ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Ir al canal en Telegram
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Mostrar más669
Suscriptores
-224 horas
+57 días
+130 días
Archivo de publicaciones
+3
ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አግናጢዮስ ኤፍሬም በተገኙበት በሶርያ ደማስቆ በሚገኘው በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል ተከበረ !
ታኅሣሥ 16 ቀን 2017 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
"እመቤቴ ኪዳነ ምሕረት ኾይ 🙏
በአካል ሦስት ሲኾን በመለኮታዊ ባሕርዩ በአንድነቱ ጸንቶ የሚኖር የብርሃን መገኛ እርሱ እግዚአብሔር አብ ለቃል ኪዳንሽ የተሰጠውን ልዩ ክብር ብሩህ አድርጎ ያሳየኝ ዘንድ የቸርነቱ ጸዳለ ብርሃን ዓይነ ልቡናዬን ያብራልኝ። 🤲🤲🤲
የቃል ኪዳኗ እመቤቴ ኾይ 🙏 ከእግዚአብሔር በታች በሰማይም በምድርም አንቺ የኹሉ እመቤት ነሽ "
✥መልክአ ኪዳነ ምሕረት✥
መዝሙር ጥናቱ ሊጀመር ነው ሁላችሁም እየገባቹ
የአንድነት ዝማሬ በአሰላ
ታህሳስ 28 ከቀኑ 9:00 ጀምሮ
በአሰላ መስቀል አደባባይ
አዘጋጅ የአርሲ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት
የአርሲ ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አድነት የቴሌግራም ቻናልን ይቀላቀሉ ለሌሎችም ያጋሩ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት
ለመቀላቀል
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
👉 https://t.me/ardssu👈
👉https://t.me/ardssu 👈
👉 https://t.me/ardssu👈
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊
" የቤተክርስቲያን ሕይወት በመስቀል ላይ ስለሆነ ፈተና ይበዛበታል። ስለዚህ ከግል ሕይወታችሁ በላይ የቤተክርስቲያንን አቋም አጠናክሩ።
ቤተ ክርስቲያን ሰው የላትም ሰው ሁኑላት የብረት አጥር ሁኗት ቅዱስ ጊዮርጊስን ሁኑላት።"
የብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ ሊቀ ጳጳስ ዘሸዋ /1932 1982/
የብፁዕነታቸው ቃለ በረከት
ቤተ መቅደስህ ቅዱስ ነው በጽድቅም ድንቅ ነው። በምድር ዳርቻ ሁሉና በሩቅ ባሕር ውስጥ ላሉ ተስፋቸው የሆንህ፥ አምላካችንና መድኃኒታችን ሆይ፥ ስማን።
❤መዝሙር 65፥5❤️
(የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 3)
----------
19፤ ብርሃንም ወደ ዓለም ስለ መጣ ሰዎችም ሥራቸው ክፉ ነበርና ከብርሃን ይልቅ ጨለማን ስለ ወደዱ ፍርዱ ይህ ነው።
20፤ ክፉ የሚያደርግ ሁሉ ብርሃንን ይጠላልና፥ ሥራውም እንዳይገለጥ ወደ ብርሃን አይመጣም፤
21፤ እውነትን የሚያደርግ ግን ሥራው በእግዚአብሔር ተደርጎ እንደ ሆነ ይገለጥ ዘንድ ወደ ብርሃን ይመጣል።
ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ በሰላም ዘርፍ እጩ በመሆን ተመረጡ !
ታኅሣሥ 12 ቀን 2017 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ አዲስ አበባ)
አንቴክስ የተሰኘ የቻይና ልብስ አምራች ድርጅት ባዘጋጀው BIWs prize ብፁዕ አቡነ ኤርምያስን በሰላም ዘርፍ እጩ አድርጓቸዋል።
ብፁዕነታቸው በጦርነት ውስጥ ሆነው ሁሌም ስለ ሰላም የሚሰብኩና ለተገፉ ሁሉ የሃይማኖትና የዘር ልዩነት ሳያደርጉ ከልብ በመነጨ ሰብአዊነት ከወደቁበት ለማንሳት ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ለዓለም ኹሉ የሚያስተጋቡ መሆናቸው ተገልጿል።
የብፁዕነታቸው የመወዳደሪያ ኮድ 08 ሲሆን BIW በማስቀደም ማለትም BIW08 በማስገባት 9355 ላይ በSMS ድምፅ መስጠት የሚቻል ሲሆን ድምጽ መስጠቱ እስከ ሐሙስ ታኅሣሥ 17 ቀን 6፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ የሚቆይ ሲሆን የዘርፉ አሸናፊ የ 10 ሚሊዮን ብር ተሸላሚ እንደሚሆንም ተገልጿል።
የክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን አለች፤ በዚያ ደግሞ ሰዎች አሉ!
.
ቤተ ክርስቲያን የክርስቶስ ናት! ክርስቶስ ደግሞ ቤተ ክርስቲያንን ያፀናት በመከራው ነው፤ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያንን ለዘለዓለም ወዷታልና ፈጽሞ አይተዋትም፡፡
.
ቤተ ክርስቲያንን የምንወዳት ስለ ክርስቶስ ነው፤ ክርስቶስን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ስለምናገኘው፤ ስለምናየውና ስለምንሰማው ቤተ ክርስቲያን መሔድን እናዘወትራለን!
.
ቤተ ክርስቲያን ከክርስቶስ የተነሳ የዕረፍትና የሐሴት ስፍራ ናት! ወደ ክርስቶስ የምንጠጋባትና የምንደርስባት ስለሆነች ከቤተ ክርስቲያን ልንወጣና ልንርቅ አንችልም!!!
.
ቤተ ክርስቲያን የእግዚአብሔር የጸጋው ግምጃ ቤት ናት! ሥርየተ ኀጢአትን እንቀበልባታለን፤ ሀብተ እግዚአብሔርን እንታደልባታለን፤ የክርስቶስን ሥጋና ደም እንቀበልባታለን! ከክርስቶስ ዘንድ እንደርስባታለን፤ ክርስቶስንም እናገኝባታለን!!
.
በክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ወስጥ ደግሞ ሰዎች አሉ . . . ግዴለሾች፤ ለሰው ስሜት የማይገዳቸው፤ የሌሎች መዳን ጉዳያቸው ያልሆነ፤ የእግዚአብሔርን ደጅ በሰዎች ፊት የሚዘጉና የሚከፍቱ፤ ለደካሞች የማይራሩ፤ ገንዘብ ካገኙ ጸጋ እግዚአብሔርን ከመሸጥ ወደ ኋላ የማይሉ፤ የወንጌል ሰባኪነት ሥራ ግዴታቸው እንደሆነ የማያውቁ፤ ፍቅር የሌላቸው፤ ምእመናን ሊያገኙት ስለሚገባቸው ተገቢ የሆነ አገልግሎት ደንታ ቢስ የሆኑ፤ አገልግሎት ደሞዝ የሚቀበሉበት ሥጋዊ ሥራ የሚመስላቸው . . .
.
ለመተባበርና አብሮ ለመሥራት የማይፈቅዱ፤ የሚቀኑ፤ የትጉኀንን ክንድ የሚያዝሉ፤ ማሩን የሚያመሩ፤ ወተቱን የሚያጠቁሩ፤ በጎ የማይታያቸው፤ ከመራገምና ከመንቀፍ በቀር ምርቃት የሌላቸው፤ ምስጋናና በጎ ቃላት ብርቃቸው የሆነ፤ ከጠማማው በቀር በጎው የማይታያቸው፤ ለቤተ ክርስቲያን በመቅናት ስም ሌሎችን የሚያሳድዱና ሥፍራ የሚያሳጡ፤ ይቅርታ መጠየቅ ዳገት የሚሆንባቸው፤ ተሳስተው ለመታረም የማይፈቅዱ፤ ከሌሎች በቀር አንድም ቀን ራሳቸውን ለመመልከት የማይወዱ፤ ለወንድሞቻቸው የገሃነምን ያህል ታላቅ ቁጣ ያላቸው፤ በሌሎች ዕንባ የሚስቁ፤ በወንድማቸው ውድቀት አታሞ የሚደልቁ . . . በክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ወስጥ አሉ!!!
.
እነዚህ ሰዎች በክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ምሕረት ተደርጎላቸውና የእግዚአብሔር ትእግስት በዝቶላቸው የሚኖሩ ናቸው እንጂ የክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን እንደራሴዎች ወይም ወኪሎች አይደሉም!!! ልክ እንደ እኛ ተጨማሪ ዕድልና በጎነት የተጨመረላቸው ናቸው እንጂ የክርስቶስ መልኮች ወይም በክርስቶስ ፈንታ አይደሉም!!!
.
ቤተ ክርስቲያን የክርስቶስ ናት፤ ክርስቶስን ብለን የምንሔድባት፤ ክርስቶስን አግኝተን የምናርፍባትና ደስ የምንሰኝባት፤ ለክርስቶስ ብለን የምንሠራላትና የምንደክምላት፤ ከክርስቶስ ጋር የምንተባበርባት፤ ዋጋችንን ከክርስቶስ የምንጠብቅባት፤ ለክርስቶስ ብለን የምንተጋባትና ጾር የምንታገሥላት . . . ብቻ እንጂ ሰዎችን ተመልክተን፤ በሰዎች ተከፍተንና ተበሳጭተን የምንተዋትና ጥለናት የምንወጣ ምድራዊ ጥቅምና በጎነት አይደለችም!!!
.
የክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን አለች፤ በዚያ ደግሞ ሰዎች አሉ!
በመንግሥትና በጠቅላይ ቤተ ክህነት ትኩረት የተነፈገው የሽርካ ኦርቶዶክሳውያን ግድያ እንደቀጠለ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ገለጹ !
ታኅሣሥ 10 ቀን 2017 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ሽርካ ወረዳ ታኅሣሥ 5 እና 6 ቀን 2017 ዓ.ም የወረዳ ቤተ ክህነቱን ሥራ አስኪያጅ ጨምሮ 20 ኦርቶዶክሳውያን በታጣቂዎች ግድያና እገታ እንደተፈጸመባቸው ነዋሪዎቹ ገልጸዋል፡፡
ከታገቱት ውስጥም የወረዳው ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅና ሌሎች 8 ኦርቶዶክሳውያን ገንዘብ ከፍለው የተለቀቁ ሲሆን ቁጥራቸው ያልታወቁ ሰዎች ግድያ እንደተፈጸመባቸው እንዲሁም ያሉበት እንደማይታወቅ አክለዋል፡፡ በዚህ ዕለት ብቻ ከ80 በላይ የኦርቶዶክሳውያን ከብቶች በታጣቂዎች ተወስደዋልም ተብሏል፡፡
ሀገረ ስብከቱ በየዓመቱ በሚካሄደው በ43ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በ2016 ዓ.ም 271 ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸውን መግለጹ የሚታወስ ነው፡፡
በተጨማሪም ከ10 ቀበሌ ገበሬ ማኅበር ውስጥ 91 ሰዎች ሕይወታቸው ሲያልፍ ቁጥራቸው ከፍተኛ የሆነ ምእመናን ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል ሲል በጠቅላላ መንፈሳዊ ጉባኤው ሪፖርቱ መጥቀሱ አይዘነጋም፡፡
በጀጁ ወረዳ ቡርቃ ጉራቻ ቅ/ማርያም ቤተ ክርስቲያን አካባቢ የሚኖሩ 150 ምእመናን በጉሬ ደቢኖ ቅ/እግዚአብሔር አብና አርጆ ቅ/ጊዮርጊስ ከ30 በላይ ምእመናን መገደላቸው የተገለጸ ሲሆን 499 አባወራና እማወራ ለስደት መዳረጋቸውም ተገልጿል፡፡
በጠቅላይ ቤተ ክህነትም ሆነ በመንግሥት ትኩረት የተነፈገው የኦርቶዶክሳውያን ግድያ ተባብሶ ኅዳር 19 እና 20 ቀን 2017 ዓ.ም የ13 ዓመት ታዳጊና የ80 ዓመት አዛውንትን ጨምሮ 11 ሰዎች በጥምቀተ ባሕር ማክበሪያው ላይ ተወስደው መገደላቸውንና 6 ምእመናን ደግሞ ያሉበት አለመታወቁን መዘገባችን የሚታወስ ነው፡፡
ኦርቶዶክሳውያን ያለማንም ከልካይ በተገኙበት ሁሉ በሚገደሉበት በዚያ ሀገረ ስብከት የ45 ቀን አራስ ሕጻንን ጨምሮ በርካታ ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸውና አብያተ ክርስቲያናት ላይም ጥቃት እየተፈጸመ መቆየቱ በተለያዩ ሚዲያዎች ሲዘገብ ቆይቷል፡፡
በመሆኑም የኦርቶዶክሳውያን ግድያና ስደት እንዲሁም የሀብት ዝርፊያ ሰሚ ያጣና በወረዳው ተጠናክሮ የቀጠለ በመሆኑ የአካባቢው ምእመናን በትልቅ ተስፋ መቁረጥ ውስጥ መሆናቸውን ለማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ገልጸዋል፡፡
“የማይጠቅሙና ፋይዳ የሌላቸው ጉዳዮችን ሲዘግቡ የሚስተዋሉ ሚዲያዎች የእኛ ሞት እንደምን ቀለላቸው?” ያሉት ኦርቶዶክሳውያን ነዋሪዎች ከሀገረ ስብከቱ ጀምሮ እስከ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በወረዳችን እየተፈጸመ ያለው ግፍ ትኩረት አለመሰጠቱ እጅጉን አሳዝኖናል ብለዋል፡፡
በመሆኑም ሰብዓዊነት የሚሰማችሁ ግለሰቦችና የግፍ ግድያውን የምትቃወሙ ሚዲያዎች ሀብት ንብረት ባፈራንበት ወልደን ከብደን በተቀመጥንበት ሀገራችን እንዳውሬ እየታደንን ስንገደል ድምጽ ትሆኑን ዘንድ እንማጸናችዋለን ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
አስተያየት ሰጭዎች አክለውም መንግሥት የዜጎቹን ደህንነት የመጠበቅ ግዴታ እንዳለበት በመገንዘብ ሞታችንን ሊያስቆምና መፍትሔ ሊያመጣ ይገባዋል ሲሉም አሳስበዋል፡፡
ምንጭ ፦ ማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት
Repost from የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት
New challenge
video ለtiktok, post, history, instagram, facebook reels, ለምትፈልጉ
Profile , History , post በማድረግ ለሁሉም እንዲደርስ እናድርግ።የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ከታች ያለው ነው ሊንኩ 👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/ardssu https://t.me/ardssu https://t.me/ardssu
ታህሳስ 13
ከታህሳስ 11-13 ድረስ የሚቆይ መንፈሳዊ ጉባኤ በአሰላ አንቀፀ ምህረት ቅዱስ ሩፋኤል ወዑራኤል ቤተ ክርስቲያን እዲሁም ታህሳስ 13 የሊቀ መላዕክ የቅዱስ ሩፋኤልን ክብረ በዓል ኑ በጋራ እናክብር ።
የአርሲ ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አድነት የቴሌግራም ቻናልን ይቀላቀሉ ለሌሎችም ያጋሩ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት
ለመቀላቀል
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
👉 https://t.me/ardssu👈
👉https://t.me/ardssu 👈
👉 https://t.me/ardssu👈
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊
Repost from የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት
New challenge
Profile , History , post በማድረግ ለሁሉም እንዲደርስ እናድርግ።የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ከታች ያለው ነው ሊንኩ 👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/ardssu1 https://t.me/ardssu1 https://t.me/ardssu1
Repost from የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት
New challenge
Profile , History , post በማድረግ ለሁሉም እንዲደርስ እናድርግ።የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ከታች ያለው ነው ሊንኩ 👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/ardssu1 https://t.me/ardssu1 https://t.me/ardssu1
Repost from የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት
New challenge
Profile , History , post በማድረግ ለሁሉም እንዲደርስ እናድርግ።የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ከታች ያለው ነው ሊንኩ 👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/ardssu1 https://t.me/ardssu1 https://t.me/ardssu1
Repost from የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት
New challenge
Profile , History , post በማድረግ ለሁሉም እንዲደርስ እናድርግ።የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ከታች ያለው ነው ሊንኩ 👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/ardssu1 https://t.me/ardssu1 https://t.me/ardssu1
Repost from የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት
New challenge
Profile , History , post በማድረግ ለሁሉም እንዲደርስ እናድርግ።የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ከታች ያለው ነው ሊንኩ 👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/ardssu1 https://t.me/ardssu1 https://t.me/ardssu1
Repost from የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት
New challenge
Profile , History , post በማድረግ ለሁሉም እንዲደርስ እናድርግ።የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ከታች ያለው ነው ሊንኩ 👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/ardssu1 https://t.me/ardssu1 https://t.me/ardssu1
Repost from የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት
New challenge
Profile , History , post በማድረግ ለሁሉም እንዲደርስ እናድርግ።የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ከታች ያለው ነው ሊንኩ 👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/ardssu1 https://t.me/ardssu1 https://t.me/ardssu1
