3 743
Suscriptores
-624 horas
-317 días
-12930 días
Archivo de publicaciones
3 743
አንዳንድ ነገሮች‼️
አለም ፊቱን ዞሮበት፥ ወይንም እንደፍጥርጥሩ ለእጣፋንታው ትቶት "ረስቶት" እያለ
"መተን ቀብረነዋል" የተባለው የአማራ ህዝብ "መቃብር" ፈንቅሎ ብድግ አለ።
ያለ አንዳች መካሪና ተቆርቋሪ፥ ያለ አንድ ሰው ሃሳብ አበዳሪ ከመከራው ተምሮ፥ ከራሱ መክሮ አማራ የራሱን አቢዮት ራሱ ፈጠረ።ሲነሳ በደነገጡት ጠላቶቹ ፊት ራሱን በፍጥነት አደራጅቶ የህልውና ትግሉን ጀመረ።እፍኝ የማትሞላ ተተኳሽ በመቶ ሽዎች ብር እየገዛ፥ ታጣቂም አስታጣቂም ራሱ ሆኖ ወደ ራሱ ግብ መገስገስ ቀጠለ። እነሆ ሶስት አመት አለፈው።
ትልቁ ብሄራዊ ሃብት ሰው ነው። የሁሉም ነገር... የፖለቲካውም፥ የታንኩም፥የዲፕሎማሲውም ፥ የርእዮተ አለሙም ግርግር ማእከሉ፥ መቋጫው ሰው ነው። ለሰው ልጆች የተሻለ ነገር ለማምጣት የሚደረግ ነው። የራሱን ህዝብ በሰማይም በምድርም እሳት አሰማርቶ የሚያነድ ዘረፈጅ ሥርዐት ስለ ብሄራዊ ክብርና ሉአላዊነት የት ያውቃል? ስለ ሃገር ለማውራት ሞራሉስ ከየት ይገኛል?አንገቷ ላይ ቆሞ እያነደዳት ያለችን ሃገር እወዳታለሁ ሊለን ይሞክራል። የጥፋት ተልእኮ ይዞ ሃገር እያቃጠለ ሳያፍር ሌላውን ሃይል በተላላኪነት ሊከስ ይዳዳዋል። ለግብፅ መላላክን፥ ለፕሬዝዝዳንት ኢሳያስ መሽቆጥቆጥን፥ ለህወሃት መንበርከክን አብይና ቡድኑ እንጅ ፋኖ አያውቀውም።
በኛ በኩል የአለም ጥቅሞች ሁሉ ተሰልፈው ቢመጡ፥ መዳፋችን ላይ ቢቀመጡ አንዲት ግራም የአማራን ህዝብ ጥቅም አሳልፈን አንሰጥም። የአማራ ህዝብ ህልውና፥ ጥቅሙና ምኞቱ ለድርድር አይቀርቡም፥ "ቅዱስ" ናቸው። ቅዱሱን የሚነካም የሚያስነካም ማንም የለም።ነገር ግን ካለፉት ረጅም አመታትም ፥ከራሱ ከብልፅግና ስህተትና ውደቅትም ተምረን ከቀጠናዊና አለምአቀፋዊ ልውጥውጡ የማንም ወኪል ሳይሆኑ መጠቀምን እናውቅበታለን።በሊማሊሞ ገደል አናት በተወጠረ ገመድ ላይ አይናችን ታስረን እንኳን አመጣጥነን መራመድ እና ወደ ነገ መሻገር እንችላለን። ይህ መከራ ከእድሜው በላይ ያስተማረው ትግል ነው። ስለሆነም በፍፁም አንሳሳትም። ከኢትዮጲያውያን ሃይሎች ጋር በጋራ መርፌ የመግዛት ተልእኮ እንኳን ቢኖረን የአማራ ህዝብ በይፋ ሳያውቀው የምንጓዘው አንድም እንኳን ስውር እርምጃ የለም።
ጠላት ግን ይጮሃል። "ይህን ውሃ ምን ያስጮኸዋል ቢሉት፥ በውስጡ ያለው ድንጋይ" ብሎ መለሰለት አሉ። በዚህ ወቅት ብልፅግና የተባለ የኩሬ ቦይን የሚያስጮሁት "ድንጋዮች" ሁለት ናቸው፦
1)ፍርሃት። አብይ የቀጠናውና የሃገር ውስጥ ሃይሎች ከተባበሩ እድሜዬ በአንድ እጄ እጣቶች ልክ የተቆጠሩ ናቼው ብሎ ስለሚያምን ደንግጧል። እናም ድንገት ጥቂቶችን አደናግሬ የማምሻ እድሜ ባገኝ ብሎ ሌት ተቀን ይጮሃል።ከሞት የማያድን ጩኸት።
2)ጦርነት። በአብይ አህመድ ስሌት የአማራ፥ የትግራይ፥ የአፋርና ሌሎች ህዝቦች ገና በበቂ አልደቀቁም። ስለዚህ በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ መድቀቅና መጥፋት አለባቼው። ይህ ይሆን ዘንድ ግን "ሰበብ " ያስፈልጋል። ስለሆነም አቅም አግኝቶ ነገ ወደ አንድ ተረኛ ህዝብ ቢተኩስ ለአለሙ የሚነግረው ሰበብ "ተባብረው ሊያጠፉኝ ሲሉ ራሴን ለመከላከል ጦርነት ከፈትሁ" ይሆናል ማለት ነው። ይኸው ነው።
ይህ ትግል የአማራንና የሃገራችን ህልውናን የማረጋገጥ ትንቅንቅ ብቻ አይደለም፥ ቢያንስ ለሚቀጥሉት አምስት መቶ አመታት የጥይት ድምፅ የማይሰማ ትውልድ የመፍጠር ተልእኮም ነው።
ብልፅግና ይወገዳል፥የአማራ ህልውና ይረጋገጣል። ኢትዮጲያ ለኢትዮጲያውያን የፍቅርና የደስታ ምድር ትሆናለች፥ ሰላም ትሆናለች።
ክፋት ለማንም፥ በጎነት ለሁሉም!
አዲስ ትውልድ ፥አዲስ አስተሳሰብ፥አዲስ ተስፋ!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
ሰኔ-21/2018 ዓ. ም!
አርበኛ ዘመነ ካሴ!
3 743
የኤቢሲ ቴቪ የYoutube ገፃችንን በመቀላቀል ዝግጅቶቻችንን ይከታተሉ።
ከYoutube ገፃችን በተጨማሪ የRumble ገፃችንን በመቀላቀል የሚድያችንን ዝግጅቶች ይከታተሉ !!
ከዩቲዩብ አፈና ለመውጣት በተለይ የረምብል ገፃችንን በመቀላቀል እና በማስተዋወቅ ይተባበሩ !!
➻ Youtube (Abc breakdown) - https://youtube.com/@abcbreakdown?si=dIi94A-5pyW9TWJw
➻ News channel (zenaabc) - https://youtube.com/@zenaabc?si=eR_GXzh-1bUuZHgW
➻ Rumble - https://rumble.com/user/AbcTvAmhara
ኤቢሲ ቴቪ
ትጋታችን ለሕልውናችን !!
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
