es
Feedback
ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

Ir al canal en Telegram

በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:-  @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

Mostrar más
671
Suscriptores
+324 horas
+77 días
+430 días
Archivo de publicaciones
እግሮቻችሁ በብረት ችንካር እንደ ተተከሉ እንደ ጽኑ አምዶች ጸንታችሁ በቤተ እግዚአብሔር ትኖሩ ዘንድ እነግራችኋለሁ።"                             ✨️️✨️️🌿ቅዱስ አትናቴዎስ 

ቋሚ ሲኖዶስ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ቅድስት ድንግል ማርያምን በማስመልከት ባስተላለፉት ትምህርት ዙሪያ ተወያየ። ሚያዚያ ፲፭ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም ; አዲስአበባ -ኢትዮጵያ +++++++++++++++++++
ቋሚ ሲኖዶስ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ቅድስት ድንግል ማርያምን በማስመልከት ባስተላለፉት ትምህርት ዙሪያ ተወያየ። ሚያዚያ ፲፭ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም ; አዲስአበባ -ኢትዮጵያ +++++++++++++++++++++++++++++++++ ቋሚ ሲኖዶስ ዛሬ ማለዳ ባደረገው መደበኛ ስብሰባ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ባለፈው አርብ በስቅለት ዕለት በፎኖተ ጽድቅ ቴሌቪዥን በቅድስት ድንግል ማእያም ዙሪያ ያስተላሐፉትን ትምህርት በተመለከተ ውይይት አድርጓል። ብፁዕነታቸው  የተላለፈውን ትምህርት ዝርዝር ሁኔታን በመመርመርም ውሳኔ ለማስተላለፍ  ይቻል ዘንድ ሁሉም የቋሚ ሲኖዶስ አባላት በምልዓት በተገኙበት  ለአርብ ሚያዚያ ፲፯ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም ቀጠሮ ተይዞል። በተያያዘ ዜና የሮም ካቶሊክ ቤተክርስቲያን መሪ በሆኑት በብፁዕ ወቅዱስ ፖፕ ፍራንሲስ ስርዓተ ቀብር ላይ፦ ብፁዕ አቡነ ዲዮናስዮስ በየምሥራቅ ጎጃም እና በአውሮፓ ጀርመን አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የጣልያንና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ቤተክርስቲያናችንን በመወከል እንዲገኙ ተወስኗል። © የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

በሥላሴ ገመድ ፍጹም ታስረናል፤ከልባችን በማይነቀል በቅንዋተ ፍቅሩ ተቸንክረናል፣እርሱ ወዶናል አይጠላንም።እኛም በእምነት ይዘነዋል አንተወውም።"                               ✨️️✨️️🌿አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ

ፎቶ :-13/08/2017 ዓ.ም ሁለተኛ ቀን የነድያን ምገባ ተከናወነ።
+5
ፎቶ :-13/08/2017 ዓ.ም ሁለተኛ ቀን የነድያን ምገባ ተከናወነ።

ፎቶ :- 12/08/2017 ዓ.ም በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት የ2017 ዓ.ም የትንሣኤ በዓል ነድያንን ጾም የማስፈቻ እና ምገባ መርሀ ግብር ከ1000 በላይ ነድያንን
+9
ፎቶ :- 12/08/2017 ዓ.ም በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት የ2017 ዓ.ም የትንሣኤ በዓል ነድያንን ጾም የማስፈቻ እና ምገባ መርሀ ግብር ከ1000 በላይ ነድያንን በመመገብ በአማረና ደስ በሚል መልኩ ተከናወነ። በአገልግሎታችን ሁሉ የማይለየን አምላካችንን መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ስሙ ለዘለዓለም የተመሰገነ ይሁን።

ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን፤ በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን፣ አሰሮ ለሰይጣን፤ አግዐዞ ለአዳም፣ ሰላም፤ እምይእዜሰ፣ ኮነ፤ ፍስሐ ወሰላም። "ሕያውን ከሙታን መካከል ስለምን ትፈልጋላችሁ ተነሥቷል እንጂ በዚህ
ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን፤ በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን፣ አሰሮ ለሰይጣን፤ አግዐዞ ለአዳም፣ ሰላም፤ እምይእዜሰ፣ ኮነ፤ ፍስሐ ወሰላም። "ሕያውን ከሙታን መካከል ስለምን ትፈልጋላችሁ ተነሥቷል እንጂ በዚህ የለም።" ሉቃ. ፳፬፥፭      እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን፤ መልካም የትንሣኤ በዓል🙏💐🌹

"ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሳ፤ ሞቶ ሞትን አጠፋው በመቃብሩ ላሉ የዘላለም ዕረፍት  የሚሆን ሕይወትን ሰጠ"

✨ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ ትንሣኤ በሰላም አደረሳችሁ!!! ወተንሥአ እግዚአብሔር ከመ ዘንቃህ እምንዋም ወከመ ኃይል ወኀዳግ ወይን ወቀተለ ፀሮሙ በድኀሬሁ ትርጉም እ
✨ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ ትንሣኤ በሰላም አደረሳችሁ!!! ወተንሥአ እግዚአብሔር ከመ ዘንቃህ እምንዋም ወከመ ኃይል ወኀዳግ ወይን ወቀተለ ፀሮሙ በድኀሬሁ ትርጉም እግዚአብሔር ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተነሳ የወይን ሰካር እንደ ተወው ኀይለኛም ሰው ጠላቶቹን በኋላቸው መታቸው መዝ ፸፯-፷፭ 77  65 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27

ቅዳሜ ማለት ቀዳሚት ሰንበት (የመጀመሪያዋ ሰንበት) ማለት ነው መጀመሪያነቷም ከሀዲስ ኪዳኗ ሰንበት ከእሁድ ነው ይህችንም ቀዳሚት ሰንበትን እግዚአብሔር  በመጀመሪያ፦ ዓለምን ፈጥሮ ጨርሶ አርፎባታል ወአዕረፈ እግዚአብሔር እምኩሉ ግብሩ በሳብዕት እለት  እግዚአብሔርም በሰባተኛዋ ቀን ከስራው ሁሉ አረፈ                 ዘፍ 2÷2 በሁለተኛ፦ በዚህ ምድር ሥጋ ለብሶ ሲመላለስ ሙታንን አስነስቶባታል ድውያንን ፈውሶባታል ለምጻሞችን አንጽቶባታል እውራንን አብርቶባታል በሦስተኛ፦ ሠላሳ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር በልብሰተ ሥጋ ከተመላለሰ በኋላ በተለይም ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ወንጌልን ካስተማረ በኋላ በዕደ አይሁድ ተይዞ ተሰቅሎ ተገርፎ ሞቶ በመቃብር አርፎባት ውሏል በአራተኛ ፦ በዓለም ፍጻሜ (ምጽዐት) የሰው ልጅ ሞቶ የሚያልቀው ዓርብ ነው ቅዳሜ የሰው ልጅ ሁሉ ከድካመ ሥጋ አርፎ ይውላል መሬትም አርፋ ትውላለች። ይህችም ቀዳሚት ሰንበት ቅዳም ሥዑር ትባላለች ቅዳም ሥዑር ማለትም የተሻረች ቅዳሜ ማለት ነው ይህንን በመያዝ አንዳንድ ሰዎች የተሻረች ማለት ከበዓልነቷ መስሏቸው የስራ መስሪያ እለት የሚያደርጓት አሉ ይህ ግን ፈጽሞ ስሕተት ነው። የተሻረች ማለት ግን ከመበላት ነው ፍትሐ ነገሥት ፍትህ መንፈሳዊ ሰንበታትን የሚያፆም ካህን ቢኖር ከክህነቱ ይሻር ይላል አን 15÷551 ስለዚህ በመጾም የተሻረች አለመጾሟ የተሻረባት መብል መጠጥ የተከለከለባት ማለት ነው ። አክፍሎት፦ አክፍሎት ማለት ማክፈል ማለት ነው ከምግብ ከመጠጥ ተከልክሎ ሳይበሉ ሳይጠጡ መዋል ይህንንም የጀመሩት ሐዋርያት ናቸው ሐሙስ ምሽት ጀምረው የተበተኑ ሐዋርያት ጌታ ከተሰቀለና ከሞተ ወደመቃብርም ከወረደ በኋላ ተሰብስበዋል ከዚህ በኋላም ሊመገቡ ሲሉ ከመካከላቸው አንዱ ያዕቆብ ጌታየ እሞታለሁ በሦስተኛው ቀን እነሳለሁ ብሏልና ትንሳኤውን ሳላይ አልመገብም አለ እርሱን አብነት አድርገው ሁሉም ሐዋርያት አክፍለዋል የአክፍሎት ጊዜ ፦ የተቻለው ከሐሙስ ጀምሮ ያከፍላል ምክንያቱም ሐዋርያት ሐሙስ ምሽት በግዐ ፋሲካውን ከተመገቡ በኋላ እሑድ ነውና የተመገቡ ያልተቻለው ግን ዓርብ ይመገባል ቅዳሜን አክፍሎ ውሎ እሑድ አስቀድሶ የተቻለው ሥጋውን ደሙን ተቀብሎ ያልተቻለው ጸበሉን ጠጥቶ ይሔዳል ሥርዐተ ቄጤማ ፦ በዚህች ዕለት አንዱና ጎልቶ የሚታወቀው ካህናትና ዲያቆናት በየቤቱ እየዞሩ ቄጤማ ያድላሉ ሲያድሉም አዳም ተመረመረ ዲያብሎስ ታሰረ እያሉ ነው ይህም ማለት የአዳምን ነጻ መውጣት የዲያብሎስን መጋዝ የሚያመለክት ነው ጌታ ተመረመረ ዲያብሎስ ታሰረም ይባላል ይህም ክርስቶስ በሄሮድስና በጲላጦስ ፊት ቆሞ ተመርምሮ ምንም እንዳልተገኘበት ለማመልከት ነው ቄጤማ ፦ በኦሪቱ ብዙ በጎ ትውፊት አለው በኖኅ ዘመን ርግቧ ኀጸ ማየ አይኅ ነትገ ማየ አይኅ የጥፋት  ውሃ ጎደለ ስትል ለኖኅ በአፏ ቀጤማ ይዛ መጥታለች ካህኑም (ዲያቆኑ) ሐጸ ማየ ኃጢት ነትገ ማየ ኃጢአት የኃጢአት ውሃ ጎደለ ሲል ለሕዝቡ የምሥራች የለመለመ ቄጤማ ያድላል ። መልካም የአክፍሎት ቀን 🌴🌴🌴🌴🌴🌴              🌒 ዘመልአክ ዳግም 🌗

በዘጠኝ ሰዓትም አሞትና ከርቤ አጠጡት በአፉ ውስጥም ጋቱት ሰይጣንና ሞትን ይጠብባቸዋል ዘንድ በቃሉ ጮሆ ወደ አባቱ አመለከተ ....መዝገበ ሃይማኖት....

*ዘጠኝ ሰዓት ሲሆን*        ዘጠኝ ሰዓት ሲሆን አባት ሆይ በመስቀል ሆነህ አባት ሆይ ድምጽህን በማሰማት አባት ሆይ ነፍስህን ሰጠህ አባት ሆይ ከዋክብተ ሰማይ በሙሉ ረገፉ ጨረቃና ፀሐይ ደምን አጎረፉ ብርሃናት ጨለሙ ጠፍተው ተለያዩ ሥጋህን በመስቀል ተገልጦ ስላዩ ጌታችን ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሳለ አሰምቶ ጮኸ ተጠማሁ እያለ ማርና ወተትን ለሚመግበው ሐሞት አመጡለት ይቅመሰው ብለው አካሉ ሲወጋ ውኃ ደም ፈሰሰ በምድር ተረጭቶ ዓለምን ቀደሰ የእሥራኤል ሴቶች ዋይ ዋይ ሲሉልህ ለእነርሱ አዘንክ እንጂ ለአንተስ አላሰብክም እናትህ ስታለቅስ በመስቃል ሥር ሆና ዮሐንስን ሰጠህ ጠብቆ እንዲያፅናና መላእክትም ታዩ አጋንንትም ሸሹ የአይሁድ ሠራዊት ፈርተው ተረበሹ

ዘጠኝ_ሰዓት_ሲሆን_አባት_ሆይ_ሊቀ_መዘምራን_ኪነጥበብ_ወ_ቂርቆስ_lik_Mezemeran_Kinti.m4a5.46 MB

ዓርብ ዓርብ ማለት መካተቻ መፈጸሚያ ማብቂያ ማለት ነው። ፩, , እግዚአብሔር ፳፪ቱን ሥነፍጥረት ፈጥሮ የጨረሰበት ዕለት ነው። "እግዚአብሔርም የሠራውን ሥራ በሰባተኛው ቀን ፈጸመ፤ በሰባተኛውም ቀን ከሠራው ሥራ ሁሉ ዐረፈ። እግዚአብሔርም ሰባተኛውን ቀን ባረከው ቀደሰውም፤ እግዚአብሔር ሊያደርገው ከፈጠረው ሥራ ሁሉ በእርሱ ዐርፎአል"    ዘፍ ፪÷ ፪ ፪, አዳም አርባ ቀን የምድር ኑሮውን ጨርሶ ወደ ገነት የገባበት ዕለት  ነው ። "እግዚአብሔር አምላክም ሰውን ወስዶ ያበጃትም ይጠብቃትም ዘንድ በዔድን ገነት አኖረው" ዘፍ ፪ ÷ ፲፭ ፫, አዳም የገነት ኑሮውን ፈጽሞ የተባረረበት ዕለት ነው። "ስለዚህ እግዚአብሔር አምላክ ከዔድን ገነት አስወጣው፥ የተገኘባትን መሬት ያርስ ዘንድ። አዳምንም አስወጣው፥ ወደ ሕይወት ዛፍ የሚወስደውንም መንገድ ለመጠበቅ ኪሩቤልንና የምትገለባበጥ የነበልባል ሰይፍን በዔድን ገነት ምሥራቅ አስቀመጠ"    ዘፍ ፫ ÷ ፳፫~፳፬ ፬, እስራኤል ፵ ዘመን መና ከደመና እየወረደላቸው ሲመገቡ ኑረው ርደተ መናው ተፈጽሞ የከነአንን ፍሬ መመገብ የጀመሩበት ዕለት ነው ። "ወዓርበ መና በፊንቆን እን እንጀራም በፊንቆን ቀረ የከነዓንንፍሬም መመገብ ጀመሩ" ፭, የክርስቶስ የሠላሳ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ጉዞ የነፍሳት አምሥት ሺኽ አምስት መቶ ዘመን ጉዞ ተፈጸመ "ኢየሱስም ሆምጣጤውን ከተቀበለ በኋላ፦ “ተፈጸመ፡” አለ፥ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ" ዮሐ ፲፱÷፴ ሲኦል ተነዋወጠች መሠረቶቿም እፈርስ እፈርስ አሉ  ምድርን ያለጊዜዋ እንዳታልፍ አጸናት ደሙን በምድር ላይ አፈሰሰ ከኅልፈት ጠበቃት በእርሷ ያለውንም ሁሉ ጠበቀ ስለ ፍጥረት ሁሉ ሥጋውን በመስቀል ላይ እንደተሰቀለ ተወው ነፍሱ ግን ወደ ሲኦል ወርዳ ከዚያው ተግዘው የነበሩ ነፍሳትን አዳነች ሲኦልንም በዘበዘች ፍጥረትንም ሁሉ ገንዘብ አደረገች ሥጋውም በመቃብር ያሉ ሙታንን አስነሣ ነፍሱም በሲኦል የነበሩ ነፍሳትን ፈታች            ሃይ አበ ዘአትና ፳፮ ÷ ፲፰~፳፩ ፮, በዕለተ ከእሑድ እስከ ዓርብ ተፈጥሮ በዕለተ ዓርብ ፍጻሜ ያገኘ ሥነ ፍጥረት በኅልፈት ፍጻሜ የሚያገኝ በዚህ እለት ነው ። ወሶበ ተፈጸመ ኵሉ አሜሃ ለእሊአሁ ለኅሩያኒሁ ወለጻድቃኒሁ ደብተራ ብርሃን ይተክል ወመንጦላዕተ ብስሃን ይሰፍሕ ዘቦ ፯ቱ ምሥዋር ትርጕም፦ ሉሉ ከተፈጸመ በኋላ ያን ጊዜ ለመረጣቸው ለወዳጆቹ ለጻድቃኖቹ የብርሃን ድኖኳን ይተከላል ሰባት መሠወሪያ ያለው የብርሃን መጋረጃ ይዘረጋል        ቅዳ አት  ፩÷ ፺፫ @ምሥራቀ ጸሐይ ጉባዔ ቤት

ፎቶ :- 10/8/2017 ዓ.ም የስቅለት በዓል ዝግጅት በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል ።
+4
ፎቶ :- 10/8/2017 ዓ.ም የስቅለት በዓል ዝግጅት በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል ።

🌿🌿🌿✨✨✨🌿🌿🌿✨✨✨🌿🌿🌿✨✨✨ "በወገቡ የታጠቀውን ማድረቂያ አይተው መላእክት አደነቁ፤ ስሙ ከፀሓይና ከጨረቃ በፊት የነበረ እርሱ አገልጋይ ኾነ፤ ሕያው ጌታን ሱራፌል ያመሰግኑታል፤ ቦታውን ግን አያውቁም፤ ሱራፌልን የፈጠረ እርሱ በእራት ጊዜ ወገቡን ዘርፍ ባለው ዝናር ታጠቀ፤ እንዳያቃጥል በመፍራት የማይታይ እሳት ለሐዋርያት አገልጋይ ኾኖ አብነት ይኾናቸው ዘንድ የትሕትና ሥራን የሚሠራበትን ውሃ በኩስኩስት ቀዳ የደቀ መዛሙርቱን አለቃ ጴጥሮስንም እግሩን ሊያጥበው ጠራው" 🌿✨ሃይማኖተ አበው ዘያዕቆብ ዘሥሩግ "ተራሮችን በኃይሉ የሚያስታጥቃቸው ለማገልገል ማበሻ ጨርቅ ታጠቀ፡፡ የባሕርን ውኃ እንደ አቁማዳ የሚሰበስበው በቀላያትም መዝገቦች የሚሾማቸው እርሱ ከወዳጁ ከአልዓዛር ቤት የውኃ ማድጋ አንሥቶ እግሮችን ለማጠብ ያገለግልባት ዘንድ ወደ ኩስኩስት አፈሰሰ፡፡ እጆቻቸውንና እግሮቻቸውን በሚታጠቡበት ገንዘብ የናስ ኩስኩስት ሠርቶ በደብተራ ኦሪት ደጃፍ እንዲያኖራት ሙሴን ያዘዘው ውኃውን በኩስኩስት ሞልቶ የደቀ መዛሙርቱን እግር ሊያጥብ ዠመረ፡፡ የተረከዞቻቸውንም እድፍ በታጠቀው ማበሻ ጨርቅ አሸ፡፡" 🌿✨ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ   🌿🌿🌿✨✨✨🌿🌿🌿✨✨✨🌿🌿🌿✨✨✨