cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

Marcel Planiol

Laws, law books, case discussions, cassation decisions, proclamations, regulations, directives, articles, law journals and commentaries!

Mostrar más
Publicaciones publicitarias
206
Suscriptores
Sin datos24 horas
+97 días
-430 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

KAN HIIKAME: FALMATAA DABOO
Mostrar todo...
ሁለም የገጠር የእርሻ መሬት ጋር የተያያዘ የክስ ዓይነት ላይ ተመሳሳይ የይርጋ ደንብ ተፈጻሚ ሊሆን አይችልም፡፡ ክሱ ይዞታ እንዲለቀቅ የሚቀርብ የይዞታ መብትን ለማስከበር የሚቀርብ ክስ ወይም የገጠር መሬት ውርስ ይገባናል በሚል የቀረበ ክስ ወይም ከገጠር መሬት ጋር የተያያዘ ውልን መሠረት ያደረገ ክስ መሆኑ እየታየ እንደክሱ የዳኝነት መሠረት ክሱ በይርጋ ቀሪ የሚሆንበት ጊዜና ለጉዳዩ ተፈጻሚ የሚሆነው የይርጋ ደንብ ወይም ድንጋጌ የተለያየ ነው፡፡ ስለሆነም የክሱን መሠረት መለየት የይርጋ ክርክሩንም ሆነ ቀጣይ ያለ ሂደቶችን ለመመራት አስፈላጊ መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ #Click Ethiopian Laws 👆👆👆⚖⚖⚖👆👆👆
Mostrar todo...
ሰ/መ/ቁ/ር-216240 ጥር 24ን 2015 ዓ.ም #Click Ethiopian Laws አንድ ፍ/ቤት የሰጠውን ውሳኔ ይግባኝ ሰሚው ፍ/ቤት በሥነ-ሥርዓት ሕጉ በተቀመጠው ሥርዓት መሠረት ግራ ቀኙን አከራክሮ ከሻረው በኃላ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 314፣ 320(1)፣ 327 እና ሌሎች የሥነ-ሥርዓት ሕጉ ድንጋጌዎች መረት ይግባኝ ቀርቦበት ካልተሻረ በቀር ይግባኝ ሰሚው ፍ/ቤት ለውሳኔው መረት ያደረገው ምክንያት ተገቢነት የለውም ወይም ውሳኔው ስልጣን በሌለው ፍ/ቤት የተሰጠ ውሳኔን መረት ያደረገ ነው በሚል ብቻ ውሳኔው ዋጋ የሚያጣበትና የመጀመሪያው ፍ/ቤት ውሳኔ ሕይወት የሚዘራበት ወይም ተፈጻሚ የሚሆንበት የሕግ አግባብ የለም:: የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 212 ድንጋጌ በግልጽ በይግባኝ ታይቶ እንዲታረም ካልተደረገ በስተቀር የተሰጠ ውሳኔ አገዳጅነትና የመጨረሻ ውሳኔ መሆኑ ተመላክቷል፡፡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችልት በሰ/መ/ቁ 85718 በሰጠው ውሳኔ አንድ ጉዳይ ለማት በሕግ ስልጣን ባለው ፍ/ቤት ታይቶ የተሰጠ ውሳኔ በይግባኝ ታይቶ እንዲታረም ካልተደረ በቀር በጉዳዩ ላይ አስገዳጅነት ያለው ስለመሆኑ ገዥ ትርጉም ሰጥቶበታል፡፡ ከዚህ መገንዘብ የሚቻለው ስልጣን የሌለው ፍ/ቤት ጉዳዩን ተመልክቶ የሰጠው ውሳኔ በይግባኝ ወይም በሰበር ሰርዓት ታይቶ እስካልታረመ ድረስ ዋጋ የሚያጣበት ወይም ውሳኔውን ተመርኩዞ የተሰጠ ውሳኔ ዋጋ አልባ ነው የሚባልበት የሕግ አግባብ የለም፡: #Click Ethiopian Laws 👆👆👆⚖⚖⚖👆👆👆
Mostrar todo...
ረቂቁ የዳኝነት ክፍያ ደንብ👆👆👆
Mostrar todo...
ሰ/መ/ቁጥር 230249 መጋቢት 26 ቀን 2015 ዓ/ም በብድር ውል ላይ ያለው ፊርማ በመካዱ በፎረንሲክ እንዲመረመር ትዕዛዝ ተሰጥቶ ፊርማውን የሚመረምረው አካል በሰነዱ ላይ ያለው ፊርማ የማን እንደሆነ ማረጋገጥ እንደማይቻል ምላሽ ከሰጠ የብድር ውል መኖሩን በብድር ሰነዱ ላይ ባሉት የምስክሮች ቃል ማስረዳት አይቻልም። #Click Ethiopian Laws ከብር 500 በላይ የሆነ የብድር ገንዘብን ለማስረዳት ሊቀርብ ስለሚገባው የማስረጃ አይነት በፍ/ሕ/ቁጥር 2472/1 ላይ የተዘረዘረ ሲሆን በዚህ ድንጋጌ የብድር ግንኙነት መኖሩን ማስረዳት የሚቻለው በጽሁፍ፤ ወይም በፍርድ ቤት በተደረገ የእምነት ቃል ወይም በመኃላ ቃል ብቻ ነው፡፡ የብርድ ውል መኖሩን ለማስረዳት ከእነዚህ ሌላ የማስረጃ አይነት ማቅረብ እንደማይቻል ተመልክቷል፡፡ #Click Ethiopian Laws የብድር ውል በማስረጃነት ቀርቦ ፊርማው ስለተካደ በሳይንሳዊ ዘዴ ፊርማው እንዲመረመር ተድረጎ በሰነዱ ላይ ያለው ፊርማ ፊርማውን የካደው ሰው ፊርማ መሆኑን ማረጋገጥ ካልተቻለ የጽሁፍ የብድር ውል ማስረጃ ሊሆን አይችልም፡፡ በጽሁፍ የተደረገ የብድር ውል ላይ ያለ ፊርማ በተካደ ጊዜ የብድር ውል በጽሁፍ መደረጉን በምስክሮች ማረጋገጥ የሚቻል ስለመሆኑ የፍ/ሕ/ቁጥር 2472 አያመለክትም፡፡ ይልቁንም በፍ/ሕ/ቁጥር 2472/2 ለብድር ውል ሌላ ማናቸውንም ማስረጃ ማቅረብ አይቻልም ማለቱ የብድር ውል በተካደ ጊዜ በብድር ውሉ ላይ የተቆጠሩ ምስክሮችም ቢሆን የብድር ውል ስለመደረጉ ማስረጃ ሊሆኑ እንደማይችሉ አመላካች ነው፡፡ #Click Ethiopian Laws 👆👆👆⚖⚖⚖👆👆👆
Mostrar todo...