ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Ir al canal en Telegram
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Mostrar más670
Suscriptores
-224 horas
+57 días
+130 días
Archivo de publicaciones
ኑ! ለእግዚአብሔር እናበድር!
"ለድሀ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሔር ያበድራል በጎነቱም መልሶ ይከፍለዋል" ምሳ 19፥17የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
ኒቆዲሞስ፦
የዓቢይ ጾም የመጨረሻው ሳምንት ኒቆዲሞስ ነው።ከኒቆዲሞስ ፍጻሜ በኋላ ያለው ሳምንት የሕማማት ክፍለ ጾም ነው።
ይሄ ሳምንት ኒቆዲሞስ ተብሎ የተሰየመው ሌሊት ሌሊት ወደ መድኅን ክርስቶስ እየመጣ ይማር በነበረው እና ኋላም በዕለተ ዓርብ የመድኅን የክርስቶስን ሥጋ በገነዘው አረጋዊ አባት ነው።
ኒቆዲሞስ የአይሁድ መምህር የነበረ ቢሆንም ራሱን ዝቅ አድርጎ ቀን ሲያስተምር ሲያስታርቅ እየዋለ ማታ ማታ ከጌታችን ዘንድ ሂዶ ሲማር ያድር ነበር።
ይልቁንም ድንቅ ምሥጢር የሆነውን ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ከማሕፀነ ዮርዳኖስ የመወለድን ምሥጢር በቅድሚያ የተማረው ኒቆዲሞስ ነው።
መልካም ዕለተ ሰንበት🙏
🍂️️️️️️🍂️️️️️️🍂️️️️️️✨✨✨🍂️️️️️️🍂️️️️️️🍂️️️️️️✨✨✨
''ሰላም ለዝክረ ስምከ ዘኢረከቡ ተፍጻሚተ፤
መላእክተ ሰማይ ወምድር እለ ለመዱ ስብሐተ፤
መድኃኔዓለም ተወከፍ እንተ አቅረብኩ ንስቲተ።
ዘሰተይከ በእንቲአነ ከርቤ ወሐሞተ።
🍂️️️️️️✨✨
መድኃኔዓለም ሆይ ምሥጋና የሁል ጊዜ ተግባራቸው የሆነ ሰማያውያን መላእክት ምድራውያን ጻድቃን ሰማዕታት ተመራምረው ለማይደርሱበት ለስም አጠራርህ ሰላም እላለሁ። ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ በሞትህ ሞትን ታጠፋው ዘንድ ከርቤ የተቀላቀለበት መራራ ሐሞትን ስለኔ ሕይወት የጠጣህ ያቀረብኳትን አነስተኛ የምሥጋና መባ በቸርነትህ ተቀበል።''
✨✨✨መልክአ መድኃኔዓለም
ለዝክረ ስምከ
🍂️️️️️️🍂️️️️️️🍂️️️️️️✨✨✨🍂️️️️️️🍂️️️️️️🍂️️️️️️✨✨✨
መድኀኔዓለም ክርስቶስ ሆይ ክቡዱንና ግዙፉን ዕፀ መስቀል በመሸከም ምንኛ ድካምንና መከራን ልትታገስ ቻልክ። ለዚህ ረቂቅ ትህትናህ አንክሮ ይገባል።
✝️መልክዐ መድኃኔዓለም✝️
ነገ የአባታችን የመድኃኔዓለም ጥንተ ስቅለቱ ነው።
እንኳን አደረሳችሁ
ይህን ያህል ሰውን መውደድ እንደምን ያለ ፍቅር ነው።❤❤❤
ማገልገል ማለት ምንድን ነው?
አንድ አባት ሁሌ በቅዳሴ በኪዳን ሁሌ ቤተ መቅደስ ያገለግሉ ነበር። ከእለታት አንድ ቀን በምሥጋና እንዳሉ በተመስጦ ቁጭ ብለው ያለቅሱ ጀመረ እንባቸው መሬት ጠብ ጠብ ጠብ አለም
ምዕመናን ጨነቃቸው ምን ሁነው ይሆን ብለው አዘኑ። መምህሩ ባፋቸው የሚሉት ነገር አላቸው። ጠጋ ብለው አደመጧቸው
ጌታዬ ሆይ እባክህ ለቅዱስ ሥጋህና ለክብር ደምህ አብቃኝ ነበር የሚሉት። ምዕመናኑ ተገርመው አባ ምነው ምን እያሉ ነው ብለው አፋጠው ያዟቸው። እርሳቸውም አንተን ለማገልገል ለሥጋና ለደምህ አብቃኝ እያልኩ ነው። አሏቸው
ምዕመናኖቹም አባታችን ይህን ያክል ዘመን እያገለገሉ እንኳን ለርስዎ እኛን እያቆረቡ እንደት እንድህ ይላሉ አሏቸው። እርሳቸውም የመስቀሉ ፍቅር ገብቶኝ ለሰው ሳይሆን ለራሴ ብየ የማገለገግልበት የስጋና ደሙም ፍቅሩ ገብቶኝ የምቀበልበት ቀን ነው የምለምነው ብለው መለሡ።
ወዳጆቼ ብዙ ጊዜ እንዲህ አይነት ክርስትና በየሰፈሩ አለ።
ለሰው የምንሠራው ወይም ግዴታ ተጥሎብን የምናገለግል ብዙ ነን። አገልግሎት ማለት የፈቃደኝነት ባርነት ነው እንዲሉ በእንዲህ መልኩ መጓዝ ሲገባን ሰው ዓይተን ጀምረን በሰው አገልግሎት ያቆምን ብዙ ነን። አንዳንዶቻችን ቤተ ክርስቲያን መሄድ ፣ መፆም ፣ መስገድ ፣ መጸለይ ፣ መቀደስ ፣ መዘመር ፣ መስበክ ፣ ነጠላ መልበስ ፣ ግደታ አልያም ሕግ ነው ብለን የምንተገብር ብዙ ነን። መቼ ነው ግን ፍቅሩ ገብቶን ስለፍቅሩ እነዚህን የምንተገብራቸው። ሰው ያየናል ይደርስብናል ብለን ኃጢአትን ከመስራት የምንከለከል ብዘ ነን። አምላክን ፈረተን ሲዖል እንገባለን ብለን ክፉ ነገርን እንተወዋለን። ግን ስለፍቅሩ ብለን ፍቅሩ ገብቶን ኃጢአት የሆነውን ሁሉ
የምንተወው መቼ ይሆን??
#ታማኝ አገልጋይ ማን ነው?
# ስንት አትርፈን ይሁን በተሰጠን መክሊት ??
+3
በበአርሲ ሀገረ ስብከት ለመጀመሪያ ጊዜ የተጀመረው አዲሱ የሰ/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የመጀመሪያ መንፈቀ ዓመት የማጠቃለያ ፈተና በመሰጠት ላይ ይገኛል። እስካሁን በመንበረ ጵጵስናው ወረዳ ቤተክህነት በ5 አጥቢያ ሰ/ትቤቶች ከ1ኛ እስከ 9ኛ ክፍል በሁለቱም ቋንቋዎች ማለትም በአማርኛም በኦሮምኛም ከ450 ተማሪዎች በላይ የመጀመሪያ መንፈቅ ዓመት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ሲሆን አሁን ፈተናው አሁን ከወሰዱት ውጪ ሌሎች በአጀማመር ወቅት በተለያየ ምክንያት ወደ ኋላ የቀሩ (ዘግይተው የጀመሩ አጥቢያወች) በሚቀጥሉት ሳምንታት የሚሰጥ ይሆናል።
የአርሲ ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አድነት የቴሌግራም ቻናልን ይቀላቀሉ ለሌሎችም ያጋሩ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት
ለመቀላቀል
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
👉 https://t.me/ardssu👈
👉https://t.me/ardssu 👈
👉 https://t.me/ardssu👈
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊
መክሊት
ጎርጎርዮስ አምስቱ መክሊት የሚላቸው ዐይን፣ ጆሮ፣ አፍ፣ አፍንጫ እግር ናቸው። ሰው ረድቶበት፣ መጽውቶ፣ ጽፎ የሚበላበት መክሊት ነው፣ እኛ በእጃችን ምን ሠራን የወደቀ እንድናነሣ ሰጥተን እንድንጠቀም ነው።
ዓይኖችንን ምን ሠራንበት? ደሃን እንድናይበት፣ መጽሐፍ እንድናነበት ነው። ወይስ ፊልም ማየት ዩቲዩብ ማየት፣ በጆሮ ምን አደረግንበት ትምህርት መስማት፣ ቃለ እግዚአብሔር መስማት፣ ያዘኑትን መስማት። ወይስ ዘፈን ፣ ከንቱ ንግግር እንድንሰማበት።
አፍንጫችን እጣን እንዲያሸትበት ነው፣ የአፍ መክሊት መምከር ማስተማር እውነት መመስከር ነው። በነዚህ አፍአዊ መክሊቶች አምስቱን የውስጥ ሕዋስ እንጠብቃለን።
ሁለቱ መክሊት ፍቅረ እግዚአብሔር ፍቅረ ቢጽ ናቸው። የሕግ ፍጻሜ ፍቅር ነው
አንድ መክሊት ሃይማኖት ነውና ቆፍሮ መቅበር የሥጋ ሥራ የሥጋ ፈቃድ ነው ሃይማኖቱን በሥጋ ምኞቱ የቀበረ። የጥንቆላ የዝሙት የዘረኝነት፣ ሱስ፣ ስካር አፈር የቀባ ነው። አጥልቆ መቅበር ፈጽሞ የከፋ ማለት ነው። ሃይማኖትን በዘረኝነት እየቀበርን ነው።
መ/ር ንዋይ ካሳሁን
🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁
«ገብር ኄር ወገብር ምእመን ዘአሥመሮ ለእግዚኡ፤ ጌታውን ያስደሰተው አገልጋይ ታማኝና ቸር አገልጋይ ነው፤መኑ ውእቱ ገብር ኄር፤ ቸር አገልጋይ ማን ነው?»እያሉ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ይዘምራሉ፤ በቅዳሴው ደግሞ የማቴዎስ ወንጌል ፳፭፤፲፬-፴ ይነበባል። የመክሊቱ ባለቤት አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፤ ባለ አምስት፤ ባለ ሁለትና ባለ አንድ መክሊት የተቀበሉት በጥምቀት ጸጋ መንፈስ ቅዱስን የተቀበሉ፤ተምረው የሚያስተምሩ መምህራን ናቸው፡፡ የስጦታው መለያየት መበላለጥን ለማሳየት ሳይሆን የአንዱ ጸጋ ከሌላው እንደሚለይ የሚያጠይቅ ነው፤
«መንፈስ ቅዱስ አንድ ሲሆን ስጦታው ልዩ ልዩ ነው፡፡ ጌታም አንድ ሲሆን ልዩ ልዩ አገልግሎቶች አሉ» ፩ቆሮ ፲፪፥ ፬፡፡ባለ አምስትና ባለ ሁለት መክሊት የተባሉት አገልጋዮች ቃለ እግዚአብሔርን ከተማሩ በኋላ መክረው አስተምረውና ራሳቸውን አስመስለው ያወጡ ናቸው፡፡ ባለ አንድ መክሊት የተባለው ዐላውያን ነገሥታት፤ ዐላውያን መኳንንት እሳት ስለት አሳይተው ቢያስክዱኝ፣መናፍቃን ተከራክረው ቢረቱኝ፣ ምላሽ ቢያሳጡኝ፣ ሃይማኖቴን ቢያስቱኝ ብሎ ከማገልገል ይልቅ ሃይማኖቱን የማያስተምርና የማይመሰክር ነው፡፡ «ስለዚህ በሰው ፊት ለሚመሰክርልኝ ሁሉ እኔም በሰማያት በአለው አባቴ ፊት እመሰክርለታለሁ፤ በሰው ፊት የሚክደኝን ግን እኔም በሰማያት በአለው አባቴ ፊት እክደዋለሁ» ብሏል፤ ማቴ ፲፤፴፪ ፡፡ ስለዚህ በተሰጠን መክሊት በተባለ ጸጋ በሰው ሁሉ ፊት በማገልገል ልንመሰክር ይገባል፡: ጾሙን ጾመ በረከት ያድርግልን! 🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿
✨✨✨🍂🍂🍂✨✨✨🍂🍂🍂✨✨✨🍂🍂🍂
የተሰጠህን ጸጋ እንዳታጣ ያልተሰጠህን አትሻ፡፡ ወደ ጸጋ ወደ ክብር ለመድረስ እግዚአብሔር ቢያበቃህ ያሳየህን እይ ያላሰየህን አያለሁ አትበል። አንድም ያልተሰጠህን ጸጋ አትሻ፣ በተሰጠህ ጸጋ ለእግዚአብሔር ተገዛ፡፡ ማር አብዝቶ መመገብ እንዳይመች እንደዚህም ሁሉ ያልተሰጠውን መሻት አይገባም አያስመስግንም፡፡
ነፍስ ያልተሰጣትን ጸጋ በመሻት እንዳትደክም ያልተሰጠህን ጸጋ አትሻ፡፡ የምታየው ማየት ቢኖር እውነተኛውን ምትሐት ሆኖ ታየዋለህ ፤ ሕሊና ያልሰጡትን ጸጋ በመሻት በማውጣት፣ በማውረድ የተሰጠውን ያጣል፡፡
ሰሎሞን መልካም ነገር ተናገረ "በሰጡት ጸጋ የማይኖር ሰው ቅጽር የሌላትን አገር ይመስላል" ብሎ ያን ማንም እየገባ እንዲዘረፈው እሱም የተሰጠውን ጸጋ ያጣል ፤ አንተ ብሩህ አእምሮ ሰውነትህን ያልተሰጣትን ጸጋ እንዳትሻ ከልክላት፡፡
ከቁመተ ሥጋ የወጣ አብዝቶ መገበርን ከአንተ አርቅ ያልተሰጠህን መሻት ከአንተ አርቅ፡፡ ባልተሰጠህና በተሰጠህ ጸጋ መካከል ትሕትናህን፣ ንጽሕናህን መጋረጃ አርጋቸው:: አንድም በተሰጠህ ጸጋ ላይ ያልተሰጠህን ጋርደው፡፡ በንጽሕና፣ በትሕትና፣ በልቡናህ የምታስበውን መንፈሳዊ ክብር ታገኛለህ::
ምክር ወተግሣጽ ዘማር ይስሐቅ
✨✨✨🍂🍂🍂✨✨✨🍂🍂🍂✨✨✨🍂🍂🍂
"ትህትናን ውደዷት ኃጢአታችሁን የምትሸፍን ናትና፡፡ ሁሉም ኃጢአት በእግዚአብሔር ፊት የተጠላ ቢሆንም ከኃጢአቶች ሁሉ መጥፎ የሆነው ግን የልብ ትዕቢት ነው:: ራሳችሁን አዋቂ አድርጋችሁ ከፍ ከፍ አታድርጉ፡፡ ይህን ምታድረጉ ከሆነ ጥረታችሁ ሁሉ ፍሬ አልባ ይሆናል፡፡"
#አባ_እንጦንስ
+1
የመማርያ መጻሕፍት ሥርጭት በቅርብ ቀን
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ ዕድሜን መሠረት ያደረገ ወጥ የሆነ ሥርዓተ ትምህርት አዘጋጅቶ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት በትግበራ ላይ ይገኛል።
ለሥርዓተ ትምህርት ትግበራውም ለረጅም ጊዜያት በቤተክርስቲያን ሊቃውንትና መምህራን እንዲሁ በሥርዓተ ትምህርት ባለሙያዎች ሲደከምበት የኖረውን የሥርዓተ ትምህርት መማርያ መጻሕፍት በባለፈው ዓመት ከ1ኛ-4ኛ ክፍል 23 የመማሪያ መጻሕፍት በማሳተም በሥርጭት ላይ ማዋሉ ይታወቃል።
በዘንድሮውም ዓመት ደግሞ በአምላካችን ቅዱስ ፈቃድ
👉 ከ1-4ኛ ክፍል 23 የኦሮምኛ ትርጉም የመማርያ መጻሕፍት በአራት ጥራዝ
👉 ከ5ኛ እስከ 7ኛ ክፍል በ3 ጥራዝ የተዘጋጁ 18 መጻሕፍት በአጠቃላይ 41 መጻሕፍት ተዘጋጅተው ለኅትመትና ለሥርጭት በቅተዋል።
ምን ጊዜም ቢሆን ስለ እግዚአብሔር አስቡ ለእርሱ ያላችሁ ፍቅር ምልክቱ እርሱን ሁል ጊዜ በአሳባችሁ ውስጥ መያዛችሁ ነው። ነቢዩ ዳዊትን አስታውሱት! እርሱ ንጉሥ እና መሪ እንደ መሆኑ በብዙ ሥራዎች ቢጠመድም " አቤቱ ፦ ሕግህን እንደ ምን እጅግ ወደድሁ! ቀኑን ሁሉ እርሱ ትዝታየ ነው ።" (መዝ 118፥97) በማለት ተናግሯልና።
አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
የምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ከዚጊቲ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ የጻድቁን በዓል አክብረው በመመለስ ላይ በመኪና አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የአንድ ሚሊዮን ብር የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ ወሰነ !
መጋቢት 15 ቀን 2017 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ/ ኢትዮጵያ]
ሀገረ ስብከቱ በመግለጫው መግቢያ "በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሥርዓት መሠረት መጋቢት 5/2017 ዓ.ም የጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዓመታዊ ክብረ በዓል በገሞጎፋ ዞን ሀገረ ስብከት ስር በሚገኘው ዚጊቲ ደብረ ሰላም አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤ/ክ ለማክበር ከሻሸመኔ እና ከአጎራባች ከተሞች ምእመናን ከክብረ በዓሉን አክብረወው መጋቢት 6 ቀን 2017 ዓ/ም በመመለስ ላይ እያሉ በወላይታ ዞን ልዩ ስሙ በዴሳ በተባለ ቦታ ላይ መንፈሳውያን ተሳላሚዎች ይዞ ሲንቀሳቀስ የነበረው መኪና የመገልበጥ አደጋ ደርሶበት አሰቃቂ የሞት አደጋና ከፍተኛ የአካል ጉዳት መድረሱን ከሻሸመኔ ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤት ከተሰጠው መግለጫ፤ ከጉዳቱ የተረፉ አካላት ከተጎጂ ቤተሰብ ከሰጡት ማስረጃ ፤ እንዲሁም ከማኅበራዊ ሚዲያ ማረጋገጥ ተችሏል፡፡" በማለት ሁነቱን ያስታወሰ ሲሆን በዚህም በደረሰው አደጋ የሰዎች ሕይወት መጥፋትና የአካል ጉዳት በደረሰባቸው ምዕመናን የተሰማውን ልባዊ ሐዘን ገልጧል፡፡
በሞት የተለዩ 13 ወገኖች ክብራቸውን በሚመጥን መንገድ እንደ ቤተክርስቲያን ሥርዓት ጸሎተ ፍትሐት ተደርጎ የቀብር ሥነ-ሥርዓታቸውን የሀገረ ስብከቱ የሥራ ኃላፊዎችና ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ የሟች ቤተሰቦችና ወዳጆች፣ የኃዘኑ ተካፋይ የሆኑ ሁሉ በተገኙበት በሻሸመኔ ከተማ ባሉ አራት አድባራት ላይ መፈጸሙን በማውሳት ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው 19 የሚሆኑ ታማሚዎች በወላይታ ሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል በፅኑ ሕሙማን ክፍል የሕክምና ድጋፍ እየተደረገላቸው እንደሚገኙ መታወቁን አክሏል፡፡
ሀገረ ስብከቱ የአስተዳደር ጉባኤው አስቸኳይ ስብሰባ በመጥራት፤ የአድባራትና ገዳማት የአብያተ ክርስቲያናት አስተዳዳሪዎች፣ ምክትል ሊቃነ መናብርት፣ የሰ/ት ቤት እና የማኅበራት ተወካዮች ልዩ ልዩ አካላት እንዲሁም ከተጎጂ ቤተሰብ ጋራ ውይይት በማድረግ ተጎጂዎችን ለመርዳት ያስችል ዘንድ ሁሉን ያሳተፈ የጋራ ውሳኔንም አስተላልፏል፡፡
ከውሳኔዎቹም መካከል፡-
1ኛ. እንደ ቅድስት ቤተክርስቲያናችን ሥርዓት ላረፉት ዐሥራ ሦስት ወገኖች የጋራ ጸሎተ ፍትሐት ለማድረግ ፣ በሕይወተ ሥጋ ያሉት ቅዱስ አምላክ እንዲምራቸቸው በጸሎት ማሰብ፣
2ኛ. ጠቅላላ የሀገረ ስብከት ሠራተኞች ሙሉ የአንድ ወር ደመወዛቸውን ጨምሮ ከሀገረስብከቱ የውስጥ ገቢ 1,000,000 (አንድ ሚሊየን ብር) ለተጎጂዎች ለመለገስ፣
3ኛ. የወረዳ ቤተክህነት ሠራተኞችን ሙሉ የአንድ ወር ሙሉ ደመወዝ
4ኛ. በሀገረ ስብከቱ ሥር የሚገኙ አድባራትና የገዳማት አብያተ ክርስቲያናት ጠቅላላ ሠራተኞች የአንድ ወር ደመወዛቸውን ለመለገስ፣
5ኛ. አድባራትና የገዳማት አብያተ ክርስቲያናት እንደ ተቋም ለመርዳት መወሰኑን በመግለጫው አሳውቋል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ሀገረ ስብከቱ ለከተማው ከንቲባ ጽ/ቤት ባቀረበው መሠረት የሻሸመኔ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት ከተጎጂዎች መካከል በኪራይ ቤት ያሉ የመኖሪያ ቤት የሌላቸውን በመለየት የመኖሪያ ቤት ለመሥጠት ቃል የገባ ሲሆን ከዚህም ሌላ የከንቲባ አስተዳዱሩ ጽ/ቤት ሠራተኞችም በጉባኤ በመወሰን የገንዘብ ድጋፍ እንደሚያደርጉ የከተማው ከንቲባ አቶ አዳነ ተ/ጊዮርጊስ ገልጸዋል፡፡
የሀገረ ስብከቱ አስተዳደር ጉባኤ አባላት፣ የሀገረ ስብከቱ የየክፍል ኃላፊዎች፣ የአድባራት እና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ምክትል ሊቃነ መናብርትና የሰ/ት/ቤት ተወካዮች፣ የማህበረ ቅዱሳን አባላትና፣ በጎ አድራጊ ባለሃብቶች እንዲሁም ልዩ ልዩ አካላትን በመሰብሰብ ስለ ተፈጠረው ችግር በቀጣይ ምን መሥራት እንዳለብን እና በምን አይነት መንገድ የሟች ቤተሰቦችንና በፅኑ ሕሙማን ክፍል በሕክምና የሚረዱ ወገኖቻችንን መደገፍ እደሚገባ የሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዜና ማርቆስ የጉጅ ምዕራብ ጉጂ ቦረና ሊበንና የምዕራብ አርሲ አህጉረስብከት ሊቀ ጳጳስ የቅዱስ ሲኖዶስ አባል መመሪያ መስጠታቸውንም ጨምረው በመግለጫው ላይ አስታውቀዋል፡፡
ከሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት፤ ከሻሸመኔ ከተማ አስተዳደር፣ ከአድባራትና ገዳማት አብያተ ክርስቲያናት፣ ከሰ/ት/ቤት ወጣቶች ፡ ከማኅበረ ቅዱሳን፣ በአካባቢው ከሚገኙ እድሮችና እቁቦች፣ ከሀገር ሽማግሌዎች፣ ከአባ ገዳዎች፣ እንዲሁም ሃዳ ሲንቄዎችን ያካተተ ኮሚቴ የተዋቀረ ሲሆን ይህም ኮሚቴ ለተጎጂዎች አስፈላጊውን እርዳታ ለማድረስ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት በመክፈት ገቢ የሚያሰባበስብ መሆኑን በስተመጨረሻ በመግለጫው ላይ አሳውቋል፡፡
