ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Ir al canal en Telegram
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Mostrar más671
Suscriptores
+324 horas
+77 días
+430 días
Archivo de publicaciones
የህይወት መንገድ ለጨለመባችሁ የድንግል ማርያም ልጅ ቸሩ መድኃኔዓለም በእለተ ቀኑ እውነተኛውንና ቀጥተኛውን መንገድ ይምራችሁ🤌🤲🤲🤲
በችንካር ቸነከሩህ፣
አንተ ግን ይህንን - ለዚያ በሽታቸው፣
ለመድኃኒትነት - ለፈውስ አደረግኸው።
በሰይፍ ወጉህ፤
ኃጢአታቸው እንዲነፃ - ከዚያ ከወጉህ ቦታ፣
ይታጠቡበት ዘንድ - ወዲያውም ውኃ ወጣ።
በመደነቅ ይቆሙ ዘንድ፣
ደምህንም ከእጃቸው - ታጥበውበት እንዲነጣ፣
ወዲያውም ደግሞ ውኃ - ደምም ጭምር ከዚያ ወጣ።
የታረደው እርሱ፡
ከራሱ ደም፡ አራጆቹ - በዚያ እንዲታጠቡ፣
ውኃን ከጎኑ ሰጠ -ሕይወትንም እንዲያገኙ - ነጽተውም
እንዲታሰቡ።
(Virginity 30:10)
(ከብርህት ዓይን ከገጽ 143-144 የተወሰደ)
"ማንም እግዚአብሔርን እወዳለሁ እያለ ወንድሙን ቢጠላ ሐሰተኛ ነው ፤ ያየውን ወንድሙን የማይወድ ያላየውን እግዚአብሔርን ሊወደው እንዴት ይችላል ?"
1ኛ ዮሐ 4÷20
✨✨✨🍁✨✨🍁
ከጠላት ፈተናዎች ተጠንቀቅ!
ዲያቢሎስ ቀስቱን ሲወረውርብንና በውጊያው ሲያውከን ይህ በእኛ ላይ ብቻ የተደረገ ቁጣና ጠላትነት አይደለም፤ ምክንያቱም እርሱ የእግዚአብሔርም ጠላት ነውና በእኛ ላይ ሚደርሰው መከራ በእግዚአብሔር ላይ የሚደረግ ተቃውሞ ነው። ዲያቢሎስ እግዚአብሔርን ማጥቃት ባለመቻሉ ፍጥረታቱን በማታለልና ከእርሱ ከእርሱ ጋር ወደ ዘላለማዊ ቅጣት እንዲገቡ በማድረግ ሊበቀለው ይጥራል፡፡
የተወደድኸው ሆይ! ይህንን ነገር አስተውል! ዲያቢሎስን ስትቃወመውና ስትዋጋው ክፉን ነገር ከእናንተ እያራቅህ ብቻ አይደለም፤ ለእግዚአብሔርም ክብር እየተዋጋህ ነው፡፡ ስለዚህም የክፉውን ዲያቢሎስ ዲያቢሎስ ማማለያና መደለያ በመቀበል እግዚአብሔርን ከማሳዘን ይልቅ ፈተናውን በጽናት ስትታገል በውጊያው ላይ ብትሞት ይሻልሃል፡፡
✨🍁✨
ለአፍታም ቢሆን ብቻህ እየተዋጋ እንዳለህ አድርገህ አታስብ፡፡ ምክንያቱም እግዚአብሔር በጠላትህ ላይ ድል መንሣትን ይሰጥሃል፡፡ "አቤቱ አምላክ ሆይ፥ ተነሥ እጅህም ከፍ ከፍ ትበል ድሆችን አትርሳ፡፡ ኃጢአተኛ ስለ ምን እግዚአብሔርን አስቆጣው? በልቡ:: አይመራመረኝም ይላልና፡፡" (መዝ ፲ ፥ ፲፪ -፲፫) ጥሩርና ጋሻ ያዝ፤ እኔንም ለመርዳት ተነሥ፡፡ ሰይፍህን ምዘዝ የሚያሳድዱኝንም መንገዳቸውን ዝጋ ነፍሴን፦ መድኃኒትሽ እኔ ነኝ በላት።›› (መዝ. ፴፭፥፪-፫)
"አሁንም ያዕቆብ ሆይ፥ የፈጠረህ፥ እስራኤልም ሆይ፥ የሠራህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ተቤዥቼሃለሁና አትፍራ በስምህም ጠርቼሃለሁ፥ አንተ የእኔ ነህ፡፡ በውኃ ውስጥ ባለፍህ ጊዜ ከአንተ ጋር እሆናለሁ፥ በወንዞችም ውስጥ ባለፍህ ጊዜ አያሰጥሙህም፤ በእሳትም ውስጥ በሄድህ ጊዜ አትቃጠልም፥ ነበልባሉም አይፈጅህም።" (ኢሳ. ፫፥፩-፪)
✨🍁✨
በነፍሳችን ላይ ደካማነትን እስካላየ ድረስ ሰይጣን አያጠቃንም፡፡ ጎበዝ አዳኝ ወፎችን ለማደን እንደሚያደርገው ዲያቢሎስም ወጥመዱን ለማስገባት ሁልጊዜ ከእኛ ላይ ቀዳዳን ይፈልጋል፡፡ ብዙ ጊዜም ይዋጋናል፣ ይሸነግለናል በምኞቶቻችንም እየገባ ያገኘናል፡፡
አዳምን በሔዋን፣ ሶምሶንን በምወድደው ደሊላ፣ ንጉሥ ሰሎሞንን በእንግዶች ሴቶች ፍቅር፣ የአስቆሮቱ ይሁዳንም በገንዘብ ፍቅር እንደጣላቸው አላየህም፡፡ ስለዚህ እንደ ጎበዝ ሐኪም ሁን፣ ጉድለትህንና ሕመምህንም አክም፤ ኩራትህን በትሕትናና በየዋህነት ድል አድርገው፣ የትዕቢት በሽታህንም አንተነትህን በመናቅ ፈውሰው፡፡ በተአምራትና በታላቅ ነገሮችም ከመመካት ተጠበቅ ምክንያቱም ዲያቢሎስ ራሱ በብርሃን መልአክ መመስል ይችላል፡፡ በስብ ውስጥ መርዙን ሊከት፣ በማጥመጃው ዘንግ ውስጥም የመደለያ ጣፋጭ ምግብን ሊያደርግና መልካምና ጠቃሚ ነገር ይከተላል ብለህ እንድታምን ሊያታልልህ ይችላል፡፡ አንተ ግን ፈጽሞ አትታለል፣ በከንቱም አትነዳ፡፡ ይልቅስ ከዲያቢሎስ ጥቃት ትጠበቅ ዘንድ ሁሉን ነገር አስተውልና መርምር፡፡
ይሁዳ ጌታውን አልከዳምን? ኢዮአብስ ወዳጅና የሚታመን ሰው መስሎ አሜሳይን አልገደለውምን? (፪ነገ. ፳ ፥ ፱)✨🍁✨ በእግዚአብሔር ታመን! ከመሪ በላይ አጥብቀህ ያዘው፤ ሁሉን ነገር ወደ እርሱ አምጣው፡፡ ድጋፍህና መጠጊያህ አድርገው፤ እርሱ ሁለንተናህ አድርገው። 📚ሊቀ ዲያቆናት ሀቢብ ጊዮርጊስና ሥራዎቹ ገጽ 43-45 - 📝ከዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜
እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ ሕንፀተ ቤታ (ሕንፀታ) በሰላም አደረሳችኹ
ሰኔ ፳፩ (ሕንፀታ ወቅዳሴ ቤታ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን) ከእመቤታችን ፴፫ቱ በዓላት አንዱ ነው፡፡
ጌታችንም ከእመቤታችን እና ከቅዱሳን መላእክት ጋር ከሰማየ ሰማያት ወርዶ እመቤታችንን ታቦት፣ ሐዋርያትን ልዑካን አድርጎ፣ እርሱ ሠራዒ ካህን ኾኖ ቀድሶ ካቈረባቸው በኋላ ‹‹እምይእዜሰ አንትሙኒ ከመዝ ግበሩ፤ ከዛሬ ጀምሮ እናንተም እንደዚህ አድርጉ›› ብሎ አዝዟቸው በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐርጓል፡፡ ከዚህ በኋላ ሐዋርያት ከጌታ እንዳዩት በዓለም ዞረው ቤተክርስቲያንን አንፀዋል።
እግዚአብሔር አምላክ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ፍቅር፥ ረድኤት፥ ጸጋ - የቡሩካን ሐዋርያቱን በረከት ያሳድርብን! አሜን🙏
🔱🔱🔱🔱🔱🔱🔱🔱🔱🔱🔱🔱🔱🔱
✨✨✨🍂✨🍂
ዳግመኛም ስማኝ ልንገርህ! ለዘለዓለም ላንተ ይብስብሃልና ባደርክበት ኹሉ ቃልህን አትለውጥ። በሰዎች መካከል ጥልን አትዝራ፤ አነዋወርህ ኹሉ በሰላም ይኹን፤ ወደ ልቡናህም ቍጣን አታስገባ፤ ወንድምህ የበደለህን ከቶ አታስብ። የቍጡ ሰው ድካሙ ኹሉ በዐይን ጥቅሻ በከንፈር ንክሻ ፈጥኖ ያልፋልና፡፡ ቂምን በልቡናው የሚያኖር ሰው የሰይጣን ደቀ መዝሙሩ ነው፤ የዘለዓለም ሕይወትንም አያያትም። ማንንም ማንን አትማ፤ ከማንም ጋር አትከራከር፤ የባልጀራህን ንብረት አትመኝ የሌላውንም አትቀማ።
✨✨🍂
ሐሜተኛ ሰው የእግዚአብሔር ጠላቱ ነው፡፡ በጠላትህ ውድቀትና ሞት ደስ አይበልህ፤ ባዘኑት ላይ አትሣለቅ፤ ለዕውሩ መሰናክል አታኑርበት። ስትጸልይ ለመቀመጥ አትቸኩል፤ ለጸሎት ጽሙድ ኾነህ በቆምክበት ቦታ ኹሉ አትነቃነቅ፤ በመካነ ጸሎትህ ላይ አዘውትረህ ቆመህ ተገኝ። ለለመነህ ኹሉ ስጥ፤ ከሌለህ ደግሞ እግዚአብሔርይስጥህ ካለው ያድርስህ ብለህ በለዘበ ቃል ተናገር፡፡ የምትሠራውን ሥራ ኹሉ ፊት አይተህ አድልተህ አትሥራ። የደረሰብህን ኹሉ እግዚአብሔርን አመስግነህ ተቀበል።
✨✨🍂
ይህንን ያደረግህ እንደ ኾነ በእግዚአብሔር ትእዛዛትና ሕግጋት አንተ በእውነት ፍጹም ነህ። እኔስ በእውነት የእግዚአብሔርን ጥበብ አደንቃለሁ። የፈጠረው ፍጥረት ሁሉ መልኩ በአርአያው እንደማይመሳሰል ልቡም እንዲሁ አንድ አይደለምና፡፡ ሁሉም አንዱም አንዱ የወደደውን ያስባል፡፡ ምክሩም ልዩ ልዩ ነው፡፡ እግዚአብሔር ግን ፍጥረት በየራሱ ያሰበውን የሁሉንም ልብ ያውቃል፡፡ ከሥራው ሁሉ ምንም ምን የሚሳነው የለም፡፡ ከሰው እስከ እንስሳት የፍጥረትን ልብ ሁሉ ያውቃል፡፡
📚መጽሐፈ ወግሪስ
📝በአባ ገብረ ኪዳን ግርማ
ገጽ 51-52
✨✨✨🍂✨🍂
"ገብርኤል አንተ ሐዋርያ ክርስቶስ ወለወላዲቱ፤አዕርገኒ እምግበ ደይን ዘኢይጠፍእ እሳቱ፤ወዕፄሁ ትጉህ ዘንዋም አልቦቱ።"
"ገብርኤል ሆይ የክርስቶስና የወላጅ እናቱ ሐዋርያ አንተ ነህና፤እሳቱ ከማይጠፋ ትሉ ከማያንቀላፋ የኲነኔ ጉድጓድ መንጭቀህ አውጣኝ።"
🌹አባ ገሪማ (ይስሐቅ )ማለት⁉🌹
«#ወር በገባ በ17 የአባ ገሪማ ዘመደራ ወርኀዊ መታሰቢያ በዓላቸው ነው አባ ገሪማ (ይስሐቅ) ዘመደራ🌹
📌•••አቡነ ገሪማ የተወለዱት በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን ሮም ውስጥ ነው:: ወላጆቻቸው መስፍንያኖስና ሰፍንግያ እግዚአብሔርን የሚወዱ የሮም ከተማ ንጉሥና ንግሥት ነበሩ:: ልጅ በማጣታቸው እመቤታችንን ለመኑ::
+እመ ብርሃንም ደግ ፍሬ ሰጠቻቸው:: ስሙን #ይስሐቅ ብለው አሳደጉት:: ገና በልጅነቱ አባቱ ድንገት በመሞቱ ይስሐቅ በዙፋኑ ተተክቶ ነገሠ:: ለ7 ዓመታት ሕዝቡን በፍትሕ እያስተዳደረ : መጻሕፍትንም እያጠና ኑሯል::
+አንድ ቀን ግን ከግብፅ በርሃ የተላከ ደብዳቤ ደረሰው:: ላኪው #አባ_ዸንጠሌዎን ሲሆኑ መልዕክቱ "ምድራዊ ንግሥና ምን ያደርግልሃል? ይልቁኑስ በሰማይ ለዘለዓለም እንድትነግሥ ወደ በርሃ ና" የሚል ነበር::
+ንጉሥ ይስሐቅ አላመነታም ሌሊት ተነስቶ ወደ ፈጣሪው ጸልዮ በለበሳት ልብስ ብቻ ዙፋኑን ጥሎ መነነ:: ድንገት ግን #ቅዱስ_ገብርኤል ደርሶ በቀኝ ክንፉ ነጥቆ ግብፅ አባ ዸንጠሌዎን በዓት ላይ አኖረው::
+እርሳቸውም ተቀብለው ፍኖተ አበውን አስተምረው አመነኮሱትና ዘጠኝ ሁነው ወደ #ኢትዮዽያ መጡ:: ተስዓቱ ቅዱሳን በሃገራችን ብዙ ሲሰሩ አንዱና ታላቁ አባ ይስሐቅ (ገሪማ) ናቸው:: ሰውነታቸውን በገድል ቀጥቅጠውት ቆዳና አጥንታቸው ተጣብቆ ነበር::
+አንድ ቀን አባ ይስሐቅ በልቶ ቀደሰ ብለው ነግረዋቸው አባ ዸንጠሌዎን አዘኑ:: ልምከር ብለው "ልጄ ይስሐቅ የሰማውብህ ነገር አለና ሰዎችን አርቅልኝ" አሉ:: አባ ይስሐቅ ግን "ሰዎች ብቻ አይደሉም:: ዛፉም እንጨቱም ገለል ይበል" ቢሉ የቤተ ክርስቲያኑ አጸድ አንድ ምዕራፍ ተጠራርጎ ሸሸ::
+ይሕንን የተመለከቱት አባ ዸንጠሌዎን "ወልድየ ይስሐቅ ገረምከኒ" (ልጄ ይስሐቅ ገረምከኝ) አሏቸው:: ከዚያ ጊዜ ጀምሮም "#አቡነ_ገሪማ" ተብለው ቀሩ::
+አቡነ ገሪማ ወደ #መደራ ሲሔዱ እነዚያ የሸሹ ዛፍና ድንጋዮች "ገሪማ ለእኛም ግሩም ነህ" እያሉ በዝማሬ ተከትለዋቸዋል:: ይህም የተደረገው በዚህች ቀን (መስከረም 30) ነው::
+ጻድቁ ወንጌልን : ገዳማትን ከማስፋፋት ባለፈ ብዙ ተአምራትን ሰርተዋል:-
1.ስንዴ ጠዋት ዘርተውት በ9 ሰዓት ያፈራ ነበር::
"ነግሃ ይዘርዕ ኪነቶ:: ወሠርከ የዓርር ገራኅቶ::" እንዲል::
2.ጧት የተከሉት ወይን በ9 ሰዓት ያፈራ ነበር::
3.አንድ ቀን ምራቃቸው ቢወድቅ ጸበል ሆኖ ዛሬም አለ::
4.ብዕራቸው ወድቃ አብባ አፍርታለች::
5.አንድ ቀን ድርሳን እየደረሱ (ወንጌለ ዮሐንስን ሲጽፉ) ሊመሽ በመሆኑ ፀሐይን አቁመዋታል::
+ከእነዚህ ሁሉ ዘመናት በሁዋላ #ጌታችን ተገልጦ በማይዋሽ ንጹሕ አንደበቱ ቃል ኪዳን ሰጣቸው:: "ስምሕን የጠራ : መታሰቢያህን ያደረገ : እስከ 12 ትውልድ እምርልሃለሁ:: አንተ ግን ሞትን አትቀምስም" ብሏቸው ተሰወረ:: ያን ጊዜ መላእክቱ በሠረገላ ጭነው እየዘመሩ #ብሔረ_ሕያዋን አድርሰዋቸዋል::
=>ቸሩ አምላካችን ከታላቁ ቅዱስ ጸጋ በረከት ይክፈለን:: በምልጃቸውም ይቅር ይበለን::
=>+"+ ለእግዚአብሔር ክብርን ስጡ::
ግርማው በእሥራኤል ላይ : ኃይሉም በደመናት ላይ ነው::
እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ነው::
የእሥራኤል አምላክ እርሱ ኃይልን : ብርታትንም ለሕዝቡ ይሰጣል::
እግዚአብሔርም ይመስገን:: +"+ (መዝ. 67:34)
+3
" እግዚአብሔር፥ ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ እስከ አሁንም ስለምታገለግሉአቸው፥ ያደረጋችሁትን ሥራ ለስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ ዓመፀኛ አይደለምና።"
ዕብራውያን 6:10
🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓
🎓🎓🎓 እንኳን ደስ አላችሁ🎓🎓🎓
🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓
በዛሬው ዕለት የሰንበት ት/ት ቤታችን እንቁ አገልጋዮች የሆኑ ወንድም እና እህቶቻችን ከተለያዩ የሀገራችን ዩኒቨርስቲዎች ተመርቀዋል። ውድ አባላቶቻችን እንኳን ደስ አላችሁ መልካም የስራና የአገልግሎት ዘመን እንዲሆንላቹ ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ትምህርት ቤት ትመኝላቹሀለች።
ዜና እረፍት
“የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።” — መዝሙር 116፥15በአርሲ ዞን በርካታ የገጠር አብያተ ክርስቲያናትን ቅዳሴ ቤት ባርኮ ለአገልግሎት በማብቃት ታላቅ ሥራ የሠሩት የእድሜ ባለፀጋ የሆኑት ታላቁ አባታችን ቆሞስ አባ ብርሃኑ በዛሬው እለት ከጠዋቱ 3 ሰዓት አርፈዋል ስርዓተ ቀብራቸውም ነገ ቅዳሜ 4:30 ላይ በአሰላ መንበረ ጵጵስና ርዕሰ ገዳማት ወአድባራት ደብረ ምፅላል ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ይፈፀማል በረከታቸው ይደርብን #የአርሲ_ሀገረ_ስብከት_የሰንበት_ትምህርት_ቤቶች_አንድነት
ከእድር ወደሠርግ ድንኳን
እግዚአብሔር ልጆቹን ሊታደግ ሲፈልግ መልአኩን ልኮ ሞትን ገድሎ ከእድር ድንኳን ወደ ሠርግ ድንኳን ያሸጋግራል።
✅ የተቆፈረውን ጥልቅ መቃብር የዝማሬ ዐውደ ምሕረት ያደርገዋል።
መሻገር የሌለበትን ፈርዖንን እስከ ሠራዊቱ በመንገድ ላይ በባሕር ውስጥ ይቀብራል።
መሻገር ያለበትን ሙሴን እስከ ሠራዊቱ በመንገድ ላይ ከባሕር አሻግሮ ከበሮ አሸክሞ በድል ያዘምራል።
ከእናቱ ማህፀን ጀምሮ ሞት የተደገሠለት ባሕራንንም መንገድ ላይ መልአኩን ልኮ ጠላት በእጁ ያስጨበጠውን ደብዳቤ የሠርግ መጥሪያ ካርድ አደረገለት።
ቢሞት እንኳን መቃብር የሚቆፍርለት፣ የእድር ድንኳን የሚተክልለት፣ ዝክረ ስሙን የሚያስታውስለት፦ የማያገኘውን ምስኪን የሠርግ ድንኳን አዘጋጅቶ ደግሶ ዳረው።
እኛንም ከሞት ወደሕይወት፣ ከበደል ወደ ወንጌል።፣ ከኀሣር ወደ ክብር ይለውጠን።
እንኳን አደረሳችሁ ለቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ በዓል?
#የአገልግሎት_ትርፌ_ምንድነው?🤔
የልብ ወዳጅ ሲራክ የዕለት ጉርሴ የሆነውን ምክር ይሰጠኛል። ማኅበረሰባዊ ፍልስፍናው መንፈሳዊ ከፍታን የሚያመጡ ምክሮቹ ይማርኩኛል መጸሐፍ ቅዱስ ስገለጥ የእርሱን ንባብ ሳልጎበኝ አልወጣም። ለዛሬ በአንድ ክፍሉ ያለውን ከልቤ የወደቀውን ቃል ወደ እኛ ሕይወት ልቀይረው ወድጅያለው።
ጠቢቡ እንዲህ ይላል "የአገልግሎት ትርፌ ምንድነው ከእንግዲህስ ወዲያ የማገኝው መልካም ነገር ምንድ ነው አትበል" ሲራክ 11:23
➤ከሞላ ጎደል ይነስም ይብዛም በቤተክርስቲያን አገልግሎት ላይ ያሉ ሰዎች ጥያቄ ይመስለኛል። ነገሮች ሲከፉብን የወጠነው ከመሐል ሲቀር፤ ቀድመን ያሰብነው ሁሉ ሲመክንብን፤የያዘነው ሁሉ ሲበትንብን ኑሮ አልገፋ ሲለን የአገልግሎት ትርፋችን ምንድነው? የሚል ከሰጋ ደካም የሚመጣ ጥያቄ እናነሳለን። ህመም ሲጸና፤ ጠላት ሲበዛ፤አገለገልን ባልን ጊዜ የደቦ ፍርድ ስድብና ሽሙጥ ሲበዛብን የአገልግሎት ተርፌ ምንድ ነው? የሚል ውስጣዊ ሙግት እንጀምራለን። አገልግሎታችንን ከማጣትና ከማግኝት ጋር ከመመስገንን ከመስደብ ጋር እናያይዘዋለን። አገልግሎቱን ሳይስታጉል የደከመ ቤተሰቡን ሥራውን ኑሮውን እየጎዳ የወጣ የወረድ እንደሆነ ደግሞ አንድ ፈተና ሲያናውጸው ይህን ሙግት እንዲያነሳ ያስገድደዋል።
➤ነገሩ የሚጸነው ኃጢአተኛ ያልናቸው ዓልያም ደግሞ አለማውያን የተባሉ ሰዎች አኗኗር የተሻለና የሰመረ መሆኑን በተመለከትን ጊዜ የሚፈጠርብን ጥያቄ ነው። ክብረ እግዚአብሔርን የማያቁ፤ በመንፈሳዊ ትሩፋት ያላለፉ ፤በቤቱ ያልደከሙ፤ ከበዓል ያልዘዘል ክርስትና የሌላቸው ሰዎች ያያላቸው የኑሮ ስኬት አንድ አንዴ መረር ያለ ጥያቄ እንድናነሳ ያስገድደናል። የእኛን መንፈሳዊ አገልግሎት ከእነርሱ ኃጢአት ጋር ማነጻጸር እንጀምራለን። ጠቢብ ሲራክ እዚው ክፍሉ ላይ እንዲህ ይህን ጉዳይ በተመለከተ ይመክረናል። "የኃጢአተኞች ሥራቸው አያስጎምጅህ በእግዚአብሔር እመን ድካምህንም ተስፋ አድርግ ሁሉ በአንድ ጊዜ ለእግዚአብሔር ቀላል ነው ድሃውንም ድንገት ይባርከዋልና"
➤ ሲራክ በዓለማውያን የተሳካ ኑሮ ባላቸው በተረፋቸው ነገሮች ሁሉ እንዳንጎመጅ ነገረን። ድካማችን ከንቱ እንደማይቀር ነገር ግን በመጽናትና በእግዚአብሔር በማመን ድንገት ወደ ህይወታችን የሚመጣ ነገር እንዳለም አስከተለልን። አንድ አንድ ተስፋ አስቆራጭ ንግግሮችም ይገጥሙሀል። በአገልግሎት መድከምህን ካጣሃቸውና ካለህበት የኖሮ ደረጃ ጋር እያነጻጸሩ ምን አገኝህ? በሚል ሥጋዊ ሐሳብ ሐሳብ ውስጥ ይከቱሃል።
➤ ብርቱ አገልጋዮች በዓለማዊ ህይወታቸው መድከም ተደብቀዋል። ብርቱ ብዕሮች በሥጋ ድካም ከስመዋል። ብርቱ ዕውቀቶች ተስፋ በመቁረጥ ተቀብረዋል። እነዚህ የኑሮ ድካሞች የሚያደበዝዟቸው ጸጋዎች አሉ። ነገር ግን መንፈሳዊነት ማለት ቁሳዊ በሆነ ዓለም ተደላድሎ መኖር ሳይሆን የመንፈሳዊ ልዕልና የሚያመጡ ትግሎችን አልፎ ለክብር መብቃት ነው።
➤እግዚአብሔርን ደፍሮ የሚከራከረው ማነው? አጥፍተሀል ብሎ የሚሞግተው አዋቂስ ከየት ይገኛል? እርሱ አድርጎ ትክክል ያልሆነ ነገር ምንድነው? በቃሉ ተናግሮ የተሳሳተውስ መቼ ነው? አይሆንም ብሎ የሆነ ነገር ምን አለ? ይሆናል ብሎ ያለሆነስ ምን አለ? ሰማይና ምድር የማይችሉት እርሱን ትክክል አይደለህም የሚለው ከእኛ ወገን ማን ነው? ዝምታውን ሞኝነት መዓቱን ጨካኝነት አድርጎ የሚወቅሰውስ ማነው? እርሱ ሠርቶ የተሳሳተው ምን አለ? እርሱ ቃል ገብቶ የሻረበት ጊዜ መቼ ነው? ልብ በሉ በህይወታችን ውስጥ አንድ ትክክል አለ ሲሰጥም ሲነሳም ሐዘንንም ደስታንም ሲያፈራርቅ ትክክል የሆነ እርሱ እግዚአብሔር ብቻ ነው። ትክክል አይደለህም የሚለው የሚለው አላዋቂ ማን ነው?በሕይወቴ ያደረከው ሁሉ ትክክል ያልሆነበት ጊዜ የለም።እንበለው እንጂ ጠቢቡ ሲራክ እንዳለው
"የአገልግሎት ትርፌ ምንድነው ከእንግዲህስ ወዲያ የማገኝው መልካም ነገር ምንድ ነው አትበል"
እግዚአብሔርን ጠብቀው ሥራህ ሩጫህ ትግልህ ድንገት ሲያብብ ታየዋለህ።
✍️ዲ/ን ሞገስ አብርሃም
በየዓመቱ ነዳያንንና ካህናትን የሚመግበው ሰንበት ትምህርት ቤት በደብሩ ሰበካ ጉባኤ መታሸጉ ተገለጸ !
ሰኔ 7 ቀን 2017 ዓ.ም [ተሚማ/ አዲስ አበባ]
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በአርሲ ሀገረ ስብከት ካሉት ቀደምት እና አንጋፋ ሰንበት ትምህርት ቤቶች መካከል አንዱ የሆነው የአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ትምህርት ቤት መታሸጉን የሚዲያ ክፍላችን ከምንጮቻችን መረጃ አግኝቷል ።
ሰንበት ትምህርት ቤቱን ያሸገው የካቴድራሉ ሰበካ ጉባኤ እንደሆነ የገለጹልን ምንጮቻችን ለመታሸጉ መንስኤ የሆነው በሚያዝያ 08/2017 ዓ.ም በሰበካ ጉባኤ በቁጥር አካ/ደመ/መዓ/ቤክ/ሰጉ/0320/17 በተጻፈ ደብዳቤ የሰ/ት/ቤቱን ሊቀመንበርና የሕጻናት ክፍል መምህር ዲ/ን አበበ ይልማን ከሥራና ከሰ/ት/ቤቱ ሰብሳቢነት ማገዳቸውን በመግለጹ ሰንበት ት/ቤቱ በቀን 15/08/2017 ዓ.ም ምልዓተ ጉባኤ አድርጎ የዲ/ን አበበ ይልማ አለአግባብ እና አለጥፋቱ መነሳቱ ሰንበት ት/ቤቱ ውሳኔውን እንደማይቀበልና የመሻርና የመሾም ሥልጣን ያለውን የሰንበት ት/ት ቤቱን ሥልጣን የሚጥስ መሆኑን እና የሰ/ት/ቤቱን ኅልውና መንካት መሆኑን ፤ መምህሩን ከሚሠራበት ማንሳትና ማገድ የቤተክርስቲያኒቱ የሠራተኞች መተዳደሪያ ደንብ አካሄዱን ያልጠበቀ መሆኑን ጠቅሶ ለሰበካ ጉባኤው በደብዳቤ ለወረዳው ቤተክህነት እና ለወረዳው ሰ/ት/ቤት አንድነት ቢያስገባም ተገቢው ምላሽ ሳይሰጠው ቀርቷል።
ጉዳዩን በቀን 16/08/2017 ዓ.ም ለወረዳው ቤተክህነት በደብዳቤ ሰ/ት/ቤቱ በግልባጭ ለሀገረ ስብከቱ አስገብቶ የነበረ ሲሆንና የወረዳው ቤተክህነት ጉዳዩን ተመልክቶ መምህር ዲ/ን አበበ ይልማ አለአግባብ መታገዱንና የሰ/ት/ቤቱን መብት የነካ ተግባር መሆኑን አምኖ ለሰበካ ጉባኤው በቁጥር 97/2017 በቀን 17/08/2017 ዓ.ም እገዳው እንዲነሳ ቢጽፍም ሰበካ ጉባኤው ተፈጻሚ አለማድረጉን በማወቁ በ25/09/2017 ለብፁዕ አቡነ ያሬድ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ቤተክህነት የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ኃላፊና የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ ቋሚ አባል ጠቅሰው ያስገቡት ደብዳቤ ምላሽ ሳይሰጣቸው ሰንበት ትምህርት ቤቱ በግንቦት 24 ቀን 2017 ዓ.ም ታሽጎ አገልግሎት መስጠት ማቆሙን ሚዲያችን ለማወቅ ችላለች።
የዲ/ን አበበ ይልማ መታገድ መንስኤ ቢሆንም ሰበካ ጉባኤው ለሰ/ት/ቤቱ በጻፈው ደብዳቤ ላይ ሰንበት ት/ቤቱ በዓለ ትንሣኤን አስመልክቶ ለነዳያን መግቦት እያደረገ ያለውን ቅድመ ዝግጅት ከሰበካ ጉባኤው ጋራ ስለሚኖረው የአሠራር ኅብረትና አንድነት በሚገመግምበት ወቅት የሰንበት ት/ቤቱ ሊቀ መንበር ከሰንበት ት/ቤቱ እና ከአሰላ ከተማ የሰ/ት/ቤት ኅብረት መሪነቱ በገዛ ፈቃዱ መልቀቁን በፌስቡክ ገጽ አይቶ ማዘኑን እና እስኪጣራ ከሰ/ት/ቤት ሊቀመንበርነት እና መምህርነቱ ታግዶ እንዲቆይ እና ጉዳዩ እልባት እስኪያገኝ ሰ/ት/ቤቱ በምክትል ሊቀመንበር እንዲመራ መወሰኑን መጥቀሱን ለማወቅ ከደብዳቤ ለማየት የቻልን ቢሆንም፤ ስለተፈጠረው ጉዳይ ምንጮቻችንን በመጠየቅ ያገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ሰንበት ትምህርት ቤቱ ለዘመናት በሚያደርገው የነዳያን ምገባ በቀድሞው ሊቀጳጳስ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል መመሪያ ሰጪነት መሠረት <<ስትመግቡ መንፈሳውያን ነዳያን የሆኑት ካህናትን መመገብ እንዳትረሱ>> መባላቸውን በማስታወስ እና የብፁዕነታቸውን አባታዊ አደራ በመጠበቅ ለዘመናት እያከናወኑ እንደሚገኙና ሰ/ት/ቤቱንና ማኅበረ ካህናቱን ለማለያየትና በቅጽረ ቤተክርስቲያን ውስጥ አንድነት ፣ ኅብረትና ሰላም እንዳይሰፍን በሚፈልጉ ጥቂት የሰበካ ጉባኤ አካላት የተጠነሰሰ መሆኑን የመረጃ ምንጮቻችን ገልጸውልናል።
ከዚህም በዘለለ በሰንበት ት/ቤቱ ላይ የሂሳብ ክፍተት አለ የሚለው ሰበካ ጉባኤ ፤ የሚገኙ ገንዘቦችን በሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ 49 “የቤተ ክርስቲያን የገቢ ክፍያ ሥርዓት” በቃለ ዐዋዲ አንቀጽ 56/4 ላይ “ስለ ሰበካው ቤተክርስቲያን ልዩ ልዩ ገቢ” ላይ በተጠቀሰው መሠረት “ማናቸውም ዓይነት የሰበካው ገንዘብና ንብረት ገቢ ለቁጥጥር እንዲያመች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የበላይ ተቈጣጣሪነትና በመንበረ ጵጵስና ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ኃላፊነት ታትሞ በሚወጣው በአንድ ዓይነት ሕጋዊ ደረሰኝ /ካርኒ/ ብቻ ይሰበሰባል፡፡” ያለውን በመተው ሰንበት ት/ቤቱ ያለ ደረሰኝ በእጁ ያለውን ገንዝብ እንዲያስረክብ በመጠየቁ ሰንበት ት/ቤቱ አላስረክብም ማለቱን ምንጮቻችን የገለጹልን ሲሆን፤
ይህንን አስመልክቶ የሚዲያ ተቋማችን የካቴድራሉን አስተዳዳሪ አባ ፍቅረ ሥላሴን በተደጋጋሚ ደውለን ለማነጋገር ብንሞክርም ስልክ ያላነሱ ሲሆንና ባነሱበት ወቅትም ስለጉዳዩ ስንጠይቃቸው በአካል ካልሆነ በስልክ ሃሳብ አልሰጥም ያሉ ሲሆን፤ የወረዳው ሊቀ ካህን እና የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ኅሩያን ታምራት ወልዴ ጋራ በተደጋጋሚ ብንደውልም ስልካችንን ሊያነሱ አለመቻላቸውን ጣቢያችን ማሳወቅ ይወድዳል።
በተጨማሪም ጣቢያችን ባደረገው ክትትል ዛሬ ሰኔ 6 ቀን 2017 ዓ.ም ከሀገረ ስብከቱ የተላኩ ልዑካን በተገኙበት የታሸገው የሰንበት ት/ቤት ሂሳብ ነክ እና አባላት ቁጥርን ከያዘው ሳጥን ባሻገር ሌላው የታሸጉት ተከፍተው ሰ/ት/ቤቱ ወደ አገልግሎት እንዲመለስ የሀገረ ስብከቱ አስተዳደር ደብዳቤ ጽፎ ቢልክም ሰበካ ጉባኤው የታሸገውን ለመክፈት ፈቃደኛ ሳይሆን በመቅረቱ ጉዳዩ ወደ ሕግ አካላት ማምራቱን ለማወቅ ችለናል።
ሚዲያችን በዚህ ሐሳብ ላይ ተጨማሪ ማብራሪያም ሆነ የተጠቀሰው ነገር ላይ ቅሬታ ያለው አካል ቢመጣ ለማስተናገድ ክፍት መሆኑን ጨምረን መግለጥ እንወድዳለን።
