es
Feedback
ሙላት አድኖ(የፈራ ይመለስ)

ሙላት አድኖ(የፈራ ይመለስ)

Ir al canal en Telegram
3 520
Suscriptores
-1524 horas
-267 días
-6930 días
Archivo de publicaciones
Document from የአኪለስ ተረከዝ

ብዙ ጊዜ የጎጃም ጎጠኞች እና ተለጣፊው የገዱ ቲም የጎንደር አማራን ለማሸማቀቅ የሰሊጥ ብሔርተኞች ፣ ለቁራጭ መሬት ብለን አንዋጋም ሲል ይደመጣል። ቁራጭ መሬቱ ላይ ማን እንደሚጠቀምበት፣ የሰሊጥ ብሔርተኛው ማን እንደሆነ በማስረጃ ማስረዳት ግድ ብሎናል። ከዚህ በፊትም በሚዲያ ከወልቃይት ጠገዴ ጠለምት አርማጭሆ መተማ ቋራ ባለው ሰፊ የእርሻ መሬት በኢንቨስትመንት የተሰማሩ ባለሃብቶች ዳታ አለኝ ብያችሁ ነበር። የዛሬ አመት የቀጠናው ገበሬ የመሆር ሰብሳቢ የቀን እና ቋሚ ሠራተኛ ማስታወቂያ ማውጣቱን ተከትሉ አስረስ ማረ ዳምጤ " ፋኖ መንገድ ዝጋ የአማራ ወጣት ለብልፅግና መኸር አይሰበስብም" ብሎ ነበር። በጥሪው መሠረት ብልፅግና ነው ስለተባልን እርምጃ ብንወስድ ይፈረድብናል። ለማንኛውም በኢንቨስትመንት ከተያዘው መሬት 2% የጎንደር አማራ ሲሆን 98%ቱ መሬት የወሰዱት ከጎንደር አማራ ውጭ የሆኑ አማራዎች እና ሌሎች አንዳንድ ኢትዮጵያዊያንና የውጭ ዜጎች ናቸው ናቸው። ለቅምሻ የባለሃብቶችን ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል ስማቸውን አውጥቸዋለሁ። የመጡበት አካባቢ፣ በፐርሰንት ሁሉ ሠርተነዋል። በግሎባል ፋኖ ሚዲያ በነገው ዕለትም አቀርበዋለሁ። ይለይለት ይውጣ ከተባለ ደግሞ ፋኖዎቻችንን አማክረን እንወስናለን። ምክንያቱም ጥናቱን ያካሄደው ፋኖም ጭምር ስለሆነ። በአግባቡ እየተነጋገርን እየተማመንን መሄድ ስላለብን ነው። ከዚህ ውስጥ የፀረ ጎንደር ዘመቻ አዝማች በፋይናንስ ደጋፊ ካሉ በፋኖ ህግ ይጠየቃሉ። ማሳሰቢያ ====== ይህ ለቅማሻ ነው። ሰነዱ ብዛት ገፅ ያለው ነው። በሁሉም የሚዲያ ፕላት ፎርሞች ማብራሪያ ይሰጥበታል። አስረስ ማረ የሰሊጥ አራሹ የብልፅግና ባለሃብት ነው ብሎ በጠቆመን መሠረት የጎንደር ፋኖ ወደ ዲያስፖራ ከሚያንጋጥ ከብልፅግና ባለሃብቶች ቢቀርጥ ይሻለዋል። አስረስ ማረ ስለ ጥቆማህ በጣም እናመሠግናለን።

" የወሰንና ማንነት ጉዳዮቻችን የትግላችን የአፍ መፍቻ ቋንቋችን ነው" " አገዛዙ የወሰንና የማንነት ጉዳዮችን እንደ መጫዎቻ ካርድ ነው የሚጠቀመው" " አገዛዙን አጀንዳ አሳጥተነዋል" " ተከዜ እና አሸንጌ ሀይቅ የሚያሻማ ድንበር ነው" " መከራና ቀንበር መሸከም ያቃታቸው ለጠላት እጅ ሰጥተዋል" https://youtu.be/v9UGEG-kKKw?si=rYpL-ae3zfS_1X2N

ራያ እና አላማጣን ለህውሃት የሸጡ ነፃ አውጭዎቻችን‼ እነ ሄኖክ አዲሴ የራያ አላማጣን ህዝብ ለወያኔ አሳልፈው በመሸጥ እንደፈለጉ መቀሌ እየተመላለሱ እየታከሙ ነው። ቁስለኛ ለማሳከም ብለው ህዝብን ለ
ራያ እና አላማጣን ለህውሃት የሸጡ ነፃ አውጭዎቻችን‼ እነ ሄኖክ አዲሴ የራያ አላማጣን ህዝብ ለወያኔ አሳልፈው በመሸጥ እንደፈለጉ መቀሌ እየተመላለሱ እየታከሙ ነው። ቁስለኛ ለማሳከም ብለው ህዝብን ለጣላት ማስያዣ ያደረጉ ነፃ አውጭዎቻችን ናቸው። ይሄ ጥቁር ጠባሳ ነገ በታሪክ ተሰንዶ ይጠብቃቸዋል። ከሁሉም የሚገርመኝ የእነ ሞላ ደስየን ፣ የእነ መሀመድ ቢነኝን ፣ የእነ አሸናፊን ፣ በላጎ ተራራ የቀሩትን ወንድሞቻችንን አጥንት ላይ መረማመዳቸው ነው። የሰማዕታትን አደራ ቅርጥፍጥፍ አድርገው በልተውታል። ህዝብን ለገዳይ አሳልፎ በመስጠት የአማራን የአይደፈሬነት ትርክት ሰብረውታል። ይሄን የወደቀ ሞራላቸውን ለማከም ደግሞ ሌላውን ፋኖ ለመበታተንና በህውሃት ስር እንዲጠረነፍ እየሠሩ ይገኛሉ። ሞራለ ቢስነትን ለሌላው ለማውረስ እየሠሩ ይገኛሉ። በተለይ ደግሞ ህውሃትን ተሸክመን አናመጣም የሚለውን ሁሉ ከጀርባ ለማስመታት አልመው እየሠሩ ነው። እንዲህ ዓይነት የሞራል ዝቅተት በዘራችሁ አይድረስ‼ህውሃት አልፈልግም ብሎ ነው እንጅ እስከ ቆቦ ፈቅደውለታል። ታድያ እነዚህ በምን ሞራላቸው የአማራ ነፃ አውጭ ነኝ ማለት ይችላሉ። የሚያሳዝነኝ የምሬ ወዳጆን በዚህ ሁኔታ ማየታችን ነው። በቁስለኛ ህዝብ አይቀየርም። ለነገሩ ነፃ አውጭ ነን ብላችሁ አታናፉ እንጅ በየቤታችሁ አንዳንድ የህውሃት ወደል ካድሬ ማስገባት ትችላላችሁ። የሚኒሊክ ዕዝ ሠራዊት በረቀቀ መንገድ የወያኔ ሠራዊት እየተደረክ መሆኑን እወቀው። አንተ ለአማራ እታገላለሁ ትላለህ እነ ሄኖክ ደግሞ ከህውሃት ጋር ተዋውለውብሃል። ደግሞ እኮ በጀነራል አሳምነው ፅጌ ይምላሉ😂😂😂 የገዱ መንጋዎች ስክሪን ሻቱን ወስዳችሁ አባዙት😂😂😂

ጥር ወር እና ጎንደር ====+++=++== ​ጎንደር ለ250 ዓመታት የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ሆና መቆየቷ የጀግንነት፣ የኪነ-ጥበብ፣ የሥነ-ጽሁፍ፣ የዜማ እና የሕግ መፍለቂያ እንድትሆን አድርጓታል። የጥ
+2
ጥር ወር እና ጎንደር ====+++=++== ​ጎንደር ለ250 ዓመታት የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ሆና መቆየቷ የጀግንነት፣ የኪነ-ጥበብ፣ የሥነ-ጽሁፍ፣ የዜማ እና የሕግ መፍለቂያ እንድትሆን አድርጓታል። የጥር ወር ጥምቀት ደግሞ ይህን ሁሉ የታሪክ ክብር ወደ አደባባይ አውጥቶ የሚያሳይ ወር ነው። በተጨማሪም ኢኮኖሚያዊ ክንውኖች በጥር ወር በመላው ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና የውጭ አገር ጎብኚዎች ወደ ጎንደር ስለሚጎርፉ፣ ወሩ የከተማዋ የንግድ እንቅስቃሴ ከፍተኛ ደረጃ ላይ የሚደርስበት ወቅት ነው። አንዳንዶች ደግሞ ጥር ወርንና ጎንደርን ለማለያየት ሲደክሙ ይታያሉ። ድከሙ ሲላቸው። ብዙዎች ራሱ ጥር ወርን በጎንደር ምክንያት የሚያውቋት ይመስለኛል። ጥር ወር እና ጎንደር ላይፋቱ የተጋቡ ናቸው። ፍቅረኛሞች ሆይ የጎንደርንና የጥር ወርን ፍቅር ይስጣችሁ‼

ሀሰተኛ መረጃ ነው!! ሀጎስ የሚባል የፋኖ መሪ በጎንደር አይታወቅም!! ባለፉት ዓመታት ልዩ ኃዬልን በማፍረስ ፋኖንና መላ አማራን ትጥቁን አይደለም ቀበቶውን እናስወልቀዋለን በሚል እብሪት አማራ ላይ ጦርነት የከፈተው ዓብይ አህመድ መራሹ ፋሽስት ቡድን ያልገመተውና ያልተነተነው አፀፋዊ ርምጃ ተወስዶበት እየፈራረሰ ይገኛል። ነገሩ ወዲህ ነው በጠለምት፣ወልቃይት ጠገዴና አካባቢው በተለይም የተከዜ ተፋሰስ እና ዘሪማ ተፋሰስ የዓብይ ባለስልጣናትና የጦር መሪዎች ከነ ጌታቸው ረዳ ጋር የማዕድን ቁፋሮ ህገ ወጥ ኔትወርክ አላቸው። ታድያ የማዕድን ብዝበዛው ዝም ብሎ የሚሰራ ሳይሆን የጥቅም ኔትወርኩ አካል የሆነ የታጠቀ ቅጥረኛ ጥበቃ ቡድን ያስፈልጋቸዋል።በጥንቃቄም ተመልምሎ ተዘጋጀ። ከዚህ በፊት በማይጋባ፣በጠለምትና አካባቢው ንፁሃን የጨፈጨፈ፣ከተከዜ ወደ ሰሜን ከተከዜ ወደ ደቡብ እየተዛወረ ከአማራ ግዛት አለ ስትለው ከትግራይ ግዛት የሚሻገር በወንጀል ተጨማልቆ ተስፋ የቆረጠውን ሀጎስ የተባለ ግለሰብ ከግብራበሮቹ ጋር መልምለው ለወርቅ ማውጣት ተግባር የታጠቀ የጥበቃ የኃይል አማራጭ አድርገው በቅጥረኝነት በደሞዝና በጥቅማ ጥቅም ተሰማራ።(የማዕድን መንግስታዊ ዝርፊያ እስከ ኔትወርኩ በቀጣይ በሰፊው ይፋ የምናደርግ ሁኖ)... ይህ ቡድን ከዚህ ቀደም በፈፀመው ወንጀል በፋኖ ሲታደን ትግራይ ሽሬ መሽጎ መቆየቱ የሚታወቅ ሲሆን በኦህዴድ ጀኔራሎች የዝርፊያ ኔትወርክ ከለላ እየተሰጠው ከወርቅ ማዕድን በዝርፊያና በቅጥረኝነት ተሰማርቶ ቆይቷል። ጦርነትን በድል የመቋጨት ስንፈተ አቅም ያጠቃው ዓብይና ቡድኑ በቅርቡ በሀሰተኛ የሚዲያ ጫጫታ ብዥታ ለመፍጠር በማለም የወርቅ ዝርፊያ ተባባሪ የሆነውን ቡድን የፋኖ መዋቅር አካል የነበረ በማስመሰል ፕሮፖጋንዳ ለመስራት ተጋግጠዋል። በየትኛው ድርጅት ?በየትኛው ክ/ጦር?በየትኛው ብርጌድ ተጠርንፈው እንደነበረ ያልተረጋገጠ መሆኑን መገንዘቡ ነገሩ የተለመደ የሴራ ቅጥፈት መሆኑን የሚያጋልጥ ሲሆን ባለፉት ዓመታት በፋኖ ትግል አሰላለፍ ምንም አበርክቶ እንዳልነበራቸው ትጥቃቸውና ጠቅላላ ቁመናቸው ልብ ብሎ ለተመለከተ አስቂኝና አሳቃቂ የከሸፈ ትወና ነበር።ተመሳስለው የሚሰራጩ የጠላት መረጃዎች ራሳችን እንጠብቅ እያልን ሀጎስ ምህረት የሚባል በፋኖ የሚፈለግ ወንጀለኛ እንጅ የፋኖ አመራር አልነበረም ኖሮም አያውቅም ። እየለየን ዱባና ቅል ለየቅል!! ዮሐንስ ንጉሱ ሙጨ

ከዓለምአቀፍ ፋኖ ሚዲያ - Global Fano Media የተሰጠ ማብራሪያ አለማቀፍ ፋኖ ሚዲያ - Global Fano Media ነሐሴ 2016 ዓ.ም ጀምሮ የአማራ የህልውና ትግልን በይፋ በሚዲያው ዘርፍ በመቀላቀል እለታዊ መረጃዎችንና ፕሮግራሞችን በመስራት ትግሉ አለማቀፋዊ ተደራሽነት እንድኖረውና ያጋጠሙ ችግሮችም የመፍትሄ አቅጣጫ እንዲበጅላቸው በብርቱ ሰርቷል : በመስራት ላይም ይገኛል:: ሚድያችን በሚገርም ፍጥነት ያለምንም ማስታወቂያ ትልቅ ስም(brand) ሊያፈራም ችሏል:: ይሁንና ስራዎቻችን ይተላለፉበት ከነበረው የመረጃ ሳተላይት ቴሌቪዥን በመውረዱ ከፋኖ አባላት: ከአድማጭ ተመልካቾችና ደጋፊዎቻችን ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እየደረሱን በመሆኑ ተከታዩን ማብራሪያ ለመስጠት ወደናል:: አለማቀፍ ፋኖ ሚድያ በሚሰራቸው ስራዎች ተወዳጅነት እያተረፈ በመሄዱ የበለጠ የትግሉን አድማስ ለማሳደግ: ለህዝባችን ሁለንተናዊ እገዛ እንዲያደርግ ፣ የአገዛዙን ሁሉን አቀፍ ጭፍጨፋ ላለማቀፉ ማህበረስብ ግንዛቤ ለማስጨበጥና የአገዛዙን ወንጀለኝነት ለማጋለጥ በማሰብ ከመረጃ ሳተላይት ቴለቪዥን ጋር በጋራ ለመስራት ስምምነት ላይ በመድረስ ካለፉት 8 ወራት በፊት ማርች/2025 ጀምሮ ስርጭቱ እስከተቋረጠበት ጊዜ ድረስ ስንሰራ ቆይተናል። በጋራ በሥራ ላይ በነበርንባቸው ወራትም ሥራዎቻችን ከፍተኛ ተመልካች እንዳለው : የህልውና ትግሉን መሠረት ያደረገ ወቅታዊና ጥራት ያለው ዝግጅት እንደነበር ከጣቢያው ስራአስኪያጅ አቶ ኤልያስ ክፍሌ ተደጋጋሚ አዎንታዊ አስተያየት ይደርሰን ነበር : በዚህም የጣቢያው ወርቃማ ሰዓት/Prime time / በቀዳሚነት ተሰጥቶን ቆይተናል። ከላይ እንደተገለፀው ባለፍንባቸው ወራቶች በጋራ ለህልውና ትግሉ አመርቂ ስራ የሠራን ቢሆንም ጳጉሜን 1 እና 2 ወይም በፈረንጆቹ Septemper 6-7/2025 ዓ/ም አፋብኃ በጋራ በስኬት ያካሄደውን ሲምፖሲየም ተከትሎ አጠቃላይ የሲምፖዚየም አፈፃፀምን በተመለከተ በነበረ ግምገማ ወቅት የሚድያችን ቦርድ አመራር ቀለብ ስዩም አንዷ አዘጋጅ በመሆኗና በወቅቱ "የሲምፖዝየሙ ውጤትንና የተገኘውን ድጋፍ ለሕዝብ ማሳወቅ እንደሚገባና የኦዲት ክትትል ለአፋብኃ የቦርድ አመራሮች መደረግ ይገባዋል፣ ይህ ከሆነ በቀጣይ ለምናደርጋችው ስራዎች ተዓማኒነትን ያስገኛል " የሚል ቁርጠኛ ተቋማዊ እና የመርህ ጥያቄ መጠየቋን ተከትሎ ሲምፖዚየሙን በበላይነት እኔነትን ባህል ያደረገ በሚመስል መልኩ ከሚያስተባብሩት አንዱ የነበረው የመረጃ ቴሌቪዥን ሥራ አስኪያጅ አቶ ኤልያስ ክፍለ ይሄን የመርህ ጥያቄ ለምን እንደዚህ ይደረጋል? በሚል ብስጭት ሴፕቴምበር 22/2025 በአፋብኃ ብር ማሰባሰብ ሲምፖዚየሙ ዝግጅት ጊዜ ቀለብ ስዩም በአፋብኃ ሲምፖዜምና በቴሌቶኑ ስራዎች ባነሳችው የአሰራርና የመርህ ጉዳይ ምክንያት ግሎባል ፋኖ ሚዲያ የራሱ አሰራር ያለው እራሱን የቻለ ተቋም ሆኖ እያለ ኤሊያስ ክፍሌ ግን በማናለብኝ ስሜት ስርጭቱን ሰርዞታል /ዘግቶታል። ይህም ብዙዎችን በተለይ ደግሞ የአፋብኃ ኮማንድ አባላትን ግራ ያጋባ ውሳኔውም መረጃ ቲቪን ከተቋቋመለት አውድ ውጭ በሆነ መንገድ እንደ እጅ መጠምዘዣት በመጠቀም የወሰነው ውሳኔ እና የሲምፖዝየም ስራው የተለያየ መሆኑ ጥርጣሬ ውስጥ ሊከት ችሏል። የመርህ፣ : የተጠያቂነት እና የግልፀኝነት ተጠየቅን ለምን ይነሳል በሚል የግል ጉዳይን የፋኖ ድምፅ የሆነን ሚዲያ በመዝጋት ምላሽ ሰቷል:: ጉዳዩን የሚዲያችን ቦርድ አባላት እና የአፋብኃ የኮማንድ አመራሮች ከአቶ ኤሊያስ ክፍሌ ጋር ውይይት ካደረግንበት እና ራሱም ከስርጭት ማውረዱን ስህተት መሆኑን አምኖበት ይቅርታ በማለት በፈረንጆች ሴፕቴምበር 24/2025 ዓ/ም ድጋሜ ወደስርጭት እንዲመለስ የተደረገ ሲሆን ለ6 ቀናት ስርጭታችን አየር ላይ ከዋለ በኃላ ምክንያቱ ባልታወቀ ምክንያት ድጋሜ ሚዲያችንን ከስርጭት አግዶታል። ለምን ከስርጭቱ እንደሚያግደው በተደረገለት ተጠየቅ ትግላችንን በማይመጥን ቋንቋ አስተናግዷል። ቀደም ሲል እንደገለፅነው ሚድያችን የአማራ ሚዲያ ፎረም አባል ሆኖ ከአፋብሃ የሚዎጡ መረጃዎችን የሚሰራና ትልልቅ ዘመቻዎችም ተደራሽ እንድሆኑ ትልቅ ኃላፊነቱን ተወጥቷል:: ይህ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ጉዳዩን የአፋብኃ የህዝብ ግንኙነትና የፖለቲካ ዘርፍ አመራሮች እንድያውቁት በማድረግ አቶ ኤሊያስም ለፈፀመው ድርጊት ለአመራሮቹ ይቅርታ ጠይቆ ችግሩ ተፈቶ የነበረ ቢሆንም October 14 ቀን 2025 ያለምንም በቂ ምክንያት የአማራ ፋኖ ድምፅ የሆነውን አለማቀፍ ፋኖ ሚዲያ ድጋሜ ከስርጭት አግዶታል:: በጥቅሉ በሁለት ሳምንት ውስጥ ያለ በቂ ምክንያት ሶስቴ አውርዶ መልሶ ይቅርታ እየጠየቀ ሰቅሎታል በመጨረሻም አውርዶታል። የአፋብኃ የሴንተራል ኮማንድ አባሎች እና የእያንዳንዱ የፖለቲካ ዘርፍ ተጠሪዎች፣ የህዝብ ግንኙነት ተጠሪዎች ከኤሊያስ ክፍሌ ጋር ባደረጉት ውይይት የተደረገበት እና ይቅርታ የጠየቀበት የድምፅ ቅጅ እጃችን ላይ ይገኛል። ከዚህ በኃላ እኛም የአቶ ኤሊያስ ክፍሌ አካሄድ ሚዲያውን በመጠቀም የአማራን ትግል በእጅ አዙር በተለይ ደግሞ የአፋብኃ ሀይልን የመጠምዘዝ እና ክህደት የመፈፀም ድርጊት ተፈፅሟል ብለን ያመንንና ድብቅ ፍላጎት እንዳለው በመረዳት " መረጃ ቲቪ እስከምናውቀው በሚዲያ ህግ የሚመራና የራሱ የሆነ ቦርድ ያለው በመርህ የሚመራ መስሎን ነበር፣ ይሁን እንጅ ሚዲያው ለአማራ ህዝብ ሲሰጠው ከነበረው ዓላማና አውድ ውጭ የግለሰብ እና የቡድን ድብቅ የፖለቲካ መሳሪያ መሆኑን ተረድተን፣ የአማራ ህዝብ ትግል የተነሳው የህዝብን ጥያቄ አዝሎ እንጅ መረጃ ቲቪን ተማምኖ ወደ ትግል እንዳልገባ ፣ በአሁኑ ሰዓት በርካታ የሚዲያ አማራጮች ባሉበት ወቅት ሚዲያን የግልና የቡድን ፍላጎት ማስፈፀሚያ ማድረግ እንደማይቻል አምነንበት" ከአቶ ኤሊያስ ክፍሌ ጋር ያለንን ጉዳይ ፋይሉን ዘግተናል። *ይሁንና ጉዳዩን ዘግተናል ብለን የምንተወው ሳይሆን የአፋብኃ ማዓከላዊ ኮማንድ ይህንን ትህነግ/ህወሃትና ብአዴን ያደርጉት ከነበረው አፈናና ተቁአም የማፍረስ ሂደት የማይተናነስ ድርጊት እንዴት ትመለከቱታላችሁ የሚል ተጠየቅ ማንሥት እንወዳለን::* **የአፋብኃ የሴንተራል ኮማንድ አባሎች እና የእያንዳንዱ የፖለቲካ ዘርፍ ተጠሪዎች፣ የህዝብ ግንኙነት ተጠሪዎች ከዚህ ቀደም ላደረጋችሁት ጥረት እያመሰገንን ማአከላዊ ኮማንዱ ይህንን አውቆ ከስርዓቱ ያልተናነሰ በደል እየፈፀመ ያለውን ችግር በኛ ይበቃ ዘንድ : አፋብኃ አጣርቶ እርምጃ እንድወስድ እንጠይቃለን::* በዚሁ አጋጣሚ ሁሉንም የውይይት መንገዶችን በአማራዊ ጨዋነት እና ትግሉ በሚጠይቀው ስነ ስርዓት ተጠቅመን የተፈጠረውን ችግር በመቅረፍ ስርጭታችንን በመረጃ ሳተላይት ቴሌቪዥን ለመመለስ ያደረግነው ጥረት ከላይ ባነሳናቸው ምክንያቶች ባለመሳካቱ በጀመርነው የዩቱዩብ ማሰራጫ ተጠቅመን እያስተላለፍን መሆኑን ለመላው የፋኖ አባላትና አመራሮች: ለትግሉ ደጋፊ ለአድማጭ ተመልካቾችና ደጋፊዎቻችን ማሳወቅ እንወዳለን:: አለማቀፍ ፋኖ ሚዲያ - Global Fano Media የፋኖ ድምፅ !

ደቡባዊ ጎንደር መሀል አለም በር ከተማ ላይ የተፈፀመውን ጭካኔና አውሬነት መግለፃችን ይታወቃል። ይህ ጭካኔና ነውር የተፈፀመው አድማ በተን የሚባለው እና መከላከያ ተቆጣጥሬዋለሁ ብሎ በተቀመጠበት ነው። ፋኖ ከአለም በር በብዙ ርቀት ላይ ይገኛል። ከዚህ በፊት እንደገለፅነው አገዛዙ ባለበት የሚፈፀም ማናቸውም ወንጀል ተጠያቂው ራሱ አገዛዙ ነው። ፋኖ ባለበት ለሚፈፀምም ተጠያቂው ፋኖ ነው። ባጣራሁት መረጃ መሠረት ድርጊቱን ፈፃሚዎች ከሟች ግሮሰሪ የሚጡ እንደሚጠጡ እና የደፈራትን ልጅ ደግሞ ያለ ፍላጎቷ ሲያንገራግሯት እንደሰነበቱ ነው። ሟችም ለአድማ በተን ጉዳዩን አመልክታ ነበር። ይሁን እንጅ እነኝህ ሁለት ግለሰቦች ሲጠጡ አምሽተው በስካር እናትን በጭካኔ ገለው ልጅቷን ደግሞ በደቦ ደፍረው ጥለዋት ሂደዋል። አቤት ጭካኔ። እነኝህ አረመኔዎች በፋኖ መዋቅር ውስጥ ጭራሹን የሌሉ ሲሆን ከአድማ በተን ጋር ሲጋፉ የሚውሉ መሆኑን ለማረጋገጥ ተችሏል። ጉዳዩ በተፈፀመ ጧት ህዝቡ አደባባይ ወጥቶ አድማ በትንን አውግዟል። " አድማ በትን ጠብቆ ላይጠብቅን በታጣቂዎች እያስገደለን ነው ከዚህ ከተማ ውጡሉን ፋኖ ይጠብቀናል" ብለዋል። እንደዚህ ብለው የጠየቁትን አድማ በትን አስሯቸዋል። ይሄን ወንጀል አድማ በትንም የፋኖ ዩኒፎርም ለብሶ በመፈፀም መልሶ ዩኒፎርሙን ለብሶ ካምፑን ይቀመጣል። ከዛም አብሮ ወንጀለኛ ፈላጊ ይሆናል። በአጠቃላይ ፋኖ የተፈፀመውን ነገር አውግዞ ወንጀለኞችን አሳዶ ከህዝብ ፊት እርምጃ መውሰድ አለበት። ግሮሰሪው ላይ አብረው ያመሹ አካላት ተይዘው መጣራት አለበት። ወንጀለኞችን ሲጋብዙ ያመሹ አካላት እንደነበሩ አረጋግጠናል። ዙሮ ዙሮ ፋኖ በዚህ ጉዳይ ወንጀለኞችን አሳዶ በመቅጣት በስሙ የሚነግዶትን ማጋለጥና ራሱን ነፃ ማድረግ አለበት። የወንጀለኞቹን ተልዕኮ በውል ማወቅ አለበት። ይሄን ካላደረገ አገዛዙ እና አገዛዙ ያሠማራቸው በፋኖ እያሳበቡ በርካታ ወንጀሎችን እየፈፀሙ ይቀጥላሉ። ድል ለፋኖ‼

የአቋም መግለጫ ==========+ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ፣ ለመላው የአማራ ህዝብ ፣ ለመላው የትግሉ ደጋፊ እና ለመላው የአማራ ፋኖ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል( አፋብኃ) ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ 4ኛ ደጅ አዝማች ኮር በአምስት ክፍለ ጦሮች ከተመሠረተ ጊዜ አንስቶ በታላቅ ተጋድሎ ጎዳና ይገኛል። ፋሺስት ፣ ወራሪው የብልፅግና አገዛዝ በአማራ ህዝብ ላይ እያደረሰ ያለውን ሁሉን ዓቀፍ መዋቅራዊ ግፍ እና በሌሎችም ብሔርብሔረሰቦች ላይ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ኪሳራ እያደረሰ ይገኛል። በአማራ ህዝብ ላይ ዘርን መሠረት ያደረገውን ጭፍጨፋ የአማራ ህዝብ እንደህዝብ በሠላማዊ መንገድ ጭፍጨፋዊ እንዲቆም ቢጠይቅም አገዛዙ ጭፍጨፋውን አጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን ጠያቂውን ደግሞ በአፈሙዝ ምላሽ ሰጥቶታል። ሁሉም የሰላማዊ መንገድ አማራጮች በአገዛዙ መዘጋታቸውን ያየው ፋኖ ዱር ቤቴ በማለት ጨፍጫፊዎችን በመጡበት አግባብ እያስተናገደ ይገኛል። የአፋብኃ እና የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ለኮርና ለክፍለ ጦር አመራሮች ከጥቅምት 20/02/2018 ዓ/ም እስከ ህዳር 13/03/2018 ዓ /ም ለተከታታይ 23 ቀን ሲሰጥ የቆየው አጫጭር ተቋማዊ ስልጠናዎች ማለትም ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ ስልጠናዎችን የወሰድን ሲሆን እንዲሁም ከዚህ በፊት በነበረ የትግል ጉዟችን የነበሩትን ጠንካራ እና ተግዳሮቶቻችንን በመገምገም ከዚህ በተጨማሪም ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ፣ ከአፋሪካ እና ከዓለም ዓቀፍ ሀገራት ጋር የሠራውን ዲፖሎማሲ በመገምገም እና በቀጣይ ለምናደርጋቸው ጉዟችንን አቅጣጫ በመስጠት ባለ 9 ነጥብ የአቋም በመግለጫ በማውጣት መድረኩ ተጠናቋል። 1ኛ. እኛ የኮርና የክፍለ ጦር አመራሮች በአፋብኃ እና በዕዝ ከፍተኛ አመራሮች የተሠጡንን ተቋማዊ ግዴታዎች፣ ተልዕኮዎች ለመፈፀም እና ድርጅታችንን አፋብኃን ለመጠበቅ በሙሉ ዝግጅት ላይ እንገኛለን። አጠናክረንም እንቀጥላለን። 2ኛ. ከፍተኞ አመራሮቹ በተከታታይ ሲሰጡት የሰነበቱትን ስልጠናዎች እስከ ብርጌድ አመራሮች ፣ ሻለቃ አመራሮች እና አባላት በማድረስ አንድ አይነት አመለካከት ፣ ግንዛቤ እና እውቀት እንዲኖረን እናደርጋለን። 3ኛ. ፋሺስቱ፣ ወራሪው ፣ ዘራፊው የብልፅግና አገዛዝ በአማራ ህዝብ ላይ እያደረሰ ያለውን መዋቅራዊ የዘር ማፅዳት ዘመቻ ከህዝባችን ጋር በመሆን እኛ ፋኖዎች እንመክታለን። 4ኛ. ደመኛ ጠላቶቻችን ፋኖ ገዳይ ነው፣ ፋኖ ዘራፊ ነው፣ ሌሎች ብሔርብሔረሰቦችን ገፊ ነው ፣ የድሮ ስርዓት ናፋቂ ነው እያለ የሚሠራውን ትርክት የሀሰት ትርክት ሲሆን በአማራ ህዝብ ላይ የጀመረው ሁሉን ዓቀፍ ወረራ በመግደልና በማፈናቀል ሌሎችም ብሔርብሔረሰቦች በእቅድ የሚያስቀጥልና ራሱ ገዳይ መሆኑ የጊዜ ጉዳይ እንጅ በራሱ ጊዜ ይገለጣል። ስለዚህ ይሄን ስርዓት ከስረ መሠረቱ ነቅሎ ለመጣል ከፋኖ ጎን እንድትቆሙ ጥሪ እያስተላለፍን ሁሉም ኢትዮጵያዊ በእኩል ዓይን የሚያይ ስርዓተ መንግስት እናቆማለን። 5ኛ. በፋሺስቱ፣ በወራሪው፣ በዘራፊው የብልፅግና አገዛዝ መዋቅር ውስጥ እያገለገላችሁ የምትገኙ ከተራ አባል እስከ ላይኛው ወታደራዊ እርከን ያላችሁ ከህዝባችሁ ይልቅ ለጊዜአዊ ጥቅም ብላችሁ ባንዳነትን የመረጣችሁ ከዚህ በፊት ባደረግንላችሁ ጥሪ መሠረት በርካቶች ፋኖን ተቀላቅላችሁ እየተገላችሁ ያላችሁ ሲሆን አሁንም በጠላት መዋቅር ውስጥ ያላችሁ የበደላችሁትን ህዝብ ለመካስ ፋኖን ተቀላቅላችሁ እንድትታገሉ ጥሪ እናስተላልፋለን። 6ኛ. በውጭና በሀገር ውስጥ ለምትኖሩ ኢትዮጵያዊያን የትግላችን ደጋፊዎች በሙሉ የፋኖ ትግል በአጭር ጊዜ ይቋጭ ዘንድ በፋይናንስ፣ በዲፕሎማሲ እና በእውቀት ሽግግር እንድታግዙ ጥሪ እናስተላልፋለን። 7ኛ. ለሚዲያ ባለሙያዎች፣ ጋዜጠኞች፣ ሙሁራኖች፣ አንቂዎች ፣ ለሚዲያ ተጠቃሚዎች በሙሉ በአማራ ህዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን መዋቅራዊ ሰብአዊ ፣ ቁሳዊ እና ስነ ልቦናዊ ጉዳት ለዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብ በአንድነት ሁናችሁ እንድታሳውቁ ስንል ጥሪ እናስተላልፋለን። 8ኛ. ከወራሪው፣ ከጨፍጫፊው፣ ከዘራፊው የብልፅግና አገዛዝ የፀጥታ መዋቅርና የፖለቲካ ክንፍ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት እና ተልዕኮ በመቀበል በየአውራ መንገዶች ህዝባችንን የምትዘርፉ፣ የምታግቱ፣ የምታንገላቱ በውስጣችን ያላችሁ እንዲሁም " አፈንጋጭ" የሚል የዳቦ ስም ያላችሁ የመዋቅራችን የመረጃ ክፍል ባከሄደው ጥናት አረጋግጧል። በትልልቅ ከተሞች ማለትም በባህርዳር በጎንደር ከተማ ሳይቀር ከአገዛዙ ጋር ተናባችሁ የእገታ፣ የዘረፋ፣ የግድያ ወንጀል እንደሚፈፅሙ ተደርሶባቸዋል። ይህን የምታደርጉ አካሎች ከፋሺስቱ አገዛዝ በላይ ጠላት መሆናችሁን በማመን ከድርጊታችሁ በማትታቀቡት ላይ የማያዳግም እርምጃ እንወስዳለን። 9ኛ. በአጠቃላይ የአማራ ፋኖ አንድ ጎጆ እንዲሠራ እንጅ ሁለት አማራ ስለሌለ እንድ ቤት እንድንገነባ የበኩላችንን አስተዋፅኦ እናበረክታለን። ድል ለአማራ ህዝብ ድል ለአማራ ለፋኖ አፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ 4ኛ ደጃዝማች ኮር

በቀጠናውም ሠላም መስፈን እንደማይችል በጽኑ እናምናለን። ስለሆነም በውስጥ የሃገሪቱ ሁሉንአቀፍ ቀውስ እንዲስተካከል በውጭ ቀጠናዊ ቀውሱ እንዲስተካከል ቀውስ ጠማቂውን በተባበረ ክንድ ማስወገድ ቁልፉ ተግባራችን እንደሆነ ያለንን ጽኑ አቋም እንገልጻለን።      ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!! ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) በላይ ዘለቀ ዕዝ