es
Feedback
ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

Ir al canal en Telegram

በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:-  @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

Mostrar más
669
Suscriptores
+124 horas
+37 días
-330 días
Archivo de publicaciones
ጥያቄ? የወጣትነት ጊዜውን በቅድስት ቤተ ክርስቲያን በአገልግሎት እያሳለፈ ላለ ወጣት ያለን አመለካከት ግን ምን አይነት ነው?
Anonymous voting

"አቤቱ አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ ከአንተ ዘንድ ከሰማይ የሚገኝ ሰላምን ሁሉ በሁላችን ልቡና አሳድርብን። በእርስዋም የሕይወትን ሰላም ስጠን።ለሀገራችን ኢትዮጵያም ሰላሟን አጽናላት።"           ሥርዓተ_ቅዳሴ

✨️️️️️️️🍁🍁✨️️️️️️️🍁🍁✨️️️️️️️🍁🍁✨️️️️️️️🍁🍁✨️️️️️️️🍁🍁 ቅዱስ ጴጥሮስ በደብረ ታቦር ተራራ የጌታችን መልኩ ተለውጦ ሲያበራ፤ ልብሱም በምድር አጣቢ ሊያነፃው ከሚችለው በላይ ነጭ ሲሆን፤ ሙሴና ኤልያስም መጥተው ከጌታ ጋር ሲነጋገሩ አይቶ የመጣለትን ሀሳብ የገለጠበት ቃል ነው
” በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው”።
🍂🍂🍂 አባቶች ቢርበንና ቢጠማን ሙሴ መና እያወረደ ውሃ እያፈለቀ፤ ጠላት ቢነሣብን ኤልያስ እሳት አውርዶ እያጠፋ፤ አንተ ደግሞ ብንታመም እየፈወስኸን ብንሞት እያነሳኸን በዚህ መሆን መልካም ነው ማለቱ እንደ ሆነ ይተረጉማሉ።  ቅዱስ ጴጥሮስ በዚህ ንግግሩ በዚያ ሥፍራ ብንገኝ ልናስበውና ልንመኘው የምንችለውን  ሁላችንን ወክሎ  ስሜታችንን ነው የተናገረው። ለሥጋችንና ለስሜታችን ምቾትና ደስታ የሚሰጥ ቦታ መሆን የሁላችን ምኞት ነው:: ቢሆንልን መሆን የምንፈልግ የት ይሆን? አሁን ያለንበት ቦታና ሁኔታ ውስጥ ያለነውስ ተመችቶን ወይም ያን ሆነን መኖርን አምነንበት ነው? 🍂🍂🍂 በእውነታው አንድ ነገር መሆንና (ሆኖ መገኘትና) የሆነውን መኖር እጅግ በጣም የተለያዩ ነገሮች ናቸው። ከትንሹ ብንጀምር በተሰማራንበት ሙያ ባለሙያ መሆንና ሙያውን መኖር ይለያያል። አንድ ሰው ፖሊስ ቢሆን ዩኒፎርም ለብሶ በሚንቀሳቀስበት የሥራ ሰዓቱ ወንጀል እየተከላከለ ከሥራ ውጭ ነኝ ብሎ ባሰበበት ሰዓት ወንጀል ሲፈፀም አይቶ በግዴለሽነት ካለፈ ፖሊስ ሆነ እንጂ ሙያውን አይኖረውም፡፡ 🍂🍂🍂 የሕክምና ባለሙያስ ሙያውን መኖር ያለበት የት ይሆን? ብዙዎቻችንን የምንደስተው በ “መሆን” አችን እንጂ የሆነውን ስለ “መኖር” ተጨንቀን አናውቅም። መሆን ውስጥ ያለው ደስታና ምቾት ሲሆን መኖር ውስጥ ግን የሚጠብቀን ተግባርና ኃላፊነት ነው። ብዙዎቻችን ጌታ እግዚአብሔርን የምንለምነው የለመነውን ነገር እንድንሆን እንጂ የሆነውን እንድንኖረው አይደለም። 🍂🍂🍂 ....... ቀሲስ ታምራት ውቤ ✨️️️️️️️🍁🍁✨️️️️️️️🍁🍁✨️️️️️️️🍁🍁✨️️️️️️️🍁🍁✨️️️️️️️🍁🍁

እጅግ በጣም የሚያሳዝን ዜና ደብረ መድኃኒት መጥተው አውደ ምህረት ላይ አስተምረው ከሄዱ መምህራን መካከል የመጀመሪያውና ታላቁ መምህር ነው ለአንድም የመጽሐፍ ቅዱስ ማስረጃ ማስታወሻ የማይገልጥ መጽሐ
እጅግ በጣም የሚያሳዝን ዜና ደብረ መድኃኒት መጥተው  አውደ ምህረት ላይ አስተምረው ከሄዱ መምህራን መካከል የመጀመሪያውና ታላቁ መምህር ነው ለአንድም የመጽሐፍ ቅዱስ ማስረጃ ማስታወሻ የማይገልጥ መጽሐፍ ቅዱስን በቃሉ የያዘ የትኛውም ጉባኤ ላይ ሄዶ አበል ገንዘብ የማይቀበል የመናፍቃን መዶሻ ከገጠር እስከ ከተማ በቅንነት ያገለገለ እጅግ ሃይማኖትን ከምግባር ጋር ያስተባበረ ቅን ታማኝ ተወዳጅ የሆነ የጎፋ ገብርኤሉ ንጉስ ታላቁ የወንጌል መምህር በእውነት ቤተክርስቲያን ታላቅ ሰው አጥታለች። የእውነት እጅግ በጣም የሚያሳዝን ሞት የወንጌል በረከትህ ይደርብን።

🔔ዐቢይ ጾም 🔔 🔔አራተኛ ሳምንት🔔 🔔መጻጉዕ🔔 ምስባክ የዕለቱ ምንባባት ገላ 5÷1-ፍ ያዕ 5÷14-ፍ ሐዋ 3÷1-13 የዕለቱ ምስባክ እግዚአብሔር ይረጽኦ ውስተ ዐራተ ሕማሙ ወይደመጥ ሎቱ ኩ
🔔ዐቢይ ጾም 🔔 🔔አራተኛ ሳምንት🔔       🔔መጻጉዕ🔔 ምስባክ የዕለቱ ምንባባት ገላ 5÷1-ፍ ያዕ 5÷14-ፍ ሐዋ 3÷1-13 የዕለቱ ምስባክ እግዚአብሔር ይረጽኦ ውስተ ዐራተ ሕማሙ ወይደመጥ ሎቱ ኩሎ ምስካቤሁ እምጼዋሁ እንሰ እቤ እግዚኦ ተሠሃለኒ መዝ 40÷3 ትርጉም እግዚአብሔር በሕማሙ አልጋ ውስጥ ላለ  ይረዳዋል  መኝታውም ከደዌው የተነሣ ይለውጥለታል እኔስ አቤቱ ይቅር በለኝ እላለሁ ። የዕለቱ ወንጌል  ዮሐ 5÷1-25 ቅዳሴ ዘእግዚእነ 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🤲🤲🤲🕯🕯🕯🕯🕯 ዕለተ ሰንበት በማስቀድስ እናሳልፍ ያንን ተስፋ ያልነበረውን በሽተኛ ከደዌ ሥጋው ፈውሶ ሕይወትን የሰጠው አምላክ፣ እኛንም በውስጥ በአፍአ ካለብን ደዌ ሥጋና ደዌ ነፍስ እንዲፈውሰን፤ ቁስለ ኃጢአታችንን እንዲያደርቅልን፣ በሕይወትና በጤና እንዲጠብቀን የእርሱ የጌታች ቅዱስ ፈቃድ ይሁንልን፡፡ ኑ እያስቀድስን ድውይ ነን አንተ አድነን እንበለው 🤲 #ጌታ ሆይ ልንድን እንወዳለን

ሁለት ሰዎች በአንድ ጉዳይ አብረው ይጸልያሉ አንደኛው ጸሎቱ ተመለሰለት፤ አንደኛው ሳይመለስለት ቀረ። በዚህ ጊዜ ጸሎቱ ያልተመለሰለት "ጌታ ሆይ ሁለታችንም እኩል ጸልየን ለእርሱ ሰጥተኸው ለእኔ ከለከልኝ ለምንድ ነው?" አለው። እግዚአብሔርም "ለእርሱ ባልሰጠው ይጠፋል፣ ላንተ ከሰጠኹህ ደግሞ ትጠፋለህ" አለው ይባላል። እግዚአብሔር ከራሳችን በላይ እኛን ያውቀናል። ለአንዳችን በመስጠት፣ አንዳችንን በመከልከል ዕድሜያችንን ያረዝመዋል። መስጠቱም መንሳቱም ሁለቱም በፍቅር ነውና በልመናችን በጸሎታችን የአንተ ፈቃድ ይሁንልን ማለት ይገባናል። ስለሁሉም የእግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን። አሜን!!

ከአባታችን ከመድኃኔዓለም በላይ ማንም ሊያስብልን አይችልም።

እንኳን ለአባታችን እና ለአምላካችን ለመድኃኔዓለም ወርሀዊ በዓል በሰላም አደረሳቹ🙏 መድኃኔዓለም የነገራቹትን ፣ያዋያቹትን፣ የምትሹትን መልካም ምኞታችሁን ሁሉ ይፈጽምላቹ።
እንኳን ለአባታችን እና ለአምላካችን ለመድኃኔዓለም ወርሀዊ በዓል በሰላም አደረሳቹ🙏 መድኃኔዓለም የነገራቹትን ፣ያዋያቹትን፣ የምትሹትን መልካም ምኞታችሁን ሁሉ ይፈጽምላቹ።

"አስትንፋስ አፍንጫው ላይ ባለች በሰው አትታመኑ ፤ ከቶ ምን የሚበጅ ነገር አለው!"    ኢሳ 2÷22

መርሐባ ፍኖተ ወንጌሎች ነን! እልፎችን በእልፍኛችን ሰንቀን፣ የትውልድ ቅብብሎሽን ጌጣችን አድርገን፣ ከማይነጥፍ እኛነታችን ብዙዎችን ቤተሰብ አድርገን፣ በወንጌል ጎዳናችን ላይ ስንኳትን ቆይተናል። ከ
መርሐባ ፍኖተ ወንጌሎች ነን! እልፎችን በእልፍኛችን ሰንቀን፣ የትውልድ ቅብብሎሽን ጌጣችን አድርገን፣ ከማይነጥፍ እኛነታችን ብዙዎችን ቤተሰብ አድርገን፣ በወንጌል ጎዳናችን ላይ ስንኳትን ቆይተናል። ከትላንት የተረከብነውን ከነገ የተዋስነውን አደራ ለማቆየት ሰለቸን ደከመን ሳንል የህወት ትንታጋችንን አስታግሰን አለን። የሉም ሞተዋል ሲሉን በዝተን አለን በእግዚአብሔር ሁሉን አልፈን እኛልን ብላቴና ሳለን ገና በለጋ ዕድሜያችን ከደጀ ሰላሙ ታዛ ሆነን እግዚአብሔር እረኛዬ ነው... እያልን ያደረስናት ጸሎት ደጀን ሆናን ከሞት አፋፍ ጠብቃን የማይታለፉ የሚመስሉ ክፉ ቀናትን አሳልፋን ዛሬም አለን አጃኢብ! በታሪክ ድርሳን ትርክታችንን ከትበን ማለፍ እርስ በርስ በፍቅር መተሳሰር ከላይ የተሰጠን ጸጋ ነው። እኛ ፍኖተ ወንጌሎች ነን! የተሰቀለውን ክርስቶስን መስበክ ግብራችን ነው! ግራችንን ሲመቱን ቀኛችንን እየደገምን በወንጌል ጎዳናችን ስንጓዝ የቆየን አገልግሎት ስላለን አንታክትም እያለን ወደ አባታችን ቤት ስናቀና የከረምን! እነሆ አብራችሁን ሆናችሁ ከማያልቀፍ እልፍኛችን እኛነታችንን እየቀሰማችሁ ከጎጇችን ሰንብታችሁ ቤተሰባዊ መተሳሰብን ስንቃችሁ አድርጋችሁ ከጻድቁ በረከት ትሳተፉ ዘንድ በወንጌላ ጎዳናችን ላይ አብረን እንጓዝ እንሎታለን። እነሆ ታላቅ ነው አዘጋጇ ፍኖተ ወንጌል ናትና መንፈሳዊ ጉዞ ነው መንፈሳዊነትን ተላብሰን በመንፈስ ተቃኝተን እንጓዛለንና ወደምድረ ከብድ ነው ከአቡዬ ደጅ የአባታችን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስን የንግስ ክብረ በዓል ተገን አድርገን!  ኑ! አብረን ወደ ምድረ ከብድ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ገዳም! መጋቢት 04/2018ዓ.ም ወደቦታው ተጉዘን መጋቢት 06/2018ዓ.ም እንመለሳለን!   በወንጌል ጎዳና ላይ ከመጓዝ የሚከለክለኝ ማነው? ማንም!

"አቤቱ ኅጢአቴ እጅግ ነውና ስለ ስምህ ይቅር በለኝ"       መዝ 24÷11

አድዋ "በአንተ ጠላቶቻችንን እንወጋቸዋለን፥ በስምህም በላያችን የቆሙትን እናዋርዳቸዋለን።" መዝ 43፡5 እንኳን ለአድዋ ድል መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ! መልካም በዓል!
አድዋ "በአንተ ጠላቶቻችንን እንወጋቸዋለን፥ በስምህም በላያችን የቆሙትን እናዋርዳቸዋለን።" መዝ 43፡5 እንኳን ለአድዋ ድል መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ! መልካም በዓል!

🍁🍁🍀🍀✨🍁🍁🍀🍀✨🍁🍁🍀🍀✨ ጊዮርጊስ ሆይ፤ ለክብርት ክንድህና ተባባሪዋ ለሆነችው መዳፍህም ሰላም እላለሁ። እንዲሁም ለጣቶችህና እንደ ዕንቍ ፊርጥ ለሚያበሩ የእጆችህም አጽፋር ሰላም
🍁🍁🍀🍀✨🍁🍁🍀🍀✨🍁🍁🍀🍀✨ ጊዮርጊስ ሆይ፤ ለክብርት ክንድህና ተባባሪዋ ለሆነችው መዳፍህም ሰላም እላለሁ። እንዲሁም ለጣቶችህና እንደ ዕንቍ ፊርጥ ለሚያበሩ የእጆችህም አጽፋር ሰላም እላለሁ። ተአምር ሠሪው ሰማዕት ሆይ፤ የሰማዕታትና የጭፍሮቻቸው ሁሉ አለቃ ነህና አቤቱ በጥበብህ ከባሕረ ኅዘን አሻግረን በባሕር ላይ መሄድ ያልለመደ የባሕርን ጠባይ ሊያውቅ አይችልምና። #መልከአ ጊዮርጊስ 🍁🍁🍀🍀✨🍁🍁🍀🍀✨🍁🍁🍀🍀✨

🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 እነኾ ውብ የኢትዮጵያ እና የተዋህዶ ታሪክ ቅንጭብ! አንድ የኢጣሊያ እሥረኛ ንጉሡ አጼ ምኒልክ የተማረኩ እሥረኞችን በሚፈቱበት ዕለት እንዲኽ አላቸው። "ንጉሥ ኾይ ያኔ ጦርነቱ  ሲካኼድ በነጭ ፈረስ ላይ ተቀምጦ ወታደርዎትን ይመራ የነበረው የኛን ትጥቅ የሚመስል የለበሰውን ጄኔራሎትን አንዴ ያሳዩኝ?" እርሳቸውም ማን እንደኾነ ገባቸውና "እሱማ የኢትዮጵያ ንጉሥ ነው 🙏!!!" ብለው ሲመልሱለት በመደንገጥ  "እርስዎስ 👀?" አላቸው። እርሳቸውም "እኔማ ባሪያው ነኝ"  አሉት፡፡ በዚህ የተነሣ በየዓመቱ አራዳ ጊዮርጊስ እንዲነግሥ አደረጉ። የሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ረድኤቱ እና በረከቱ እንዲኹም ጥበቃው አይለየን! 🙏🙏🙏 ♥️♥️♥️♥️♥️♥️♥️♥️♥️♥️♥️

"ጎረቤቱን የሚንቅ ኀጢአት ይሰራል ለተቸገሩት የሚራራ ግን ቡሩክ ነው።"        ምሳ 14÷21

"እርስ በእርሳችን መፋቀር ይገባናል ይህች ፍቅር ደክመን የምንሰራውን ስራ ያለ ድካም እንድንሰራው ታደርጋለች እና።"      ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

🔔ዐቢይ ጾም 🔔 🔔ሥስተኛ ሳምንት🔔 🔔ምኩራብ🔔 የካቲት 22 የዕለቱ ምንባባት ቆላ 2÷16-ፍ ያዕ 2÷14-ፍ ሐዋ 10÷1-9 የዕለቱ ምስባክ እስመ ቅንዓተ ቤትከ በልዐኒ ትእይርቶሙ ለእለ ይት
🔔ዐቢይ ጾም 🔔 🔔ሥስተኛ ሳምንት🔔       🔔ምኩራብ🔔 የካቲት 22 የዕለቱ ምንባባት ቆላ 2÷16-ፍ ያዕ 2÷14-ፍ ሐዋ 10÷1-9 የዕለቱ ምስባክ እስመ ቅንዓተ ቤትከ በልዐኒ ትእይርቶሙ ለእለ ይትዔየሩከ ወድቀ ላዕሌየ ወቀጻዕክዋ በጾም ለነፍስየ ። መዝ 80÷9 ትርጉም የቤትህ ቅናት በልቶኛልና የሚሰድቡህም ስድብ በላዬ ወድቋልና ሰውነቴን በጾም አደከምኩት የዕለቱ ወንጌል : ዮሐ 2÷12-ፍ ቅዳሴ  ዘእግዚእነ 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🤲🤲🤲🕯🕯🕯🕯🕯 ዕለተ ሰንበት በማስቀድስ እናሳልፍ #ዕለተ ምኩራብን #በደብረ መድኃኒት

ባልንጀሮችህ አንድ ሺ ሊሆኑ ይችላሉ ያንተን ምሥጢር ደብቆ የሚይዘው ግን አንድ ነው፡፡ ባልንጀራን በማብዛት ለእግዚአብሔር ጊዜ አትጣ፡፡ ተግሳጽ በመጨረሻ በኃጢአት ጥልቅ ውስጥ ገብተን እንዳንሰጥም የሚጠብቀን የሕሊናችን ቅዱስ መልሕቅ ነው፡፡ ስለዚህ ልጄ ሆይ ተግሳጽን አትጥላ አትናቅምም፡፡                        ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

🌹 እንኳን ደስ አላችሁ!🌹 ስለ ሁሉም ነገር እግዚአብሔር ይመስገን🙏 🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹 እህታችን ሮማን ወደ ሀገርዋ ህክምናዋን ጨርሳ በሰላም ገብታለች። 🌹🌹🌹🌹🌹�
🌹 እንኳን ደስ አላችሁ!🌹 ስለ ሁሉም ነገር እግዚአብሔር ይመስገን🙏 🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹 እህታችን ሮማን ወደ ሀገርዋ ህክምናዋን ጨርሳ በሰላም ገብታለች። 🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹