es
Feedback
ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

Ir al canal en Telegram

በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:-  @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

Mostrar más
669
Suscriptores
+124 horas
+37 días
-330 días
Archivo de publicaciones
ፎቶ :- የከተራ በዓል በአሰላ 2018 ዓ.ም
+7
ፎቶ :- የከተራ በዓል በአሰላ 2018 ዓ.ም

ፎቶ :- የከተራ በዓል በአሰላ 2018 ዓ.ም
+6
ፎቶ :- የከተራ በዓል በአሰላ 2018 ዓ.ም

ፎቶ :- የከተራ በዓል በአሰላ 2018 ዓ.ም
+4
ፎቶ :- የከተራ በዓል በአሰላ 2018 ዓ.ም

ፎቶ:- የከተራ በዓል በአሰላ 2018 ዓ.ም
+4
ፎቶ:- የከተራ በዓል በአሰላ 2018 ዓ.ም

“ስለዚህ በዓሉን የምናከብረው እንደ አረማዊ በዓል ሳይሆን እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ነው በዓለማዊው መንገድ ሳይሆን ከዓለም በላይ በሆነ መንገድ ነው።የራሳችን ጉዳይ  ሳይሆን የኛ የሆነውን ወይም የጌታችንን ጉዳይ የምናከብረው ስለ ሕመም ሳይሆን ስለ ፈውስ ነው።"               ቅዱስ ጐርጐርዮስ ዘእንዚናዙ

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ እንኳን ለከተራ ፣ ለጥምቀትና ለቃና ዘገሊላ በዓል በሰላም በጤና በፍቅር አደረሳችሁ ። የአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራ ታቦተ ኪዳኑ የሚነሳው 7:00 ሰዓት ላይ
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ እንኳን ለከተራ ፣ ለጥምቀትና ለቃና ዘገሊላ በዓል በሰላም በጤና በፍቅር አደረሳችሁ ። የአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራ ታቦተ ኪዳኑ የሚነሳው 7:00 ሰዓት ላይ መሆኑን አውቃችሁ በጊዜ በአጥቢያችን ተገኝተን ታቦቱን እንድንሸኝ ስንል መልዕክታችንን እናስተላልፋለን። ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ መልካም በዓል ይሁንልን🙏 ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

"አገልጋይ (ፀሐይ) አንተን ለማገልገል ቀድማ ተነስታ ስትጠብቅህ ጌታዋ የተባልከውን አንተ ግን አስከዚች ሰዓት ተኝተህ መገኘትህ አያሳፍርህምን?" "አእምሮ ረጋ ብሎ ሳለ የህይወትህን መሪ እግዚአብሔርን አናግረው ። ፀሐይ ሳትቀድምህ አንተ ፀሐይን ቅደማት።"    ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

🛑 3 ቀን ቀረ ✨ እንኳን ለጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ! "ያን ጊዜ ኢየሱስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ።" ማቴ 3፡13
🛑 3 ቀን ቀረ ✨ እንኳን ለጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ! "ያን ጊዜ ኢየሱስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ።" ማቴ 3፡13

​​🙏 እናምናለን 🙏 እናምናለን እናምናለን እኛስ ምስጢረ ሥላሴን እናምናለን እኛስ(፬) ንግበር ሰብዐ ብለው ሥላሴ ሲፈጥሩን ተምረናል እኛ ከዚህ ሶስትነትን በስም በአካል በግብር ሦስት እያልን ብናምንም አንድ እግዚአብሔር እንጂ ሦስት አምላክ አንልም በአካል በስም በግብር በፍፁም ሦስት ነው ሁለትም አይደለ አራተኛም የለው እናምናለን እናምናለን እኛስ ምስጢረ ሥላሴን እናምናለን እኛስ(፪) በባሕሪይ በአገዛዝ በመለኮት ክብር እናምናለን እኛ አንድ ነው እግዚአብሔር ነውና እግዚአብሔር አንድም ሲሆን ሦስት እንደተገለጠው በአብርሃም ቤት እናምናለን እናምናለን እኛስ ምስጢረ ሥጋዌን እናምናለን እኛስ(፪) የሰውን ባሕሪይ ገንዘብ ያደረገው ከሦስቱ አካል አንዱ ፍፁም ሰው የሆነው ምስጢረ ስጋዌ ያለጥርጥር የማይመረመር ጥልቅ ነው ምስጢር ፍፁም አምላክ ሆኖ ፍፁም ሰው የሆነው በተዋሃደው ሥጋ እኛን ለማዳን ነው እናምናለን እናምናለን እኛስ ምስጢረ ጥምቀትን እናምናለን እኛስ(፪) ከመንፈስ ከውሃ ያልተወለደ ሰው በፍፁም አይድንም ጌታችን እንዳለው በባህረ ዮርዳኖስ በዮሐንስ እጅ ተጠመቀ ጌታ ነፃነት ሊያውጅ ዕዳ በደላችን የግዞት ማህተብ ተደምስሷልና በጥምቀቱ ሰላም እናምናለን እናምናለን እኛስ ምስጢረ ቁርባንን እናምናለን እኛስ(፪) የዘላለም ህይወት አምላክ እንዲሰጠን እንብላ ስጋውን እንጠጣ ደሙን ኢየሱስ በመስቀል ደሙን ያፈሰሰው በሥጋ ወደሙ እኛን ሊያከብረን ነው እናምናለን እናምናለን እኛስ ትንሳኤ ሙታንን እናምናለን እኛስ(፪) በመጨረሻው ቀን ጌታችን ሲመጣ መንግስተ ሰማያት ስትታይ ተገልጣ መለከት ሲነፋ ነጋሪት ሲመታ የሰው ልጅ ይነሳል መቃብር ተከፍታ ሙታን አካል ገዝፈው ለፍርድ ይመጣሉ ሀሉም በጌታ ፊት ይሰበሰባሉ እናምናለን እናምናለን እኛስ አእማደ ምስጢርን እናምናለን እኛስ እናምናለን እናምናለን እኛስ ምስጢረ ሥላሴን እናምናለን እኛስ እናምናለን እናምናለን እኛስ ምስጢረ ሥጋዌን እናምናለን እኛስ እናምናለን እናምናለን እኛስ ምስጢረ ጥምቀትን እናምናለን እኛስ እናምናለን እናምናለን እኛስ ምስጢረ ቁርባንን እናምናለን እኛስ እናምናለን እናምናለን እኛስ ትንሳኤ ሙታንን እናምናለን እኛስ                      ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ <<… በማኅበር እልፍ ቃላት በልሳን ከመናገር ይልቅ አምስት ቃላት በአእምሮዬ ልናገር እወዳለሁ>>               ፩ቆሮ ፲፬፥፲፱

ነአምን በአብ ወነአምን በወልድ ወነአምን በመንፈስ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ አምላክ ፍጹም አሐዱ ውእቱ 🙏🙏🙏 ኵሉ ይሰግድ ለሥላሴ ፤ ወይትቀነይ ኵሉ ለመንግሥተ ሥላሴ፤ እስመ ኮነ ዘይነብር ዲበ ኪሩቤል
ነአምን በአብ ወነአምን በወልድ ወነአምን በመንፈስ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ አምላክ ፍጹም አሐዱ ውእቱ 🙏🙏🙏 ኵሉ ይሰግድ ለሥላሴ ፤ ወይትቀነይ ኵሉ ለመንግሥተ ሥላሴ፤ እስመ ኮነ ዘይነብር ዲበ ኪሩቤል፤ ወበዓይኑ ይኔጽር ቀላያተ፡፡ 🌹እንኳን ሥሉስ ቅዱስ የባቢሎንን ግንብ ላፈረሱበት ዕለት እና ለቅዳሴ ቤታቸው ለከበረበት ዕለት በሰላም  አደረሳችኹ!🌹 ቅድስት ሥላሴ የእኛንም መለያየት እና የከበበንን መከራ እንደባቢሎን ግንብ አፍርሰው ለሕይወት ያብቁን 🤲🤲🤲 አሜን በእውነት!

ሊገርዙት ስምንት ቀን በሞላ ጊዜ፥በማሕፀን ሳይረገዝ በመልአኩ እንደ ተባለ፥ስሙ ኢየሱስ ተብሎ ተጠራ። ሉቃስ 2÷21

"አቤቱ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! እንደ ቸርነትህ ብዛት እንጂ እንደ በደላችን አይደለም። ያንተን ስም ሰምቶ ሞት ይደንግጥ፤ ቀላያት ይሠንጠቁ፤ ጠላትም ይረገጥ፤ የጥፋት መንፈስ ይንቀጥቀጥ፤ ከይሲም ይወገድ፤ አለማመንም ይራቅ።ወንጀለኛ ይቸገር፤ ቁጣ ጸጥ ይበል፤ ቅናት ጥቅም አያግኝ፤ ኃጢአትን የሚያዘወትር ይገሠጽ። ወርቅን የሚወዱ ይነቀሉ፤ ድካም ይወገድ፤ ሐሰተኛ ይጣል፤ መርዝ ያላቸው የፍጥረታት ወገን ሁሉ ይበተኑ። ​ሰውን ሁሉ የምታድን ሆይ! እኛን ባሮችህን ጠብቀን። በዚህ ክቡር ሥጋህና ደምህ የምንሳተፍ ሁላችንንም አንጻን፤ ቀድሰን። ካንተ ጋር አንድ የምንሆንበትን፣ በቅድስና የምንኖርበትን፣ አንተን የምናመሰግንበትን ጸጋ ስጠን።"      ቅዳሴ እግዚእ የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel

ይህን ያውቁ ኖሯል? ጥር 6 አራት ታላላቅ ዓመታዊ ክብረ በዓላት በቤተክርስቲያናችን ይከበራሉ። 👉በዓለ ግዝረት 👉የቅዱስ ኤልያስ ዕርገት 👉የቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያ ዕረፍት 👉የቅድስት አርሴማ የተወለደችበት የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel

"መምህራ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ከቀዳማዊ አብ ጋራ አንድ የምትሆን፤ ንጹሕ የሚሆን የአብ ቃል፤ የማሕየዊ መንፈስ ቅዱስም ቃል፤ ከሰማያት የወረድህ የሕይወት ኅብስት አንተ ነህ፡፡ ስለ ዓለሙ መዳን ነው
"መምህራ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ከቀዳማዊ አብ ጋራ አንድ የምትሆን፤ ንጹሕ የሚሆን የአብ ቃል፤ የማሕየዊ መንፈስ ቅዱስም ቃል፤ ከሰማያት የወረድህ የሕይወት ኅብስት አንተ ነህ፡፡ ስለ ዓለሙ መዳን ነውር የሌለበት መሥዋዕት እንድትሆን መናገርን አስቀደምህ፡፡ አሁንም ከበጎነትህ ቸርነት እንለምናለን እንማልዳለን፡፡ ሰው ወዳጅ ሆይ ....አምላካችን ክርስቶስ የሁላችን ንጉሥ አንተ ነህ፡፡ ከፍ ያለ ምስጋናንና ክብርን ስግደትንም ላንተ እንልካለን፡፡ ቸር ከሚሆን ከሰማያዊ አባትህ ጋራ ካንተ ጋራ ከሚተካከል ከማሕየዊ መንፈስ ቅዱስም ጋራ ዛሬም ዘወትርም ለዘላለሙ፤ አሜን፡፡"    ሥርዓተ ቅዳሴ

"ታገስ ዝም በል ጸልይ እግዚአብሔር ይዋጋልሃል።"     አባ አርሳንዮስ

የፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት ብርቅዬ አገልጋይ የሆነው ወንድማችን መዘ/ር ደበሌ ኮራ በትላንትናው ዕለት በአስኳላ ትምህርት ተመርቋል። መላው የፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት አባላት ወንድም እና እህቶችህ መል
የፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት ብርቅዬ አገልጋይ የሆነው ወንድማችን መዘ/ር ደበሌ ኮራ በትላንትናው ዕለት በአስኳላ ትምህርት ተመርቋል።    መላው የፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት አባላት ወንድም እና እህቶችህ መልካም የስራ ዘመን እና የአገልግሎት ዘመን እንመኝልሃለን። 🙏🙏🙏

የፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት ብርቅዬ አገልጋይ የሆነችው እህታችን መዘ/ት መነን ዮናስ በዛሬው እለት በአስኳላ ትምህርት ተመርቃለች። መላው የፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት አባላት ወንድም እና እህቶችሽ መልካ
የፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት ብርቅዬ አገልጋይ የሆነችው እህታችን መዘ/ት መነን ዮናስ በዛሬው እለት በአስኳላ ትምህርት ተመርቃለች።    መላው የፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት አባላት ወንድም እና እህቶችሽ መልካም የስራ ዘመን እና የአገልግሎት ዘመን እንመኝልሻለን። 🙏🙏🙏

የፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት ብርቅዬ አገልጋይ የሆነችው እህታችን መዘ/ት መነን ዮናስ በዛሬው እለት በአስኳላ ትምህርት ተመርቃለች። መላው የፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት አባላት ወንድም እና እህቶችሽ መልካ
የፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት ብርቅዬ አገልጋይ የሆነችው እህታችን መዘ/ት መነን ዮናስ በዛሬው እለት በአስኳላ ትምህርት ተመርቃለች። መላው የፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት አባላት ወንድም እና እህቶችሽ መልካም የስራ ዘመን እና የአገልግሎት ዘመን እንመኝልሻለን። 🙏🙏🙏

የፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት ምክትል ሊቀ መንበር የሆነችው አመለ ሸጋዋ ፣ ሳቂታዋ እና ከሁሉ ጋር ተግባቢ የሆነችው እህታችን ሰርካለም ተክሌ በዛሬው ዕለት ተመርቃለች። እንኳን ደስ አለሽ እህታችን
የፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት ምክትል ሊቀ መንበር የሆነችው አመለ ሸጋዋ ፣ ሳቂታዋ እና ከሁሉ ጋር ተግባቢ የሆነችው እህታችን ሰርካለም ተክሌ በዛሬው ዕለት ተመርቃለች። እንኳን ደስ አለሽ እህታችን መላው የፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት አባላት ቀሪው ዘመንሽ የተባረከ እንዲሆንልሽ እንመኛለን🙏🙏
🙏

"እግዚአብሔር በወጀብና በዐውሎ ነፋስ ውስጥ መንገድ አለው ደመናም የእግሩ ትቢያ ነው" ናሆም 1÷3