎ ሾመው። "ወአንሰ እብለከ ከመ አንተ ኰኵሕ ወዲበ ዛቲ ኰኵሕ አሐንፃ ለቤተ ክርስቲያንየ ወአናቅጸ ሲኦል ኢይኄይልዋ ወእኁበከ መራኁተ መንግሥተ ሰማያት ወዘአሰርከ በምድር ይከውን እሱረ በሰማያት ወዘፈታህከ በምድር ይኩን ፍቱሐ በሰማያት፡ እኔ እልሃለሁ አንተ ዐለት ነህ በዚያች ዐለት ላይም ቤተክርስትያኔን እሰራታለሁ። የሲኦል ደጆችም አይበራታቱባትም። የመንማያትንም መክፈቻዎች እሰጥሃለሁ፤ በምድር የምታስረው በሰማያት የታሰረ ይሆናል፤ በምድርም የምትፈታው በሰማያት የተፈታ ይሆናል።" አለው ። ማቴ 16 ፤18። ይህም ሲቀ ጳጳሳት ማለት ነው። ለሐዋርያት አለቃ ጴጥሮስ ከጽንፍ እስከ ጽንፍ የጳጳሳት አለቃ ይኾን ዘንድ ይገባዋል ፣ ይገባዋል እያሉ ሰማያውያን መላእክት ምድራዊያን ስዎች ሦስት ጊዜ አሰምተው ተናገሩ። ከዚህም በኋላ ጌታችን ሐዋርያትን የቁርባኑን ቅዳሴ ሥርዓት ያከናውኑ ዘንድ ለሕዝቡም ሥጋውንና ደሙን ያቀብሏቸው ዘንድ አዘዛቸውም፤ እንዲህም የሚል አለ ራሱ ቀድሶ መድኃኒታችን ሥጋውንና ደሙን ለሐዋርያት አቀበላቸው ። እንዲህም አላቸው፤ በዚኽችም ዕለት የእጃቸውን ሥራ እንዳይሠሩ ሕዝቡን ነገራቸው። ይኸውም በሰኔ 21 ቀን ነው። ከዚኽም መድኃኒታችን ከእርሳቸው ዘንድ በታልቅ ምስጋና ወደ ሠማይ ዐረገ። ከዚያችም ቀን ጀምሮ አባቶቻችን ሐዋርያት በዓለሙ ሁሉ ውስጥ አምላክን በወለደች በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስም ቤተክርስቲያንን የሚያሳንፁ ሆኑ። ከመጽሐፈ ታሪክ የተወሰደ። እንኳን ሕንጸተ ቤታ ለእግዝትነ ቅድስት ድንግል ማርያም አደረሰን፤ አደረሳችኹ።
Mostrar todo...
👍 1
ቅዱስ ሚካኤል የርኅራኄ መዝገብ፣ ትሑት፣ ታዛዥና ለዘለዓለም ፈጣሪውን አመስጋኝ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ጌታ በሚያደርገው ቸርነት ላይ ለሰው አንድ ወገን የሚሆን መልአክ ነው፡፡ (ሄኖ.፮፥፭፣፲፪፥፭፣፲፥፲፪)
Mostrar todo...
👍 2
Photo unavailableShow in Telegram
ዳንኤልን ያዳንከው -  ከአፈ አናብስት፤ ሶስናን የታደግክ - ከምክረ ረበናት፤ የእስራኤል መሪያቸው - ታጋያቸው ለዕርስት፤ የአፎምያ ጋሻ - የባሕራን ሕይወት፣ የላዕልይበላ ክንድ - የምህንድስናው ኪነት፤ በቅድመ እግዚአብሔር - በላይ በጸባኦት፤ ክንፍኽን ዘርግተኽ  - በመንበረ ስብሐት፤ ዘወትር የምትቆም - በቀንም በሌሊት፤ የኹላችን አባት - ሊቁ ሊቀ መላእክት፤ መጋቤ ብሉይ - የዳዊት ረዳት፤ ሰዳዴ ሳጥናኤል - አኃዜ መንጦላዕት፤ መዝገበ ርኅራኄ - ደራሽ - ለተራቡ ነፍሳት፣ መልአከ ምክሩ - ለሥላሴ ቅድስት፤ ለሰው ልጆች ኹሉ  - የምትለምን ምሕረት፤ በአለም  ማዕበል - ተውጠን በኃጢያት፤ ሰጥመን እንዳንቀር - እንዳንጠፋ በሞት፤ ስምኽን ስንጠራው ስንል መልዓከ ምሕረት፤ ለምንልን ዛሬም -  ለውሉደ ጥምቀት። ፈጥነኽ ድረስልን - ታደገን ከጥፋት። እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!!
Mostrar todo...
👍 3
††† ✝✝✝🌹እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል እና ለቅዱሳኑ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣አደረሰን። ††† †††✝✝✝ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††✝✝✝ ††† በዚህች ቀን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤልን ጨምሮ ቅዱስ ላሊበላ: ቅድስት አፎምያና ቅዱስ ባሕራን ቀሲስ ይከበራሉ:: ††† ✝ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት †††✝ ††† ቅዱስ ሚካኤል በጥንተ ተፈጥሮ በኢዮር: ኃይላት በተባሉት ነገደ መላእክት ተሹሞ ነበር:: ሳጥናኤል በካደ ጊዜ እግዚአብሔር ባወቀ: አንድም በትሕትናውና ደግነቱ በ99ኙ ነገደ መላእክት ላይ ሁሉ ተሹሟል:: ከፍጥረት ወገን ከእመቤታችን ቀጥሎ የቅዱስ ሚካኤልን ያሕል ክብርና ርሕሩሕ የለም:: በምልጃውም: በረዳትነቱም የታወቀ መልአክ ነው:: መጽሐፍ "መልአከ ምክሩ ለእግዚአብሔር" ይለዋል:: "ወስሙ መስተሣሕልም" ይለዋል:: ቂም የሌለው: ለምሕረት የሚፋጠን: ደግ መልአክ ነውና:: በብሉይ ኪዳን በመከራ ለነበሩ ቅዱሳን ሁሉ ሞገስ: ረዳትና አዳኝ ቢሆናቸው "መጋቤ ብሉይ" ተሰኝቷል:: እሥራኤልን 40 ዘመን በበርሃ መርቷል: መግቧልም:: ቅዱስ መጽሐፍ ስለ እርሱ ብዙ ይላል:: (ዘፍ. 48:16, ኢያ. 5:13, መሳ. 13:17, ዳን. 10:21, 12:1, መዝ. 33:7, ራዕይ. 12:7) ደስ የሚለው ደግሞ ርሕሩሑ መልአክ ከእመቤታችን ጋር ልዩ ፍቅር አለው:: ከእናቷ ማሕጸን ጀምሮ እስከ ዛሬ እነሆ አብሯት አለ:: ደስ ብሎት ይታዘዛታል:: ማማለድ ሲፈልግም "እመቤቴ ሆይ! ቅደሚ" ይላታል:: ወደ እሳት መጋረጃ አብረው ገብተው ለዓለም ምሕረትን: በረከትን ያወርዳሉ:: ቅዱስ ሚካኤልን በዚሕች ዕለት ስለ እነዚህ ነገሮች እናከብረዋለን:- 1.በመላእክት ሁሉ ላይ አለቃ ሆኖ መሾሙን 2.ቅዳሴ ቤቱን (ግብፅ ውስጥ) 3.ቅድስት አፎምያን መርዳቱን 4.ቅዱስ ባሕራንን መጎብኘቱን 5.ቅዱስ ላሊበላን ወደ ሰማያት ማሳረጉን 6.ለፍጥረታት ሁሉ ምሕረት የሚጠይቅበት ዕለት ነውና:: ††† ሊቀ መላእክት በክንፈ ረድኤቱ ከክፉ ሁሉ ይጠብቀን:: ††† ✝✝ቅዱስ ላል ይበላ ንጉሥ †††✝✝ ††† በ12ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ ላይ በሃገራችን የነገሠው ቅዱስ ላሊበላ:- ¤በብሥራተ መልአክ ተወልዷል ¤ቅዱሳት መጻሕፍትን ገና በልጅነቱ አጥንቷል ¤የንጉሥ ዘር ቢሆንም በጾምና ጸሎት: በትሕርምት አድጓል ¤በወንድሙ ቢገረፍም ቂም አልነበረውም ¤ስለ ወዳጆቹ ፍቅር መርዝ ጠጥቷል ¤በዙፋን ላይ የኢትዮዽያ ንጉሥ ሆኖ ቢቀመጥም እርሱስ አኗኗሩ ገዳማዊ ነበር ¤ከተባረከች ሚስቱ ቅድስት መስቀል ክብራ ጋር አንዲት ማዕድ ብቻ በቀን ይቀምሱ ነበር:: ለዛውም ለምለሙን ለነዳያን ሰጥተው እነርሱ የሚበሉት የእንጀራውን ቅርፍት (ጠርዝ) ብቻ ነበር:: በአካለ ሥጋ ወደ ሰማያት ተነጥቆ ብዙ ምሥጢራትን አይቷል ¤በምሳሌውም ሃገረ ሮሃን (ላስታን) ገንብቷል ¤ዛሬም ድረስ ምስጢር የሆኑት ፍልፍል አብያተ መቃድስ የእጆቹ ሥራዎች ናቸው:: ሥራውን ከፈጸመ በኋላ መንግሥቱን ለቅዱስ ነአኩቶ ለአብ አውርሶ: በመንኖ ጥሪትና በቅድስና ኑሮ በዚሕች ቀን አርፏል:: ጌታችን ስምህን ያከበረ: ዝክርህን የዘከረ: ከቤትህ ያደረውን: ከርስተ መንግስተ ሰማያት አካፍለዋለሁ ሲል ቃል ኪዳን ገብቶለታል:: ††† በረከቱን: ክብሩን ያድለን:: ††† ቅድስት አፎምያ ††† ከቅዱስ አስተራኒቆስ ጋር በተቀደሰ ትዳር የኖረች ¤ምጽዋትን ያዘወተረች ¤በፍቅረ ቅዱሳን የጸናች ¤ንጽሕናዋን ጠብቃ ሰይጣንን ያሳፈረች ደግ እናት ናት:: ዛሬ የቅዱስ ሚካኤልን ስዕል ታቅፋ: በትእምርተ መስቀልም አማትባ አርፋለች: ቅዱሱ መልአክም ወደ ገነት አሳርጓታል:: ††† ✝✝ቅዱስ ባሕራን ቀሲስ †††✝✝ የደጋግ ክርስቲያኖች ግን የድሆች ልጅ: ¤በሕጻንነቱ በግፍ ወደ ባሕር የተጣለ: ¤በእግዚአብሔር ጥበብ አድጎ የግፈኛውን ንብረት የወረሰ: ¤በመልካም ትዳር በቅስና ያገለገለ: ¤ምጽዋትን ያዘወተረ: አብያተ ክርስቲያናትን ያሳነጸ ደግ ክርስቲያን ነው:: ¤በዚህች ቀን አርፎ ቅዱስ ሚካኤል ወዳጁ በዕረፍተ ገነት አኑሮታል:: ††† አምላካችን እግዚአብሔር ከቅዱሳኑ በረከት ይክፈለን:: አሜን:: ††† ††† ሰኔ 12 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1.ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት 2.ቅዱስ ላሊበላ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮዽያ) 3.ቅድስት አፎምያና ባለቤቷ ቅዱስ አስተራኒቆስ 4.ቅዱስ ባሕራን ቀሲስ 5.ቅዱስ እለ እስክንድሮስ ሊቅ 6.አባ ዮስጦስ ሊቀ ዻዻሳት (የሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ ደቀ መዝሙር) 7.አባ ቄርሎስ ሊቀ ዻዻሳት ††† ወርሐዊ በዓላት 1.ቅዱስ ማቴዎስ ሐዋርያ 2.ቅዱስ ድሜጥሮስ 3.ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ 4.ቅዱስ ቴዎድሮስ ምሥራቃዊ (ሰማዕት) 5.ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ 6.አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ ††† "በሰማይም ሰልፍ ሆነ:: ሚካኤልና መላእክቱ ዘንዶውን ተዋጉ:: ዘንዶውም ከመላእክቱ ጋር ተዋጋ:: አልቻላቸውምም:: ከዚያም ወዲያ በሰማይ ሥፍራ አልተገኘላቸውም:: ዓለሙንም ሁሉ የሚያስተው ዲያብሎስና ሰይጣን የሚባለው ታላቁ ዘንዶ እርሱም የቀደመው እባብ ወደ ምድር ተጣለ::" ††† (ራዕይ. 12:7) ††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር ††† https://t.me/zikirekdusn
Mostrar todo...
ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ)

በዚህ ቻናል ዲ/ዮርዳኖስ የሚያስተምራቸው ወቅታዊ እና የነገረ ቅዱሳን (ዝክረ ቅዱሳን ትምህርቶችን ከእርሱ በመቀበል እናስተላልፋለን):: "ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/

👍 2
Elige un Plan Diferente

Tu plan actual sólo permite el análisis de 5 canales. Para obtener más, elige otro plan.